ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 084
Подписчики
Нет данных24 часа
+227 дней
+1330 день
Архив постов
"አስተዳደሩ የክህሎት ልማቱ በአመራሩ የቅርብ ክትትልና አመራር ሰጪነት ለቀጣይ ውጤት አምጪ የኢንደስትሪ ኮሪደርነት ጉዞ መደላድል ለመፍጠርና ዜጎችን  ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ።" ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በድሬዳዋ አስተዳደር የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጉብኝትና  ድጋፍና ክትትል ማጠቃለያ መርሃግብር በዛሬው ዕለት ተደርጓል። ከመርሃግብሩ መጠናቀቅ በኋላ ክብርት ሚንስትሯ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በመገኘት በአጠቃላይ በክህሎት ልማት፣ በአሰሪና ሰራተኛ እንዲሁም በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፉ በምልከታ የታዩ እና በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው በሚገቡ ጉዳዮች ላይ የአስተዳደራችን ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር፣የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ፅ/ቤት ምክትል ኃላፊ ሻኪር አህመድ፣ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋን ጨምሮ የኮሌጅና የአንድ ማዕከላት አመራሮች በተገኙበት  ምክክር አድርገዋል፡፡ ክብርት ሚንስትሯ በአስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር የሚመራው አመራር ባለፉት አመታት የአስተዳደሩን ገጽታ የቀየሩ ሥራዎች ምስጋና የሚቸራቸው መሆናቸውና በዚህም ውስጥ የሥራና ክህሎት ዘርፉን ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ የሚገባ መሆኑና እና በቀጣይ ጥራትና ተደራሽነትን ከማስፋት አንጻር በተለይ የአስተዳደሩን የገጠር ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ ላይ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት  ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 15/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

"አስተዳደሩ የክህሎት ልማቱ በአመራሩ የቅርብ ክትትልና አመራር ሰጪነት ለቀጣይ ውጤት አምጪ የኢንደስትሪ ኮሪደርነት ጉዞ መደላድል ለመፍጠርና ዜጎችን  ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ።" ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በሐረሪ ክልል የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጉብኝትና  ድጋፍና ክትትል ማጠቃለያ መርሃግብር በዛሬው ዕለት ተደርጓል። ከመርሃግብሩ መጠናቀቅ በኋላ ክብርት ሚንስትሯ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በመገኘት በአጠቃላይ በክህሎት ልማት፣ በአሰሪና ሰራተኛ እንዲሁም በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፉ በምልከታ የታዩ እና በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው በሚገቡ ጉዳዮች ላይ የአስተዳደራችን ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር፣የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ፅ/ቤት ምክትል ኃላፊ ሻኪር አህመድ፣ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋን ጨምሮ የኮሌጅና የአንድ ማዕከላት አመራሮች በተገኙበት  ምክክር አድርገዋል፡፡ ክብርት ሚንስትሯ በአስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር የሚመራው አመራር ባለፉት አመታት የአስተዳደሩን ገጽታ የቀየሩ ሥራዎች ምስጋና የሚቸራቸው መሆናቸውና በዚህም ውስጥ የሥራና ክህሎት ዘርፉን ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ የሚገባ መሆኑና እና በቀጣይ ጥራትና ተደራሽነትን ከማስፋት አንጻር በተለይ የአስተዳደሩን የገጠር ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ ላይ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት  ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 15/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

በብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ተጠቃሚ ለመሆን በአስተዳደሩ የወረዳ አንድ ማዕከላት የተመዘገባችሁ ሰልጣኞች ከመጋቢት 16/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና የምትወስዱ ሲሆን ሰኞ ከጠዋቱ 2:00  የምትጀምሩ ይሆናል። በዚህም 👉 በወረዳ-1 አንድ ማዕከል 👉 በወረዳ-2 ዋናው አንድ ማዕከል 👉 በወረዳ-2 ቅርንጫፍ-1  አንድ ማዕከል የተመዘገባችሁ ወጣቶች ስልጠናችሁ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሆን፤ ---------------------------------------------------------- 👉 በወረዳ-2 ቅርንጫፍ-2  አንድ ማዕከል 👉 በወረዳ-4  አንድ ማዕከል የተመዘገባችሁ ደግሞ በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ተገኝታችሁ ስልጠናውን የምትወስዱ ይሆናል። ማሳሰቢያ፡- የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ  እና 2 ፎቶ ግራፍ ይዛችሁ እንድትገኙ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ

photo content

ኢ-መደበኛ አንቀሳቃሾችን ወደ መደበኛ ኢንተርፕራይዝ እንዲሸጋገሩ ከድሬ ብድርና ቁጠባ ጋር በመተባበር በቀጣይም ብድር የሚያገኙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ይህን የስልጠና መድረክ ለኢ-መደበኛ አንቀሳቃሾች ሲያዘጋጅ የሥራን ጠቀሜታ በመረዳትና ለሥራ ያላቸውን ተነሳሽነት በመጨመር የራሳቸውንና የቤተሰቦቻቸውን ህይወት እንዲለውጡ አስፈላጊና ጠቃሚ የሆኑ መሠረታዊ የንግድ ክህሎቶች እንዲጨብጡ ታሳቢ ያደረገ ነው፤ የኢንተር ፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ መቅደስ ከፈለኝ እንደገለጹት አንቀሳቃሾቹ ይህን ስልጠና ከወሰዱ በኋላ በሥራ ፈጠራና ሥራ ፈጣሪነት ላይ ግንዛቤያቸውን የሚጨምር ሲሆን በንግዱ ሙያ ውስጥ ውጤታማ ሊያደርጉ የሚያስችላቸውን ባህሪ በመላበስና ብቃቶችን እንዲገነዘቡ የሚያስችላቸው እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት  ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 14/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር በክብርት ወ/ሮ ሙፈርሃት ካሚል  እና በከተማችን ክቡር ከንቲባ ከድር  ጁሀር  የተመራው የፌደራል እና የከተማችን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የሱፐርቪዥን ቡድን በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የሥራ ጉብኝት አካሂዷል። የሱፐቪዥኑ ቡድን በ ኮሌጁ ሲደርስ በኮሌጁ አመራሮች እንዲሁም ሠራተኞች ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን በነበራቸው ቆይታም በተቋሙ የተከናወኑና እየተሰሩ ያሉ የለውጥ ስራዎችን እንዲሁም በሰልጣኝ ተማሪዎች የተሰሩ ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል:: በመሥክ ጉብኝቱ  መሠረት ልኡክ ቡድኑ በኮሌጁ የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ የለዉጥ ስራዎች እንዲሁም በአስተዳደሩ ለኮሌጁ እየተደረገ ያለው ድጋፍ በተጨማሪም የፕሮጀክት የማስፈጸም ተግባራቶች በሙሉ ለሌሎች እንደ ተሞክሮ የሚወሰድ ሲሆን ካለው አቅም አንጻር ከዚህ በላይ መስራት እንደሚጠበቅበት አቅጣጫ ተሠጥቷል:: ድሬዳዋ  ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 14/2016 ዓ.ም

photo content
+6

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር በክብርት ወ/ሮ ሙፈርሃት ካሚል እና በከተማችን ክቡር ከንቲባ ክቡር ጁሀር የተመራው የፌደራል እና የከተማችን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የሱፐርቪዥን ቡድን በዛሬው ዕለ
+6
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር በክብርት ወ/ሮ ሙፈርሃት ካሚል  እና በከተማችን ክቡር ከንቲባ ክቡር  ጁሀር  የተመራው የፌደራል እና የከተማችን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የሱፐርቪዥን ቡድን በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የሥራ ጉብኝት አካሂዷል። የሱፐቪዥኑ ቡድን በ ኮሌጁ ሲደርስ በኮሌጁ አመራሮች እንዲሁም ሠራተኞች ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን በነበራቸው ቆይታም በተቋሙ የተከናወኑና እየተሰሩ ያሉ የለውጥ ስራዎችን እንዲሁም በሰልጣኝ ተማሪዎች የተሰሩ ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል:: በመሥክ ጉብኝቱ  መሠረት ልኡክ ቡድኑ በኮሌጁ የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ የለዉጥ ስራዎች እንዲሁም በአስተዳደሩ ለኮሌጁ እየተደረገ ያለው ድጋፍ በተጨማሪም የፕሮጀክት የማስፈጸም ተግባራቶች በሙሉ ለሌሎች እንደ ተሞክሮ የሚወሰድ ሲሆን ካለው አቅም አንጻር ከዚህ በላይ መስራት እንደሚጠበቅበት አቅጣጫ ተሠጥቷል:: ድሬዳዋ  ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 14/2016 ዓ.ም

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት ለኮሌጁ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ፣ EASTRIP GRM ኮሚቴ እንዲሁም ለፕሮጀክቱ ማህበረሰብ ተወካዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ። የግንዛቤ ማስጨበጫ
+5
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት ለኮሌጁ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ፣ EASTRIP GRM ኮሚቴ እንዲሁም ለፕሮጀክቱ ማህበረሰብ ተወካዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ። የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው የተሰጠው በፌዴራል 1ኛ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኛ የተከበሩ አቶ ባይሳ ጅሩ ሲሆን የዚህ የኮሌጁ ማህበረሰብ ቅሬታዎች ከመነሻቸው እንዴት እንደሚፈቱ፣ ችግሮቹ ወደ ውጭ አካላት ከማደጉ በፊት በጊዜ በውስጥ አቅም በመጠቀም እንዴት መፍታት እንደሚቻል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ዋና አላማዎች ሲሆኑ ሁሉም የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች ከኮሌጁ ማህበረሰብ እና ከግንባታ ፕሮጀክት የሚነሱ ማናቸውንም ቅሬታዎች ለመፍታትና ለመቆጣጠር የአለም ባንክ ቅሬታ አፈታት መርሆዎችን ተከትሎ መፍታት እንዴት እንደሚቻል በስልጠናው ወቅት ለተሳታፊዎች ለማስገንዘብ ተችሏል ። በመዝጊያ መርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የEASTRIP ፕሮጀክት አስተባባሪ ወ/ሪት አሽረፊያ አብዲ እንደተናገሩት ሁሉም ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች ከባለድርሻ አካላት የሚነሱ ቅሬታዎችን ከኮሌጁ ቅሬታ እና የ EASTRIP GRM ኮሚቴ ጋር በጋራ ለመፍታት በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 13/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር በክብርት ወ/ሮ ሙፈርሃት ካሚል የተመራው የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የሱፐርቪዥን ቡድን በዛሬው ዕለት በኮሌጃችን የመስክ ምልከታ አካሂዷል።     የሱፐቪዥኑ ቡድን በ ኮሌጁ ሲደርስ በኮሌጁ አመራሮች ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን በነበራቸው ቆይታም በተቋሙ የተከናወኑና እየተሰሩ ያሉ የለውጥ ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 13.2016 ዓ.ም

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች እና አመራሮች የግማሽ ምርጫ ዘመን የልማት የሰላምና መልካም አስተዳደር አፈጻጸምና የቀሪ ምርጫ ዘመን ቀጣይ አቅጣጫዎችን ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡ ለውይይት በቀረበው የአፈጻጸም ሪፖርት ባለፉት ሁለት አመት ተኩል ጊዜ ውስጥ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በትብብር መስራት፣ በንቅናቄ የተሰሩ ስራዎች ተፋሰስ፣ ስንዴ ልማት፣ የደንጊ እና የችኩጉኒያ ወረርሽኝ ለመከላከል የተሰሩ ስራዎች፣ የጤና መድን ሽፋን ለማስፋት የተሰሩ፣ የክረምትና በጋ በጎ ፍቃድ ስራዎች፣ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እድገትና መዋቅራዊ ሽግግርን ያመላከቱ ሃሳቦች ቀርበዋል፡፡ በተለይ ከ30ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፈጠሩ እና በሰላምና ጸጥታ ረገድ ወደ ከተማዋ በተለያዩ ዘርፎች በኢንቨስትመት ለመሰማራትም ሆነ ለተለያዩ ጉዳዩች ተመራጭ መሆኗና የታየው የኢኮኖሚ እድገትም በተሳታፊዎች ምስጋና የተቸረውና በዚሁ እንዲቀጥል የተጠየቀ ሲሆን ሌሎችም ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው በመድረክ መሪዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት  ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 12/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

“ሀገር በቀል እውቀትና ክህሎቶችን በማልማት እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ገፅታዎች ዙሪያ ላሉ ክፍተቶች መፍትሄ ይሆኑ ዘንድ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርበን በመስራት ላይ እንገኛለን፡፡” የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በእንግሊዘኛዉ በዋናነት “Indigenous knowledge & Skill” የሚለው የሚገልፀው ሲሆን “Traditional knowledge & Skill“ ወይም “Local knowledge & Skill” የሚሉትም ሊተኩት ይችላሉ፡፡ የማህበረሰብ እውቀትና ክህሎት ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና አካባቢያዊ የህይወት ገፅታዎች የሚዳሰሱበትና መፍትሄ የሚሰጥበት የተገለፀና ያልተገለፀ እውቀትና ክህሎትን ያጠቃለለ ነው ፡፡ በብዙ ዘመናት ልምድ የዳበረና በባህል ውስጥ ሰርፆ ከትውልድ ትውልድ በተለያዩ መንገዶች በአካባቢው ቋንቋና አተገባበር የሚተላለፍ እውቀትና ክህሎት ነው ፡፡ እየዘመንን ብንመጣም ትምህርቶችን ወደ ተግባር ቀይረን ችግሮቻችንን በመቅረፍ ረገድ የሚታይ እውቀትና ክህሎት ብዙም አልሰራንም። በተለይም ባለፉት ጊዜያት ሀገር በቀል የሆኑ እውቀቶችንና ክህሎቶችን ትኩረት ባለማግኘታቸው ለችግሮቻችን መፍቻ የሚሆን ሀገር በቀል እውቀትና ክህሎት በማጣት ዘወትር የሌሎችን እርዳታ ጠባቂ ሆነን ቆይተናል አሁን ላይ ግን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በሀገር በቀል እውቀትና ክህሎት ባለቤቶችና አዋቂዎች እና በተመራማሪዎች መካከል የጋራ ጥቅም የሚያስገኝ ትስስር እንዲፈጠር መረጃ ለማሰባሰብና ጥናት ለማድረግ የሚያስችል መርኃግብር ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሂዷል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት  ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 12/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር መተግበር ላይ ያለው የEASTRIP ፕሮጀክት ከአለም ባንክና ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች የልህቀት ማዕከሉን የህንጻው ግንባታ አፈጻጸም በ
+4
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር መተግበር ላይ ያለው የEASTRIP ፕሮጀክት ከአለም ባንክና ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች የልህቀት ማዕከሉን የህንጻው ግንባታ አፈጻጸም በዛሬው እለት ገመገሙ፡፡ ለግምገማው የመጣውን ልኡክ ቡድን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እንዲሁም የኮሌጁን ሁኔታ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በመቀጠልም ስለ ልህቀት ማእከሉ የህንጻ ግንባታ እንዲሁም አሁን ያለበትን ሁኔታና በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች የአማካሪ ድርጅቱ መሐንዲስ ዮሃንስ እቁባይ አማካኝነት ቀርቧል፡፡ ከሪፖርቶና ከመስክ ጉብኝቱ በኋላ በቀረበው አፈጻጸም ላይ ልኡክ ቡድኑ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም ላይ  አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 11/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 በጀት አመት መደበኛ ስራ የ6ወር አፈጻጸምና የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት አፈጻጸም ለኮሌጁ የቦርድ አባላት በዛሬው እለት ቀረበ፡፡ የኮሌጁ
+5
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 በጀት አመት መደበኛ ስራ የ6ወር አፈጻጸምና የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት አፈጻጸም ለኮሌጁ የቦርድ አባላት በዛሬው እለት ቀረበ፡፡ የኮሌጁን ሪፖርት ያቀረቡት የኮሌጁ ዲን በአቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ የኮሌጁ ከዝግጅት ምእራፍ እሰከ ትግበራ ምእራፍ ድረስ የተሰሩ ስራዎችንና የተገኙ ውጤቶችን የገለጹ ሲሆን በቀጣይም የሚሰሩ ስራዎችን ለቦርድ አባላት አቅርበዋል፡፡በመቀጠልም የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት አፈጻጸም በፕሮጀክቶ M&E specialist በአቶ መሳይ ጥላሁን ቀርቧል፡፡ ከሪፖርቶቹ በኋላም በቀረበው የእቅድ አፈጻጸም ላይ የቦርድ አባላቶች የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም በቦርዱ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ የብልጽግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቦርድ ሰብሳቢ በኮሌጁ እንዲሁም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም ላይ ማጠቃለያ እንዲሁም የስራ መመሪያ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 10/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ