ru
Feedback
Comparative Religion

Comparative Religion

Открыть в Telegram

{እዚሁ ውስጥ ያላችሁ ክርስቲያን ወገኖቻችን በእስልምና ዙሪያ ጥያቄ ካላችሁ,መስለም ከፈለጋችሁ እና በተጨማሪ ነፃ የምክር አገልግሎት ከፈለጋችሁ በውስጥ መስመር ጥቆማ መስጣት ትችላላችሁ ።} @AMDALA6_BOT

Больше
4 395
Подписчики
Нет данных24 часа
+187 дней
+3830 день
Архив постов
ጥያቄ ተሳተፉከአላህ ውጭ ባለ ፍጡር መማል "ሺርክ" ነው።የካፊሮች ቅጥፈት መልስ የሚሰጥበታ ቻናል ነው ጎራ በሉ ➢@mustefa_Apologetics

🌟  ነፃ የትምህርት ዕድል! 🌟 የ«አል-ኢዝሃር ኢስላማዊ ጥናት እና ምርምር ተቋም» የ4ተኛ ዙር የንፅፅር ትምህርት (Comparative Religion) ምዝገባ ጀምሯል!
💫 ምን ይማራሉ?
በእስልምና እና በክርስትና መካከል ያለውን አንድነትና ልዩነት በንፅፅር። 🔹 ቆይታ፦ ለ5 ወራት (weekly 2-3) 🔹 ክፍያ፦ ሙሉ በሙሉ ነፃ (Free)! 🔹 የት?፦ በኦንላይን (online)። 🔹የምስክርነት ወረቀት፦ በአግባቡ ተምረው ካለፉ በሰርተፍኬት ይመረቃሉ።
ልዩ ትኩረት
ለመንግስት ሰራተኞች፣ ለተማሪዎችና ለእህቶች ልዩ ክትትል እናደርጋለን።
የምዝገባ ጊዜ፦
ከዛሬ ሰኔ 3 ጀምሮ እስከ ሰኔ 8 ለ አምስት ቀናት የሚቆይ ሲሆን ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ፈጥነው ይመዝገቡ።
የምንሰጣቸው የትምህርት ዓይነቶች
➔ ነገረ-ክርስቶስ(christology) ሙሉ ጥናት ➔ ሥላሴ(Trinity) ሙሉ ጥናት ➔ መሰረታዊ የግሪክ ቋንቋ--- ናቸው
አል-ኢዝሃር ኢስላማዊ ጥናት እና ምርምር ተቋም ሰኔ 03/2018 ዓ.ል
ይሄንን ሊንክ በመንካት ወደ መመዝገቢያ ግሩፕ ይግቡ። https://t.me/+WxUlgdaUFsU5MjQ0

ጎሽተ ሞተ ነቃን? በአላህ ሱም ስረም ጥሽት ሩህሩህ ስረም ጥሽት ተመራሪ በሆነይ፡፡ እነይ ቡቆ መንቄ ባሶት በሼሽት ኡስቤ ላፍታትነ ሊንዤነይሙ ኡሁንም፦ የቂነም ጎሽተ ሞታን?የሞተቢ መሰከ ምንግዝን? ሀቀም ጎሽተ ሼሽተ አሮት ዋ ሼሽተ ማልተ በቀብር ኡስጥ ናረን? ሊሎነይ ሱልቸ  ቡርኩት ኩችብቸ ለንቀልነ ሊንዥነ።
1,የቂነም ጎሽተ ሞታን?
ሰመዬይ፣ ደቼይ፤ ከልቀይ በሁንዱሉሌከ የሀለቀይ ጎሽተ ኡሀ በሀለቀይ ከልቅ ሞተ እላነይ የነሳራሮይ አሽር «ኡማር በፈየ አፍሸ እሶከ ትበላት» ኢላነይ መክማቾት ያቴክሳን።መሳምከ በፈያይ አፍ ቦዝ አሳወ በሎትም ጎሽተ ሞተ በሎትኒ።
ቁርአን ዋ ሀዲስ ምን እላን?
መውት፦ በሎት « م و ت » ቲላን የአረብኘ ቃል የትረሀበ ቲዮን ቡር ቀውልከ «موت»ን። መውት "የሀቂቀኜ መውት "الموت الحقيقي/الطبيعي ዋ "ቀሊ መውት (ሚኜት)"الموتة الصغرى በበሎት በሆሽት ሳድነ ልንዥነይሙ።ጎሽተ ተእታይ ቶሆሽትሚ የጠለለን።
የሀቂቀኜ መውት
ሀቂቀኜ መውት እሉያነይ በአረብኘ «الموت الحقيقي» በበሎት እጠሩያ ቲዮን ሂነይ መንቄ ባሶት አሏህ ሂንኩ እላን ሱራ አል-አንዓም (6)፥ 61   "...حَتَّىٰ إِذَا جَاءَ أَحَدَكُمُ الْمَوْتُ تَوَفَّتْهُ رُسُلُنَا وَهُمْ لَا يُفَرِّطُونَ"  "...ተአቱሙም አደይ መውትት በመጠቢ ወክት  መላይካኮይ ዮስዱያን፤ ኡሁኑም እለዛገጉ፡፡" ቢእታይ ቁርአን ኡስጥ «مَوْتُ» የትባለይ ሀቂቀኜኒ መውት። ጎሽተንገ ተሀቂቀኜም ዋ ተቀልሚ (ተምኜት) የጠለለን። ለእታመይኮ አሏህ በቀውልከ ኡስጥ ሂንኩ ኢላነይ፦ ሱረቱል 25:58 وَتَوَكَّلْ عَلَى الْحَيِّ الَّذِي لَا يَمُوتُ وَسَبِّحْ بِحَمْدِهِ ۚ وَكَفَىٰ بِهِ بِذُنُوبِ عِبَادِهِ خَبِيرًا ነሳራርቸንገ «ጎሽተ ሞታኔ በሼሽት ማልት ዋ አሮት ዞፎ ተሞተ ነቃን» እሎን።ሀቀም ሼሽተ ማልተ ዋ አሮት ቄራን? ሊላነይ ሱል በገነ አሽር ሙሻወሬ እልነብያን።እነካሌይ አሳወ ቡርኩት ሱልቸ እነቅላን። ለባይትከ ጎሽተ በሞተቢ ሳት ጎሽታይ ማኒ ናር? ፣ ጎሽታን ኡሀ የሀለቀይ ከልቅ ቀተለይ በሎት መቅቡልነት አለይ? በኪታብኒሙ ኡስጥ በ 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥17 “ብቸከ ጎሽተ ለሆነይ ለይጠፋነይ ለይትራነይ----"ኢላን። በእታይ ኤት «ለይጠፋነይ» ሊላነይ ቀውል በፈረንጂ አፍ(እንግሊዝኛይ፦ KJV, NIV, ESV) የገበይ ቀውል «immortal» ቲዮን የቀውሊ አወል(ቃሙሰኜ) አነግን ሰተተኜ ማእነከ "አይሞታን ፣ኢነብራን" በሎትን።ዡቦይ የበዘ ላትፋህሞት የ ግሪኪ ኪታብ "ለይጠፋነይ" ሊላነይ የገበይ ቀውል "ἀφθάρτῳ" (አፍታርቶ) ኢላነኒ። ይታይ ቀውል በአማራይ አፍ "የማይጠፋው" ቢለይም በፈረንጂ አፍ ዋ በግሪኪ አፍ በጠቀለ ሃለት "አይሞታነይ" በበሎት ተከተባን። Οἴδαμεν δὲ ὅτι καλὸς ὁ νόμος, ἐάν τις αὐτῷ νομίμως χρῆται, Τῷ δὲ βασιλεῖ τῶν αἰώνων, ἀφθάρτῳ, ἀοράτῳ, μόνῳ σοφῷ Θεῷ, τιμὴ καὶ δόξα εἰς τοὺς αἰῶνας τῶν αἰώνων· ἀμήν. Α Προσ Τιμοθεον Επιστολη 1,17 እታይ አይጠፋነይ ጉሽተ ለሼሽት አሮት ዋ ማልት ሞተ ነቃን በሎተ ተሀቅ የራቀን ዡቦ። ሆነም ታሌ የመርየምነ ልጅ ኢሰ (ዐ.ሰ) የልሞተኮ ዋ የልትሰቀለኮ በቁርአን ኡስጥ በቡርኩት ኤትቸ ተጬቀማን።ለባይትከ፦ሱረቱል ኒሳ 4:157 وَقَوْلِهِمْ إِنَّا قَتَلْنَا الْمَسِيحَ عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ رَسُولَ اللَّهِ وَمَا قَتَلُوهُ وَمَا صَلَبُوهُ وَلَٰكِن شُبِّهَ لَهُمْ ۚ وَإِنَّ الَّذِينَ اخْتَلَفُوا فِيهِ لَفِي شَكٍّ مِّنْهُ ۚ مَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ إِلَّا اتِّبَاعَ الظَّنِّ ۚ وَمَا قَتَلُوهُ يَقِينًا «እኘ የአለሃነይ ሉክተኘ የመርየምነ ልጄ አልመሲሕ ኢሳነ ቀተልነ» በበሎትኒሙ ( አጠፋነይሙ)፡፡ አልቀተሉያነም አልሰቀሉያነም፡፡---- ቢእታይ ቁርአን ኡስጥ «وَمَا قَتَلُوهُ» በሎትም «አልቀተሉያነም» ቲል በመንቄም አለህ የገበኒ አህድ ናረ። ኢታሚ አህድ ዩሃነ (ሆሽትለኜይ ሰመይ) ኤት ሊነቅለይ አህደ የገበኒኮ በቁርአኒ ኡስጥ ኢንኩ በበሎት ተጎበላን(ተከተባን)፦ ሱረቱል አል-ኢምራን 3:55 إِذْ قَالَ اللَّهُ يَا عِيسَىٰ إِنِّي مُتَوَفِّيكَ وَرَافِعُكَ إِلَيَّ وَمُطَهِّرُكَ مِنَ الَّذِينَ كَفَرُوا ---- «--- አላሀም በባለ ወክት ኢክስ ኢሳ ሆይ! እሄ ዮስደሃው የሄነም ኤት እነቅለሃው፡፡---» በኢታይ ቁርአን ኡስጥ አላህ የገበኒ አህድ «مُتَوَفِّيكَ» "ዮስደሃው" ዋ «وَرَافِعُكَ» "እነቅለሃው" እሎነን ሱር። ኢነይ አህደ በሱረቱል ኒሳ 4:158 بَل رَّفَعَهُ اللَّهُ إِلَيْهِ ۚ وَكَانَ اللَّهُ عَزِيزًا حَكِيمًا « አላህ (ኢሳን) ዩሃን ኤት ነቀለይ፡፡»---- አላህ የገበኒ አህደ «رَّفَعَهُ اللَّهُ» በሎትም «ነቀለይ» በበሎት አትጎበለያን።በእታይ ዱም በሎትም «የሀቂቀኜ መው» በጎሽተ ዬለቢኮ ዋ ሂንኩምንገ በመሪያም ልጅ በኢሰ(አ.ሰ) አኩ ጃንጎ ባለይ ሀቂቀኜ መውት የልነቼይኮ አንዤናን። ሆነምታሌ የገናሚ ሰበኮ ኡሃም ኢሞትቢያን ወክት ያለይኮ ያለሃይ ሉክተኘ ኤወዱናን።
ቀሊ መውት (ምኜት)"الموتة الصغرى
ምኜተኝ በቁአን ኡስጥ በቡርኩት ኤትቸ "መውት" በበሎት አላህ ጠራያን። ለባይትከ፦ اللَّهُ يَتَوَفَّى الْأَنفُسَ حِينَ مَوْتِهَا وَالَّتِي لَمْ تَمُتْ فِي مَنَامِهَا ۖ 39:42 « አላህ ሩህቻይ በሞቱ ወክት ዮስደይማን፡፡----» በእታይ ቁርአን ኡስጥ «حِينَ مَوْتِهَا» የትባለይ)"الموتة الصغرى" በሎትም ምኜተይኒ። የመርየም ልጅ ኢሰ(አ.ሰ) ምኜት ናረቢ። ነሳራርቸ ኢሰ ጎሽታን ባሎ ያምኖን። ጎሽተንገ ተምኜት የጠለለን። የነሳራርቻይ ኪታብ ኢሰ አነግነ ቡሁኒ መጥሬ ኢየሱስ እኛኔ ሰብ ነቀለይ እላን። ሀቀም ሰመዬይ ዋ ደቼይ(አርዱላን) የሀለቀይ ጎሽተ ዪኛኔ ኡሀ በሀለቀይ ከልቅ ኢብራጋን? ማርቆስ 4:38 "ቢእታሚ ወክት ኢየሱስ፥ በሰፊናይ በሬር አዘርከ ትራስ ተራሳኔ እኜ ነር፤ ተኬታይቻምከ አብራገጉይ-"
መስበቼ (አክቾት)
ለደር በነቀልነይ ዱም በሎትም «የቂነም ጎሽተ ሞታነን? ቢላነይ ኩትብ "መውት በሎት ምን በሎት ዮነኮ" ዋ መውትንገ የሮሬ(ሀቂቀኜ) "الموت الحقيقي" ዋ ቀሊ መውት(ምኜት) "الموتة الصغرى" በበሎት በሆሽት እትሳዳነኩ አንዤናን። ጎሽተ ቲእታይ ግዝቸ የጠለለ ቲዮን ገሽተ ኢሞታን ዋ ዪኛን በሎት በጎሽተ ደር ክዝበ አዋልኮት። ሊእታይኮ የመሪየም ልጅ ኢሰ(አ.ሰ) የሁዳዶ የልቀተሉይኮ ዋ የልሰቀሉይኮ በቁርአን ዋ በፎልኒሙይ ኪታብ ተከተባን አንዤናነም ጃንጎ። የመሪየም ልጅ ኢሰ(አ.ሰ) ዪኝ የናረኮ በኪታብኒሙ አንዤናን። ጎሽተ ቢኜ የሀለቀይ ከልቅ ማኒ ኢቄራይ ናር? ኢላነይ ሱል ኢነቅላን። ጎሽተነ «لَا تَأْخُذُهُ سِنَةٌ وَلَا نَوْمٌ» በበሎት ተከተባን። ቢቄጥላነይ ኩትብ የቀሩይ ሆሽተይ ዱምቸ ያንዥናን። አስናጂሎ የናሲሪ አምዳለ t.me/comparativeRelgion

ፈጥኖ ማን ይመልስ! ⁉️ ጥያቄ፦ ሙዚቃ መዝፈንም ይሁን ማዳመጥ ሐራም ነዉ። ቻናል ለመቀላቀል  

photo content

ፈጥኖ ማን ይመልስ! ⁉️ ✅በቁርዓን ውስጥ ስንት ነብያት በስም ተጠቅሷወሉ⁉️ የካፊሮች ቅጥፈት መልስ የሚሰጥበታ ቻናል ነው ተቀላቀሉ➢@mustefa_Apologetics

አላህ ጀሀነም እንደሚገቡ እያወቀ ለምን ፈጠራቸው? ​ይህ ጥያቄ የብዙዎቻችንን አእምሮ የሚረብሽ፣ ጠለቅ ያለ ማብራሪያ የሚፈልግ ጥያቄ ነው። አንድ አዛኝ የሆነ ፈጣሪ፣ ፍጡሩ መጨረሻው ጥፋት እንደሚሆን አስቀድሞ እያወቀ ለምን ወደዚህ ዓለም እንዲመጣ ይፈቅዳል? የሚለው ሀሳብ መሠረታዊ የዲን እውቀት ከሌለን አንዳንዴ ወደ ተሳሳተ ድምዳሜ ሊወስደን ይችላል። ነገር ግን ጉዳዩን በጥልቀት ስንመረምረው፣ እውነታው ሌላ ሆኖ እናገኘዋለን። ​ይህንን ሀሳብ በሚከተሉት ሶስት መሰረታዊ ነጥቦች ማየት እንችላለን፡-
አንደኛ፤ ማወቅ እና ማስገደድ የተለያዩ ነገሮች ናቸው።
የችግሩ መነሻ የፈጣሪን ቅድመ እውቀት እና ሰውን ማስገደድ ማቀላቀላችን ላይ ነው። አላህ የሰዎችን መጨረሻ ማወቁ፣ ያንን መጨረሻ በግድ ጫነባቸው ማለት አይደለም። ለምሳሌ ያህል፣ አንድ ብሩህ አእምሮ ያለው መምህር ዓመቱን ሙሉ ክፍል የማይገባንና የማያጠናን ተማሪ በመመልከት ይህ ተማሪ መውደቁ አይቀርም ብሎ አስቀድሞ ያውቃል። ተማሪው በፈተናው ሲወድቅ፣ መምህሩ አስቀድሞ ስላወቀ ነው የወደቀው ወይስ ተማሪው ስላላጠና? መምህሩ ማወቁ ተማሪውን አላስገደደውም። የአላህም እውቀት ከዚህ በላቀ መልኩ የሰዎችን ነፃ ምርጫ አያፍንም።
ሁለተኛ፤ የነፃ ምርጫ ጉዳይ
አላህ የሰውን ልጅ ሲፈጥር እንደ ሮቦት ፕሮግራም አድርጎ ሳይሆን፣ ማሰብና መምረጥ የሚችል ፍጡር አድርጎ ነው። ታላቁ ጌታችን በቁርኣን እንዲህ ይላል፡- ​"እኛ መንገዱን መራነው፤ አመስጋኝ ወይም ከሓዲ (ይኾናል)፡፡" (አል-ኢንሳን 76፥3) ​ወደ ጥፋት የሚገባው ሰው የሚገባው አላህ ስለፈጠረው ሳይሆን፣ በራሱ ሙሉ ነፃ ፈቃድ የጥፋትን መንገድ ስለመረጠ ነው። ​
ሶስተኛ፤ ፍትህ እና ምክንያት አለማስቀረት
አላህ ሰውን ሳይፈጥረው አስቀድሞ አንተ ጥፋተኛ ስለምትሆን ወደ ቅጣት ግባ ብሎ ቢፈርድበት ኖሮ፣ ያ ሰው እኔኮ መጥፎ ነገር አላደረግኩም፣ እድል ብታገኝ ኖሮ ጥሩ እሰራ ነበር ብሎ የመከራከር መብት ይኖረው ነበር። አላህ ፍፁም ፍትሀዊ ስለሆነ ወደዚች ምድር አምጥቶ፣ አእምሮ ሰጥቶ፣ መልዕክተኞችን ልኮ ነፃ ምርጫን ከሰጠው በኋላ፤ ሰውየው ራሱ መጥፎውን ሲመርጥ የራሱን ፍርድ በራሱ ላይ አጸደቀ ማለት ነው። ቁርኣን እንዲህ ይላል፡- ​"ጌታህም አንድንም አይበድልም፡፡" (አል-ካህፍ 18፥49) ​የጌታችን እዝነት ከቁጣው የሰፋ ነው።​ስለዚህ፣ መፈጠር ራሱ ትልቅ ጸጋ ነው። መጥፎውን መንገድ በራሳቸው ፈቃድ መርጠው ራሳቸውን ለሚያጠፉ ሰዎች ስንል፣ መልካሙን መርጠው በዘላለማዊ ጸጋ ለሚኖሩት ሰዎች የመፈጠር እድል ሊነፈጋቸው አይገባም። አላህ ሰዎችን የፈጠራቸው ሊቀጣቸው ሳይሆን፣ በራሳቸው ምርጫ አውቀውትና አምልከውት በእዝነቱ እንዲካተቱ ነው። ©የሕያ ኢብኑ ኑህ ቻናል t.me/comparativeRelgion ቻናል t.me/comparativeRelgion

አልሃምዱሊላህ እዚህ ቻናላችን ላይ እስካሁን ከ ሁለት መቶ በላይ አርቲክሎችን እና PDF ፤ ከሚሽነሪዎች በኩል ለሚነሱ አጣብቀኝ ክሶች ምላሽ በተለያዬ መንገድ አውስተናል። እነኚን ፅሁፎች ቀላልና ምቹ በሆነ መንገድ  ተጋብዛችኋል። ክፍል¹ 1-70 ያሉትን ለማግኛት «ይጫኑኝ» ክፍል² 71-128  ያሉትን ለማግኛት «ይጫኑኝ» ክፍል³ 129- 202 ያሉትን ለማግኛት «ይጫኑኝ»
የፈለጉትን ርዕስ መርጠው ይጫኑ።
📗ወንድም አምዳላ ናሲር

አሠላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ በ «አል-ኢዝሃር ኢስላማዊ ጥናት እና ምርምር ተቋም» በአይነቱ ለየት ያለ የሦስተኛ ዙር የ አረብኛ ቋንቋ "Arabic grammar" ትምህርት ለ ተከታታይ ሥ
+2
አሠላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ  በ «አል-ኢዝሃር ኢስላማዊ ጥናት እና ምርምር ተቋም» በአይነቱ ለየት ያለ የሦስተኛ ዙር የ አረብኛ ቋንቋ "Arabic grammar" ትምህርት ለ ተከታታይ ሥስት(3) ወራት ለመስጣት እናንታን በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።

“Leenca kessaan hin ajjeesinaa, Saree gandaatu isin ciniinaa”
ቻናል t.me/comparativeRelgion ቻናል t.me/comparativeRelgion

ፈጥኖ ማን ይመልስ! ⁉️ ✅በቁርዓን ውስጥ ስንት ነብያት በስም ተጠቅሷወሉ⁉️ የካፊሮች ቅጥፈት መልስ የሚሰጥበታ ቻናል ነው ተቀላቀሉ➢@mustefa_Apologetics

ክርስቲያን ወገኖች "የቁርኣን ግጭት ነው" በሚል ከሚያነሷቸው ጥያቄዎች አንዱ "ቁርኣን መላእክት ለአላህ ብቻ እንደሚሰግዱ (ቁርኣን 7፥206) እየተናገረ፣ በሌላ በኩል ደግሞ አላህ መላእክት ለአደም እንዲሰግዱ አዘዘ (ቁርኣን 2፥34) ማለቱ እንዴት ይታረቃል?" የሚል ነው። ሀሳቡን በማብራራት እንደተባለው ግጭት እንዳልሆነ ከዚህ በታች እንመልከት፦ ፩/ የስግደት (ሱጁድ) አይነቶች በእስልምና አስተምህሮ (በአረብኛ ቋንቋም ጭምር) "ስግደት" (ሱጁድ) በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል፦
ሀ/ የአምልኮ ስግደት (ሱጁደል ዒባዳ)፦ ይህ አምላክነትን አምኖ የመገዛት ስግደት ሲሆን፣ በየትኛውም ዘመን ቢሆን ከፈጣሪ (ከአላህ) ውጭ ለማንም አይፈቀድም።
ለ/ የክብር/የሰላምታ ስግደት (ሱጁደል ተሒያ ወል-ኢሕቲራም)፦
ይህ ታላቅነትን፣ ክብርን ወይም ሰላምታን ለመግለጽ የሚደረግ ማጎንበስ ወይም ስግደት ነው። መላእክት ለአደም (ዐ.ሰ) ያደረጉት ስግደት የአምልኮ ሳይሆን ይህ የክብር ስግደት ነው። ፪/ ጭብጡን እናብራራው
ሀ/ የአላህን ትእዛዝ መፈጸም ራሱ አምልኮ ነው።
መላእክቱ ለአደም የሰገዱት አደምን አምላክ አድርገው በራሳቸው ፈቃድ ተነስተው አይደለም፤ አላህ "ስገዱ" ብሎ ስላዘዛቸው ነው። የአላህን ትእዛዝ ያለምንም ጥያቄ መፈጸም ደግሞ ትልቁ አምልኮ ነው። ሙስሊሞች በጸሎታቸው ወቅት ወደ ካዕባ ዞረው ይሰግዳሉ። ይህ ማለት ግን "ካዕባን ያመልካሉ" ማለት ሳይሆን፣ "ወደዚያ ዞራችሁ ስገዱ" ያለውን የአላህን ትእዛዝ መፈጸም ነው።
ለ/ አደም እንደ ቂብላ (አቅጣጫ)
ታላላቅ የቁርኣን አዋቂዎች (ሙፈሲሮች) እንደሚያብራሩት፣ አደም ለመላእክት ልክ እንደ ቂብላ ነበሩ። ትእዛዙን በማክበር ስግደቱ ለአላህ ሲደረግ፣ ክብሩ ደግሞ ለአላህ ድንቅ ፍጡር ለሆነው ለአደም ነበር። ዲያቢሎስ (ኢብሊስ) የተረገመውም አደምን አላመልክም በማለቱ ሳይሆን፣ ትዕቢተኛ በመሆን የአላህን ትዕዛዝ በመጣሱ ነው። ፫/ ኢስላማዊ አስተምህሮ የክብር ስግደት ከነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በፊት በነበሩት ነቢያት ሕግጋት (ሸሪዓዎች) የተፈቀደ ነበር። ለምሳሌ በቁርኣን ሱራ 12 (ዩሱፍ) አንቀጽ 100 ላይ እንዲህ ይላል፦ "ወላጆቹንም በዙፋኑ ላይ አወጣቸው፡፡ ለእርሱም ሰጋጆች ኾነው ወረዱለት..." የዩሱፍ አባት ነቢዩ ያዕቆብ (ዐ.ሰ) ናቸው። አንድ የአላህ ነቢይ ለልጁ ሰገደ ሲባል፣ ልጁን አመለከ ማለት ፈጽሞ እንደማይሆን ግልጽ ነው። ይልቁንም አላህ ለዩሱፍ የሰጠውን ጸጋ እና የስልጣን ደረጃ ለማክበር የተደረገ የመከባበር ስግደት ነው። ማስታወሻ፦ በነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመጨረሻው ሕግ (ሸሪዓ) ላይ ይህ "የክብር ስግደት" ሙሉ በሙሉ ተሽሯል። በአሁኑ የእስልምና ህግ ለሰው ማጎንበስም ሆነ መስገድ "ሺርክ" (ማጋራት) ወደሚል ትልቅ ወንጀል ሊያመራ ስለሚችል እርም (ሐራም) ተደርጓል። ፬/ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮን እንደ ንጽጽር በመጽሐፍ ቅዱስ አምልኮ ለእግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ በግልጽ ተቀምጧል (ዘጸአት 20፡2-5)። ነገር ግን ሰዎች ለሰዎች የሰገዱባቸው በርካታ ታሪኮች አሉ፦
➺ አብርሃም ለኬጢያውያን ሕዝብ ሰግዷል፦ ዘፍጥረት 23፥7 ➺ ሎጥ ለመላእክት ሰግዷል (ዘፍጥረት 19፡1)። ➺ ያዕቆብ ለኤሳው ሰግዷል (ዘፍጥረት 33፡3) ➺ የዮሴፍ ወንድሞች ለዮሴፍ ሰግደዋል፦ (ዘፍጥረት 42፡6) ➺ ነቢዩ ናታን ለንጉሥ ዳዊት ሰግዷል (1ኛ ነገሥት 1፡23)
ለክርስቲያኖች የሚቀርበው ጥያቄ፦ እነዚህ የእምነት አባቶችና ነቢያት (አብርሃም፣ ሎጥ፣ ያዕቆብ፣ ናታን) የፈጸሙት ጣዖት አምልኮ ነውን? ወይስ የክብር እና የሰላምታ ስግደት? በእርግጥም ክርስቲያን ወገኖች "ይህ የክብር ስግደት እንጂ የአምልኮ አይደለም" ብለው እንደሚመልሱ የታወቀ ነው። እስልምናም መላእክት ለአደም ያደረጉትን ስግደት የሚገልጸው ልክ ክርስቲያኖች የመጽሐፍ ቅዱሱን ስግደት በሚያብራሩበት በዚሁ ተመሳሳይ ሎጂክ እንጅ በግጭት መልኩ በቀረበበት መልኩ አይደለም። © የሕያ ኢብኑ ኑህ ቻናል t.me/comparativeRelgion ቻናል t.me/comparativeRelgion

«በአክሱም መስጂድ ከተሰራ መካ ላይ ቤተክርስቲያን እንሰራለን» በአክሱም መስጂድ እንዲሰራ ሲጠየቅ «አክሱም ላይ መስጂድ ከተሰራ መካ ላይ ቤተክርስቲያን እንሰራለን» የሚለው ቅድመ ሁኔታ ሲቀርብ ይደመጣል። ይህ አመለካከት አክሱምን ከመካ ጋር በማነፃፀር የተሳሳተ ትይዩ ከመፍጠሩም በላይ፣ የአክሱም ሙስሊሞችን ትግራዋይነትና ኢትዮጵያዊነት በመካድ እንደ ሳውዲ አረቢያ መንግሥት ተወካዮች ይፈርጃቸዋል። ጉዳዩን በዜጎችና በመንግሥት መካከል ካለ የመብት ጥያቄ ይልቅ፣ በሁለት አገራት መካከል እንዳለ የዲፕሎማሲ ድርድር በመሳል የኢትዮጵያ ተወካይ ለሳውዲው ዲፕሎማት «በአክሱም ዉስጥ መስጂድ መስራት ከፈለጋችሁ እኛም ለሳውዲ ዜጎች ቤተክርስቲያን እንገነባለን» የሚል መከራከሪያ ያቀርባል። ይህም ይህ ትርክት የሚከተሉት አደገኛ አንድምታዎች አሉት፦ 1. ማንነትንና ዜግነትን መግፈፍ፦ ዜጎችን እንደ ባዕድ ወኪል በመቁጠር የሀገር ባለቤትነት ስሜታቸውንና ማህበራዊ ትስስርን ያዳክማል። 2. መብትን እንደ መደራደሪያ ማየት፦ ሕገ መንግሥታዊ መብቶችን በሕግ ምትክ መካ ዉስጥ ቤተክርስቲያን ያለመኖሩን የበቀልና የመደራደሪያ አጀንዳ" ለማድረግ በመሞከር። 3. አግላይነትን ሕጋዊ ማስመስል፦ የመብት ጥያቄን እንደ ውጭ ስጋት በመሳል፣ መድልዎን እንደ "ፍትሃዊ ብሔራዊ መከላከል" ያቀርባል። 4. ታሪካዊ ማንነትን መካድ፦ ሙስሊሙን ማህበረሰብ እንደ አዲስ መጤ በመሳል፣ ለዘመናት የነበረውን አገር በቀል የታሪክ ድርሻ ይክዳል። 5. የአብሮ መኖር ውልን መናድ፦ የነጃሺንና የፍትህን ምድር እሴት በመዘንጋት፣ አገሪቱን የአንድ ወገን ብቻ አስመስሎ በማቅረብ አንድነትን ይበጥሳል። 6. ጉዳዩን ዓለም አቀፋዊ ግጭት ማድረግ፦ የሀገር ውስጥ የሲቪል መብቶችን ወደ ጂኦ-ፖለቲካዊ ሽኩቻ በመለወጥ የአገርን ሉዓላዊነት ለአደጋ ያጋልጣል። 7. ሕገ-መንግሥታዊ ዓለማዊ ስርዓትን መናድ፦ ሃይማኖትና መንግሥት መለያየታቸውን የሚደነግገውን መርህ በመጣስ፣ የመንግሥት ውሳኔዎች በሃይማኖታዊ የበቀል ስሌት እንዲመሩ በማድረግ ሥርዓቱን ያናጋል። 8. ሁለተኛ ደረጃ ዜግነትን ማረጋገጥ፦ ሙስሊሙ ማህበረሰብ መብት የማይገባውና ሁልጊዜ በድርድርና በፈቃድ መኖር ያለበት አስመስሎ በማቅረብ፣ የዜጎችን እኩልነት በሥነ-ልቦና ደረጃ ይሰብራል። 9. የቦታ የበላይነትን (Spatial Hegemony) ማጽናት፦ አክሱምን የአንድ ማንነት ብቻ የግል ንብረት አድርጎ መሳል፣ በሌሎች አካባቢዎችም ተመሳሳይ አግላይነት እንዲስፋፋና አገሪቱ ወደ መንደርተኝነት እንድትከፋፈል በር ይከፍታል። © አህመዲን ጀበል t.me/comparativeRelgion t.me/comparativeRelgion

ፈጥኖ ማን ይመልስ! ⁉️ ጥያቄ፦ ሙዚቃ መዝፈንም ይሁን ማዳመጥ ሐራም ነዉ። ቻናል ለመቀላቀል  

🚀 ማስታወቂያ 🚀 ቻናላችሁን በአጭር ጊዜ ማሳደግ እና ለብዙ ሰው ተደራሽ እንዲሆን የምትፈልጉ የቻናል ባለቤቶች በሙሉ፤ ከታች ያለውን መስፈርት መሰረት በማድረግ ፈጥናችሁ ተቀላቀሉ! 🎈🔐 መስፈርት፦ ❶ የንፅፅር ቻናል የሆነ ❷ ከ2,000 በላይ አባላት ያለው ❸ ለንግድና ማስታወቂያ ያልተከፈተ መስፈርቱን የምታሟሉ ከታች ባለው ሊንክ ላኩልን፤ አይተን እንቀበላለን 👇         👉@mustefa_1_2 👈         👉 @mustefa_1_2 👈 እስካሁን በዚህ የንፅፅር ቻናል ዌብ ውስጥ ያሉ ቻናሎች ለማየት እና ለመቀላቀል ከታች ➾JOIN 👈ንኩት

በአክሱም ሙስሊሞች የሚደርሰውን ግፍ፣ ማነው ተው የሚል ማነው የሚያሳርፍ? መስጊድ ሲረጋገጥ ቁርአን ሲቀደድ፣ ማን አለብኝ በሚል እምነት ላይ ሲቀለድ። 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ሰላምና አንድነት በማይወድ ደደ
በአክሱም ሙስሊሞች የሚደርሰውን ግፍ፣ ማነው ተው የሚል ማነው የሚያሳርፍ? መስጊድ ሲረጋገጥ ቁርአን ሲቀደድ፣ ማን አለብኝ በሚል እምነት ላይ ሲቀለድ። 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ሰላምና አንድነት በማይወድ ደደብ፣ ኢማም ሲንገላታ እንዲህ ሲጣስ አደብ፣ ውስጣችን ሲታመም አንጀታችን ቆስሎ፣ ፍትህ የሚያሰፍን የለም ወይ በቶሎ? 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 በገዛ ሀገራቸው ተደርገው ባይተዋር፣ በጠራራ ፀሀይ ባፀያፊ ምግባር፣ እንዲህ ሲበደሉ ያውም በምነታቸው፣ ማነው የሚቆመው ሀቅ ይዞ ጎናቸው ? 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ሰላም ለማደፍረስ የሰው  ደም ለማፍሰስ፣  ሆን ብሎ የሚሮጥ ሆዳምና አጋሰስ፣ እንቅልፍ  ተነስቶ በሰው ደህና ማደር፣ እንዲህ ሲበጠብጥ  ካንሰር ሲሆን ላገር፣ ሕግ ሚባል የለም ወይ? አቅም ያለው ለማሰር። 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ትንሹም ትልቁም  ወንዱም ሆነ ሴቱ፣ እምነቱ ነውና   ዋናው ስሱ ፓርቱ። እምነቱ ሲንቋሸሽ _  እምነቱ ሲዘለፍ፣ መቆጣቱ  አይቀርም  _ ብርቱም ሆነ ሰነፍ። 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 በእምነት የመጣ _  ቁጣና መናደድ፣ ቀሎ እንደተፃደው  _ በዋዛ  የሚበርድ፣ አሁን የሚሰራው _ ይሄ የግፍ  መዘዝ፣  አቅም አለውና _ ሺዎችን መመረዝ ። 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 እምነት እንዳለው ሰው _  በስክነት  በማሰብ፣ ማን አለብኝ ባዩን አሲዙልን አደብ። 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰 ቻናል  t.me/αmdαlα nαsir ቻናል  t.me/αmdαlα nαsir

ይሄ ነው እድገት እንዲሁ ብልፅግና፣ ሂጃብ ተከልክሎ የእምነት ቅድስና? —————————————— ሰው በሰውነቱ መከበር ሲገባው፣ ሰላም የሚመጣው በእኩልነት ነው፣ የእምነት ነፃነት የሰው ልጅ መብት ነው
ይሄ ነው እድገት እንዲሁ ብልፅግና፣ ሂጃብ ተከልክሎ የእምነት ቅድስና? —————————————— ሰው በሰውነቱ መከበር ሲገባው፣ ሰላም የሚመጣው በእኩልነት ነው፣ የእምነት ነፃነት የሰው ልጅ መብት ነው። —————————————— ዛሬም ነገም ቢሆን የማይታጠፈው፣ ትውልድ የሚዳኘው በታሪክ መነጽር ነው የእምነት ነፃነት መሠረታዊ መብት ነው። —————————————— እቅድ እያወጡ ቀን እየጠበቁ፡ በእምነታችን መርጠው እኛን እያጠቁ፡ ለምን ይሆን ሁሌ የምንገደለው? ምን አጥፍተን ይሆን የምንበደለው!? —————————————— ብሎ የሚጠይቅ ጀግና ስለጠፋ፡ አመፀኛው በዛ ደም አፍሳሹም ከፋ። —————————————— ሰዎች ልጠይቅ ግራ ገባኝ ሁኔታው፡ ሕግ ባለበት ሀገር ምንድነው አላማው? እንተሳሰብ ካልን እንናገር የእውነት፡ በዚህች በኛ ሀገር የት አለ እኩልነት? —————————————— ከትናንት እስካሁን እድሜ ያልመከረህ፡ ፍትህ እኩልነት በአዕምሮህ ያልዞረህ፡ ጥላቻን በዚህ ልክ ማነው ያስተማረህ? ——————————————
በአጭሩ ልንገርህ--
ለተፈጠረበት አይፈራም ለምነቱ፡ ላመነበት ጉዳይ ታልፋለች ህይወቱ። —————————————— በሀይማኖት ሽፋን ሙስሊሙን መበደል፡ በመደመር ስም ሙስሊሙን መግደል፡ ስንቴ ነው ምትከታት ሀገሪቱን ገደል? —————————————— 📕 ወንድም አምዳላ ናሲር ቻናል t.me/αmdαlα nαsir ቻናል  t.me/αmdαlα nαsir

ሐሰነ አል-በስሪይ ማን ናቸው? በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። ሐሰን ኢብን ያሲር የተወለደው በዑመር ኢብን አል-ኸጣብ ዘመን በ21 ሒጅራ በመዲና ነው። አባትና እናቱ ሁለቱም ባሮች ነበሩ። አባቱ ሙስሊሞች በኢራቅ በበስራ እና በዋሲጥ መካከል የምትገኘውን ሚሳን የተባለች ቦታ ሲቆጣጠሩ ተማርኮ ወደ መዲና መጣ። አባቱ የሰሃባው የየዚድ ኢብን ሳቢት አገልጋይ በመሆን እስልምናን ተቀብሎ በመዲና መኖር ጀመረ። በኋላም ኸይሪያህ የተባለች የነቢዩ ﷺ ባለቤት የዑሙ-ሰለማን አገልጋይ አገባና ሐሰን ተወለደ። ዑሙ-ሰለማም ሐሰን ሲወለድ ኸይሪያህን ነፃ አወጣቻት። እንደሚባለው አንድ ቀንም እናቱ ወደ ገበያ ስትሄድ ሐሰን ማልቀስ ሲጀምር ዑሙ-ሰለማ አጠባችው። በዚህም የጡት ልጇ ሆነ።
ሐሰን ያደገው በነቢዩ ﷺ ቤተሰቦች መካከል ሲሆን ዑሙ-ሰለማ ወደተለያዩ ሰሃባዎች በመውሰድ ዱዓዕ ታስደርግለት ነበር። ዱዓዕ ካደረጉለት አንዱ ዑመር ኢብን አል-ኸጣብ ሲሆኑ ❝አላህ ሆይ! የኢስላም አዋቂና በሰዎች ዘንድ የሚወደድ አድርገው።❞ ብለው አላህን ለምነውለታል። ሐሰን ብለው ስም ያወጡለትም ዑመር እንደሆኑ ይነገራል።
ሐሰን በልጅነቱ ቁርኣንን ሐፈዘ። ከዚያም በነቢዩ ﷺ መስጂድ በመቀማመጥ ከበርካታ አንጋፋ ሰሃባዎች ስር ተማረ። ከእነሱም መካከል ዑስማን ኢብን ዐፋን፣ ዐሊይ ኢብን አቡ-ጣሊብ፣ አቡ-ሙሳ አል-አሽዓሪ፣ አቡ-ሑረይራህ፣ ዐነስ ኢብን ማሊክ፣ ዐብደላህ ኢብን ዐባስ፣ ዐብዱላህ ኢብን ዑመር እና ሌሎችም ይጠቀሳሉ። በ36 ሒጅራ በዐሊይ ዘመን ሐሰን የ15 ዓመት ልጅ ሳለ ቤተሰቦቹ ወደ ኢራቅ በስራ በመሄድ ከተሙ። በዚያ የተነሳም ❝ሐሰን-አል በስሪ❞ የሚል ስያሜ ተሰጠው። ሐሰን በወቅቱ በበስራ ይኖሩ በነበሩ በርካታ ሶሃቦች እጅ ፊቅህን፣ ሐዲስን እና ነህውን የተማረ ሲሆን የቁርኣን መምህሩ ሐጣን ኢብን ዐብዱላህ አር-ረቃሺይ፥ የቋንቋ መምህሩ ደግሞ ገጣሚው ኢብን ሱረይ አት-ተሚሚይ ነበሩ። ሐሰን ሰማያዊ ዐይን ያለው መልከመልካም ሲሆን ኢብን ቀዪም ሲናገሩ ❝ሴቶች ለዒድ ቀን ወጥተው ሲመለሱ ከኻጢቡ የበለጠ መልከኛ አላየንም ይሉ ነበር። እሱም ሐሰን አል-በስሪይ ነው።❞ ብለዋል።
ሐሰን ከጥልቀቱ ብዛት በባህር የሚመሰለውን እውቀቱን ከሰበሰበ በኋላ በዚያው በበስራ ማስተማር ጀመረ። በባህሪው ይህንን ዓለም የናቀ ዛሂድ፣ አብዛኛውን ቀን የሚፆም፣ ሌሊቱን በተሐጁድ የሚያሳልፍ፣ ቁርኣን ሲያነብ የሚያለቅስ፣ ብዙም ሳቅ የሌለው፣ ንግግር አዋቂ፣ ለስላሳ፣ የተግባር ሰው፣ ትምህርቱ በማስረጃ የዳበረና ቀጥተኛ በመሆኑ ተቀባይነቱ ከሁሉም ከፍ አለ። በወቅቱ የነበሩ ብዙ ተራኪዎች ነገሮችን የማጋነን ዝንባሌ ስለነበራቸው ከሐሰን በቀር ሁሉም መስጊድ ውስጥ እንዳይተርኩ እስከመታገድ ደረሱ።
በበስራ ይኖሩ የነበሩት ሰሃባው ዐነስ ኢብን ማሊክ የሐሰንን የእውቀት ደረጃ በማየት ሰዎች ሲጠይቋቸው ❝ሐሰንን ጠይቁት። እሱ እኛ የረሳነው የሚያውቀው ይኖራል።❞ ይሉ ነበር። የሐሰን ዕድሜ አብዛኛው በፊትና ያለፈ ነው። አጥፊ መሪዎችን ፊትለፊት የሚጋፈጥ በመሆኑ ምክንያት በበኑ-ዑመያዎች ዘመን ብዙ መከራና መሳደድ ደርሶበታል። ሙዓዊያህ ሞቶ ልጁ የዚድ በተተካ ጊዜ የየዚድን አካሄድ በግልፅ ከተቃወሙት አንዱ ሐሰን አል-በስሪይ ነው። ለበስራ ሰዎችም ከእርስበርስ ውጊያ እንዲታቀቡ ጥሪ አቅርቦላቸው ነበር። በበስራ የተወከለው  አል-ሙሐለብ ኢብን አቢ-ሱፍራህ ❝ይሄ ጠማማ ሸይኽ ሰዎች በአላህ መንገድ እንዳይጋደሉ እያገደ ነውና ከተግባሩ የማይታቀብ ከሆነ የሚገባውን እሰጠዋለሁ።❞ እስከማለት ደረሰ። በኋላም የቁም እስረኛ ተደረገ።
(ዙህድ አል-ሐሰን አል-በስሪ 77)
ሐሰን ከአዋቂነቱ ባለፈ ጂሐድን የሚወድ በጣም ጀግና በመሆኑ በብዙ ውጊያዎች ተሳትፏል። አል-ሙሐለብ ኢብን አቢ-ሱፍራም ይህንን ስለሚያውቅ ሐሰንን ከፊት መስመር ያሰልፈው ነበር። በዐብዱልመልክ ኢብን መርዋን ዘመን ሐጃጅ በኢራቅ እንደተሾመ በሚሰራው ግፍ ከሐሰን ጋር ግጭት ውስጥ ገባ። ሐጃጅም ሊገድለው ይፈልግ ስለነበረ ሐሰን ብዙ  ዘመኑን ከቦታ ቦታ በመዘዋወርና በመደበቅ አሳለፈ። በኋላም ሐጃጅ ሊሞት ሲል የህመሙ ስቃይ ሲበረታበት ሐሰንን ጠርቶ ዱዓዕ እንዲያደርግለት ጠየቀው። ሐሰንም ❝ሰዎችን አታሰቃይ ብዬ አልነገርኩህም ነበርን?❞ አለው። ሐጃጅም ❝እኔ ከአላህ ምህረትን እንድትለምንልኝ አልጠራሁህም። ሞቴን አፍጥኖ ከስቃዩ እንዲገላግለኝ ብቻ ጠይቅልኝ።❞ አለው። ሰዎችም ይህንን ሲሰሙ አለቀሱለት። ከሱለይማን ኢብን ዐብዱልመሊክ በኋላ ዑመር ኢብን ዐብዱልዓዚዝ እንደተተካ ሐሰንን ዋና አማካሪ አደረገው። ሐሰንም በበስራ ቃዲ በመሆን ካለክፍያ ማገልገል አገለገለ።
(ሲየር አዕላም 4/588)
ዑመር ከሞተ በኋላ ሐሰን ኸሊፋዎቹ መንገድ እንዳይስቱና ህዝቡም እንዳይጠፋ በመምከርና በመገሰፅ የሚችለውን ሁሉ አደረገ።
ከሐሰን ታሪክ ጋር አብሮ ከሚነሳው አንዱ የሙዕተዚላዎች ጉዳይ ሲሆን መስራቹ ዋሲል ኢብን አጣዕ የሐሰን ተማሪ ነበረ። ከዚያም አንድ ቀን ሐሰንን ❝ወንጀል የሰራ ሰው አማኝ ነው ከሃዲ?❞ በማለት ጠየቀቸው። ሐሰንም ❝በወንጀሉ ይጠየቃል። ነገርግን ሙስሊም ነው።❞ አለው። ዋሲልም ❝ወንጀል የሰራ ሰው አማኝም ከሃዲም ሊባል አይችልም።❞ በማለት ተሟገተና ትቷቸው ወጣ። በዚህ ጊዜ ሐሰን ❝ዋሲል ከእኛ የወጣ ነው።❞ አለ። ከዚያ በኋላም የዋሲል ተከታዮች ❝ሙዕተዚላዎች❞ ወይም ❝የወጡ❞ ተባሉ።(አል-ፈርቅ በይን አል-ፉሩቅ 118)
ሐሰን አል-በስሪይ በዚህ ሁኔታ ዘመኑን ካሳለፈ በኋላ በረጀብ ወር 110 ሒጅራ በጁሙዓ ዕለት በ86 ዓመቱ ይህንን ዓለም ተሰናበተ። ቀብሩም በዚያው በበስራ የተፈፀመ ሲሆን ህዝቡ ለሽኝት ወጥቶ ስለነበረ ከተማዋ ባዶ ሆኖ አሳለፈች። ስለ ሐሰን አል-በስሪይ ልቅና በዘመኑ የነበሩትም በኋላ የመጡትም የኢስላም ዑለማዎች መስክረውለታል። ለአብነት ኢብኑ ሰዕድ ❝አጥ-ጠባቃት❞ በተሰኘው ዝነኛ መጽሐፋቸው ❝ሐሰን አል-በስሪይ እውቀቱ ሰፊ፣ ዐቢድ፣ ግልጽ ተናጋሪ፣ መልከመልካምና በጣም ጀግና ነው። ነቢይ ቢሆን እንጅ እርሱን የሚመስል የለም።❞ ብለዋል። ኢብን ቡርዳህ ❝ከነቢዩ ሶሐቦች ጋር እንደ እርሱ የሚመሳሰል አላየንም።❞ ሲሉ ተናግረዋል። በተመሳሳይ አቡ-ቀታዳህ ❝እንደ አል-ሐሰን አመለካከቱ የዑመር ኢብን አል-ኸጣብን የሚመስል ሰው አላየሁም።❞ ብለዋል። በአንድ ወቅት አጧዕ ኢብን አቢ-ረባህ ለሞተ ሰው ቁርኣን ስለመቅራት ሲጠየቅ ❝ለሟች እንደሚቀራ አልተማርንም ወይም አልሰማንም።❞ አለ። ጠያቂውም ❝አል-ሐሰን ግን መቅራት አለብን ይላል።❞ ሲለው ❝እንግዲያውስ ይህንኑ ተከተል። ምክንያቱም አል-ሐሰን ታላቅ ዐሊም ነውና።❞ በማለት መልሶለታል። ኻሊድ ኢብኑ ሰፍዋን የአል-ሐሰን አል-በስሪ የቅርብ ጎረቤት ነበር። በአንድ ወቅት ስለ ሐሰን ሲናገር ❝እንደ እርሱ ያለ ሰው አይቼ አላውቅም። ውጫዊ ገጽታው ከውስጣዊ ማንነቱ ጋር አንድ ነው። ንግግሩም ከተግባሩ ጋር ይገጥማል። መልካም ነገርን ካዘዘ ቀድሞ የሚተገብረው እርሱ ነው። ከመጥፎ ነገር ሲከለክልም ከሁሉ በላይ እርሱ ይርቃል። ከሌሎች ሰዎች ምንም ፍላጎት የለውም። ነገር ግን ሰዎች ወደ እርሱ ፈላጊዎች ነበሩ።❞ ብሏል። የሐሰንንና የዑመርን የተዋዱዕ ሰላት ያየው የዚድ ኢብን ሐውሻብ ደግሞ ❝ሐሰን አል-በስሪይ እና ዑመር ኢብን ዐብዱልዓዚዝን ሲሰግዱ ላያቸው ጀሃነም ከእነሱ በቀር ለሌላ የተፈጠረች አይመስለውም።❞ ሲል ተናግሯል።
(ሲፋቱ ሰፍዋህ 1/156)
© ሰልማን
t.me/comparativeRelgion

(ሲፋቱ ሰፍዋህ 1/156
)     © ሰል
ማን t.me/comparativeRelg
ion

Comparative Religion - Статистика и аналитика Telegram-канала @comparativerelgion