ru
Feedback
SDA የትንቢት ጹሑፎች

SDA የትንቢት ጹሑፎች

Открыть в Telegram

“ዘመኑ ቀርቦአል፤ እንግዲህ ይህን የትንቢት ቃል የሚያነብ ብፁዕ ነው፤ የሚሰሙትና የተጻፈውንም የሚጠብቁ ብፁዓን ናቸው።” — ራእይ 1፥3 (አዲሱ መ.ት)

Больше
2 317
Подписчики
+424 часа
+137 дней
+5930 день
Архив постов
መልካም ሰንበት
መልካም ሰንበት

መልካም ሰንበት
መልካም ሰንበት

መልካም ሰንበት
መልካም ሰንበት

እግዚአብሔር ቢኖር ኖሮ... አንድ ፀጉር አስተካካይ የአንድን ሰው ፀጉር እየቆረጠ ሳለ ፀጉሩን ለሚያስተካክለው ሰው እንዲህ አለ፦ “እኔ በእግዚአብሔር መኖር አላምንም።” ​ደንበኛው ፦ “ለምን?” ሲል ጠየቀው። ​አስተካካዩም ፦ “በዓለም ላይ በርካታ መከራና ምስቅልቅል አለ። እርሱ ቢኖር ኖሮ ይህ ሁሉ ችግር አይኖርም ነበር” አለ። ​ደንበኛውም ፦ “እኔም በፀጉር አስተካካዮች አላምንም...” አለ። ​አስተካካዩም ግራ በመጋባት፦ “ምን ማለትህ ነው?” ሲል ጠየቀ። ​ደንበኛውም ለአስተካካዩ፦ “እነዚያን ውጭ ያሉ የተንጨባረረ ፀጉር ያላቸውን ሰዎች ታያቸዋለህ?” አለው። ​አስተካካዩም ፦ “አዎ” አለ። ​ደንበኛውም ፦ “ፀጉር አስተካካዮች ቢኖሩ ኖሮ፣ ረጅም እና ያልተስተካከለ ፀጉር ያላቸው ሰዎች አይኖሩም ነበር” አለ። ​ አስተካካዩም ፦ “እኛ አለን፤ ነገር ግን ሰዎች ወደ እኛ አይመጡም!” አለ። ​ ደንበኛውም በመቀጠል፦ “ትክክል። እግዚአብሔር አለ፤ ነገር ግን ሰዎች ለመስተካከል ወደ እርሱ አይመጡም። በዓለም ላይ በርካታ ችግሮች የበዙበትም ምክንያት ለዚህ ነው” አለው። (ፖል ዊልያም)

Audio from Dubushe

Audio from Mesay D Dubushe

Happy Sabbath from Ethiopian SDA Church South Africa, DURBAN
+5
Happy Sabbath from Ethiopian SDA Church South Africa, DURBAN

ይህንን ቪዲዮ እንደ SDA አባልነታችን እንዴት እንመለከታለን ? እንዲህ ይቻላል እንዴ?🤔

የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች ምዕራፍ 4:- የእግዚአብሔር የመጨረሻው ዘመን ቤተክርስቲያን (የመጨረሻ ክፍል) ➡️ በተሰጣቸው ብርሃን ይፈረዳሉ የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን በቤተ መቅደስ ሚዛን ትመዘናለች። የምትፈረደው በተሰጡአት አጋጣሚዎችና ጥቅሞች ነው። መንፈሳዊ ልምምዷ ክርስቶስ ታላቅ ዋጋ በመክፈል ከሰጣት ጥቅሞች ጋር የማይጣጣም ከሆነ የተሰጡአት በረከቶችም ለተሰጣት ሥራ ካላዘጋጁአት፣ በራሷ ፈቃድ “ቀለሽ ተገኘሽ" የተባለው አረፍተ ነገር ይነገርባታል። በተሰጣት ብርሃንና በተሰጡአት ዕድሎች ትፈረዳለች።.. አገልግሎት እንዲሰጡ በተገነቡ ውድ በሆኑ ሕንጻዎች ውድመት የተገለጡ አስፈሪ ተግሳጾች [ባትል ክሪክ የነበረው በዓለም ላይ ትልቁና እጅግ ታዋቂ የነበረው የአድቬንቲስት የጤና ተቋም፣ እ.አ.አ. የካቲት 18፣ 1902 ዓ.ም ተቃጥሎ አመድ ሆኗል፡፡] ለእኛ እንዲህ የሚል መልእክት ያስተላልፋሉ፡- “አሁንም ከወዴት እንደወደቅህ አስብ፣ ንስሃም ግባ፣ የቀደመውንም ሥራ ሥራ።" (Revelation 2:5).... በራሷ ወደ ኋላ ማፈግፈግ እየቦካች (እየኮመጠጠች) ያለች ቤተ ክርስቲያን ንስሃ ካልገባችና ካልተለወጠች ራሷን እስከምትጠላ ድረስ የሥራዋን ፍሬ ትበላለች። ክፉን ተቃውማ መልካምን ስትመርጥ፣ ራሷን በማዋረድ እግዚአብሔርን ስትሻ እና በክርስቶስ የቀረበላትን ታላቅ ጥሪ ስትቀበል ትፈወሳለች። ያኔ እግዚአብሔር በሰጣት የዋህነትና ንጽህና ከምድራዊ ጥልፍልፍ ተለይታ እውነት አርነት እንዳወጣት በማሳየት ትኖራለች። እንዲህ ሲሆን አባላቷ በእርግጥ የእግዚአብሔር ምርጦችና የእርሱ ተወካዮች ይሆናሉ።— Testimonies for the Church 8:247-251 (April 21, 1903). ➡️ የእሥራኤላውያን ታሪክ ለእኛ ማስጠንቀቂያ ነው በዚህ የመጨረሻ ዘመን የጥንት እሥራኤላውያንን ያጋጠመው ዓይነት ተመሳሳይ አደጋ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ያጋጥማቸዋል። እግዚአብሔር የሚሰጣቸውን ማስጠንቀቂያዎች የማይቀበሉ ሁሉ የጥንት እሥራኤላውያን ባለማመናቸው ምክንያት በወደቁባቸው አደጋዎች ውስጥ ይወድቃሉ፡፡ ካለማመናቸው የተነሳም ወደ እረፍቱ ሳይገቡ ይቀራሉ። የጥንቶቹ እሥራኤላውያን በማያምን ልባቸውና ፈቃዳቸውን ካለማስገዛታቸው የተነሣ መከራ ደርሶባቸዋል። በመጨረሻም የተለየ ሕዝብ የመሆን መብት ያጡት በራሳቸው አለማመን፣ በራስ በመተማመናቸው፣ ንስሃ ባለመግባታቸው፣ በአእምሮ እውርነታቸውና በልበ ደንዳናነታቸው ምክንያት ነበር። በእነርሱ ታሪክ አማካኝነት በእኛ ፊት የአደጋ ምልክት ከፍ ብሎ ተሰቅሏል። “ወንድሞች ሆይ፥ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስከዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፤... የመጀመሪያ እምነታችንን እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ፥ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና።” (ዕብራውያን 3:12, 14)። Letter 30, 1895. ➡️ በጦር ሜዳ ያለችው ቤተ ክርስቲያን ፍጹም አይደለችም በጦር ሜዳ ያለችው ቤተ ክርስቲያን ድል የነሳች አይደለችም፣ ምድርም ሰማይ አይደለም። ቤተ ክርስቲያን ለዚህ ሕይወትና ለወደፊቱ ዘላለማዊ ሕይወት ለመሰልጠን፣ ለመታረምና እውቀት ለማግኘት በክርስቶስ ትምህርት ቤት እየተማሩ ካሉ ተሳሳችና ፍጽምና ከጎደላቸው ወንዶችና ሴቶች የተውጣጣች ነች።— The Signs of the Times, January 4, 1883. አንዳንድ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄዱ ሁሉም ነገር ተሟልቶ ንጹህና ፍጹም ከሆኑ ሰዎች ጋር ብቻ የሚገናኙ ይመስላቸዋል። ለእምነታቸው ቅናት ስላላቸው በቤተ ክርስቲያን አባላት ውስጥ ስህተት ሲያዩ “ዓለምን ትተን የመጣንበት ምክንያት ከክፉ ጠባያት ጋር ግንኙነት (ሕብረት) እንዳይኖረን ነበር፤ ነገር ግን እዚህም ክፋት አለ" ይላሉ። በምሳሌው የነበሩ ባሪያዎች እንደጠየቁት “እንክርዳዱ ከወዴት መጣ?” በማለት ይጠይቃሉ፡፡ ነገር ግን ጌታ ቤተ ክርስቲያን ፍጹም ናት ወደሚል ማጠቃለያ የሚያመጣንን ማረጋገጫ ስላልሰጠን ተስፋ መቁረጥ የለብንም፡፡ በጦርነት ላይ ያለችውን ቤተ ክርስቲያን እንደ አሸናፊዋ ንጹህ ቤተ ክርስቲያን አድርገን የምናይ ከሆነ ለእውነት ያለን ቅናታችን ሁሉ ስኬታማ ሳይሆን ይቀራል። - Testimonies to Ministers and Gospel Workers, 47 (1893). ➡️ አሸናፊዋ ቤተ ክርስቲያን ታማኝና ክርስቶስን የምትመስል ትሆናለች ሥራው በቶሎ ሊዘጋ ነው፡፡ ታማኝነታቸውን ያረጋገጡ በጦርነት ላይ ያለችው ቤተ ክርስቲያን አባላት የአሸናፊዋ ቤተ ክርስቲያን አባላት ይሆናሉ።— Evangelism, 707 (1892). የክርስቶስ ሕይወት በእግዚአብሔር ፍቅር መለኮታዊ መልእክት የተሞላ ነበር። ይህንን ፍቅር በሙላት ለማጋራት ጥልቅ ምኞት ነበረው። ከፊቱ ርኅራኄ ይንጸባረቅ ነበር። ጸባዩ በጸጋ፣ ራስን ዝቅ በማድረግ፣ በእውነትና በፍቅር የተሞላ ነበር። እያንዳንዱ በጦር ሜዳ ያለችው የእርሱ ቤተ ክርስቲያን አባል የአሸናፊዋ ቤተ ክርስቲያን አባል መሆን ከፈለገ ተመሳሳይ ብቃቶችን ማሳየት አለበት።—Fundamentals of Christian Education, 179 (1891). @MesayD ምዕራፍ 5 ይቀጥላል ...

የመጨረሻው ዘመን ክስተቶች ምዕራፍ 4:- የእግዚአብሔር የመጨረሻው ዘመን ቤተክርስቲያን (ክፍል ሰባት) ➡️ መንፈሳዊ መነቃቃት አሁንም ያስፈልጋል መታመንን በሚጠይቁ የሀላፊነት ቦታዎች የተቀመጡ ሰዎች የእግዚአብሔርን ፈቃድና መንገድ ተከትለው ቢሆን ኖሮ ባለፈው የጄኔራል ኮንፍራንስ [1901] ስብሰባ ላይ ሊከናወን ይችል ስለነበረው ሥራ አንድ ቀን በእኩለ ቀን ጊዜ እየጸፍኩ ነበር። ትልቅ ብርሐን የተሰጣቸው ሰዎች በብርሃኑ አልተመላለሱም። ስብሰባው ተዘግቷል፣ እረፍትም አልተደረገም፡፡ ሰዎች ማድረግ እንደሚገባቸው ራሳቸውን በእግዚአብሔር ፊት ዝቅ አላደረጉም፣ መንፈስ ቅዱስም አልተሰጠም። ራሴን በሳትኩ ሰዓት እስከዚህ ድረስ የጻፍኩ ሲሆን በባትል ክሪክ እየሆነ ያለውን ትዕይንት የምመለከት መሰለኝ፡፡ በቤተ መቅደሱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተሰብስበን ነበር። ጸሎት ተደርጎ መዝሙር ተዘመረና እንደገና ጸሎት ተደረገ፡፡ ልባዊ የሆነ ተማዕጽኖ ወደ እግዚአብሔር ቀረበ። በስብሰባው ላይ የመንፈስ ቅዱስ መገኘት ታይቶ ነበር።… በቦታው ከተገኙት መካከል ማንም ልባዊ ኑዛዜ ማድረግ እስከማይችል ድረስ በትዕቢት የተወጠረ ሰው አልነበረም፡፡ በዚህ ሥራ ውስጥ ይመሩ የነበሩ ሰዎች ተጽእኖ ማሳደር የሚችሉ ሰዎች ነበሩ፣ ነገር ግን ከዚህ በፊት ኃጢአቶቻቸውን ለመናዘዝ ድፍረት አልነበራቸውም ነበር። በቤተ መቅደሱ ውስጥ ከዚህ በፊት በፍጹም ተሰምቶ የማይታወቅ ደስታ ነበር። ራሴን ከሳትኩበት ተነሳሁና ለተወሰነ ጊዜ የት እንደነበርኩ ማሰብ አቃተኝ፡፡ ብዕሬ እስካሁን በእጄ ነበር። እንዲህ የሚሉ ቃላት ተነገሩኝ፦ “ይህ ሊሆን ይችል ነበር። ጌታ ይህን ሁሉ ለሕዝቡ ሊያደርግ እየጠበቀ ነበር። ሰማይ በሙሉ ቸርነትን ለማድረግ እየጠበቀ ነበር።" ባለፈው የጄኔራል ኮንፍራንስ ጊዜ የተሟላ ሥራ ተሰርቶ ቢሆን ኖሮ የት ልንሆን እንችል እንደነበር አሰብኩ። -Testimonies for the Church 8:104-106 (January 5, 1903). በሌሊት በፊቴ ያለፉ ትዕይንቶች ጥልቅ ስሜት ፈጥረውብኛል። ትልቅ እንቅስቃሴ--የመነቃቃት ሥራ በብዙ ቦታዎች እየተከናወነ ያለ መሰለኝ፡፡ ሕዝባችን ለእግዚአብሔር ጥሪ ምላሽ በመስጠት በመስመር እየሄዱ ነበር።—Testimonies to Ministers and Gospel Workers, 515 (1913). (ኤለን ኋይት በ1913 የጄኔራል ኮንፍራን ወቅት ካስተላለፈችው የመጀመሪያ መልእክት የተወሰደ።] ➡️ እግዚአብሔር በሕዝቡ ላይ ያለው ትዕግሥት ቤተ ክርስቲያን በአሳዛኝ ሁኔታ አዳኝዋ የሚጠብቅባትን ሳትፈጽም ቀርታለች። ሆኖም እግዚአብሔር ከሕዝቡ አልተለየም። ነገር ግን አሁንም ይታገሳቸዋል። ይህንን የሚያደርገው በእነርሱ ውስጥ መልካምነት ስለተገኘ ሳይሆን ስሙ በእውነትና በጽድቅ ጠላቶች ፊት እንዳይዋረድና የሰይጣን ወኪሎች የእግዚአብሔርን ሕዝብ በማጥፋት ድል እንዳያገኙ ነው፡፡ በአመጸኝነታቸው፣ ባለማመናቸውና በሞኝነታቸው ታግሷቸዋል። በአስደናቂ ትዕግሥትና ርኅራኄ ቀጥቷቸዋል። መመሪያውን ቢያዳምጡ ኖሮ በዘላለማዊ ድነት በማዳንና የጸጋው ኃይል ዘላለማዊ ሐውልቶች በማድረግ ከግትር ዝንባሌዎቻቸው ያነጻቸው ነበር። -The Signs of the Times, November 13, 1901. ቤተ ክርስቲያን ደካማና ጉድለት ያለባት ብትሆንም ክርስቶስ ከፍተኛ ትኩረት የሚያደርግባት ብቸኛ አካል እንደሆነች ማስታወስ አለብን። ስለ እርሷ ከልብ በማሰብ ያለማቋረጥ ነቅቶ እየጠበቃትና በመንፈስ ቅዱስ እያበረታታት ይገኛል።—Selected Messages 2:396 (1902). ➡️ እግዚአብሔር ታማኞች ከሆኑት ጋር ይሰራል ጌታ ኢየሱስ ሁል ጊዜ የሚያገለግሉት የተመረጡ ሕዝቦች ይኖሩታል። አይሁዶች የሕይወት ልዑል የሆነውን ኢየሱስን አልቀበል ባሉ ጊዜ መንግሥትን ከእነርሱ ወሰደና ለአህዛብ ሰጠ። እግዚአብሔር በእያንዳንዱ የሥራ ዘርፍ በዚህ መርህ መስራቱን ይቀጥላል። ቤተ ክርስቲያን ለጌታ ያላትን ታማኝነት ስታጎድል፣ የፈለገውን ያህል ሥልጣን ቢኖራቸውም፣ መጠራታቸውም የፈለገውን ያህል ታላቅና ቅዱስ ቢሆንም፣ እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር መስራቱን አይቀጥልም፡፡ አስፈላጊ ሀላፊነቶችን ለመሸከም ሌሎች ይጠራሉ። ነገር ግን እነዚህም ነፍሳቸውን ከስህተት ድርጊቶች ካላነጹ እና በየወሰናቸው ንጹህና ቅዱስ መርሆዎችን ካልመሰረቱ፣ ጌታ በአሰቃቂ ሁኔታ መከራ በማምጣት ዝቅ ያደርጋቸዋል፡፡ እነርሱም ካልተናዘዙ ከቦታቸው በማስወገድ መሳለቂያ ያደርጋቸዋል።—Manuscript Releases 14:102 (1903). @MesayD ይቀጥላል ....