ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 567 подписчиков, занимая 8 356 место в категории Технологии и приложения и 2 162 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 567 подписчиков.

Согласно последним данным от 24 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 24, а за последние 24 часа — 19, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.91%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.83% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 035 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 465 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 25 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 567
Подписчики
+1924 часа
+197 дней
+2430 день
Архив постов
በጣቢያው የቤቶች እድሳት እየተከናወነ ነው .........///......... የጣቢያውን ሠራተኞች መኖሪያ እና የእንግዳ ማረፊያ ቤቶችን እድሳት እያከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 1 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ገለጸ። የጣቢያው ሲቪል መሐንዲስ አቶ ምንተስኖት ወዬሳ እንደገለጹት በጣቢያው የሚገኙ ቤቶች ረጅም ዓመት ያገለገሉ በመሆናቸው ከፍተኛ ጉዳት አጋጥሟቸዋል። በጣቢያው 68 የሠራተኛ መኖሪያ እና የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች መኖራቸውን የጠቆሙት አቶ ምንተስኖት በየምዕራፉ አስር ቤቶችን ለማደስ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። እስከ አሁን 18 የሠራተኛ መኖሪያና አንድ የእንግዳ ማረፊያ ቤት እድሳት ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ከቤቶቹ እስከ ሦስት ሜትር ድረስ የተተከሉ ዛፎች የሽንት ቤት መስመሮችን የመዝጋትና በሕንጻዎቹ ላይ የመሰንጠቅ አደጋ መፍጠራቸውን የተናገሩት ባለሙያው ዛፎቹን በመቁረጥ የሻወር፣ የሽንት ቤትና የእጅ መታጠቢያ እቃዎችን ሙሉ በሙሉ በመቀየር የእድሳት ሥራው እየተከናወነ ነው ብለዋል። በተጨማሪም የጣራ መቀየርና መጠገን፣ የመሬት ፕላስቲክ ታይልስ እና የኮርኒስ መቀየር እንዲሁም የኤሌክትሪክ መስመር ዕድሳት፣ የዝገት መከላክያ እና የቀለም ቅብ ሥራዎችም የእድሳቱ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል። የቀሪ ቤቶችን እድሳትን ለማጠናቀቅም ታቅዶ እየተስራ መሆኑን ጠቁመዋል። ለጣቢያው ሠራተኞች ምቹ የመኖሪያ ከባቢን ለመፍጠር ኮሚቴ በማቋቋም ሌሎች ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል። አቶ ምንተስኖት እንዳሉት ከቤቶቹ ዕድሳት ጎን ለጎንም የመኖሪያ ጊቢውን ገፅታ የማስዋብ ሥራም ተጀምሯል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

ከተቋሙ ጋር በመስራታችን ደስተኞች ነን አሉ የታንዛኒያ ልዑክ .........///......... የታንዛኒያ ኤሌክትሪክ አቅራቢ ድርጅት የእቅድ፣ ምርምር እና ኢንቨስትመንት ምክትል ዳይሬክተር ሚስስ ሬንታ ሲ ንድጌ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት እና ሌሎች የሥራ ክፍሎችን ተዘዋውረው ጎበኙ፡፡ ዳይሬክተሯ በጎብኝታቸው ወቅት እንደተናገሩት ካምፓኒያቸው በኃይል አቅርቦት እና ተያያዥ ጉዳዮች ከተቋሙ ጋር በመስራቱ ደስተኛ እንደሆኑ ገልፀዋል፡፡ ወደ ተቋሙ ለመጀመሪያ ጊዜ የመጡት ምክትል ዳይሬክተሯ የተቋሙ ሠራተኞች ልጆቻውን በመከባከብ በሥራ ቦታ ውጤታማ እንዲሆኑ ለማድረግ ደረጃውን የጠበቀ የህጻናት ማቆያ እና የሰራተኞች ክሊኒክ መዘጋጀቱ የሚበረታታ ተግባር ነው ብለዋል፡፡ የሁለቱ ተቋማት የኃይል ሽያጭ ስምምነት በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ተግባር እንደሚለወጥ እምነታቸውን ገልፀዋል። ተቋሙ በኃይል ልማቱ ዘርፍ ያለውን የካበተ ልምድና አቅም ለካምፓኒያቸው ባለሙያዎች በማጋራት የተቋማቱን ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክር ያላቸውን እምነት ሚስስ ሬንታ ገልጸዋል ፡፡ ምክትል ዳይሬክተሯ በጉብኝታቸው የተቋሙን የህጻናት ማቆያ፣ የሠራተኞች ክሊኒክ፣ በግንባታ ላይ ያለውን የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ፕሮጀክት እና የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከልን ተመልክተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 09 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

በተቋሙ የኤሌክትሪክ ተሸርካሪዎችን ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ ነው ---///--- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የገዛቸውን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ አውቶቡሶች ወደ ሥራ ለማሰገባት የሚያስችል ስልጠና እየሰጠ መሆኑን በተቋሙ የትራንስፖርት ስምሪትና ቁጥጥር መምሪያ አሰታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ኃይላይ ተስፋይ እንደገለፁት ተቋሙ ለሠራተኞች የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ዘጠኝ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶችን ገዝቷል፡፡ እነዚህን ተሸከርካሪዎች ወደ ሥራ ለማስገባት 35 ለሚሆኑ ሾፌሮች፣ መካኒኮችና ኤሌክትሪሽያኖች ለሦስት ቀናት የሚቆይ ስልጠና ከበላይነህ ክንዴ ግሩፕ በመጡ አሰልጣኞች መስጠት መጀመሩን ገልጸዋል፡፡ ሥልጠናው ባለሙያዎቹ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ቻርጅ ለማድረግ፣ ለመጠገንና ለማሽከርከር የሚስችላቸውን ክህሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን አቶ ኃይላይ ተናግረዋል፡፡ ከስልጠናው ቀጥሎ ባሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ተሸከርካሪዎቹን ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውንም ገልፀዋል፡፡ ሁለት የተሸከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች በዋና መስሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ተገንብተው ዝግጁ መሆናቸውን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን መጠቀም መቻሉ ከተለያዩ ወጭዎች እንደሚያድነውም አብራርተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከበላይነህ ክንዴ ግሩፕ ለመግዛት ስምምነት ካደረገባቸው 12 ተሸከርካሪዎች መካከል አራት ከፍተኛና አምስት መካከለኛ አውቶብሶችን በቅርቡ በጊቢው ውስጥ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በተካሄደ የርክክብ ፐሮግራም መረከቡ ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 08 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ማከፋፈያ ጣቢያው ለከተማዋ ኢንቨስትመንት ማደግ ቁልፍ ድርሻ እያበረከተ ነው …..…..///….….. የደብረ ብርሃን ቁጥር ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ለከተማዋ እና በዙሪያዋ ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ ቁልፍ ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ዳኜ ይታገሱ እንደገለፁት ጣቢያው የደብረ ብርሃን ከተማን የኃይል አቅርቦት ችግርና በአካባቢው ያለውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ታሳቢ በማድረግ የተገነባ ነው። በመሆኑም የደብረ ብርሃን ከተማን ጨምሮ የወረዳ ከተሞችን እንዲሁም የኢንዱስትሪዎችን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ በመመለስ የአካባቢው የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲሻሻል ማድረጉን ተናግረዋል። የደብረ ብርሃን ቁጥር ሁለት የማከፋፈያ ጣቢያ 200 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የመጫን አቅም ያላቸው ሁለት ባለ 125 እና ሁለት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች እንዳሉት አቶ ዳኜ ጠቁመዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በቀጥታ ለኢንዱስትሪዎች እና ለህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ የሚያቀርቡ ዘጠኝ ባለ 33 እና አስር ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት። በ33 ኪሎ ቮልት ለደብረ ብርሃን፣ እነዋሪ፣ ጅሁር፣ ሸኖ፣ ሀገረ ማሪያም እና ጊናገር ከተሞች እንዲሁም ለደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ፣ ለብቅል፣ ለብርጭቆ፣ ለብረት ድስት፣ ለእብነ በረድ ፋብሪካዎች ኃይል እያቀረበ ነው ብለዋል። ጣቢያው አገልግሎት መስጠት በጀመረበት ወቅት ከ2 ሜጋ ዋት ያልበለጠ ኃይል ያቀርብ እንደነበር ያወሱት ሥራ አስኪያጁ በአሁኑ ወቅት በአንድ ወጪ መስመር ብቻ ከ15 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት በ33 ኪሎ ቮልት 25 ሜጋ ዋት እንዲሁም በ15 ኪሎ ቮልት 48 ሜጋ ዋት ኃይል እያቀረበ ይገኛል ያሉት አቶ ዳኜ ከጣቢያው ኃይል እያገኙ ያሉ ኢንዱስትሪዎች በሙሉ አቅማቸው ማምረት ሲጀምሩ የኤሌክትሪክ አቅርቦቱ አሁን ካለው ከፍ እንደሚልም ነው የጠቆሙት። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በዳታ ማይኒንግ ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ለሦስት የቻይና ኩባንያዎች 30 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት ኃይል እያቀረበ ነውም ብለዋል። የደብረ ብርሃን ቁጥር ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው መገንባቱ ለዞኑ እና ለከተማው መልካም አጋጣሚ መፍጠር ችሏል ያሉት አቶ ዳኜ ከተማዋ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንድትሆን አወንታዊ ሚና መጫወቱንም ገልፀዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ከጊዜ ወደ ጊዜ በአካባቢው ያለው የኢንቨስትመንት ቁጥር መጨመር ጣቢያው በየዓመቱ ከ50 ሜጋ ዋት በላይ የኃይል አቅርቦት ዕድገት እንዲያሳይ አድርጓል። በከተማዋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን ፈጣን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ታሳቢ የሚያደርጉ ተጨማሪ ወጪ መስመሮች መገንባት እንደሚኖርባቸውም ነው የጠቆሙት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 08 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

አትሌቲክስ ቡድኑ ሲያሸንፍ የሴቶች የእግር ኳስ ቡድኑ ደግሞ ነጥብ ተጋርቷል ……….///………… ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ባዘጋጀው የ2017 ዓ.ም የአይ ኤፍ ኤች የ12 ኪ.ሜ የዱላ ቅብብል ሩጫ በወንዶች ዘርፍ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አሸንፏል። በአዲስ አበባ ትናንት በተካሄደው ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በወንዶች ዱላ ቅብብል 1ኛ በመውጣት የዋንጫ እና የ60 ሺህ ብር ተሸላሚ ሲሆን የኦሮሚያ ማረሚያ እና መቻል ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል። በተመሳሳይ በሴቶች ምድብ በተካሄደው የዱላ ቅብብል የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ቢሮ አንደኛ፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሁለተኛ ደረጃን ይዘው ሲያጠናቅቁ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ 3ኛ ደረጃ ይዟል። በሌላ ዜና በ9ኛ ሳምንት የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከአዲስ አበባ ጋር ተጫውቶ አቻ ተለያይቷል። ትናንት በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስቴዲየም የተከናወነው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ያለምንም ጎል ባዶ ለባዶ ተጠናቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 07 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን ይዞታ እንደሚያስከብር የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ ….....///…….... የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር በከተማው የሚገኘውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ይዞታ የማስከበር ሥራ እንደሚሰራ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት ገለፁ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎች ከከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት ጋር በኤሌክትሪክ አቅርቦት፣ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍስሃ ጌታቸው ለከንቲባው እንደገለፁት ተቋሙ በኃይል ማመንጨት እና ማስተላለፍ ዘርፍ ለሀገር ዕድገት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል። ሁለቱ ኃይል አቅራቢ ተቋማት በስያሜ ደረጃ የተለያዩ ቢሆኑም ለህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ ተደራሽ በማድረግ በኩል ኃላፊነታቸውን በጋራ እየተወጡ እንደሚገኙ ገልፀዋል። እንደ አቶ ፍስሃ ገለፃ በደብረ ብርሃን ከተማ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ታሳቢ ያደረጉ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች እየተገነቡና አቅማቸው እያደገ ይገኛል። ከተማ አስተዳደሩ ከደብረ ብርሃን ቁጥር ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ጋር ተያይዘው ለሚስተዋሉ ችግሮች አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥም ነው የጠየቁት። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደብረ ብርሃን ዲስትሪክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉጌታ ደሳለኝ በበኩላቸው እንደተናገሩት ለህብረተሰቡ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ከዞኑ እና ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በቅርበት እየተሰራ ነው። ከኃይል መቆራረጥ ጋር የተያያዙ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ከተማ አስተዳደሩ የወሰን ማስከበር እና ዛፎችን የማፅዳት ሥራዎችን ከወረዳና ቀበሌዎች ጋር በትብብር እንዲሰራም ነው ጥሪ ያቀረቡት። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት ከተማዋ የተሻለ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖራት ተቋማቱ ላከናወኗቸው የልማት ሥራዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በከተማዋ ማስተር ፕላን ውስጥ ለአራት አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ የሚያገለግሉ ቦታዎች መካተታቸውን የጠቀሱት ከንቲባው ካሳ የተከፈለባቸው የኃይል መሰረተ ልማቶችን በማስጠበቅ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲያገኙ እናደርጋለን ብለዋል። እንደ ከንቲባው ገለፃ ከተማ አስተዳደሩ በአካባቢው ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ያማከለ ተጨማሪ የኃይል አቅርቦት እየጠየቀ ባለበት በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ደህንነት መጠበቅ ግዴታው ነው። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የኃይል አቅራቢ ተቋማቱ በከተማዋ ለሚያከናውኗቸው የልማት ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አቶ በድሉ አረጋግጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 07 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተጀመረው የኃይል ማስተላለፍ ሥራ ሙከራ በስኬት ተከናውኗል ..........///...... ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋው ባለ 400 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የሙከራ ኃይል ማስተላለፍ መጀመሩን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለፀ። የምስራቅ አፍሪካ ኤሌክትሪክ ሀይዌይ ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ በተዘረጋው የኃይል አቅርቦት መሰረተልማት በኩል ተግባራዊ መደረጉ ይታወሳል፡፡ ፕሮጀክቱ ከኢትዮ - ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመቀጠል በሁለተኛነት የተዘረጋ የምስራቅ አፍሪካ ኤሌክትሪክ ሀይዌይ ፕሮጀክት አካል ነው። የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩ የኢትዮ ታንዛኒያ የኃይል ሽያጭ ስምምነት ተግባራዊ ወደመሆን ሊሸጋገር ስለመሆኑ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። በቀጣይ የሜትሮች ፍተሻ በማድረግ መስመሩ ሥራ ሲጀምር ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን በማሳለጥ በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር በማድረግ በሀገራቱ መካካል ትብብርን እንደሚያጠክር ይታመናል። ለፕሮጀክቱ የዓለም ባንክ ፣ የአፍሪካ ልማት ባንክና የፈረንሳይ የልማት ተራድኦ ድርጅት የፋይናንስ ድጋፍ አድርገዋል።      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 06 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት እሁድ ታህሳስ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ኢስት 2 ወይም በቤላ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ
ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት እሁድ ታህሳስ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ኢስት 2 ወይም በቤላ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ በአሜሪካ ኤምባሲ፣ በኢንግሊዝ ኤምባሲ እና በጣሊያን ኤምባሲ፣ በስድስት ኪሎ፣ በሚኒሊክ ሆስፒታል፣ በአራት ኪሎ፣ በቤተ መንግስት አካባቢ በከፊል፣ በፈረንሳይ ጉራራ፣ በእንጦጦ ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን፣ በመገናኛ እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ይቆያል። በተመሳሳይ እሁድ ታህሳስ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በጎፋ የኃይል ማስተላለፊያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በቄራ፣ በጎፋ ካምፕ፣ በባቱ ኮንዶሚኒየም፣ በመካኒሳ አቦ ማዞሪያ፣ በጎፋ ኪዳነምህረት፣ በመካኒሳ ኮንዶሚኒየም፣ በቄራ ኮንዶሚኒየም፣ በጎፋ ማዞሪያ ኮንዶሚኒየም፣ በቻይና ሪል እስቴት እና በላፍቶ አካባቢ ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የሚቆይ ስለሆነ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 05 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኃይል ዘርፉ እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎችን በተመለከተ አዳዲስ ቪዲዮዎች በዩቲዩብ ቻናላችን የምናደርሳችሁ ይሆናል! ✅ የኃይል ማመንጫዎች ✅ የኃይል አስተላላፊ መስመሮችና
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኃይል ዘርፉ እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎችን በተመለከተ አዳዲስ ቪዲዮዎች በዩቲዩብ ቻናላችን የምናደርሳችሁ ይሆናል! ✅ የኃይል ማመንጫዎች ✅ የኃይል አስተላላፊ መስመሮችና ጣቢያዎች ✅ የግድብ ግንባታ 💚 ዛሬውኑ ይከተሉን ❤️፣ ይወዳጁን👍፣ ለጓደኛዎም ያጋሩ! 👉 https://www.youtube.com/@ethiopowermedia We'll be sharing more updates about Ethiopian Electric Power's work in the energy sector on our YouTube channel! ✅ Generation ✅ Transmission and Substations ✅ Construction Projects 🔔 Subscribe, 👍 Like, and 🔄 Share with your friends today! 👉 https://www.youtube.com/@ethiopowermedia Don't forget to like 👍 and share 🔄 our channel to stay informed about Ethiopian Energy. #EEP 🇪🇹 #EnergyUpdates 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ | ቲክቶክ | ድረ - ገፅ ታህሳስ 04 ቀን 2017 ዓ.ም

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፋርማሲስት 2ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፋርማሲስት 2ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት ፊትለፊት በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 04 ቀን 2017 ዓ.ም

ጣቢያው ለበጀት ዓመቱ የሚያገለግል በቂ የውሃ መጠን በግድቡ ይዟል …….///…….…. የጊቤ 3 የውha ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2017 በጀት ዓመት ኃይል ለማመንጨት የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል የውሃ መጠን በግድቡ መያዙን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሀብታሙ ሰሙ እንደገለጹት ጣቢያው በ2016 በጀት ዓመት ከፍተኛ ኃይል ለማመንጨት ሲባል እና በግድቡ ላይ ይሰሩ በነበሩ የጥገና ሥራዎች ምክንያት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ወራት በግድቡ የነበረው የውሃ መጠን ከሌሎቹ ዓመታት በተለየ ዝቅ ያለ ነበር፡፡ በግድቡ የነበረው የውሃ መጠን ከባህር ጠለል በላይ ወደ 832 ሜትር ዝቅ በማለቱ ጣቢያው በክረምቱ ወራት ወደ ግድቡ ይገባ የነበረውን ውሃ ማጠራቀም ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሲስራ መቆየቱን አንስተዋል። አሁን ላይ በግድቡ ያለው የውሃ መጠን ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ወደ 881 ነጥብ 6 ከፍ ማለቱን ተናግረዋል። ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት ጣቢያው ከክረምቱ መግቢያ በፊት በ2017 በጀት ዓመት 5 ሺ 400 ጊጋ ዋት ስዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዶ ነበረ፡፡ ይሁንና ክረምቱ ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ ግድብ የገባው ውሃ ከተገመተው ከፍ ያለ በመሆኑ በክረምት የገባውን የውሃ መጠን ታሳቢ በማድረግ 6 ሺ 165 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት የእቅድ ክለሳ መደረጉንም ገልፀዋል። አሁን በግድቡ ያለው የውሃ መጠን ጣቢያው በቀሪ በጀት ዓመት ያለምንም የውሃ እጥረት ኃይል የማመንጨት ተግባሩን በአስተማማኝነት እንዲያከናውን ለማድረግ የሚያስችለው መሆኑን አቶ ሀብታሙ ገልጸዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ እቅዱን ለማሳካት ከውሃ አስተዳደር ሥራው ጎን ለጎን ሣምንታዊና ወርሃዊ የጥገና ሥራዎች በዕቅድ ተይዘው በመከናወን ላይ ናቸው። በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ጣቢያው በዋናነት በግድቡ ውሃ ማጠራቀም ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ የነበረ ቢሆንም ግሪዱ ላይ በነበረው ፍላጎት ምክንያት የእቅዱን 141 በመቶ ኃይል ማምረት መቻሉን አስታውቀዋል። ታኅሣሥ 8 ቀን 2009 ዓ.ም ተመርቆ ሥራ የጀመረው የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአስር ተርባይን 1 ሺ 870 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 04 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4