ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 084
Подписчики
Нет данных24 часа
+227 дней
+1330 день
Архив постов
photo content
+6

ለአንድ ማዕከል ባለሙያዎችና አጋር አካላት መስመር ፕሮጀክት ለኢንተርፕራይዞች የብድር ምችችት ባዘጋጀው ፕሮግራም አሰራር ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተካሄደ። መስመር በማስተርካርድ ፋውንዴሽንና እና ፈርስት ኮንሰልት ትብብር የሚተገበር በዋናነት ለሴቶችና ወጣቶች የስራ ዕድል መፍጠር ላይ የሚያተኩር ፕሮግራም መሆኑን የኢፌዴሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዋነኛ መንግስታዊ ተባባሪ አካል ነው በዚህም ለአንድ ማዕከላቱና ባለድርሻ አካላት በቂ ግንዛቤ በመፍጠር ፕሮግራሙን ኢንተርፕራይዞች ብድር የሚገኙበት ሊንክ ለማስተዋወቅ ተችሏል፡፡ መስመር በጥቅምት 2015 የተጀመረና ለ5 አመት በመላው ኢትዮጵያ የሚተገበር ሲሆን ለ72,200 ያህል ጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ እንዲሁም ኢመደበኛና ጀማሪ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ፣ የንግድ ስራ ክህሎት ስልጠና እና የስነልቦናዊ ድጋፍ አገልግሎቶችን በማቅረብ 410,800 ስራዎችን ለመደገፍ የሚሰራ ሲሆን በተጭማሪም ለፋይናንስ ተቋማት የቴክኒክ ድጋፍ ይሰጣል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 25/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች የኢፍጣር መርሀ-ግብር አካሄዱ፤      መርሃ-ግብሩ በተለይም የቢሮው እና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞችን አብሮነት እና አንድነት በመፍጠርና በማጠናከሩ ረገድ ሚናው ላቅ ያለ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ  አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረው የዛሬውን የኢፍጣር መርሀ-ግብር ላዘጋጁና ለተሳተፉ የቢሮው ማህበረሰብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።     በዚሁ የኢፍጣር መርሃ-ግብር ላይም የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች፣ የኮሌጆች ዲኖች አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም የአንድ ማዕከላት አመራሮችና ባለሙያዎችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል ። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 24/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የድሬዳዋ ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በፀሐይ ኃይል ቴክኖለጂ ዙሪያ በንድፈ ሃሳብና በተግባር የተደገፈ የክህሎት ትምህርት ስልጠና እየሰጠ መሆኑን ገለጸ። የድሬዳዋ ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለበርካታ አመታት ብዙዎችን የቀለም ቀንድ እንዲሆኑ አድርጓል። ዛሬም ለብዙዎች የዳቦ ማዕድ እንዲያቋርሱ ሙያን ያለስስት ይቸራቸዋል። ከቅርብ አመታት ወዲህ ሙያን መሰረት ያደረገ ትምህርትን ለማህበረሰቡ የማድረስ ኃላፊነትን አንግቦ ብዞዎችን የሙያ ባለቤት እያደረገም ይገኛል የድሬዳዋ ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ። ኮሌጁ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በመደበኛ እና በአጫጭር ስልጠናዎች በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር የተደገፈ ትምህርትን ይሰጣል። በዚህም በርካቶች የሙያ ባለቤት ሆነው ኑሮቸውን መርተውበታል። በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ገበያ ተኮር የሙያ ስልጠና ከሚሰጥ መካከል በአድራ ፕሮጀክት በታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ዙሪያ በንድፈ ሃሳብና በተግባር ተኮር የተደገፈ ክህሎት ለማስጨበጥ የተዘጋጀ የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ነዉ። ፕሮጀክቱ ከጀርመን መንግሥት ድጋፍ የተገኝ ሲሆን በዋናነት በሶላር ኢነርጂ ጥገና ላይ የሚያተኩር ሲሆን በአራት የትኩረት መስኮች ላይ ስልጠናው እንደሚያተኩር የገለጹት የድሬዳዋ ኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ናቸው። መንግሥት በታዳሽ ኃይል አማራጭ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ታደለ ይህንን ሀገራዊ ዕቅድ ከመደገፍ አንጻር በዘርፉ የሠለጠነ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ ተቋሙ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ሥልጠናው በዋናነት ሠልጣኞች በመስኩ የቴክኖሎጂ ልውውጥና ሽግግር እንዲያደርጉና የተግባር ልምድ እንዲወስዱ የሚያስችል ነው ያሉት ደግሞ የኮሌጁ አሰልጣኝ ወ/ሮ ሂወት ናቸው፡፡ በሥልጠናው ሶላር ሲስተምን ዲዛይን ማድረግ፣ ማስላት፣ አስፈላጊ ቁሳቁሶችን መለየት እንዲሁም በብልሽት ጊዜ የሚደረጉ የጥገና አሠራሮች የተካተቱበት እንደሆነም ነው ያብራሩት፡፡ ሠልጣኞች በበኩላቸው ሥልጠናው ከዚህ ቀደም በንድፈ ሃሳብ ደረጃ የሚያውቋቸውን ቴክኖሎጂዎች በተግባር በማየት ሶላር ሲስተምን ዲዛይን የማድረግ እንዲሁም የመጠገን ክሂሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ ከሥልጠናው ባሻገርም ከሠልጣኞች ጋር በነበረን መስተጋብር ጠቃሚ ልምዶችን ያገኘንበት ነው ብለዋል፡፡ በሰላም ለማ ፎቶ፡- ሰላም አበበ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ፕሮጀክት አመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት እና የኮሌጁ የ EASE ፕሮጀክት ማስጀመርያ ሰነድ ለኮሌጁ ቦርድ አቀረበ::    በዕለቱ በቅድሚያ በቀረበው ሪፖርት ስለ አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ)ፕሮጀክት አላማ እና እስካሁን የተሰሩ ስራዋችን እንዲሁም ዘርፉ ያጋጠመውን ችግሮች እና መፍትሄዋቻቸው  በፕሮጀክቱ ሀላፊዎች ለቦርድ አባላት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል::    በመቀጠልም በአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) የተሰራውን የSolar Labor Market እና በድሬደዋ TVT Agency አማካኝነት የተሰራውን የSolar PV Street Light Value Chain Analysis in DD City ለቦርድ አባላት በማቅረብ የGreen Tvt  Approach ትኩረት እንዲያገኝ የሚያስችል ሰፊ ገለፃና ማብራሪያ ተሰጥቶበት የቀጣይ አቅጣጫዎችንም ተቀምጠዋል::     በመጨረሻም በመድረኩ የቀረበው የኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት Strategic Investment Plan(SIP) የቀጣይ አምስት አመት የፕሮጀክቱን ማስጀመርያ ስራዎች ሰነድ ለኮሌጁ ቦርድ አባላት ለማፀደቅ በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ የቀረበ ሲሆን የቦርድ አባላቱም የቀረበውን ሰነድ  በጥልቀት ከገመገሙ በኃላ ሰነዱን በሙሉ ድምፅ በማፅደቅ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 23 2016 ዓ.ም

በኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (E-LMIS) ላይ የወረዳ ሥራ አስፈጻሚዎችን ጨምሮ ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የምዝገባ ውጤታማነቱን ለማሳደግ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ። ይህ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት ተግባራዊ ሲደረግ ዕድሜያቸው ለስራ የደረሱ ከ60 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጲያውያንን ተጠቃሚ የሚያደርግ ስርዓት ሲሆን በስራና በሰራተኛ መካከል እንደ ድልድይ ሆኖ በማገልግል በዘርፉ ለዘመናት የቆየውን የመረጃ ችግር በመፍታት በየዕለቱ ስንት ሰው ስራ እንዳገኘ፣ ስንት ሰው ስራ እንደቀየረ፣ ስንት የስራ ማስታወቂዎች እንደወጡ፣ የት አከባቢ ምን ዓይነት ሰራተኛ እና  ስራ እንዳለ እንዲሁም በየዕለቱ ስንት ኢንተርፕራይዝ እንደተደራጀ፣ የስልጠና፣ የፋይናንስ እና ሌሎች ደጋፎች ለስንት ኢንተርፕራይዝ መስጠት እንደተቻለ እና ሌሎች ተመሳሳይነት ያላቸውን መረጃዎችን በየዕለቱ መሰብሰብ የሚችል ስርዓት ነው። በአገር አቀፍ ደረጃ የሥራ ዕድል ፈጠራውን የተሳለጠ ለማድረግ የሚረዳው ይህ የዲጂታል ስርአት ተዘርግቶ ወደ ሥራ መገባቱ የሚታወቅ ሲሆን በአስተዳደሩ የሚገኙ የወረዳ አመራሮች ያለውን ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ለማስገንዘብ መድረኩ ተዘጋጅቷል፤ በዚህም ለአመራሮቹ ስለ አዲሱ ሥርዓት (E-LMIS) በዘርፉ ያመጣውን ለውጥ ምንነትና እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ አቅም መፍጠር መቻሉንና የምዝገባውን ውጤታማነት ለማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መግባባት መፈጠሩን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 21/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

photo content

ታላቁ የረመዳን ፆም ወርን ምክንያት በማድረግ በትናንትናው እለት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ በኮሌጁ የጤና ቡድን አማካኝነት የኢፍጣር መርሀ-ግብር ተካሄደ ። ታላቁ የረመዳን ፆም ወር ከገባ ትና
+8
ታላቁ የረመዳን ፆም ወርን ምክንያት በማድረግ በትናንትናው እለት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ  በኮሌጁ የጤና ቡድን አማካኝነት የኢፍጣር መርሀ-ግብር ተካሄደ ። ታላቁ የረመዳን ፆም ወር ከገባ ትናንትና 18ተኛ ቀኑን ይዟል ። ይህንንም ምክንያት በማድረግ በትናንትናው እለት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  ግቢ ታላቅ የኢፍጣር መርሀ-ግብርም ተካሂዷል :: በዚሁ መርሀ-ግብር ላይም ጥሪ የተደረገላቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የተለያዩ ክፍል ዳይሬክተሮች ፣ የኮሌጁ አመራሮች   ፣ የኢትዮጵያ ሴት ጋዜጠኞች ድሬዳዋ ቅርንጫፍ አባላት  ፣ ከኮሌጁ ጋር በጋራ አብረው የሚሠሩ ባለ ድርሻ አካላት  ፣ የኮሌጁ ሠራተኞች ፣ አቅመ ደካማ ወገኖች እንዲሁም ሠልጣኝ ተማሪዎች  እና በርካታ የእስልምና እምነት ተከታዮች ተሳታፊ ሆነዋል:: በትናንትናው እለት የተደረገው የኢፍጣር መርሃ ግብር እንዲሳካ ትለቁን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላቶች በኮሌጁ ማህበረሰብ ስም ምስጋና ቀርቧል:: የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 20/2016 ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ከተለያዩ ለአሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ። በመድረኩም ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011፤ በህብረት ድርድር እና በሁለትዮሽ ማህበራዊ ምክክር ዝርጋታ ላይ ገለጻ ተሰጥቷቸዋል። በዚህም የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የሥራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው ይሆናል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 18/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

ሁለተኛው ዙር ብቃት_የወጣቶች_የስራ_ላይ_ልምምድ_ፕሮጀክት ትግበራ የመጀመሪያ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠና መሰጠት ጀመረ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት" ተጠቃሚ ለመሆን በአስተዳደሩ የወረዳ አንድ ማዕከላት የተመዘገቡ ወጣቶችን በዛሬው ዕለት  በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና  በኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠና መስጠት ጀምሯል። በዛሬው ዕለት በኮሌጆቹ ስልጠናቸውን መውሰድ የጀመሩትም በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ወረዳ-1 አንድ ማዕከል፣ በወረዳ-2 ዋናው አንድ ማዕከል፣ በወረዳ-2 ቅርንጫፍ-1  አንድ ማዕከል እንዲሁም በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣ በወረዳ-2 ቅርንጫፍ-2  አንድ ማዕከል፣ በወረዳ-4  አንድ ማዕከል የተመዘገቡ ስምንት መቶ ሰልጣኞች ናቸው። በዚህም ሰልጣኞች ስልጠና ከመጀመራችው በፊት አስፈላጊውን ኦሬንቴሽን የተሰጣቸው ሲሆን ስልጠናውን ለቀጣይ 10 ቀናት በኮሌጆቹ እየወሰዱ የሚቆዩ ይሆናል እንዲሁም ህፃናት ልጆች ያላቸው ሰልጣኞች ከስልጠናቸው እንዳይስተጓጎሉ በማሰብ በኮሌጆቹ የህፃናት ማቆያ በማዘጋጀት ሰልጣኞች ልጆቻቸውን አምጥተው እንዲያቆዩ መመቻቸቱን በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት  ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 16/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

ሁለተኛው ዙር ብቃት_የወጣቶች_የስራ_ላይ_ልምምድ_ፕሮጀክት ትግበራ የመጀመሪያ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠና መሰጠት ጀመረ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት" ተጠቃሚ ለመሆን በአስተዳደሩ የወረዳ አንድ ማዕከላት የተመዘገቡ ወጣቶችን በዛሬው ዕለት  በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና  በኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠና መስጠት ጀምሯል። በዛሬው ዕለት በኮሌጆቹ ስልጠናቸውን መውሰድ የጀመሩትም በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ወረዳ-1 አንድ ማዕከል፣ በወረዳ-2 ዋናው አንድ ማዕከል፣ በወረዳ-2 ቅርንጫፍ-1  አንድ ማዕከል ሲሆን በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣ በወረዳ-2 ቅርንጫፍ-2  አንድ ማዕከል፣ በወረዳ-4  አንድ ማዕከል የተመዘገቡ ስምንት መቶ ሰልጣኞች ናቸው። በዚህም ሰልጣኞች ስልጠና ከመጀመራችው በፊት አስፈላጊውን ኦሬንቴሽን የተሰጣቸው ሲሆን ስልጠናውን ለቀጣይ 10 ቀናት በኮሌጆቹ እየወሰዱ የሚቆዩ ይሆናል፤ እንዲሁም ህፃናት ልጆች ያላቸው ሰልጣኞች ከስልጠናቸው እንዳይስተጓጎሉ በማሰብ በኮሌጆቹ የህፃናት ማቆያ በማዘጋጀት ሰልጣኞች ልጆቻቸውን አምጥተው እንዲያቆዩ መመቻቸቱን በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት  ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 16/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

photo content
+6