1 739
Подписчики
-124 часа
+17 дней
-730 день
Архив постов
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግር ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ስራ ሂደት በስሩ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን እንደ ተቋም በሂደቱ በኩል በወረደው ዕቅድ ዙሪያ የግንዛቤ ስልጠና ሰጠ::
ሂደቱ በዛሬው እለት ባዘጋጀው መድረክ ላይ የ2016 ዓ.ም የቴ/ሽ/ኢ/ኤ አገልግሎት ዕቅድ ዙሪያ በሂደቱ እስተባባሪዎች ሰፋ ያለ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን በተጨማሪም የሂደቱ ፈፃሚ አሰልጣኝ መምህራን የግል እቅድ ዝግጅትና አተገባበር ላይም ያተኮረ ስልጠና ያካተተም ነበር::
የስልጠናው ተሳታፊ እሰልጣኝ መምህራንም በተሰጣቸው ስልጠና ላይ ያላቸውን ሀሳብ በማጋራት ውይይት ያደረጉ ሲሆን በመጨረሻም በስራ ሂደቱ ሃላፊ ማብራርያ ተሰቶባቸው መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥቅምት 27/2016 ዓ.ም
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
