SDA የትንቢት ጹሑፎች
Открыть в Telegram
“ዘመኑ ቀርቦአል፤ እንግዲህ ይህን የትንቢት ቃል የሚያነብ ብፁዕ ነው፤ የሚሰሙትና የተጻፈውንም የሚጠብቁ ብፁዓን ናቸው።” — ራእይ 1፥3 (አዲሱ መ.ት)
Больше2 254
Подписчики
+324 часа
+227 дней
+8330 день
Загрузка данных...
Похожие каналы
Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июль '26
июль '26
+107
в 0 каналах
июнь '26
+112
в 5 каналах
Get PRO
май '26
+93
в 1 каналах
Get PRO
апрель '26
+75
в 0 каналах
Get PRO
март '26
+46
в 0 каналах
Get PRO
февраль '26
+32
в 0 каналах
Get PRO
январь '26
+43
в 2 каналах
Get PRO
декабрь '25
+27
в 1 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+35
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '25
+37
в 1 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+32
в 1 каналах
Get PRO
август '25
+41
в 0 каналах
Get PRO
июль '25
+70
в 1 каналах
Get PRO
июнь '25
+64
в 2 каналах
Get PRO
май '25
+36
в 0 каналах
Get PRO
апрель '25
+51
в 0 каналах
Get PRO
март '25
+66
в 0 каналах
Get PRO
февраль '25
+59
в 2 каналах
Get PRO
январь '25
+156
в 4 каналах
Get PRO
декабрь '24
+141
в 2 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+121
в 2 каналах
Get PRO
октябрь '24
+268
в 3 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+92
в 2 каналах
Get PRO
август '24
+85
в 0 каналах
Get PRO
июль '24
+76
в 0 каналах
Get PRO
июнь '24
+75
в 0 каналах
Get PRO
май '24
+71
в 0 каналах
Get PRO
апрель '24
+27
в 1 каналах
Get PRO
март '24
+18
в 2 каналах
Get PRO
февраль '24
+17
в 0 каналах
Get PRO
январь '24
+37
в 4 каналах
Get PRO
декабрь '23
+18
в 1 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+18
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '23
+30
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+14
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+16
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+24
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+24
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+11
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+23
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+27
в 0 каналах
Get PRO
февраль '23
+18
в 0 каналах
Get PRO
январь '23
+41
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '22
+51
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '22
+30
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '22
+22
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '22
+27
в 0 каналах
Get PRO
август '22
+30
в 0 каналах
Get PRO
июль '22
+57
в 0 каналах
Get PRO
июнь '22
+40
в 0 каналах
Get PRO
май '22
+23
в 0 каналах
Get PRO
апрель '22
+11
в 0 каналах
Get PRO
март '22
+52
в 0 каналах
Get PRO
февраль '22
+52
в 0 каналах
Get PRO
январь '22
+27
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '21
+20
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '21
+222
в 0 каналах
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 28 июля | +4 | |||
| 27 июля | +3 | |||
| 26 июля | +4 | |||
| 25 июля | +4 | |||
| 24 июля | +5 | |||
| 23 июля | +5 | |||
| 22 июля | +5 | |||
| 21 июля | +2 | |||
| 20 июля | +1 | |||
| 19 июля | +3 | |||
| 18 июля | +5 | |||
| 17 июля | +8 | |||
| 16 июля | +5 | |||
| 15 июля | +3 | |||
| 14 июля | +6 | |||
| 13 июля | +4 | |||
| 12 июля | +1 | |||
| 11 июля | +4 | |||
| 10 июля | +5 | |||
| 09 июля | +1 | |||
| 08 июля | +4 | |||
| 07 июля | +5 | |||
| 06 июля | +1 | |||
| 05 июля | +3 | |||
| 04 июля | +8 | |||
| 03 июля | +3 | |||
| 02 июля | +1 | |||
| 01 июля | +4 |
Посты канала
| 2 | https://youtu.be/HaIGZuCDysg?si=FeqgkE9ae6n20qls | 935 |
| 3 | Audio from Dubushe | 1 169 |
| 4 | https://youtu.be/LWVaZIU6UBc?si=gCSRGYQHe-BL98Ys | 1 194 |
| 5 | Audio from Mesay D Dubushe | 1 671 |
| 6 | Happy Sabbath from Ethiopian SDA Church South Africa, DURBAN | 1 484 |
| 7 | https://t.me/+QHyQ7qCncSFlYmE0 | 1 340 |
| 8 | ይህንን ቪዲዮ እንደ SDA አባልነታችን እንዴት እንመለከታለን ? እንዲህ ይቻላል እንዴ?🤔 | 1 660 |
| 9 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 4:- የእግዚአብሔር የመጨረሻው ዘመን ቤተክርስቲያን
(የመጨረሻ ክፍል)
➡️ በተሰጣቸው ብርሃን ይፈረዳሉ
የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን በቤተ መቅደስ ሚዛን ትመዘናለች። የምትፈረደው በተሰጡአት አጋጣሚዎችና ጥቅሞች ነው። መንፈሳዊ ልምምዷ ክርስቶስ ታላቅ ዋጋ በመክፈል ከሰጣት ጥቅሞች ጋር የማይጣጣም ከሆነ የተሰጡአት በረከቶችም ለተሰጣት ሥራ ካላዘጋጁአት፣ በራሷ ፈቃድ “ቀለሽ ተገኘሽ" የተባለው አረፍተ ነገር ይነገርባታል። በተሰጣት ብርሃንና በተሰጡአት ዕድሎች ትፈረዳለች።..
አገልግሎት እንዲሰጡ በተገነቡ ውድ በሆኑ ሕንጻዎች ውድመት የተገለጡ አስፈሪ ተግሳጾች [ባትል ክሪክ የነበረው በዓለም ላይ ትልቁና እጅግ ታዋቂ የነበረው የአድቬንቲስት የጤና ተቋም፣ እ.አ.አ. የካቲት 18፣ 1902 ዓ.ም ተቃጥሎ አመድ ሆኗል፡፡] ለእኛ እንዲህ የሚል መልእክት ያስተላልፋሉ፡- “አሁንም ከወዴት እንደወደቅህ አስብ፣ ንስሃም ግባ፣ የቀደመውንም ሥራ ሥራ።" (Revelation 2:5)....
በራሷ ወደ ኋላ ማፈግፈግ እየቦካች (እየኮመጠጠች) ያለች ቤተ ክርስቲያን ንስሃ ካልገባችና ካልተለወጠች ራሷን እስከምትጠላ ድረስ የሥራዋን ፍሬ ትበላለች። ክፉን ተቃውማ መልካምን ስትመርጥ፣ ራሷን በማዋረድ እግዚአብሔርን ስትሻ እና በክርስቶስ የቀረበላትን ታላቅ ጥሪ ስትቀበል ትፈወሳለች። ያኔ እግዚአብሔር በሰጣት የዋህነትና ንጽህና ከምድራዊ ጥልፍልፍ ተለይታ እውነት አርነት እንዳወጣት በማሳየት ትኖራለች። እንዲህ ሲሆን አባላቷ በእርግጥ የእግዚአብሔር ምርጦችና የእርሱ ተወካዮች ይሆናሉ።— Testimonies for the Church 8:247-251 (April 21, 1903).
➡️ የእሥራኤላውያን ታሪክ ለእኛ ማስጠንቀቂያ ነው
በዚህ የመጨረሻ ዘመን የጥንት እሥራኤላውያንን ያጋጠመው ዓይነት ተመሳሳይ አደጋ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ያጋጥማቸዋል። እግዚአብሔር የሚሰጣቸውን ማስጠንቀቂያዎች የማይቀበሉ ሁሉ የጥንት እሥራኤላውያን ባለማመናቸው ምክንያት በወደቁባቸው አደጋዎች ውስጥ ይወድቃሉ፡፡ ካለማመናቸው የተነሳም ወደ እረፍቱ ሳይገቡ ይቀራሉ። የጥንቶቹ እሥራኤላውያን በማያምን ልባቸውና ፈቃዳቸውን ካለማስገዛታቸው የተነሣ መከራ ደርሶባቸዋል። በመጨረሻም የተለየ ሕዝብ የመሆን መብት ያጡት በራሳቸው አለማመን፣ በራስ በመተማመናቸው፣ ንስሃ ባለመግባታቸው፣ በአእምሮ እውርነታቸውና በልበ ደንዳናነታቸው ምክንያት ነበር። በእነርሱ ታሪክ አማካኝነት በእኛ ፊት የአደጋ ምልክት ከፍ ብሎ ተሰቅሏል።
“ወንድሞች ሆይ፥ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስከዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፤... የመጀመሪያ እምነታችንን እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ፥ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና።” (ዕብራውያን 3:12, 14)። Letter 30, 1895.
➡️ በጦር ሜዳ ያለችው ቤተ ክርስቲያን ፍጹም አይደለችም
በጦር ሜዳ ያለችው ቤተ ክርስቲያን ድል የነሳች አይደለችም፣ ምድርም ሰማይ አይደለም። ቤተ ክርስቲያን ለዚህ ሕይወትና ለወደፊቱ ዘላለማዊ ሕይወት ለመሰልጠን፣ ለመታረምና እውቀት ለማግኘት በክርስቶስ ትምህርት ቤት እየተማሩ ካሉ ተሳሳችና ፍጽምና ከጎደላቸው ወንዶችና ሴቶች የተውጣጣች ነች።— The Signs of the Times, January 4, 1883.
አንዳንድ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄዱ ሁሉም ነገር ተሟልቶ ንጹህና ፍጹም ከሆኑ ሰዎች ጋር ብቻ የሚገናኙ ይመስላቸዋል። ለእምነታቸው ቅናት ስላላቸው በቤተ ክርስቲያን አባላት ውስጥ ስህተት ሲያዩ “ዓለምን ትተን የመጣንበት ምክንያት ከክፉ ጠባያት ጋር ግንኙነት (ሕብረት) እንዳይኖረን ነበር፤ ነገር ግን እዚህም ክፋት አለ" ይላሉ። በምሳሌው የነበሩ ባሪያዎች እንደጠየቁት “እንክርዳዱ ከወዴት መጣ?” በማለት ይጠይቃሉ፡፡ ነገር ግን ጌታ ቤተ ክርስቲያን ፍጹም ናት ወደሚል ማጠቃለያ የሚያመጣንን ማረጋገጫ ስላልሰጠን ተስፋ መቁረጥ የለብንም፡፡ በጦርነት ላይ ያለችውን ቤተ ክርስቲያን እንደ አሸናፊዋ ንጹህ ቤተ ክርስቲያን አድርገን የምናይ ከሆነ ለእውነት ያለን ቅናታችን ሁሉ ስኬታማ ሳይሆን ይቀራል። - Testimonies to Ministers and Gospel Workers, 47 (1893).
➡️ አሸናፊዋ ቤተ ክርስቲያን ታማኝና ክርስቶስን የምትመስል ትሆናለች
ሥራው በቶሎ ሊዘጋ ነው፡፡ ታማኝነታቸውን ያረጋገጡ በጦርነት ላይ ያለችው ቤተ ክርስቲያን አባላት የአሸናፊዋ ቤተ ክርስቲያን አባላት ይሆናሉ።— Evangelism, 707 (1892).
የክርስቶስ ሕይወት በእግዚአብሔር ፍቅር መለኮታዊ መልእክት የተሞላ ነበር። ይህንን ፍቅር በሙላት ለማጋራት ጥልቅ ምኞት ነበረው። ከፊቱ ርኅራኄ ይንጸባረቅ ነበር። ጸባዩ በጸጋ፣ ራስን ዝቅ በማድረግ፣ በእውነትና በፍቅር የተሞላ ነበር። እያንዳንዱ በጦር ሜዳ ያለችው የእርሱ ቤተ ክርስቲያን አባል የአሸናፊዋ ቤተ ክርስቲያን አባል መሆን ከፈለገ ተመሳሳይ ብቃቶችን ማሳየት አለበት።—Fundamentals of Christian Education, 179 (1891).
@MesayD
ምዕራፍ 5 ይቀጥላል ... | 1 943 |
| 10 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 4:- የእግዚአብሔር የመጨረሻው ዘመን ቤተክርስቲያን
(ክፍል ሰባት)
➡️ መንፈሳዊ መነቃቃት አሁንም ያስፈልጋል
መታመንን በሚጠይቁ የሀላፊነት ቦታዎች የተቀመጡ ሰዎች የእግዚአብሔርን ፈቃድና መንገድ ተከትለው ቢሆን ኖሮ ባለፈው የጄኔራል ኮንፍራንስ [1901] ስብሰባ ላይ ሊከናወን ይችል ስለነበረው ሥራ አንድ ቀን በእኩለ ቀን ጊዜ እየጸፍኩ ነበር። ትልቅ ብርሐን የተሰጣቸው ሰዎች በብርሃኑ አልተመላለሱም። ስብሰባው ተዘግቷል፣ እረፍትም አልተደረገም፡፡ ሰዎች ማድረግ እንደሚገባቸው ራሳቸውን በእግዚአብሔር ፊት ዝቅ አላደረጉም፣ መንፈስ ቅዱስም አልተሰጠም።
ራሴን በሳትኩ ሰዓት እስከዚህ ድረስ የጻፍኩ ሲሆን በባትል ክሪክ እየሆነ ያለውን ትዕይንት የምመለከት መሰለኝ፡፡
በቤተ መቅደሱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተሰብስበን ነበር። ጸሎት ተደርጎ መዝሙር ተዘመረና እንደገና ጸሎት ተደረገ፡፡ ልባዊ የሆነ ተማዕጽኖ ወደ እግዚአብሔር ቀረበ። በስብሰባው ላይ የመንፈስ ቅዱስ መገኘት ታይቶ ነበር።…
በቦታው ከተገኙት መካከል ማንም ልባዊ ኑዛዜ ማድረግ እስከማይችል ድረስ በትዕቢት የተወጠረ ሰው አልነበረም፡፡ በዚህ ሥራ ውስጥ ይመሩ የነበሩ ሰዎች ተጽእኖ ማሳደር የሚችሉ ሰዎች ነበሩ፣ ነገር ግን ከዚህ በፊት ኃጢአቶቻቸውን ለመናዘዝ ድፍረት አልነበራቸውም ነበር።
በቤተ መቅደሱ ውስጥ ከዚህ በፊት በፍጹም ተሰምቶ የማይታወቅ ደስታ ነበር። ራሴን ከሳትኩበት ተነሳሁና ለተወሰነ ጊዜ የት እንደነበርኩ ማሰብ አቃተኝ፡፡ ብዕሬ እስካሁን በእጄ ነበር። እንዲህ የሚሉ ቃላት ተነገሩኝ፦ “ይህ ሊሆን ይችል ነበር። ጌታ ይህን ሁሉ ለሕዝቡ ሊያደርግ እየጠበቀ ነበር። ሰማይ በሙሉ ቸርነትን ለማድረግ እየጠበቀ ነበር።" ባለፈው የጄኔራል ኮንፍራንስ ጊዜ የተሟላ ሥራ ተሰርቶ ቢሆን ኖሮ የት ልንሆን እንችል እንደነበር አሰብኩ። -Testimonies for the Church 8:104-106 (January 5, 1903).
በሌሊት በፊቴ ያለፉ ትዕይንቶች ጥልቅ ስሜት ፈጥረውብኛል። ትልቅ እንቅስቃሴ--የመነቃቃት ሥራ በብዙ ቦታዎች እየተከናወነ ያለ መሰለኝ፡፡ ሕዝባችን ለእግዚአብሔር ጥሪ ምላሽ በመስጠት በመስመር እየሄዱ ነበር።—Testimonies to Ministers and Gospel Workers, 515 (1913). (ኤለን ኋይት በ1913 የጄኔራል ኮንፍራን ወቅት ካስተላለፈችው የመጀመሪያ መልእክት የተወሰደ።]
➡️ እግዚአብሔር በሕዝቡ ላይ ያለው ትዕግሥት
ቤተ ክርስቲያን በአሳዛኝ ሁኔታ አዳኝዋ የሚጠብቅባትን ሳትፈጽም ቀርታለች። ሆኖም እግዚአብሔር ከሕዝቡ አልተለየም። ነገር ግን አሁንም ይታገሳቸዋል። ይህንን የሚያደርገው በእነርሱ ውስጥ መልካምነት ስለተገኘ ሳይሆን ስሙ በእውነትና በጽድቅ ጠላቶች ፊት እንዳይዋረድና የሰይጣን ወኪሎች የእግዚአብሔርን ሕዝብ በማጥፋት ድል እንዳያገኙ ነው፡፡ በአመጸኝነታቸው፣ ባለማመናቸውና በሞኝነታቸው ታግሷቸዋል። በአስደናቂ ትዕግሥትና ርኅራኄ ቀጥቷቸዋል። መመሪያውን ቢያዳምጡ ኖሮ በዘላለማዊ ድነት በማዳንና የጸጋው ኃይል ዘላለማዊ ሐውልቶች በማድረግ ከግትር ዝንባሌዎቻቸው ያነጻቸው ነበር። -The Signs of the Times, November 13, 1901.
ቤተ ክርስቲያን ደካማና ጉድለት ያለባት ብትሆንም ክርስቶስ ከፍተኛ ትኩረት የሚያደርግባት ብቸኛ አካል እንደሆነች ማስታወስ አለብን። ስለ እርሷ ከልብ በማሰብ ያለማቋረጥ ነቅቶ እየጠበቃትና በመንፈስ ቅዱስ እያበረታታት ይገኛል።—Selected Messages 2:396 (1902).
➡️ እግዚአብሔር ታማኞች ከሆኑት ጋር ይሰራል
ጌታ ኢየሱስ ሁል ጊዜ የሚያገለግሉት የተመረጡ ሕዝቦች ይኖሩታል። አይሁዶች የሕይወት ልዑል የሆነውን ኢየሱስን አልቀበል ባሉ ጊዜ መንግሥትን ከእነርሱ ወሰደና ለአህዛብ ሰጠ። እግዚአብሔር በእያንዳንዱ የሥራ ዘርፍ በዚህ መርህ መስራቱን ይቀጥላል።
ቤተ ክርስቲያን ለጌታ ያላትን ታማኝነት ስታጎድል፣ የፈለገውን ያህል ሥልጣን ቢኖራቸውም፣ መጠራታቸውም የፈለገውን ያህል ታላቅና ቅዱስ ቢሆንም፣ እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር መስራቱን አይቀጥልም፡፡ አስፈላጊ ሀላፊነቶችን ለመሸከም ሌሎች ይጠራሉ። ነገር ግን እነዚህም ነፍሳቸውን ከስህተት ድርጊቶች ካላነጹ እና በየወሰናቸው ንጹህና ቅዱስ መርሆዎችን ካልመሰረቱ፣ ጌታ በአሰቃቂ ሁኔታ መከራ በማምጣት ዝቅ ያደርጋቸዋል፡፡ እነርሱም ካልተናዘዙ ከቦታቸው በማስወገድ መሳለቂያ ያደርጋቸዋል።—Manuscript Releases 14:102 (1903).
@MesayD
ይቀጥላል .... | 1 499 |
| 11 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 4:- የእግዚአብሔር የመጨረሻው ዘመን ቤተ ክርስቲያን
(ክፍል ስድስት)
➡️ በሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ድርጅት መተማመን እንደገና ተረጋገጠ
አሁን እግዚአብሔር የመሰረተውን መሰረት ትተን መውጣት አንችልም። ወደ አዲስ ድርጅት መግባት ማለት እውነትን መካድ ስለሆነ አሁን ወደ ማንኛውም አዲስ ድርጅቱ መግባት አንችልም።- Selected Messages 2:390 (1905).
በዓለም ላይ ላሉ አድቬንቲስቶች ይህንን እንድል ታዝዣለሁ፣ እግዚአብሔር እንደ ሕዝብ የተለየ ከቡር ሕዝብ እንድንሆን ጠርቶናል። በምድር ላይ ያለችው ቤተ ክርስቲያን እስከ ዘመን መጨረሻ ድረስ በመንፈስና በሰራዊት ጌታ ምክር ፍጹም የተባበረች እንድትሆን አስቀምጦአታል።- Selected Messages 2:397 (1908).
አንዳንድ ጊዜ የሥራው አጠቃላይ ሀላፊነት የተሰጣቸው ጥቂት ቡድኖች በጄኔራል ኮንፍራንስ ስም የእግዚአብሔርን ሥራ የሚገድቡ ጥበብ የጎደላቸውን ዕቅዶች ለመተግበር ሲሹ በእነዚህ ጥቂት ሰዎች የተወከለውን የጄኔራል ኮንፍራንስ ድምጽ እንደ እግዚአብሔር ድምጽ እንደማልቆጥር ተናግሬያለሁ። ይህ ማለት ግን ከሁሉም የሥራ መስኮች ተውጣጥተው በአግባቡ የተሾሙ የጄኔራል ኮንፍራንስ ተወካዮች ውሳኔዎች መከበር የለባቸውም ማለት አይደለም።
ከሁሉም የምድር ክፍሎች የተውጣጡ የቤተ ክርስቲያን ተወካዮች በጄኔራል ኮንፍራንስ ላይ ሲሰበሰቡ ሥልጣን እንዲኖራቸው እግዚአብሔር ቀብቷቸዋል። አንዳንዶች ሊፈጽሙ የሚችሉት ስህተት አደጋ ያለው ሊሆን የሚችለው እግዚአብሔር ለሥራው ስኬትና ወደ ፊት መሄድ በፍርድ ለቤተ ክርስቲያንና ለተሰበሰበው የጄኔራል ኮንፍራንስ ድምጽ የሰጠውን ሥልጣንና ተጽእኖ ሙሉ በሙሉ ለአንድ ሰው ወይም ለጥቂት የሰዎች ቡድን አእምሮና ውሳኔ አሳልፎ በመስጠት ነው። Testimonies for the Church 9:260, 261 (1909).
እግዚአብሔር ማንም ባይቀበል ወይም ቢንቅ ከበደል ነጻ መሆን የማይችልበትን ኃይልና ሥልጣን ለቤተ ክርስቲያኑ ሰጥቷል፤ የቤተ ክርስቲያንን ሥልጣን የሚንቅና የማይቀበል የእግዚአብሔርን ሥልጣን እየናቀ ነው።- The Acts of the Apostles, 164 (1911).
የእሥራኤል አምላክ እስካሁን ሕዝቡን እየመራ በመሆኑና ወደፊትም እስከ መጨረሻው ድረስ ከእነርሱ ጋር እንደሚሆን በመገንዘቤ ተደፋፍሬያለሁ ተባርኬያለሁም።—Selected Messages 2:406 (1913). [በጄኔራል ኮንፍራንስ ስብሰባ ጊዜ ለሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን ኤለን ኋይት ከሰጠችው የመጨረሻ መልእክት የተወሰደ ነው። እነዚህ እርግጠኛ እንዲሆኑ የተሰጡ ቃላት በጄኔራል ኮንፍራንስ ስብሰባ ላይ የጄኔራል ኮንፍራንስ ፕሬዝደንት በሆኑት በኤ ጂ ዳንኤልስ እ.አ.አ ግንቦት 27፣ 1913 ዓ.ም. ተነበው ነበር።]
➡️ በደብሊዩ ሲ የተነገረ ዓረፍተ ነገር
እናቴ የቅሬታዋን ቤተ ክርስቲያን ልምምድና ሌላ ቤተ ክርስቲያን እስኪወጣ ድረስ ሙሉ ክህደት እንዲከሰት እግዚአብሔር እንደማይፈቅድ ያስተማረችውን አዎንታዊ ትምህርቷን እንዴት ትመለከት እንደነበር ነገርኳት [ለሚስስ ሊዳ እስኮት)።—W..C. White to E. E. Andross, May 23, 1915, White Estate Correspondence File.
@MesayD
ይቀጥላል ... | 1 451 |
| 12 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 4:- የእግዚአብሔር የመጨረሻው ዘመን ቤተ ክርስቲያን
(ክፍል አምስት)
➡️ ሀላፊነትን ለማጋራት የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ
አሁን የምንፈልገው እንደገና መደራጀት ነው። ከመሰረቱ ጀምረን ልዩ በሆነ መርህ ላይ መገንባት እንፈልጋለን፡፡….
በተለያዩ አገሮች ባሉን ልዩ ልዩ ድርጅቶች፣ የትምህርት ተቋማት እና በተለያዩ ቦታዎችና ግዛቶች ባሉ ኮንፍራንሶች የሥራ መሪ የሆኑ ሰዎች አሉን፡፡ እነዚህ ሁሉ መፈጸም ያለባቸውን እቅዶች በመቅረጽና በማስተካከል ድምጽ እንዲኖራቸው እንደ ተወካዮች ሆነው መቆም አለባቸው፡፡ ጠቅላላውን ሰፊ የሥራ መስክ ለመከታተል ከአንድ ወይም ከሁለት ወይም ከሶስት ሰዎች በላይ መሆን አለባቸው። ሥራው ትልቅ ስለሆነ መሰራት ላለበት ሥራ ሁሉ ማቀድ የሚችል አንድ ሰብአዊ አእምሮ የለም።....
ይህንንም ሆነ ያንን የሥራ ዘርፍ ለመቆጣጠር የሚያስችል ንጉሣዊ ሥልጣን እግዚአብሔር እንዳልሰጠን መግለጽ እፈልጋለሁ። በየአቅጣጫው ሥራውን ለመቆጣጠር በሚደረግ ጥረት ምክንያት ሥራው በጣም ከፍተኛ በሆነ ሁኔታ ተገትቷል። ተሃድሶና እንደገና መደራጀት ያስፈልጋል፡፡ ኃይልና ብርታት አስፈላጊ ለሆኑ ኮሚቴዎች መሰጠት አለበት።" [From Ellen White's opening address on April 2, 1901, to the General Conference Session in Battle Creek.] The General Conference Bulletin, April 3, 1901, pp. 25, 26.
አዳዲስ ኮንፍራንሶች መመስረት አለባቸው። በአውስትራሊያ የተቋቋማው ኮንፍራንስ የተመሰረተው በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ነው። ምክርን ለመጠየቅ ብዙ ሺህ ማይሎችን አቋርጦ ወደ ባትል ክሪክ መላክና ለመልስ ሳምንታትን መጠበቅ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ምን መደረግ እንዳለበት በቦታው ያሉ ትክክለኛ አቋም ያላቸው ሰዎች መወሰን አለባቸው።- The General Conference Bulletin, April 5, 1901, pp. 69, 70.
➡️ እ.አ.አ. የ1909 ዓ.ም የጄኔራል ኮንፍራንስ ስብሰባ ምላሽ ሰጠ
ይህ ኮንፍራስ ከተጀመረ ወዲህ በመካከላችን ያለው ማን ነው ብላችሁ ትገምታላችሁ? በዚህ ዓይነቱ ስብሰባ ላይ የሚያስጠሉ ሁኔታዎችን የተቆጣጠረው ማን ነው? በዚህ ምኩራብ/አዳራሽ መካከል ወደ ላይና ወደ ታች የተመላለሰው ማን ነው? የሰማይ አምላክና መላእክቱ ናቸው፡፡ ወደዚህ የመጡት ሊበታትኑአችሁ ሳይሆን ትክክለኛና ሰላም የተሞላ አእምሮ ሊሰጡአችሁ ነው። በመካከላችን የነበሩት እግዚአብሔር ያቀደው ሥራ እንዲሰራና እንዳይገታ የእግዚአብሔርን ሥራ ለመስራትና የጨለማ ኃይሎችን ወደ ኋላ ለመመለስ ነው። የእግዚአብሔር መላእክት በመካከላችን ሲሰሩ ነበር።….
በዚህ ስብሳባ ላይ ነገሮች የተከናወኑበትን መንገድ ተመልከቼ የተደነቅኩትን ያህል በሕይወቴ ያስደነቀኝ ምንም ነገር የለም። ይህ የእኛ ሥራ አይደለም፡፡ ያደረገው እግዚአብሔር ነው። ይህን በተመለከተ መመሪያ ተሰጥቶኝ ነበር፣ ነገር ግን በዚህ ስብሰባ ላይ ውጤቱ እስኪሰራ ድረስ ይህንን መመሪያ መገንዘብ አልቻልኩም ነበር። በዚህ ጉባኤ ውስጥ የእግዚአብሔር መላእክት ወደ ላይና ወደ ታች ሲመላለሱ ነበር። ይህን ነገር እያንዳንዳችሁ እንድታስታውሱት የምፈልግ ሲሆን እግዚአብሔር የሕዝቡን ቁስሎች እፈውሳለሁ ማለቱንም እንድታስታውሱ እፈልጋለሁ።—The General Conference Bulletin, April 25, 1901, pp. 463, 464.
በጄኔራል ኮንፍራስ ስብሰባ ጊዜ እግዚአብሔር ለሕዝቡ በኃይል ሰርቷል። ስለዚያ ስብሰባ በማስታውስበት ጊዜ ሁሉ ጣፋጭ የሆነ የአክብሮት ስሜት ወደ አእምሮዬ በመምጣት ለነፍሴ የአመስጋኝነትን ግለት ይልካል። አዳኛችን የሆነውን የጌታን አስደናቂ እርምጃዎች ተመልክተናል። ሕዝቡን ነጻ ስላወጣ ቅዱስ ስሙን እናወድሳለን። The Review and Herald, November 26, 1901.
ጄኔራል ኮንፍራንስ ተለያይተው ባሉ ኮንፍራንሶች ሁሉ ላይ አምባገነንነትን እንዳያሳይ የዩኒየን ኮንፍራንሶችን ማደራጀት አስፈላጊ ነበር። ለኮንፍራንስ የተሰጠው ሥልጣን አንድ ወይም ሁለት ወይም ስድስት ሰዎችን ማዕከል ያደረገ መሆን የለበትም፡፡ በተለያዩ ዲቪዥኖች ላይ የሰዎች መማክርት ጉባኤ መኖር አለበት። Manuscript 26, 1903 (April 3). [በ1901 ዓ.ም በተካሄደው የጄኔራል ኮንፍራንስ ስብሰባ ላይ ስለተደረጉ የአደረጃጀት ለውጦች ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት እንሳይክሎፒዲያን ይመልከቱ (Vol. 10 of the Commentary Reference Series), Revised Edition, pp. 1050-1053.]
@MesayD
ይቀጥላል ... | 1 383 |
| 13 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 4:- የእግዚአብሔር የመጨረሻው ዘመን ቤተ ክርስቲያን
(ክፍል አራት)
➡️ ጥበብ የሌላቸው (ሞኝ) መሪዎች ለእግዚአብሔር አይናገሩም
ሥራው እንዴት መሰራት እንዳለበት በመምከር ረገድ ሥልጣን እንዳለው ይታይ የነበረው ከባትል ክሪክ ይወጣ የነበረው ድምጽ የእግዚአብሔር ድምጽ መሆኑ ቀርቷል። Manuscript Releases 17:185 (1896).
የጄኔራል ኮንፍራንስን ድምጽ እንደ እግዚአብሔር ድምጽ አድርጌ እወስድ የነበረው ከተወሰኑ ዓመታት በፊት ነበር።- Manuscript Releases 17:216 (1898).
በአንድ ወቅት ጄኔራል ኮንፍራንስ የእግዚአብሔር ድምጽ እንደሆነ እናምን እንደነበረው እነዚህም ሰዎች ለሕዝቡ እንደ እግዚአብሔር ድምጽ ለመሆን በተቀደሰ ቦታ የመቆማቸው ጉዳይ ጊዜ አልፎበታል። The General Conference Bulletin, April 3, 1901, p.25.
➡️ አዲስ የኃይማኖት ድርጅት አያስፈልግም
ከምስክሮች ውስጥ ስለ ምህረት በር መዘጋትና በእግዚአብሔር ሕዝቦች መካከል ስለሚኖረው ብጠራ የሚናገሩ አንዳንድ ጽሁፎችን በመውሰድ ከዚህ ሕዝብ መካከል ንጹህና ቅዱስ ሕዝብ እንደሚነሳ ትናገራለህ። አሁን ይህ ሁሉ ጠላትን ያስደስተዋል። አንተ ያለህን አመለካከት ብዙዎች ተቀብለው ቢናገሩና ቢፈጽሙ ኖሮ በሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ ጥራዝ ነጠቅ መነቃቃት ይፈጠር ነበር። ሰይጣን የሚሻው ይህን ነው::—Selected Messages 1:179 (1890).
እግዚአብሔር የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያንን ባቢሎን እንድትልና ከእርሷ እንዲወጡ ሰዎችን እንድትጠራ መልእክት አልሰጠህም። የዚህን ዓይነት መልእክት የሚቃወም ጽኑ ብርሃን እግዚአብሔር ስለሰጠኝ የምታቀርባቸው ምክንያቶች በሙሉ በእኔ ዘንድ ቦታ የላቸውም።....
እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያኑን እንደሚወድ አውቃለሁ፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንድትዝረከረክና ወደ ጥቃቅን አቶሞች እንድትከፋፈል አያስፈልግም፡፡ በዚህ ነጥብ ላይ ትንሽ ስምምነት እንኳን የለም። የዚህ ዓይነት ነገር እንደሚሆን የሚደግፍ ትንሽ ማስረጃ እንኳን የለም። -Selected Messages 2:63, 68, 69 (1893).
ወንድሞቼ ሆይ፣ እግዚአብሔር ሥራውን የሚሰራበት የተደራጀ አካል እንዳለው እነግራችኋለሁ። ማንም ቢሆን ከዚህ ከተደራጀ የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት ከሚጠብቅ ሕዝብ ሲለይ እና ቤተ ክርስቲያንን በራሱ ሰብአዊ ሚዛን መመዘንና በእነርሱ ላይ መፍረድ ሲጀምር፣ ያኔ እግዚአብሔር እየመራው አለመሆኑን መረዳት ትችላላችሁ፡፡ ይህ ግለሰብ ያለው በተሳሳተ መንገድ ላይ ነው። - Selected Messages 3:17, 18 (1893).
➡️ እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር በሥርዓት ያስቀምጠዋል
ሥራው እንደማይሳካ አድርጎ መፍራትና መጠራጠር አያስፈልግም፡፡ ሥራውን የሚመራው እግዚአብሔር ስለሆነ ሁሉንም ነገር በሥርዓት ያስኬደዋል። እግዚአብሔር ሥራውን እየመራ ሳለ መስተካከል ያለባቸው ነገሮች ካሉ እነዚያን ነገሮች እርሱ ይከታተላቸውና መጥፎውን ሁሉ ወደ መልካም ይለውጣል፡፡ እግዚአብሔር ሕዝቡን የተሸከመውን አስደናቂ መርከብ በሰለም ወደ ወደቡ እንደሚያደርስ እምነት ይኑረን።— Selected Messages 2:390 (1892).
እግዚአብሔር ሕያው ቤተ ክርስቲያን የለውምን? ቤተ ክርስቲያን አለችው፣ ነገር ግን ድል የነሳች ቤተ ክርስቲያን ሳትሆን በጦርነት ላይ ያለች ቤተ ክርስቲያን ነች። ጉድለት ያለባቸው አባላት በመኖራቸውና በስንዴው መካከል እንክርዳድ በመኖሩ እናዝናለን።…. ምንም እንኳን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ክፋት (እርኩሰት) ቢኖርም፣ እስከ ዓለም መጨረሻ ድረስም የሚኖር ቢሆንም፣ በዚህ በመጨረሻው ዘመን የምትኖር ቤተ ክርስቲያን በኃጢአት ለረከሰውና ለወደቀው ዓለም ብርሃን መሆን አለባት። ቤተ ክርስቲያን ደካማና ጉድለት ያለባት፣ ማስጠንቀቂያ፣ ምክርና ተግሳጽ የሚያስፈልጋት ብትሆንም፣ በምድር ላይ ክርስቶስ ከሁሉም በላይ ትኩረት የሚያደርግባት ብቸኛ አካል ነች።— Testimonies to Ministers and Gospel Workers, 45, 49 (1893).
የሰይጣን መከላከያዎች በፍጹም ድል አይነሱም፡፡ ድል የሶስተኛውን መልአክ መልእክት ይከተላል። የእግዚአብሔር ሰራዊት መሪ የኢያሪኮን ግንብ እንዳፈረሰው ሁሉ የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት የሚጠብቁ ሕዝቦችም እንዲሁ ድልን ይቀዳጃሉ። ተቃዋሚ ኃይላት በሙሉ ይሸነፋሉ።- Testimonies to Ministers and Gospel Workers, 410 (1898).
@MesayD
ይቀጥላል .... | 1 275 |
| 14 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 4:- የእግዚአብሔር የመጨረሻው ዘመን ቤተ ክርስቲያን
(ክፍል ሦስት)
➡️ መንፈሳዊ ድካምና እውርነት የታየበት ጊዜ
በሚኒያፖሊስ በተናገርኳቸው ነገሮች ሁሉ በቤተ ክርስቲያን ተሃድሶ መካሄድ እንዳለበት ማረጋገጫ ተሰጥቶኛል። በታላቅ ብርሃን እና በከበሩ ዕድሎችና አጋጣሚዎች በተባረከ ሕዝብ ላይ ስለሚታየው መንፈሳዊ ድካምና እውርነት ተሃድሶ መካሄድ አለበት፡፡ እነዚህ ሰዎች እንደ ተሃድሶ አራማጆች የእምነት ተቋም ካላቸው ቤተ ክርስቲያናት የወጡ ሲሆን አሁን እየፈጸሙ ያሉት ትተዋቸው የወጡባቸው ቤተ ክርስቲያናት ያደርጉ የነበረውን ሥራ ነው። ሌላ መውጣት አያስፈልግም ብለን ተስፋ አድርገን ነበር። [ኤለን ጂ ኋይት ከጻፈቻቸው ጽሁፎች ውስጥ በሰባተኛው ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን ድርጅት ላይ እምነት ማጣትዋን የሚገልጽ አረፍተ ነገር ይህ ብቻ ነው። የዚህ ዓይነቱ ጥርጣሬ ቀጥለው በነበሩ የሕይወት ዘመኖቿ 26 ዓመታት ውስጥ አልተደገሙም።] በሰላም ማሰሪያ “የመንፈስ አንድነትን ለመጠበቅ” ጥረት እያደረግን ሳለ ግትርነትን በብዕር ወይም በድምጽ መቃወማችንን አናቆምም።- The Ellen G. White 1888 Materials, 356, 357 (1889).
በተሰጣቸው ብርሃን ለሚኩራሩና ለማይመላለሱበት ክርስቶስ እንዲህ ይላል፡-“ነገር ግን እላችኋለሁ፡- በፍርድ ቀን ከእናንተ ይልቅ ለጢሮስና ለሲዶና ይቀልላቸዋል። አንቺ ቅፍርናሆም (ታላቅ ብርሃን የተሰጣችሁ የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስቶች) ሆይ! ራስሽን ወደ ላይ ከፍ ከፍ ያደረግሽ (ከተሰጡሽ ዕድሎች አንጻር)፣ ወደ ሲዖል ትወርጂያለሽ። በአንቺ የተደረጉ ታላላቅ ሥራዎች በሶዶም ተደርገው ቢሆን ኖሮ ሶዶም እስከ ዛሬ በኖረች ነበር።"—The Review and Herald, August 1, 1893. [በቅንፍ ውስጥ ያሉ አስተያየቶች በኤለን ኋይት የተሰጡ ናቸው።]
ቤተ ክርስቲያን በላውዶቂያነት ሁኔታ ውስጥ ነች። እግዚአብሔር በመካከልዋ አይደለም።- Notebook Leaflets 1:99 (1898).
➡️ በቤተ ክርስቲያን ዋና ቢሮዎች ሥልጣንን ያለ አግባብ መጠቀም
ጄኔራል ኮንፍራንስ እራሱ በስህተት አመለካከቶችና መርሆዎች እየረከሰ ነው።_
ሰዎች በሥልጣናቸው ሥር መሆን እንዳለባቸው ከሚገምቱአቸው አግባብነት የሌለው ጥቅም እያገኙ ነው፡፡ ግለሰቦቹን በእነርሱ ሀሳብ እንዲስማሙ ለማድረግ ወስነዋል፡፡ ይገዙአቸዋል ወይም ያጠፉአቸዋል።….
ሥልጣን ሰውን አማልክት ያደርግ ይመስል የተፈጠረው የበላይነትን የሚሰጥ ሥልጣን ያስፈራኛል፣ ማስፈራትም አለበት። ሥልጣን በማንም፣ የትም ቦታ ቢሆን በዚህ ሁኔታ ጥቅም ላይ ከዋለ እርግማን ነው። Testimonies to Ministers and Gospel Workers, 359-361 (1895).
ከአቅም በላይ የሆኑ እጅግ ከባድ ኃላፊነቶች በጥቂት ሰዎች ላይ ተጭነዋል፤ ከእነዚህ መካከል አንዳንዶቹ እግዚአብሔርን አማካሪያቸው የማያደርጉ ናቸው። እነዚህ ሰዎች በውጭ አገሮች ስላለው ሥራ ስለሚያስፈልጉ ነገሮች ምን ያውቃሉ? መረጃን ለማግኘት ወደ እነርሱ በሚቀርቡ ጥያቄዎች ላይ እንዴት መወሰን እንዳለባቸው እንዴት ማወቅ ይችላሉ? በውጭ አገር ያሉ ሰዎች ለጥያቄዎቻቸው መልስ ለማግኘት በመጻፍ ላይ መዘግየት ካልተፈጠረ ሶስት ወር ይጠይቃል።—Testimonies to Ministers and Gospel Workers, 321 (1896).
በሩቅ አገሮች የሚኖሩ ሰዎች ከባትል ክሪክ ፈቃድ ለማግኘት አስቀድመው ካልላኩ በቀር አእምሮአቸው ትክክል እንደሆነ የሚነግራቸውን ነገር አይፈጽሙም። አንድን ነገር ከማድረጋቸው በፊት (አንድ እርምጃ ከመሄዳቸው በፊት) የይሁንታን መልስ ከዚያ ይጠብቃሉ።-Special Testimonies, Series A 9:32 (1896).
በጄነራል ኮንፍራንስ አንድ ሰው ብቻ ፕሬዝደንት አድርጎ መምረጥ አይመከርም። የጄኔራል ኮንፍራንስ ሥራ ከመስፋፋቱ የተነሳ አንዳንድ ነገሮች አላስፈላጊ በሆነ ሁኔታ ተወሳስበዋል፡፡ የማስተዋል ጉድለቶች ታይተዋል፡፡ አሁን ያለውን ሁኔታ ለመለወጥ የፊልድ ክፍፍል ወይም ሌላ እቅድ መቀየስ አለበት፡፡ Testimonies to Ministers and Gospel Workers,342 (1896).
[የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን የተመሰረተችው እ.አ.አ 1863 ዓ.ም ሲሆን 3500 አባላት፣ 6 ኮንፍራንሶች፣ 30 የሚሆኑ የወንጌል አገልጋዮችና ሶስት አባላት የነበሩት የጄኔራል ኮንፍራንስ ኮሚቴ ነበራት። ለዚህ ትንሽ ድርጅት የጄኔራል ኮንፍራንሱ ፕሬዝደንት አመራርና ምክር መስጠት ይችል ነበር። እያንዳንዱን አስፈላጊ ስብሰባ በአካል ተገኝቶ ለመካፈልና ለሕትመት ሥራ የሚወጣውን ወጪ መቆጣጠር ይችል ነበር። ነገር ግን እ.አ.አ 1896 ዓ.ም አካባቢ ሥራው በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፣ በአውስትራሊያና በአፍሪካ በጣም ተስፋፍቶ ነበር። ስለዚህ ለአንድ ሰው በቂ ክትትልና መመሪያ ለመስጠት አዳጋች ነበር። በዓለም ዙሪያ ያሉ የቤተ ክርስቲያን አባሎቻችን ከአንድ ሰው ብቻ ምክር መጠበቅ ስለሌለባቸው የፊልድ ክፍፍል እንዲኖር ኤለን ጂ ኋይት ገፋፍታለች፡፡ ይህም የዩኒየን ኮንፍራንሶችንና የዓለም ዲቪዥኖችን በመፍጠር ተፈጻሚ ሆኗል።
@MesayD
ይቀጥላል ... | 1 475 |
| 15 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 4:- የእግዚአብሔር የመጨረሻው ዘመን ቤተ ክርስቲያን
(ክፍል ሁለት)
➡️ የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስቶች ልዩ ተልዕኮ
"እግዚአብሔር የሕጉ ተሸካሚዎች (ጠባቂዎች) አድርጎናል። ለሌሎች በታመኑ ማስጠንቀቂያዎች፣ ተግሳፆችና ማበረታቻዎች ሊሰጥ የሚገባውን ቅዱስና ዘላለማዊ እውነት ሰጥቶናል። "-Testimonies for the Church 5:381 (1885).
"የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስቶች ከዓለም የተለዩ ሕዝብ ሆነው በእግዚአብሔር ተመርጠዋል። በታላቅ የእውነት መቁረጫ ከዓለም ዓለት ቆርጦ ከራሱ ጋር አገናኝቷቸዋል። በመጨረሻው የድነት ሥራ ውስጥ የራሱ ተወካዮች አድርጎ አምባሳደሮቹ እንዲሆኑ ጠርቷቸዋል። ለሟች ሰው ተሰጥተው ከሚያውቁ ታላላቅ የእውነት ሀብቶች ሁሉ በላይና ከእግዚአብሔር ለሰው ተልከው ከሚያውቁ በጣም ግልጽና አስፈሪ ማስጠንቀቂያዎች ሁሉ በላይ የሆነ ማስጠንቀቂያ ለዓለም እንዲያስተላልፉ ተሰጥቷቸዋል።" Testimonies for the Church 7:138 (1902).
"የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስቶች በዓለም ውስጥ በተለየ ሁኔታ እንደ ጠባቂዎችና ብርሐን ተሸካሚዎች ሆነው ተቀምጠዋል። ለጠፊው ዓለም የመጨረሻውን ማስጠንቀቂያ የመስጠት ሀላፊነት ተሰጥቷቸዋል። በእነርሱ ላይ ከእግዚአብሔር ቃል የሚወጣ አስደናቂ ብርሐን እየበራ ነው። በጣም ታላቅ ጠቀሜታ ያለውን የመጀመሪያውን፣ የሁለተኛውንና የሶስተኛውን መላእክት መልእክት የማስተላለፍ ሥራ ተሰጥቷቸዋል። የዚህን ያህል ታላቅ ጠቀሜታ ያለው ሌላ ሥራ የለም። ምንም ሌላ ነገር ትኩረታቸውን እንዲስብ መፍቀድ የለባቸውም። "-Testimonies for the Church 9:19 (1909).
➡️ የ7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን የተቋቋመችበት ምክንያቶች
"ቁጥራችን እየጨመረ ሲመጣ የቤተ ክርስቲያን ድርጅታዊ መዋቅር ከሌለ በስተቀር ታላቅ ግራ መጋባት ከመከሰቱም በላይ ሥራው በተሳካ ሁኔታ ወደ ፊት መቀጠል አለመቻሉ እሙን ነው፡፡ ለአገልግሎቱ ድጋፍ ለመስጠት፣ ሥራውን ወደ አዳዲስ መስኮች ለማድረስ፣ ቤተ ክርስቲያኗንና መልእክቷን ከማይረቡ አባላት ለመጠበቅ፣ የቤተ ክርስቲያንን ንብረት ለመያዝ፣ እውነትን በማተሚያ ቤቶች ለማተምና ለሌሎች ብዙ ዓላማዎች የቤተ ክርስቲያን ድርጅት አስፈላጊ ነው፡፡...
"በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቅንጅትና ሥርዓት መኖር እንዳለበትና የቤተ ክርስቲያን ድርጅት አስፈላጊ ስለመሆኑ በመንፈሱ ብርሐን ተሰጥቶኛል። ሥርዓትና ቅንጅት በዓለማት ባሉ የእግዚአብሔር ሥራዎች በሙሉ ይታያሉ። ሥርዓት የሰማይ ሕግ እንደሆነ ሁሉ በምድር ላይ ያለው የእግዚአብሔር ሕዝብም ሕግ መሆን አለበት።"—Testimonies to Ministers and Gospel Workers, 26 (1902).
➡️ ድርጅት ሁልጊዜም አስፈላጊ ነው
"ቤተ ክርስቲያናት ሥርዓትን ማክበርና ማስከበር እንዲችሉ ካልተደራጁ በቀር ለወደፊት ተስፋ የሚያደርጉት ምንም ነገር ሊኖር አይችልም።"— Testimonies For The Church 1:270 (1862).
"ቅንነት የጎደላቸውን ተቃውሞዎች ለመከላከልና የእግዚአብሔር ቃል እውቅና የማይሰጣቸውን ሀሳቦች ስህተትነታቸውን ለማጋለጥ ፍጹም የቤተ ክርስቲያን ድርጅት በሚያስፈልግበትና ታላቅ ኃይል በሚሆንበት ወቅት ሰይጣን በእግዚአብሔር ሕዝቦች መካከል በመግባት ውዝግብ መፍጠር ሲችልና ሲሳካለት እጅግ ይደሰታል። ጥበብና ጥንቃቄ በተሞላበት ጥረት (ልፋት) የተገነባው የቤተ ክርስቲያን ድርጅት ሥርዓትና ቅንጅት እንዳይፈርስ መስመሮቹን በትክክል መያዝ እንፈልጋለን። በዚህ ወቅት ሥራውን ለመቆጣጠር ፍላጎት ላላቸው ሥርዓት አልበኞች ፈቃድ ሊሰጣቸው አይገባም።
"ወደ ዘመን መጨረሻ እየተቃረብን በሄድን ቁጥር እያንዳንዱ የእግዚአብሔር ልጅ ከማንኛውም የኃይማኖት ድርጅት ነጻ ሆኖ ለብቻው ይቆማል የሚል ሀሳብ ያላቸው አንዳንድ ሰዎች አሉ። ነገር ግን በዚህ ሥራ ላይ እያንዳንዱ ሰው ለብቻው ይቆማል የሚባል ነገር እንደሌላ ጌታ አስተምሮኛል።" [From manuscript read before the delegates at the General Conference Session, Washington, D.C., May 30, 1909. Testimonies for the Church 9:257, 258 (1909).
"ወደ መጨረሻው አስጨናቂ ጊዜ ስንቃረብ የተግባር ቅንጅትና መጣጣም ብዙም አያስፈልግም ብሎ ከማሰብ ይልቅ ከበፊቱ የበለጠ ሥርዓትን ተከትለን የምንሰራ መሆን አለብን።" -Selected Messages 3:26 (1892).
➡️ የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ልዩ ሥልጣን
እግዚአብሔር ማንም ባይቀበል ወይም ቢንቅ ከበደል ነጻ መሆን የማይችል ኃይልና ሥልጣን ለቤተ ክርስቲያን ሰጥቷል። የቤተ ክርስቲያንን ሥልጣን የሚንቅና የማይቀበል የእግዚአብሔርን ድምፅ ንቋል።-Testimonies for the Church 3:417 (1875).
እግዚአብሔር ከሰማይ በታች ታላቁን ኃይል የሰጠው ለቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ መከበር ያለበት በተባበረችው ቤተ ክርስቲያን ችሎታ ውስጥ ያለው የእግዚአብሔር ድምጽ ነው ።-Testimonies for the Church 3:451 (1875).
@MesayD
ይቀጥላል ... | 1 332 |
| 16 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 4:- የእግዚአብሔር የመጨረሻው ዘመን ቤተ ክርስቲያን
(ክፍል አንድ)
➡️ የእግዚአብሔር ሕዝብ ትዕዛዛቱን ይጠብቃሉ
"እግዚአብሔር በምድር ላይ የተረገጠውን ሕጉን ከፍ ከፍ የምታደርግና የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግደውን የእግዚአብሔርን በግ ለዓለም የምታቀርብ ቤተ ከርስቲያን አለችው፡፡..
"እግዚአብሔር አሁን በፈረሰው አጥር አጠገብ ያለችና አጥሩን መልሳ የምትገነባና ያረጀውንም ቦታ የምትጠግን አንዲት ቤተ ክርስቲያን በዓለም ውስጥ አለችው፡፡…
"ስለ ቅሬታዋ የተሰጠውን መግለጫ በምታሟላው ማለትም የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት በምትጠብቀውና የኢየሱስ ኃይማኖት ባላት ብቸኛ ቅሬታ ቤተ ክርስቲያን ላይ ተቃውሞን ከማንሳት ሁሉም ይጠንቀቁ።...
"እግዚአብሔር የተለየ ሕዝብ፣ ማንም የማይቀድማት ነገር ግን እውነትን ለማስተማርና የእግዚአብሔርን ሕግ ለመግለጽ ብቃት ያላት ከሁሉም በላይ የሆነች ቤተ ክርስቲያን በምድር ላይ አለችው፡፡.. ወንድሜ ሆይ፣ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን ባቢሎን ነች ብለህ እያስተማርክ ከሆነ ተሳስተሃል።"—Testimonies to Ministers and Gospel Workers, 50, 58, 59 (1893) [የራዕይ መጽሐፍ በሁለት ቡድን የእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ትኩረት ያደርጋል፡- የሚታዩ ቅሬታዎች (ራዕይ 12፡ 17) እና በባቢሎን ውስጥ ያሉ “ሕዝቤ” (ራዕይ 18፡4) የተባሉት ናቸው፡፡ ይህ ምዕራፍ የሚዳስሰው የመጀመሪያውን ቡድን እና ራዕይ ምዕራፍ 14ን ሲሆን “ታላቁ ጩኸት” የሚዳስሰው የኋለኛውን ቡድን ነው።]
➡️ የኢየሱስ ምስክር አላቸው
"መጨረሻው እየቀረበና ለዓለም የመጨረሻውን ማስጠንቀቂያ የመስጠት ሥራ እየቀጠለ ሲሄድ ከመነሻው ጀምሮ እግዚአብሔር በራሱ ፈቃድ ከሶስተኛው መልአክ መልእክት ጋር ያገናኘውን የወቅቱን እውነት የሚቀበሉ ሁሉ ስለ ምስከሮች ባህሪይና ተጽእኖ የጠራ መረዳት ማግኘት ሊኖራቸው ይገባል።"—Testimonies for the Church 5:654 (1889).
"ሰዎች የተለያዩ እቅዶችን ነድፈው ሊነሱ ይችላሉ። ጠላትም የእነርሱን ዕቅዶች በመጠቀም ነፍሳትን ከእውነት ሊያስታቸው ይሻል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ለእህት ኤለን ጂ ኋይት መልእክት እንደሰጣትና በእርሷ አማካይነት እንደተናገረ የሚያምኑ ሁሉ በዚህ የመጨረሻ ዘመን ከሚመጡ ብዙ ማታለያዎች ይድናሉ።"—Selected Messages 3:83 84 (1906).
"ራዕይ እንደተሰጣቸው የሚናገሩ ብዙዎች ይኖራሉ። ራዕዩ ከእርሱ ስለመሆኑ እግዚአብሔር ግልጽ የሆነ ማረጋገጫ ሲሰጥህ መቀበል ትችላለህ። ነገር ግን በውጭ አገሮችና በአሜሪካ ብዙ ሰዎች ከእውነት እየራቁ (እየሳቱ) ሊሄዱ ስለሆነ በማንኛውም ሌላ ማረጋገጫ መቀበል የለብህም።" -Selected Messages 2:72 (1905).
➡️ “ድንበር አመልካች ምልክቶቻቸው'' መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮዎች ናቸው
"እ.አ.አ የ1844 ዓ.ም ማለፍ በመደነቅ በተሞሉ ዓይኖቻችን ፊት በምድር ላይካለው የእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር ወሳኝ ግንኙነት ያለውን የሰማያዊውን ቤተ መቅደስ መንጻት የገለጸበት ወቅት እንደመሆኑ የታላላቅ ክስተቶች ወቅት ነበር። እንዲሁም “የእግዚአብሔር ትዕዛዛትና የኢየሱስ እምነት' የሚል የእግዚአብሔር አርማ የተጻፈባቸው የመጀመሪያውና የሁለተኛ መላእክት መልእክቶች እና የሶስተኛው መልአክ መልእክት የተገለጠበት ወቅት ስለነበር የታላላቅ ክስተቶች ወቅት ነበር። በዚህ መልእክት ሥር ከነበሩ ምልክቶች መካከል አንዱ እውነትን ወዳድ በሆነ ሕዝቡ በሰማይ የታየው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስና የእግዚአብሔርን ሕግ የያዘው ታቦት ነበር። የአራተኛው ትዕዛዝ የሰንበት ብርሃን የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት በሚተላለፉ ሰዎች ፊት ኃይለኛ የብርሃን ጮራዎችን አንጸባረቀ። ኃጢአተኞች ሟች መሆናቸው ጥንታዊ የእውነት ምልክት ነው። በጥንት ምልክቶች ሥር በሚመጣ እውነት ላይ ምንም ነገር መጨመር አልችልም።"—Counsels to Writers and Editors, 30, 31 (1889).
@MesayD
ይቀጥላል ... | 1 629 |
| 17 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 3:- እነዚህ ነገሮች የሚሆኑት መቼ ነው ?
(የመጨረሻ ክፍል)
➡️ መተላለፍ ከገደቡ ደርሷል
"የምድር ኗሪዎች የበደለኝነት ጽዋቸውን እስኪሞሉ ድረስ ለጥቂት ጊዜ መዘግየት የሚኖር ሲሆን ከዚያ በኋላ ለረዥም ጊዜ በእንቅልፍ ላይ የነበረው የእግዚአብሔር ቁጣ ይቀሰቀስና ይህ የብርሃን አገር የእርሱን ያልተቀላቀለ ቁጣ ወይን ጠጅ ይጠጣል።"— Testimonies For The Church 1:363 (1863).
"የበደለኝነት ጽዋ ለመሙላት የቀረበ ሲሆን የእግዚአብሔር የበቀል ፍርድ በበደለኞች ላይ ሊወርድ ነው ።" -Testimonies for the Church 4:489 (1880).
"የዓለም ኗሪዎች ክፋት የኃጢአታቸውን ስፍር ሞልቷል። ይህቺ ምድር አጥፊው የእርሱን ፈቃድ እንዲፈጽም እግዚአብሔር ወደሚፈቅድበት ደረጃ ደርሳለች።” Testimonies for the Church 7:141 (1902).
"መተላለፍ ከገደቡ ላይ ደርሷል። ዓለም በውዝግብ ስለተሞላ በሰብአዊ ፍጡራን ላይ በቅርቡ ታላቅ ሽብር ሊመጣ ነው፡፡ መጨረሻው እጅግ ቅርብ ነው። እኛ እውነቱን የምናውቅ ሰዎች በዓለም ላይ ከአቅም በላይ የሆነ አድናቆትን በሚጭር መልኩ ሊከሰት ስላለው ነገር መዘጋጀት አለብን።"— Testimonies for the Church 8:28 (1904).
➡️ የእግዚአብሔርን ታላቅ ቀን በአእምሮአችን ጠብቀን ማቆየት አለብን
"ከፊታችን _ ስላሉት ታላላቅ የፍርድ ትዕይንቶች ለማሰብና በሕይወታችን ለመተግበር ራሳችንን ማስተማር አለብን። ከዚያም ሁሉም ነገር የሚገለጥበትን የእግዚአብሔርን ታላቅ ቀን ትዕይንቶች በፊታችን ስንይዝ በባሕርያችን ላይ ተጽእኖ ይኖረዋል። አንድ ወንድም “እህት ኋይት፣ ጌታ በአስር አመት ጊዜ ውስጥ ይመጣል ብለሽ ታስቢያለሽ?” ብሎ ጠየቀኝ። እኔም “በሁለት፣ በአራት ወይም በአሥር ዓመት የሚመጣ ቢሆን ምን ልዩነት ያመጣል?" አልኩት። እርሱም “ጌታ በአሥር ዓመት ውስጥ የሚመጣ መሆኑን ባውቅ ኖሮ አንዳንድ ነገሮችን በተለየ ሁኔታ አደርጋለሁ ብዬ አስባለሁ” አለ። እኔም “ምን ታደርጋለህ?" አልኩት፡፡ እርሱም “ንብረቴን ሽጬ የእግዚአብሔርን ቃል መመርመር እጀምርና ሕዝቡ ለመምጫው እንዲዘጋጅ ለማስጠንቀቅ እሞክራለሁ፤ እኔም ለመምጫው ዝግጁ መሆን እንድችል ወደ እግዚአብሔር እማጸናለሁ" አለ፡፡
ከዚያም “ጌታ እስከ ሃያ ዓመት ድረስ እንደማይመጣ ብታውቅ ኖሮ ከአሁን በተለየ ሁኔታ ትኖር ነበር?” ብዬ ጠየቅኩት። እርሱም “እንደዚያ አደርጋለሁ ብዬ አስባለሁ" አለ።.
"ኢየሱስ በአስር አመት ውስጥ እንደሚመጣ ቢያውቅ ኖሮ የተለየ ሕይወት እንደሚኖር የሚገልጸው መግለጫ እንዴት ያለ ራስ ወዳድነት ነው! ሔኖክ ለምን ለ300 ዓመታት አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ? በየቀኑ ከእግዚአብሔር ጋር እየተራመድንና ነቅተን እየጠበቅን ካልሆነ ከአደጋ ነጻ እንዳልሆንን ይህ ለእኛ ትምህርት ነው ። "-Manuscript 10, 1886.
➡️ የጊዜው ማጠር
"ለእግዚአብሔር ሥራ ግድየለሽና ሰነፍ ለሆኑት ቀንም ሆነ ማታ እግዚአብሔር እረፍት አይስጣቸው፡፡ መጨረሻው ቅርብ ነው፡፡ የጊዜው አጭር የመሆን ጉዳይ ኢየሱስ ሁልጊዜ በፊታችን እንድናደርገው የሚፈልገው ነገር ነው::"—Letter 97, 1886.
"ከፊታችን ሊለካ የማይችል ዘላለም ተዘርግቶ በእጃችን የወርቅ በገናዎችንና የክብር ዘውዶችን ይዘን ከዳኑት ጋር በብርጭቆ ባህር ላይ ስንቆም ያሳለፍነው የመጠበቂያ ጊዜ ምን ያህል አጭር እንደነበር ያኔ እንመለከታለን።”—Manuscript Releases 10:266 (1886).
@MesayD
ምዕራፍ 4 ይቀጥላል ... | 1 211 |
| 18 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 3:- እነዚህ ነገሮች የሚሆኑት መቼ ነው ?
(ክፍል አራት)
➡️ የእግዚአብሔር ተስፋዎች በሁኔታዎች የሚደገፉ ናቸው
"የእግዚአብሔር መላእክት ለሰዎች ባቀረቡአቸው መልእክቶች ጊዜው እጅግ አጭር መሆኑን አመልክተዋል (ሮሜ 13፡11፣ 12፤ 1ኛ ቆሮ. 7፡29፤ 1ኛ ተሰ. 4፡15፣ 17፤ ዕብ. 10፡25፤ ያዕ. 5፡8፣ 9፤ 1ኛ ጴጥ. 4፡7 እና ራዕይ 22፡ 6፣ 7ን ይመልከቱ)። በዚህ መልክ ሁልጊዜ በፊቴ ቀርቦልኝ ነበር። በዚህ መልእክት ጅምር ላይ ከጠበቅነው ይልቅ ጊዜው እየረዘመ መምጣቱ እውነት ነው፡፡ አዳኛችን ይመጣል ባልነው ፍጥነት አልመጣም። ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል ሳይፈጸም ቀርቷልን (ዋሽቷልን)? በፍጹም! የእግዚአብሔር ተስፋዎችም ሆኑ ማስጠንቀቂያዎች በሁኔታዎች የሚደገፉ መሆናቸውን ማስታወስ አስፈላጊ ነው። (ኤር. 18፡ 7-10፤ ዮናስ 3፡ 4-10ን ይመልከቱ)።...
"ለእግዚአብሔር ባለመገዛታችን እንደ እሥራኤል ልጆች በዚህ ዓለም ለብዙ ዓመታት ልንቆይ እንችላለን፣ ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በእነርሱ የተሳሳተ መንገድ ለመጣው ነገር እግዚአብሔርን ተጠያቂ በማድረግ በኃጢአት ላይ ኃጢአትን እንዳይጨምሩ በክርስቶስ ስም እጠይቃቸዋለሁ፡:" Evangelism, 695, 696 (1901).
➡️ ክርስቶስ እየጠበቀ ያለው ነገር
"ክርስቶስ ራሱን በቤተ ክርስቲያኑ ለመግለጥ በታላቅ ናፍቆት እየጠበቀ ነው። የከርስቶስ ባህሪ በሕዝቡ ውስጥ በሙላት ሲባዛ የራሱ የሆኑትን ሊወስድ ይመጣል።
"የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን መምጣት መፈለግ ብቻ ሳይሆን ማፋጠንም የእያንዳንዱ ክርስቲያን መልካም ዕድል ነው፡፡ ስሙን የሚጠሩ ሁሉ ለእርሱ ክብር የሚሆን ፍሬ ቢያፈሩ ኖሮ የወንጌል ዘር እንዴት ባለ ፍጥነት በመላው ዓለም በተዘራ ነበር። የመጨረሻው ታላቅ መከር በፍጥነት ይበስልና ከቡር ዘሮችን ለመሰብሰብ ክርስቶስ ይመጣል።"—Christ's Object Lessons, 69 (1900).
"ወንጌልን ለዓለም በመስጠት የጌታን መመለስ ማፋጠን በእኛ አቅም ሥር ያለ ነገር ነው። የጌታን ቀን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ማስቸኮልም አለብን፡፡ (2ኛ ጴጥ 3:12 መጨረሻ )" -The Desire of Ages, 633 (1898). "
"ከእርሱ ጋር በመተባበር ይህንን የችግር ትዕይንት ወደ መጨረሻው ማምጣትን በእኛ አቅም ሥር አድርጎታል።" - Education, 264 (1903).
➡️ የእግዚአብሔር ትዕግሥት ገደብ
"ኃይሉ ወሰን የሌለው አምላክ የሕዝቦችን ሁሉ መዝገብ በማይሳሳት ትክክለኛነት ይጠብቃል። ምህረቱ ለንስሃ ከሚቀርቡ ጥሪዎች ጋር የተዋሃደ ሆኖ ሳለ ይህ መዝገብ ክፍት ሆኖ ይቆያል፣ ነገር ግን ቁጥሮቹ እግዚአብሔር ከወሰነው መጠን ላይ ሲደርሱ የቁጣ አገልግሎቱ ይጀመራል።" - Testimonies for the Church 5:208 (1882).
"እግዚአብሔር የሕዝቦችን ጉዳይ መዝግቦ ይይዛል። በሰማይ መጻሕፍት ውስጥ በእነርሱ ላይ የተጻፉ ነገሮች ቁጥር እየጨመረ ስለሆነ የሳምንቱን የመጀመሪያ ቀን ሕግ መተላለፍ ቅጣት ሲያስከትል ጽዋቸው ይሞላል።"—The S.D.A. Bible Commentary 7:910 (1886).
"እግዚአብሔር ሕዝቦችን ይቆጣጠራል።…ኃጢአት ወደተገለጸው የእግዚአብሔር ምህረት ገደብ የሚደርስበት ጊዜ ሲመጣ ትዕግሥቱ ያበቃል። በሰማይ የኃጢአት መመዝገቢያ መጻሕፍት ውስጥ የተመዘገቡ የተጠራቀሙ ነገሮች ቁጥር የመተላለፍ ድምርን ሲሞላ ቁጣ ይመጣል።" -Testimonies for the Church 5:524 (1889).
"የእግዚአብሔር ምህረት ሕግ ተላላፊውን ለረዥም ጊዜ ቢታገሰውም ሰዎች በኃጢአት መቀጠል የማይችሉበት ገደብ አለ። ያ ገደብ ሲደርስ የምህረት ስጦታዎች ይወገዱና የፍርድ አገልግሎት ይጀምራል።"—Patriarchs and Prophets, 162, 165 (1890).
"ሰዎች በማጭበርበርና በብልግና ተግባራቸው ቀጥለውበት እንዲያልፉ እግዚአብሔር የማይፈቅድበት ነጥብ ላይ የሚደርሱበት ጊዜ እየመጣ ነው፤ ያኔ የያህዌ ትዕግሥት ገደብ እንዳለው ያውቃሉ።" -Testimonies for the Church 9:13 (1909).
የያህዌ ፍርድ ከዚያ ባሻገር መዘግየት የማይችልበት ገደብ አለው።—Prophets and Kings, 417 (c. 1914).
@MesayD
ይቀጥላል ... | 1 349 |
| 19 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 3:- እነዚህ ነገሮች የሚሆኑት መቼ ነው ?
(ክፍል ሦስት)
➡️ ኤለን ኋይት በእርሷ ዘመን ክርስቶስ ይመለሳል ብላ ጠብቃ ነበር
በኮንፍራንሱ የነበረውን ቡድን እንዳይ ተደርጌ ነበር። መልአኩ እንዲህ አለ፡ - አንዳንዶች የትላትል ምግብ፣ ሌሎች የመጨረሻዎቹ ሰባት መቅሰፍቶች ሰለባ ሲሆኑ አንዳንዶች ደግሞ በክርስቶስ መገለጥ ወደ ሰማይ ለመነጠቅ በምድር ላይ በሕይወት ይኖራሉ።"-Testimonies For The Church 1:131, 132 (1856).
"ጊዜው አጭር ስለሆነ በትጋትና በዕጥፍ ጉልበት መስራት አለብን፡፡ ልጆቻችን በፍጹም ወደ ኮሌጅ ላይገቡ ይችላሉ።"—Testimonies for the Church 3:159 (1872).
"አሁን ልጆችን መውለድ በእርግጠኝነት የሚመከር አይደለም። ጊዜው አጭርነው፣ የመጨረሻዎቹ ቀን አደጋዎች በላያችን ናቸው፣ ከዚህ በፊት ትናንሽ ልጆች በአብዛኛው ይሞታሉ”——Letter 48, 1876.
"የምድር ታሪክ ትዕይንቶች በቶሎ ሊዘጉ ባሉበት እና ከዚህ በፊት በፍጹም ሆኖ ወደማያውቅ የመከራ ጊዜ ልንገባ ባለንበት በዚህ ዘመን የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ጥቂት ቢሆኑ ለወንዶችም ለሴቶችም የተሻለ ነው::"-Testimonies for the Church 5:366 (1885).
"ሰዓቱ ይመጣል፤ ሩቅ አይደለም፣ አሁን አምነው ካሉት ሰዎች መካከል አንዳንዶቻችን በምድር ላይ በሕይወት በመኖር ትንቢቱ ተፈጻሚ ሲሆን እንመለከታለን፣ የመላእክት አለቃ ድምጽና የእግዚአብሔር መለከት ድምጽ ከተራራ፣ ከሜዳና ከባህር ወደ ምድር ጫፎች ሲያስተጋባ እንሰማለን።" - The Review and Herald, July 31, 1888.
"የሶስተኛው መልአክ ታላቅ ጩኸት ኃጢአትን ይቅር ባይ በሆነው አዳኝ በክርስቶስ ጽድቅ መገለጥ ስለተጀመረ የፈተናው ጊዜ በላያችን ነው። "-Selected Messages 1:363 (1892).
➡️ መዘግየቱ ተብራራ
"የሙሽራው ረዥም ሌሊት ፈታኝ ነው፣ ነገር ግን ጌታ ቢመጣ ኖሮ እጅግ ብዙ ሰዎች ሳይዘጋጁ ስለሚገኙ ንጋቱ ወደ ፊት የገፋው በምህረት ነው::"—Testimonies for the Church 2:194 (1868).
"አድቬንቲስቶች በ1844 ዓ.ም ከገጠማቸው ታላቅ ተስፋ መቁረጥ በኋላ እምነታቸውን አጥብቀው ቢይዙና የሶስተኛውን መልአክ መልእክት በመቀበል በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ለዓለም በማወጅ እግዚአብሔር የከፈተላቸውን መሰናዶ አንድ ሆነው ተከትለው ቢሆን ኖሮ የእግዚአብሔርን ማዳን ባዩ፤ በጥረቶቻቸው እግዚአብሔር በኃይል በሰራና ክርስቶስ ሕዝቡን ሽልማታቸውን እንዲቀበሉ ለመውሰድ በመጣ ነበር።-የክርስቶስ መምጣት እንዲህ መዘግየት የእግዚአብሔር ፈቃድ አልነበረም። …አለማመን፣ ማጉረምረምና አመጽ የጥንቶቹን እሥራኤላውያን ወደ ከነዓን ምድር እንዳይገቡ ለ40 ዓመታት ዘጋባቸው። የዘመኑ እሥራኤልም ወደ ሰማያዊው ከነዓን እንዳይገባ ተመሳሳይ ኃጢአት አዘግይቶታል። በሁለቱም ሁኔታ የእግዚአብሔር ተስፋ ስህተት የለውም፡፡ በዚህ የኃጢአትና የሀዘን ዓለም ውስጥ ለብዙ ዓመታት እንድንቆይ ያደረገን የእግዚአብሔር ሕዝብ ነን በሚሉ ሰዎች መካከል ያለው አለማመን፣ ዓለማዊነት፣ አለመቀደስና ጠብ ናቸው ።"-Evangelism, 695, 696 (1883).
"የከርስቶስ ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔር እንደሾማት የተሰጣትን ሥራ ሰርታ ቢሆን ኖሮ መላው ዓለም ከዚህ በፊት ማስጠንቀቂያ በተሰጠውና ጌታ ኢየሱስ በኃይልና በታላቅ ክብር ወደ ምድራችን በመጣ ነበር። -The Desire of Ages, 633, 634 (1898).
@Mesay Desalegn
ይቀጥላል ... | 1 316 |
| 20 | የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች
ምዕራፍ 3:- እነዚህ ነገሮች የሚሆኑት መቼ ነው ?
(ክፍል ሁለት)
➡️ ጊዜን መወሰን ወደ አለማመን ይመራል
"ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ የተወሰኑ ጊዜያቶች ሳይፈጻሙ ከማለፋቸው የተነሳ በቅርቡ ሊሆን ስላለው የክርስቶስ ዳግም ምጽዓት ዓለም ከበፊቱ ይልቅ አሁን ባለማመን ጸንቷል። ጊዜን ወስነው ያልተሳካላቸውን ሰዎች በንቀት ይመለከቱአቸዋል፤ ሰዎች ከመታለላቸው የተነሳ የሁሉም ነገር መጨረሻው በደጅ ስለመሆኑ የእግዚአብሔር ቃል ድጋፍ ካለው እውነት ይርቃሉ።" - Testimonies for the Church 4:307 (1879).
"ወንድም [ኢ.. ፒ.] ዳንኤልስ ከዚህ በፊት እንዳደረገው ሁሉ ጌታ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ ይመጣል ብሎ ጊዜ እንደወሰነ እረዳለሁ። አሁን እኛ ጊዜን የምንወስን ሰዎች እንደሆንን የሚያመለክት ነገር ወደ ሌላ አገር እንደማይደርስ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ የዚህ ዓይነት አስተያየቶች አይምጡ፡፡ አይጠቅሙም። ይህን በመሰሉ ጉዳዮች ላይ ተሃድሶን ለማግኘት አትፈልጉ፣ ነገር ግን ጥራዝ ነጠቆች ሽብር ለመፍጠር ማግኘት የሚችሉትን ማንኛውም ነገር እንዳይጠቀሙና የእግዚአብሔርን መንፈስ እንዳያሳዝኑ በእያንዳንዱ ከአፍ በሚወጣ ቃል ላይ ጥንቃቄ ይደረግ።
"ስሜቶችን ለመቀስቀስና መርሆዎች የማይቆጣጠሩትን መነሳሳትን ለመፍጠር ስንል የሰዎችን ኃይለኛ ስሜቶች መቀስቀስ አያስፈልግም። ሰይጣን ጉዳት ለማድረስ ኃይል የሚሆኑትን የማታለል ስልቶቹንና መሳሪያዎቹን ሥራ ላይ ለማዋል ማድረግ የሚችለውን ሁሉ ለማድረግ ሥራ ላይ ስለሆነ በሁሉም አቅጠጫ መጠበቅ እንዳለብን ይሰማኛል። ማንኛውም የሚያውክና በተሳሳተ ነገር ላይ የተመሰረተ ሽብር የሚፈጥር ነገር በእርግጠኝነት የአጸፋ መልስ ስለሚኖረው መፈራት አለበት።"— Letter 34, 1887.
"በእግዚአብሔር ተመርተናል በሚሉ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ባሉ ሰዎች አማካይነት ሁልጊዜ የውሸትና ጥራዝ ነጠቅ እንቅስቃሴዎች ይደረጋሉ። እነዚህ ሰዎች ከመላካቸው በፊት የሚሮጡና ላልተፈጸመው ትንቢት ቀንና ዓመተ ምህረት ወስነው የሚሰጡ ናቸው። እነዚህ ሰዎች የወሰኑአቸው ቀናትና ዓመታት አለመፈጸምና ወደ ውሸት መንገዶች መምራት ግራ መጋባትንና አለማመንን ስለሚፈጥር በድርጊታቸው ጠላት ይደሰታል።"-Selected Messages 2:84 (1897).
➡️ 1844 ባሻገር ሌላ የጊዜ ትንቢት የለም
"በጃክሰን በነበረው የካምፕ ስብሰባ ላይ እነዚህ ጥራዝ ነጠቅ ሰዎች የነፍሳት ጠላትን ሥራ እየሰሩ እንደሆነ በግልጽ ተናግሬያለሁ፡፡ በጨለማ ውስጥ ነበሩ። የምህረት በር በጥቅምት 1884 ዓ.ም እንደሚዘጋ የሚገልጽ ትልቅ ብርሃን እንዳላቸው ተናገሩ። በዚያ ቦታ በሕዝብ ፊት ከ1844 ወዲህ በተሰጡ መልእክቶች ውስጥ የተወሰነ ጊዜ እንደማይኖር እግዚአብሔር ለእኔ በማሳየቱ ደስተኛ መሆኑን ነግሬያቸው ነበር።" Selected Messages 2:73 (1885).
"አቋማችን በ1844 በተፈጸሙ ትንቢታዊ ጊዜያቶችና በጌታ መገለጥ ጊዜ መካከል ምንም ዓይነት የጊዜ እወጃን ጣልቃ ሳናስገባ ነቅቶ መጠበቅ ነው::"—Manuscript Releases 10:270 (1888).
"የተወሰነ ጊዜን በተመለከተ ሕዝቡ ሌላ መልእክት አይሰጠውም። ከዚህ ጊዜን ከሚመለከት ወቅት በኋላ (ራዕይ 10:4-6)፣ ከ1842 እስከ 1844፣ የተወሰነ ትንቢታዊ ጊዜን የሚጠቅስ ሌላ ወቅት ሊኖር አይችልም። ረዥሙ የጊዜ ስሌት እስከ 1844 የመከር ወቅት ይደርሳል።" -The S.D.A. Bible Commentary 7:971 (1900).
@MesayD
ይቀጥላል .... | 1 534 |
