ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 567 подписчиков, занимая 8 356 место в категории Технологии и приложения и 2 162 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 567 подписчиков.

Согласно последним данным от 24 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 24, а за последние 24 часа — 19, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.91%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.83% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 035 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 465 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 25 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 567
Подписчики
+1924 часа
+197 дней
+2430 день
Архив постов
የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ከ620 ሚሊየን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ……...///………. ከ620 ሚሊየን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር በቀጣዩ የፈረንጆች 2025 በይፋ ሥራ ሊጀምር ነው። በኬንያ መንግሥት፣ በምስራቅ አፍሪካ ፓወር ፑል እና በዓለም ባንክ አዘጋጅነት የፑሉ አባል ሀገራት ከፍተኛ የሚኒስትሮች ጉባዔ በኬንያ የወደብ ከተማ ሞምባሳ ተካሒዷል። የምስራቅ አፍሪካ ፓወር ፑል ከታዳሽ የኃይል ምንጮች የሚገኘውን ኢነርጂ በአነስተኛ ዋጋ ቀጣይነት ባለው መልኩ በሁሉም አባል ሀገራት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚሰራ ገልጿል። የምስራቅ አፍሪካ የኢነርጂ ሚኒስትሮች ቀጣናዊ የኃይል ሽያጭን ለማሳደግ ገበያ ተኮር አሰራርን መዘርጋት፣ በኃይል ትስስር ፍኖተ ካርታ እንዲሁም የተሻለ ልምድና ተሞክሮ ከመሰል ዓለም አቀፍ ተቋማት መውሰድ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት አካሒደዋል። የተዘረጉ የኃይል መሰረተ ልማቶችን በጋራ የመጠቀምና ተወዳዳሪ የኃይል ሽያጭ ሥርዓትን የማስፈን እንዲሁም ለቀጣናዊ የጋራ ግቦችና ዘላቂ ልማት በትብብር መስራት ሚኒስትሮቹ ከመከሩባቸው አበይት ጉዳዮች መካከል ዋነኞቹ ናቸው። በጉባዔው እንደተገለፀው በቀጣናው የሚፈጠረው የኃይል ትስስር ለዜጎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ለማዳረስ የሚያስችል ነው ተብሏል። በፈረንጆቹ 2025 በይፋ ሊጀመር የታሰበው የኃይል ትስስር ለሀገራቱ ዕድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት የተገለፀ ሲሆን ዕቅዱ በቀጣናው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር በማስቻል ኢኮኖሚያዊ ምርታማነትን እንደሚያሳድግ ተስፋ ተጥሎበታል፡፡ በጉባዔው የኬንያ የኢነርጂ እና ነዳጅ ሚኒስቴር ካቢኔ ፀሐፊ ጄምስ ኦፒዮ ዋንዳይ እንደተናገሩት እንደ ፖሊሲ አውጪ አካል በአባል ሀገራቱ መካከል ለሚፈጠረው የኃይል ሽያጭ ገቢያ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ግዴታችን ነው። እንደ ፀሐፊው ገለፃ የትብብር ባህልን ማጎልበት፣ በቁጥጥር እና ቴክኒክ ማዕቀፎች ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን የመፍታት እና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ሀገራዊ ጉዳዮች ከቀጣናዊ ግቦች ጋር እንዲጣጣሙ የማድረግ ሥራ መስራት ያስፈልጋል። በአሁኑ ወቅት አባል ሀገራቱ በቀጣናው የኃይል ሽያጭ ገበያን ለማስጀመር የሚያስፈልጉ ተቋማዊ ማዕቀፎችን ለማዘጋጀት እና መድረኮችን ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የምስራቅ አፍሪካ ፓወር ፑል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሊቀመንበር ሚስተር ኦሳካይ ኦፖሎት በበኩላቸው ቀጣናዊ እና ሀገራዊ የኢነርጂ ፖሊሲዎችንና መመሪያዎችን ማዋሃድ አባል ሀገራቱ ወደ አንድ የገበያ መር ማዕቀፍ ለሚያደርጉት ሽግግር እንዲሁም የታዳሽ ኃይል ልማትን በማፋጠን የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ለማሳደግ ላላቸው ራዕይ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በቀጣናው ለኬንያ፣ ጅቡቲና ሱዳን የኤሌክትሪክ ኃይል በመሸጥ ላይ ስትሆን፣ ኬንያ በበኩሏ ኢትዮጵያን ከታንዛኒያ ጋር የሚያስተሳስረውን ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ በቅርቡ ማጠናቀቋ ይታወቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 03 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የማከፋፈያ ጣቢያውን ለማዘመን እየተሰራ ነው .........///.......... የሰመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን የኦፕሬሽንና ቁጥጥር ስርዓት ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን ጣቢያው አስታወቀ፡፡ የጣቢያው ኃላፊ አቶ ኢንድሪስ አህመድ እንዳስታወቁት የማከፋፈያ ጣቢያውን የቁጥጥር ስርዓት ጂ.አይ.ኤስ በተሰኘ ዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ለመቀየር የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የጂ.አይ.ኤስ ፓናሎችን ወደ ጣቢያው የማጓጓዝ እና ሥራው እስኪጠናቀቅ ጊዜያዊ አገልግሎት የሚሰጠው የተንቀሳቃሽ ስዊች ጊር የሚቀመጥበትን ቦታ የመምረጥና የመግቢያ መንገዶችን የማስተካከል ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል። በማዘመን ሥራው በጣቢያው ባለ33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ላይ ስድስት ብሬከሮች እንደሚተከሉም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ኢንድሪስ ገለፃ የመቆጣጠሪያ ብሬከር የማዘመን ሥራው የኃይል ብክነትን ለመቀነስ፣ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን ለማቀላጠፍ፣ የኃይል መቋረጥ ጊዜን ለማሳጠርና ለማስቀረት፣ ከኃይል መቆራረጥ ጋር በተያያዘ በደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመቀነስ እንዲሁም የጣቢያው ሠራተኞችን ጊዜ እና ጉልበት ለመቆጠብ ይረዳል፡፡ የሚቀየሩ ብሬከሮቹ ለረጅም ዓመታት የሚያገለግሉ በመሆናቸው ተቋሙ ለጥገናና ሥራ እና ለተጨማሪ ብሬከር ግዥ የሚያወጣውን ወጪ እንደሚቀንስ የጣቢያው ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ ሥራው ኃይል ሳይቋረጥ ጊዜያዊ የተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ በማስቀመጥ እንደሚከናወንም ነው የገለፁት። በተቋሙ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ አንድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፀጋዬ ጌታሁን በበኩላቸው የብሬከር ቅየራው በአካባቢው አስተማማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ ያግዛል ብለዋል፡፡ የብሬከር ማዘመኑ የኃይል መቋረጥን በመቀነስ ተቋሙ ከኃይል ሽያጭ የሚያገኘውን ገቢ ያሳድገዋል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ሥራው እስኪጠናቀቅ ጊዜያዊ አገልግሎት የሚሰጥ የተንቀሳቃሽ ሲዊች ጊር ወደ ቦታው ለማጓጓዝ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ እንደሆነና የቅየራ ሥራውን ከሁለት ሳምንት በኋላ ለመጀመር መታቀዱንም ነው ሥራ አስኪያጁ የገለፁት፡፡ የብሬከር ቅየራ ሥራው በሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን የጥገና ሠራተኞች እና ከሪጅን ማስተባበሪያ ቢሮ በተውጣጡ ባለሙያዎች እንደሚከናወን የተናገሩት አቶ ፀጋዬ በራስ አቅም መከናወኑ ተቋሙ ለውጭ ባለሙያዎች የሚያወጣውን ወጪ ያስቀራል ብለዋል፡፡ ከዚህ በፊት በተለያዩ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተመሳሳይ ሥራዎች በራስ አቅም መከናወናቸውን እና ከዚህም ለቀጣይ ሥራዎች ግብዓት የሚሆን ልምድና የዕውቀት ሽግግር እንደተገኘበት አስታውሰዋል፡፡ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ 25 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው አንድ ትራንስፎርመር፣ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ፣ ስድስት ባለ 33 እና ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የማከፋፈያ ጣቢያውን ለማዘመን እየተሰራ ነው .........///.......... የሰመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን የኦፕሬሽንና ቁጥጥር ስርዓት ለማዘመን እየተሰራ መሆኑን ጣቢያው አስታወቀ፡፡ የጣቢያው ኃላፊ አቶ ኢንድሪስ አህመድ እንዳስታወቁት የማከፋፈያ ጣቢያውን የቁጥጥር ስርዓት ጂ.አይ.ኤስ በተሰኘ ዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ለመቀየር የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የጂ.አይ.ኤስ ፓናሎችን ወደ ጣቢያው የማጓጓዝ እና ሥራው እስኪጠናቀቅ ጊዜያዊ አገልግሎት የሚሰጠው የተንቀሳቃሽ ስዊች ጊር የሚቀመጥበትን ቦታ የመምረጥና የመግቢያ መንገዶችን የማስተካከል ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል። በማዘመን ሥራው በጣቢያው ባለ33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ላይ ስድስት ብሬከሮች እንደሚተከሉም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ኢንድሪስ ገለፃ የመቆጣጠሪያ ብሬከር የማዘመን ሥራው የኃይል ብክነትን ለመቀነስ፣ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን ለማቀላጠፍ፣ የኃይል መቋረጥ ጊዜን ለማሳጠርና ለማስቀረት፣ ከኃይል መቆራረጥ ጋር በተያያዘ በደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመቀነስ እንዲሁም የጣቢያው ሠራተኞችን ጊዜ እና ጉልበት ለመቆጠብ ይረዳል፡፡ የሚቀየሩ ብሬከሮቹ ለረጅም ዓመታት የሚያገለግሉ በመሆናቸው ተቋሙ ለጥገናና ሥራ እና ለተጨማሪ ብሬከር ግዥ የሚያወጣውን ወጪ እንደሚቀንስ የጣቢያው ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ ሥራው ኃይል ሳይቋረጥ ጊዜያዊ የተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ በማስቀመጥ እንደሚከናወንም ነው የገለፁት። በተቋሙ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ አንድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፀጋዬ ጌታሁን በበኩላቸው የብሬከር ቅየራው በአካባቢው አስተማማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ ያግዛል ብለዋል፡፡ የብሬከር ማዘመኑ የኃይል መቋረጥን በመቀነስ ተቋሙ ከኃይል ሽያጭ የሚያገኘውን ገቢ ያሳድገዋል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ሥራው እስኪጠናቀቅ ጊዜያዊ አገልግሎት የሚሰጥ የተንቀሳቃሽ ሲዊች ጊር ወደ ቦታው ለማጓጓዝ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ እንደሆነና የቅየራ ሥራውን ከሁለት ሳምንት በኋላ ለመጀመር መታቀዱንም ነው ሥራ አስኪያጁ የገለፁት፡፡ የብሬከር ቅየራ ሥራው በሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን የጥገና ሠራተኞች እና ከሪጅን ማስተባበሪያ ቢሮ በተውጣጡ ባለሙያዎች እንደሚከናወን የተናገሩት አቶ ፀጋዬ በራስ አቅም መከናወኑ ተቋሙ ለውጭ ባለሙያዎች የሚያወጣውን ወጪ ያስቀራል ብለዋል፡፡ ከዚህ በፊት በተለያዩ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተመሳሳይ ሥራዎች በራስ አቅም መከናወናቸውን እና ከዚህም ለቀጣይ ሥራዎች ግብዓት የሚሆን ልምድና የዕውቀት ሽግግር እንደተገኘበት አስታውሰዋል፡፡ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ 25 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው አንድ ትራንስፎርመር፣ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ፣ ስድስት ባለ 33 እና ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይልድ ኬር የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ታህሳስ 08 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይልድ ኬር የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በላይ ስማ
+1
ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይልድ ኬር የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በላይ ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ታህሳስ 08 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

ኃይል የተቋረጠው በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተከሰተ ችግር ነበር .........///.......... በመላው ኢትዮጵያ ትላንት ምሽት ኃይል ተቋርጦ የነበረው ከታላቁ ህዳሴ ግድብ - ደዴሳ - ሆለታ በተዘረጋው ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የማስተላለፊያ መስመር ላይ አደጋ በማጋጠሙ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። በማዕከሉ የሪል ታይም ኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት እንግዳ እንዳስታወቁት ትላንት ምሽት ኃይል የተቋረጠው በከባድ ንፋስ የተነሳ ዛፍ በኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ በመውደቁ ነው። የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ደህንነት ለማስጠበቅ እስከ 30 ሜትር ድረስ አካባቢውን ከዛፍ የማፅዳት ሥራ ቢሰራም ለመስመሩ ደህንነት ማፅዳት ከተቻለው ውጪ የበቀሉ ትላልቅ ዛፎች ለኃይል መቋረጡ ምክንያት ሆነዋል ብለዋል። በተከሰተው ችግር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአራት ዩኒቶች እያመነጨ የነበረው 1 ሺህ 300 ሜጋ ዋት ኃይል ወደ ሌሎቹ የኃይል ማመንጫዎች በመተላለፉ ምክንያት የኃይል ጭነቱ በግሪድ የኔትወርክ ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ ችግር እንዲፈጠር ማድረጉን ተናግረዋል። የኃይል መቆጣጠሪያ ኔትወርኮች ህብረተሰቡ ከሚጠቀምባቸው ኔትወርኮች የተለዩ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ጉልላት የተቋረጠው ኤሌክትሪክ በሳይበር ጥቃት አልያም በውጫዊ ኃይል የተፈፀመ እንዳልሆነም አብራርተዋል። የኃይል መቆጣጠሪያ የኔትወርክ ሥርዓቱ ከሳይበር ጥቃት ስጋት የፀዳ መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ መሰል ጥቃቶችን ለመከላከል የሚያችል ጠንካራ ሥርዓት መዘርጋቱን ነው የተናገሩት። በመላው ሀገሪቱ ያለው የኃይል አቅርቦት ሥርጭት በአንድ ማዕከል ስር መቆጣጠር በሚያስችል የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት ታግዞ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በተለያዩ ምክንያቶች የሚቋረጠውን የኤሌክትሪክ ኔትወርክ መልሶ ለማገናኘት ከሦስት ሰዓት ያልበለጠ ጊዜ ይወስዳል። ይሁን እንጂ ትላንት ማምሻውን ያጋጠመውን ችግር በፍጥነት ማስተካከል ያልተቻለው ኃይል የተቋረጠበት ሰዓት ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ኤሌክትሪክ በስፋት የሚጠቀምበትና ከፍተኛ የኃይል ጭነት የሚበዛበት በመሆኑ ነው ብለዋል። የተቋረጠውን ኃይል ወደ ነበረበት ለመመለስ በኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል፣ በኃይል ማመንጫዎች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከፍተኛ ርብርብ ሲደረግ እንደነበርም ነው ያነሱት። በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ደህንነት መጠበቅ የዜጎች ኃላፊነት መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ በትዕግስት ለጠበቁ ሁሉ ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ ጉግላት ለተከሰተው ችግር በተቋሙ ስም ይቅርታ ጠይቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በመላው ሀገሪቱ የተቋረጠው ኃይል ወደነበረበት ተመልሷል ........///......... ዛሬ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በሲስተም አለመረጋጋት ምክንያት በመላው ሀገሪቱ ተከስቶ የነበረው የኃይል መቋረጥ ወ
በመላው ሀገሪቱ የተቋረጠው ኃይል ወደነበረበት ተመልሷል ........///......... ዛሬ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በሲስተም አለመረጋጋት ምክንያት በመላው ሀገሪቱ ተከስቶ የነበረው የኃይል መቋረጥ ወደነበረበት መመለሱን የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታውቋል። ማዕከሉ የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁ ደንበኞች ምስጋናውን አቅርቧል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም

በመላው ሀገሪቱ ከተቋረጠው ኃይል ከግማሽ በላይ የሚሆነው ወደነበረበት እየተመለሰ ነው ........///......... በመላው ሀገሪቱ ከተቋረጠው ኃይል ከግማሽ በላይ የሚሆነው ወደነበረበት እየተመለሰ መሆኑን የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። ማዕከሉ እንዳስታወቀው በአዲስ አበባ 85 በመቶ በሚሆነው በአብዛኛዎቹ አካባቢ፣ በአዳማ፣ በሀዋሳ፣ በጅማ፣ አርባምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ሻሸመኔ፣ ወልቂጤ፣ መቀሌ፣ አድዋ፣ አላማጣ፣ ዲላ፣ ቦንጋ፣ ሚዛን እና ሀገረማርያም ኃይል ተመልሶ ተገናኝቷል። እስካሁን ከ50 በመቶ በላይ በሚሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ኃይል መመለሱን የገለፀው ማዕከሉ በቀሪዎቹ አካባቢዎች መልሶ ለማገናኘት ርብርቡ መቀጠሉን ገልጿል። የተፈጠረው ችግር ሙሉ በሙሉ እስኪቀረፍ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠባበቁም ጠይቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የተቋረጠው ኃይል ወደነበረበት እየተመለሰ ነው ........///......... ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው ኃይል ወደነበረበት እየተመለሰ መሆኑን የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። ማዕከሉ እንዳስታወቀው የሲስተሙን ቮልቴጅ በማረጋጋት የተቋረጠውን ኃይል ደረጃ በደረጃ ለመመለስ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ ነው። በአዲስ አበባ በአንዳንድ አካባቢዎች እንዲሁም በክልል ከተሞች የተቋረጠው ኃይል ወደነበረበት መመለሰ መጀመሩን ገልጿል። ስለሆነም የተፈጠረው ችግር ሙሉ በሙሉ እስኪፈታ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም

በመላው ሀገሪቱ የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ ርብርብ እየተደረገ ነው ........///......... ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት በተፈጠረ ችግር የተነሳ በመላው ሀገሪቱ የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል። ችግሩን በመፍታት የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ በኃይል ማመንጫዎች እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው። የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እየጠየቅን ያሉትን መረጃዎች በፍጥነት የምናሳውቃችሁ መሆኑን እንገልፃለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና የኃይል አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ነው .........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና የኃይል አቅርቦቱን በተሟላ ሁኔታ ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀ። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ያለውን የኃይል አቅርቦት ለማጠናከር ከባለድርሻ ተቋማት ጋር ባካሄደው ውይይት ላይ እንደገለፁት የሀገርን ልማት ለማረጋገጥ ተቋሙ ከኃይል ፈላጊዎች ጋር በቅንጅት ይሰራል። ይህን ለማረጋገጥም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት  እና ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተውጣጣ ኮሚቴ መዋቀሩንም ጠቅሰዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ ኮሚቴው በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጣና ለሚያጋጥሙ የኃይል መቆራረጦች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያግዝ ነው። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍስሃ ይታገሱ (ዶ/ር) እንደገለፁት በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ የሚሳተፉ ባለሃብቶችን ለመጋበዝ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት መኖር ቀዳሚ ጉዳይ ነው። በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ያለውን የኃይል አቅርቦት ለማጠናከር እንዲቻል ከኃይል አቅራቢ ተቋማቱ ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባም ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የጠቆሙት። በኢንዱስትሪ ፓርኮቹ የኃይል አቅርቦት ችግር ሲያጋጥም ተቋማቱ ፈጣን ምላሽ ሲሰጡ መቆየታቸውን ያስታወሱት ዶ/ር ፍስሃ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና መስሪያ ቤት በተካሄደው ውይይት ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና የኢንዱሰትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፓሬሽን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።    💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የጨረታ ማስታወቂያ …………/……………. የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር /EEP/DS/01/17 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለተለያዩ አገልግሎት ሊውሉ የሚችሉ ንብረቶችን ባሉበት ቦታና ሁኔታ በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ለመሸጥ እንደሚከተለው በሎት በመከፋፈል አቅርቧል፤ ሎት-1- 08(ስምንት) ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች፤ቦታ ኮተቤ አካባቢ ብረታ ብረት ፊት ለፊት ከሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ግቢ፤ ሎት-2- ለተቋማችን አገልግሎት የማይሰጡ የብረት፣ የተሽከርካሪና የማሽነሪ ስክራፖች፤(ሞተር እና ቻንሲ ቆራርጦ የሚረከብ) ፤ ቦታ ኮተቤ አከባቢ ብረታ ብረት ፊት ለፊት ከሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ግቢ እና አዳማ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግቢ፤ ሎት-3- የጠጠር ማምረቻ (መፍጫ) ክሬቸር ማሽን፤ቦታ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በምዕራብ አርሲ ዞን መልካ ዋከና ኃ/ማመጫ ጣቢያ ግቢ፤ ሎት-4- ለመልካ ሰዲ የዕንፋሎት ኃ/ማመንጫ ጣቢያ ለመገንባት የመጡ ከፍተኛ መጠን፣ ዓይነትና ዋጋ ያላቸው ዕቃዎችና ማሽነሪዎች፤ ንብረቶቹ የሚገኙበት ቦታ በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መልካ ሰዲ ከተማ በፕሮጀክት ጣቢያ ቅጥር ግቢ፤ ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጹትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፤ ማሳሰቢያ፡- ውድድሩ የሚከናወነው ሙሉ በሙሉ በኦክሽን ኢትዮጵያ አክሲየን ማህበር በፈጠሩት የማወዳደሪያ ሲስተም መተግበሪያ https://onelink.to/njnamp መሰረት መሆኑን እየገለጽን መስፈርቶቹ ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል፡- 1. በጨረታው የሚወዳደሩ ተጫራቾች ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ሆኖ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ማስረጃ ወይም የታደሠ መታወቂያ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ 2. ስለጨረታው አካሄድ እና ንብረቶች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን ሰነድ የኦክሽን ኢትዮጵያ ፕላትፎርም ላይ ከንብረቶቹ መግለጫ ስር ተያይዞ የሚገኝ ስለሆነ በነጻ አውርደው መመልከት ይችላሉ። 3. ተጫራቾች የጨረታው ማስታወቂያ ከወጣበት ከሰባተኛው ቀን ጀምሮ ኦክሽን ኢትዮጵያ አክሲየን ማህበር ጋር ቀጠሮ በማስያዝ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ንብረቶቹ በሚገኙበት የተቋሙ ጣቢያዎች በመገኘት መመልከት ይቻላል፤ 4. ተጫራቾች ለሚያቀርቡት ዋጋ 15% ቫትን ጨምሮ ማቅረብ አለባቸው፡፡ 5. ተወዳዳሪዎች በሎት ሁለት ላይ ለመሳተፍ በብረት አቅላጭ ድርጅትነት የተሰማሩ መሆን ያለባቸው ሲሆን፤ የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ 6. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ለሎት አንድ በጨረታ ሰነዱ ላይ በተቀመጠው መሰረት ሲሆን ፣ ለሎት ሁለት ብር 2,000,000.00 (ሁለት ሚሊዮን)፣ ለሎት ሶስት ብር 300,000.00(ሶስት መቶ ሺህ) እና ለሎት አራት ብር 500,000.00(አምስት መቶ ሺህ) በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ስም ብቻ ሲ.ፒ.ኦ. በማሰራት የኦክሽን ኢትዮጵያ መተግበሪያ ላይ የሚጫረቱበትን ዋጋ ማስገባት ይችላሉ። 7. ጨረታው ከ27/03/2017 እስከ 11/04/2017 ዓ.ም እስከ ጠዋት 4፡00 ድረስ ይካሄዳል ስለሆነም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች የጨረታዉን ሂደት በቀጥታ (online) መከታተል ይችላሉ። 8. ተጫራቾች የኦክሽን ኢትዮጵያን መተግበሪያ ከአፕ ስቶር ወይም ኘሌይ ስቶር (Auction Ethiopia) ብለው በማውረድ ወይም (auction.et) ላይ መመዝገብ እና መጫረት ይችላሉ። 9. በጨረታው አሸናፊ ለምትሆኑ ተጫራቾች ለወደፊት አሸናፊነታችሁ በሚገለፅላችሁ ቀን ጀምሮ የሚቆጠር አምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የአሸነፉችሁበትን ዋጋ ሙሉውን ክፍያ ለወደፊት በምናሳውቃችሁ በተቋማችን ሂሳብ ቁጥር ገቢ በማድረግ የሽያጭ ውል ስምምነት መፈጸም ግዴታ ይኖርባችኋል፤ ሆኖም ግዴታቸውን የማይወጡ ተጫራቾች ለወድድር ያስያዛችሁት የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ. ለተቋማችን ገቢ ይደረጋል፤ 10. ከላይ የተጠቀሰውን እና በጨረታ ሠነዱ ላይ የተቀመጡ መመሪያዎችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ/ሊሰረዝ ይችላል፤ 11. ተቋሙ ጨረታውን ለመቀበል ወይም ላለመቀበል የሚችል ሲሆን በማንኛውም ጊዜ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፤ 12. የኦክሽን ኢትዮጵያን መተግበሪያ በተመለከተ የጥሪ ማዕከሉን ለማግኘት በአጭር የስልክ መስመር 9164 ወይም 09-05-11-5511/ 011-666-8828 በመደወል ማግኘት ይችላሉ። 13. ንብረቶቹን በተመለከተ በስልክ ቁጥር 011-558-14-24 ወይም 011-558-06-49 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡ ለበለጠ መረጃ አርብ ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ።ም የወጣዉን አዲስ ዘመን ጋዜጣ መመልከት ይቻላል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ቡድኑ ወደ ድል ተመልሷል ........///....... በ7ኛ ሳምንት የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከአዳማ ከነማ ጋር ተጫውቶ ሁለት ለባዶ አሸንፏል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሙሉ የበላይነት በወሰ
+4
ቡድኑ ወደ ድል ተመልሷል ........///....... በ7ኛ ሳምንት የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከአዳማ ከነማ ጋር ተጫውቶ ሁለት ለባዶ አሸንፏል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሙሉ የበላይነት በወሰደበት በዚህ ጨዋታ ማህሌት ምትኩ እና ኢየሩስ ወንድሙ የማሸነፊያ ጎሎቹን ለክለባቸው አስቆጥረዋል። በጨዋታው አንድ ጎል ያስቆጠረችው እና ድንቅ እንቅስቃሴ ያሳየችው ማህሌት ምትኩ ኮከብ ተጫዋች በመሆን ሽልማት ተበርክቶላታል። በ8ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ታህሳስ 02 ቀን 2017 ዓ.ም ከመቻል ጋር የሚጫወት ይሆናል።    💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም

ተቋሙ ያገለገሉ ንብረቶችን በዲጂታል ሥርዓት ሊያጫርት ነው .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በዲጂታል ሥርዓት ለማጫረት የሚያስችል ስምምነት ከኦክሽን ኢትዮጵያ ጋር ተፈራረመ። ሥምምነቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል  በኩል የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እና በኦክሽን ኢትዮጵያ በኩል ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ዮሴፍ አንኩ ተፈራርመዋል፡፡ ሥራ አስፈፃሚዋ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እንደተናገሩት ስምምነቱ ተቋሙ ያገለገሉ ንብረቶቹን ለማስወገድ የሚያደርገውን የማኑዋል  የጨረታ ሂደት ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር የሚስችለው ነው፡፡ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን ለማስወገድ ተቋሙ የሚያደርገውን አድካሚ ሂደት፣ ጊዜን እና ወጪን ቆጣቢ በሆነ መልኩ በማዘመን  ለማቀላጠፍ  ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ ሀገር በቀል የዲጂታል አጫራች ድርጅቱ ጨረታዎችን በማውጣትና ተደራሽነቱን በማስፋት በአጭር ጊዜ  ተቋሙ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም እንደሚያስገኝ እምነታቸውን ገልፀዋል። የጨረታ ሂደቱ ከሰዎች ድርድር እና ንከኪ የጸዳ፣ ለብልሹ አሰራር የማያጋልጥ እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ ያሉ ተጫራቾች በእኩልነት ለማሳተፍ የሚያስችል እና አገልግሎቱን ለመጠቀም ምንም ዓይነት ወጪ የማያስወጣ በመሆኑ ተመራጭ እንደሆነ ወ/ሮ ስመኝ አስረድተዋል፡፡ የሀገር በቀሉ የዲጂታል አጫራች ድርጅት የኦክሽን ኢትዮጵያ  ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዮሴፍ አንኩ በበኩላቸው ድርጅታቸው  በጨረታ የሚሸጡ  ንብረቶች በዲጂታል ሥርዓት ተደራሽ በማድረግ ተገቢውን ዋጋ እንዲያገኙ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከ32 ሺህ በላይ ተጫራቾችን እና ከ500 በላይ አጫራቾች ድርጅቶችን ይዞ ከ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ባለይ ማገበያየቱን ገልፀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም