en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 680 subscribers, ranking 8 053 in the Technologies & Applications category and 2 173 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 680 subscribers.

According to the latest data from 05 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 112 over the last 30 days and by -12 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.83%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.95% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 050 views. Within the first day, a publication typically gains 2 501 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 680
Subscribers
-1224 hours
-127 days
+11230 days
Posts Archive
photo content
+7

በጣቢያው የፍተሻና የሙከራ ሥራ ለማከናወን የሚያስችል የዝግጅት ሥራ እየተሰራ ነው ……..///…….. የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ የባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የፍተሻና የሙከራ ሥራ ለማከናወን የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌቱ ያደታ እንደተናገሩት የተጠናቀቁ የንፋስ ማማዎችን ከቆቃ- መልካዋከና ከሚያልፈው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጋር በማገናኘት ኤሌክትሪክ ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት ለማስገባት ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ በተለያዩ ምክንያቶች በዕቅዱ ከተቀመጠው ጊዜ በላይ ቢወስድም በአሁኑ ወቅት በንዑስ ሥራ ተቋራጮቹ አማካኝነት የ20ዎቹ ተርባይኖች የቅድመ ፍተሻ ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ላይ የሙከራና የፍተሻ ሥራው ከተጠናቀቀ በኋላ የቅድመ ፍተሻ የተከናወነላቸውን ተርባይኖች በሂደት ወደ ግሪድ የማስገባት ሥራ ይሰራል። በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ በየሳምንቱ 10 ሜጋ ዋት በድምሩ 80 ሜጋ ዋት ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት ለማስገባት ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል። በፕሮጀክቱ የተቋሙ የራስ ኃይል መምሪያ ተወካይ አስተባባሪ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው በበኩላቸው የራስ ኃይል መምሪያ በፕሮጀክቱ የሁለት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችና የሽቦ ዝርጋታ ሥራን በ3 ክሬኖች እያከናወነ ነው ብለዋል። ሥራውን በሁለት ቀናት ውስጥ በማጠናቀቅ ከቆቃ-መልካዋከና ከተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ላይ በመቀጠል የማከፋፈያ ጣቢያውን ለሙከራና የፍተሻ ሥራ ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ነው። በተመሳሳይ የበቆጂ ባለ230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የፍተሻና የሙከራ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ እንደ አገር ከንፋስ የሚመነጨውን ኃይል ከ404 ሜጋ ዋት ወደ 504 ሜጋ ዋት ከፍ በማድረግ የኃይል ስብጥሩን ለማሳደግና አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ክልሉ በአዋሽ-ወልዲያ- ሃራ ገቢያ የባቡር የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ላይ የተፈፀመውን የስርቆት ወንጀል አወገዘ .......///........ የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በአዋሽ-ወልዲያ-ሃራ ገቢያ የባቡር የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ላይ የተፈፀመውን የስርቆት ወንጀል በፅኑ እንደሚያወግዝ አስታውቋል። በአስር ቀናት ውስጥ ብቻ ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦ.ፒ.ጂ ደብሊው ፋይበር መስመር ለስርቆት መዳረጉን ተከትሎ የክልሉ መንግሥት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ አልተወጡም ያላቸውን የወረዳ የሥራ ኃላፊዎች ከሥልጣን ማንሳቱንም ገልጿል። በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሃጂ አወል አርባ የተዋቀረ ኮማንድ ፖስት የስርቆት ወንጀሉ በተፈፀመባቸው የገቢረሱ ዞን ሁለት ወረዳዎች ላይ ትናንት የመስክ ምልከታ አድርጓል። የክልሉ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት፣ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የሰላምና ፀጥታ ዘርፍ፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ጠቅላይ አቃቤ ህግ ኃላፊዎችን ያካተተው ኮማንድ ፖስት ከሁሉም የዞንና ወረዳ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተወካዮች ጋር ውይይት አድርጓል። ውይይቱ በክልሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ የመጣውን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስርቆት በጋራ ለማውገዝና በወንጀሉ ዙሪያ አፋጣኝ እርምጃ ለመውሰድ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ያለመ ነው። በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዋሽ-ወልዲያ-ሃራ ገቢያ የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተክለወይን ብርሃነአሰፋ በ2016 እና 2017 በጀት ዓመት በገቢረሱ ዞን ስር በሚገኙ ወረዳዎች ስለተፈፀሙ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች፣ የኮንዳክተር ሽቦ እና የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ስርቆት መጠንና ስርቆቱ በተቋሙ ላይ ስላደረሰው ኪሳራ ለተወያዮቹ ገለፃ አድርገዋል። በክልሉ በሁለቱ በጀት ዓመት ብቻ በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ በተፈፀመ ስርቆት ሳቢያ ከ717 ሺህ ዶላር በላይ እና ከ25 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ መድረሱን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ ሁለት ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሀሰን መሐመድ እንደገለፁት ሪጅኑ ሦስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና ከ436 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍኑ የማስተላለፊያ መስመሮችን ያስተዳድራል። ተቋሙ ለህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ ለማዳረስ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችና የኮንዳክተር ሽቦ ላይ የሚፈፀመው የስርቆት ወንጀል ማነቆ እንደሆነ አስረድተዋል። በውይይቱ ላይ የዞንና የወረዳ እንዲሁም  የፀጥታ ዘርፍ አካላት በኃላፊነት ስሜት መንቀሳቀስ አለመቻላቸው በኃይል መሰረተ ልማቶቹ ላይ ከፍተኛ የዝርፊያ ወንጀል እንዲፈፀም በር ከፍቷል ተብሏል። የስርቆት ወንጀሉን ከምንጩ ለማድረቅ በየደረጃው ያሉ ሁሉም የክልሉ አመራሮች በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባም ነው ኮማንድ ፖስቱ አቅጣጫ ያስቀመጠው። ኮማንድ ፖስቱ በክልሉ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ደህንነት ለመጠበቅ ያስችላል ያለውን የመግባቢያ ሥምምነት ከሁሉም የዞንና የወረዳ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተፈራርሟል። ሥምምነቱ በኃይል መሰረተ ልማት ስርቆት ላይ የሚሳተፉ ወንጀለኞችን ተከታትሎ ለፍርድ ለማቅረብና በየደረጃው በሚገኙ አመራሮች ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን እንዲያስችል እንዲሁም ወንጀሉ ዳግም እንዳይከሰት ለማድረግ ያስችላል ተብሏል። ህብረተሰቡ መሰረተ ልማቶቹን በእኔነት ስሜት እንዲጠብቅ ለማድረግ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እስከታችኛው የክልሉ የአስተዳደር መዋቅር ድረስ በአስቸኳይ እንዲሰራም ውሳኔ ላይ ተደርሷል። በውይይቱ ላይ የአፋር ክልል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጎልቤ ሲሌን ጨምሮ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሙሳ አብዶ፣ የክልሉ የሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ሁሴን መሐመድ፣ የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢስማኤል መሐመድ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ቢልኤ አህመድ እንዲሁም የዞንና የወረዳ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለዘመናት በሴቶች ላይ ተንሰራፍቶ የቆየው ጭቆናና በደል ያንገሸገሻቸው ሴቶች ዝቅተኛ የሥራ ሰዓት፤ የተሻለ ክፍያ እና የመምረጥ መብታቸው እንዲከበርላቸው ባካሔዱት ትግል የሴቶች ቀን እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ1909 በአሜሪካ ሶሻሊስት ፓርቲ ውሳኔ መሰረት ለመጀመሪያ ጊዜ በብሔራዊ ደረጃ በአሜሪካ ተከበረ፡፡ በቀጣዩ ዓመትም በዴንማርክ ኮፐንሃገን በተካሄደው ሁለተኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ በዓለም ላይ የሚገኙ ሴቶች ፍላጎታቸውን በሚገባ ማንፀባረቅ እንዲችሉ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንዲከበር ሃሳብ ቀረበ፡፡ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በተሳታፊዎች ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት በማግኘቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦስትሪያ፤ ጀርመንና ሲውዘርላንድ እ.ኤ.አ በ1911 ማርች 19 ተብሎ ተከበረ፡፡ በዚህ ሥነ-ሥርዓት ላይም ሴቶች መብቶቻቸው እንዲከበሩ እና በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጭቆናዎች እንዲቆሙ የተለያዩ ንቅናቄዎች ተካሂደዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ1913 በተካሄዱ ውይይቶች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በየዓመቱ ማርች 8 እንዲከበር ውሳኔ ላይ የተደረሰ ሲሆን ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ቀኑ በተለያዩ ፕሮግራሞችና መሪ ቃሎች እየተከበረ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያም በዓሉ መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማትና ድርጅቶች በተለያዩ መርሃ ግብሮች የሚከበር ሲሆን የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንም /ማርች 8/ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ114ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ "ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል’’ በሚል መሪ ቃል መካሄድ ጀምሯል፡፡ ቀኑ የሴቶችን የልማት ህብረቶችን በማቋቋምና ማጠናከር፤ የቁጠባ ባህል እንዲዳብር በማድረግ፤ ምርትና አገልግሎታቸውን በኢግዚቢሽንና ባዛር እንዲያስተዋውቁና እንዲሸጡ ሁኔታዎችን በማመቻቸት የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ፤ የማህፀንና የጡት ጫፍ ካንሰር ምርመራ እንዲያደርጉ ንቅናቄ በመፍጠርና አገልግሎቱን በማመቻቸት እንዲመረመሩ ማድረግ እንዲሁም የህዳሴ ግድብ የቦንድ ንቅናቄ መፍጠርና ሽያጭ ማካሄድ ላይ ትኩረት ያደርጋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም በዓሉ በተቋሙ የተለያዩ የሥራ ቦታዎች ላይ የሴቶችን መብቶች ለማስከበር በሚያግዙ ጉዳዮች የግንዛቤ ማስጨበጫዎችን በመስጠት ያከበራል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ፋብሪካው ያቀረበውን ተጨማሪ የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል ዝግጅት ተጀምሯል ……..///……. የናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ለሚገነባው አዲስ የኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ያቀረበውን ተጨማሪ የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ለመመለስ ከፋብሪካው ጋር ውይይት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምሥራቅ አንድ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ እንደገለፁት  ፋብሪካው ለተቋሙ ላቀረበው የኃይል አቅርቦት ጥያቄ  ምላሽ ለመስጠት ከፋብሪካው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይቶች ተጀምረዋል። በናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የመልካ ጀብዱ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ መላኩ ገብሬ በበኩላቸው ፋብሪካው በድሬዳዋ መዳረሻ መልካ ጀብዱ ላይ ሊገነባ ላሰበው የኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ እስከ 600 ሜጋ ዋት ተጨማሪ ኃይል ይፈልጋል ብለዋል። የኢንዱስትሪ ኮምፕሌክሱ የሲሚንቶ ማቀነባበሪያና ማሸጊያ ከረጢቶችን ጨምሮ ለተገጣጣሚ ቤቶች፣ ለኮንክሪት እና ኖራ ማምረቻ እንዲሁም ለኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግንባታ እና ለተለያዩ ድርጅቶች በግብዓትነት የሚያገለግሉ ምርቶችን የሚያመርቱ ፋብሪካዎችን እንደሚያካትት ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ፕሮጀክቱን በቅርቡ ለመጀመር የሚያስችሉ የአዋጭነት፣የአካባቢ ደህንነት፣ የመልክዓ ምድር ጥናቶች እና ሌሎች ቅድመ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል። የኢንዱስትሪ ኮምፕሌክሱ ለሚፈልገው እስከ 600 ሜጋ ዋት ኃይል ሪጅኑ  የተለያዩ አማራጮችን እያየ መሆኑን  ዳይሬክተሩ አቶ ወርዲ መሀመድ ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

ፕሮጀክቱ በአማካይ ከ400 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል  ........///….… የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በአማካኝ ከ400 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ጊዜያዊና ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠሩን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ፈቃዱ አብርሃም እንደገለፁት ፕሮጀክቱ 29 የንፋስ ማማዎች ተከላን፣ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፍያ ጣቢያን እና 38 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የባለ 33 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራዎችን ያጠቃልላል። ከሥራ ተቋራጩ ጋር በተደረገው ስምምነት መሰረት ከፕሮጀክቱ እስከ 25 ኪሎ ሜትር ርቀት ያሉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ቅድሚያ በመስጠት የአካባቢውን ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡ እስካሁን ባለው የፕሮጀክቱ ሂደት በአማካይ ከ400 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ ዕድል መፍጠሩንና አብዛኛው ተጠቃሚ የአካባቢው ወጣቶች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል ወጣት ቶሎሳ ሮባ እንደገለፀው በፕሮጀክቱ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ቋሚ ሥራ ስላልነበረው በሚያገኘው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብን ለማስተዳደር ትልቅ ፈተና ሆኖበት ነበር። በፕሮጀክቱ በተፈጠረለት የሥራ ዕድል ላለፉት 2 ዓመታት መስራቱንና በዚህም እሱን ጨምሮ ሦስት ቤተሰቦቹን ለማስተዳደር የሚያስችል የተሻለ ገቢ ለማግኘት እንዳስቻለው ተናግሯል፡፡ ሌላኛዋ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ወጣት ሙሉ ተካ በበኩሏ በፕሮጀክቱ ሥራ ከመጀመሯ በፊት እሷንና ቤተሰቧን ለማስተዳደር አረብ ሀገር ሄዳ ለመስራት ተገዳ እንደነበረ አንስታለች፡፡ ፕሮጀክቱ በትውልድ ቀየዋ ሥራ ከጀመረ ካለፉት 3 ዓመታት ወዲህ ግን በፕሮጀክቱ ተቀጥራ ቤተሰቧን እያስተዳደረችና ልጆቿን እያስተማረች መሆኑን ገልጻለች፡፡ ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም ባለፈ ሲጠናቀቅ አስተማማኝ ኃይል እንዲኖር በማድረግ ኢኮኖሚያዊ እድገትን የሚያፋጥኑ ፕሮጀክቶች እንዲከፈቱ ያግዛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ተቋማቱ በጋራ ለመስራት በሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ .......///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት በጋራ መስራት በሚችሉባቸው የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ ምክክሩ ሁለቱ ተቋማት ከዚህ ቀደም በጋራ ያከናወኗቸውን ሥራዎች ለመገምገምና ቀጣይ የሥራ ግንኙነቶች በሚጠናከሩበት ሁኔታ ላይ ያለመ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት ተቋሙ የኃይል ልማት ዘርፉን ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ ይገኛል። ተቋሙ በሚያከናውናቸው የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታዎች ላይ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አሻራ የጎላ መሆኑንም አንስተዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ተቋማቱ የዘረጉትን የኢ.አር.ፒ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የመረጃ ልውውጥ ሥርዓታቸውን ማሳለጥ ይገባቸዋል። ከዚህ ቀደም ከአሰራር ሥርዓትና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዘው ይነሱ የነበሩ ችግሮች ዳግም እንዳይከሰቱ ለማድረግ ከሁለቱ ተቋማት የተውጣጣ ቡድን በማዋቀር መስራት እንደሚገባም አመልክተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን በበኩላቸው የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት አሁን ለደረሰበት የግንባታ ምዕራፍ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አስተዋፅዖ ከፍተኛ ነው ብለዋል። በኃይል ልማት ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ተቋሙ ቅድሚያ ሰጥቶ እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። ተቋማቱ በፋይናንስ የመረጃ ልውውጥ ላይ ያላቸውን የአሰራር ቅልጥፍና ማዘመን እንደሚጠበቅባቸው የጠቀሱት ደግሞ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ ናቸው። በኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የሺፒንግ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካፒቴን ወንድወሰን ካሳ የተቋማቸውን አሁናዊ ገፅታ አስመልክተው ገለፃ አድርገዋል። ተቋማቸው በሀገራዊ የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ በመሆኑ ኩራት እንደሚሰማቸውም ነው የተናገሩት። ከኮንቴነር ኪራይ፣ ከደረቅ ወደብ አጠቃቀም እና ከፋይናንስ እንዲሁም ከአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት ተቋማቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የጭነትና አስተላላፊነት ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሻረው ከበደ በበኩላቸው ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት የግንባታ ዕቃዎች በወቅቱ የሚቀርቡ ከሆነ የማጓጓዝ ሥራዎችን በፍጥነት ለማከናወን ተቋማቸው ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል። በውይይቱ ላይ የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ተቋማቱ በጋራ ለመስራት በሚያስችሏቸው የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ .......///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት በጋራ መስራት በሚችሉባቸው የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ ምክክሩ ሁለቱ ተቋማት ከዚህ ቀደም በጋራ ያከናወኗቸውን ሥራዎች ለመገምገምና ቀጣይ የሥራ ግንኙነቶች በሚጠናከሩበት ሁኔታ ላይ ያለመ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት ተቋሙ የኃይል ልማት ዘርፉን ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ ይገኛል። ተቋሙ በሚያከናውናቸው የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታዎች ላይ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አሻራ የጎላ መሆኑንም አንስተዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ተቋማቱ የዘረጉትን የኢ.አር.ፒ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የመረጃ ልውውጥ ሥርዓታቸውን ማሳለጥ ይገባቸዋል። ከዚህ ቀደም ከአሰራር ሥርዓትና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዘው ይነሱ የነበሩ ችግሮች ዳግም እንዳይከሰቱ ለማድረግ ከሁለቱ ተቋማት የተውጣጣ ቡድን በማዋቀር መስራት እንደሚገባም አመልክተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን በበኩላቸው የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት አሁን ለደረሰበት የግንባታ ምዕራፍ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አስተዋፅዖ ከፍተኛ ነው ብለዋል። በኃይል ልማት ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ተቋሙ ቅድሚያ ሰጥቶ እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። ተቋማቱ በፋይናንስ የመረጃ ልውውጥ ላይ ያላቸውን የአሰራር ቅልጥፍና ማዘመን እንደሚጠበቅባቸው የጠቀሱት ደግሞ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ ናቸው። በኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የሺፒንግ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ካፒቴን ወንድወሰን ካሳ የተቋማቸውን አሁናዊ ገፅታ አስመልክተው ገለፃ አድርገዋል። ተቋማቸው በሀገራዊ የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ በመሆኑ ኩራት እንደሚሰማቸውም ነው የተናገሩት። ከኮንቴነር ኪራይ፣ ከደረቅ ወደብ አጠቃቀም እና ከፋይናንስ እንዲሁም ከአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት ተቋማቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የጭነትና አስተላላፊነት ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሻረው ከበደ በበኩላቸው ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት የግንባታ ዕቃዎች በወቅቱ የሚቀርቡ ከሆነ የማጓጓዝ ሥራዎችን በፍጥነት ለማከናወን ተቋማቸው ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል። በውይይቱ ላይ የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

የማመንጫ ጣቢያውን ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ ውይይት እየተካሄደ ነው ……..///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና የውሃ የኃይል ማመንጫ ጣቢያን ደህንነት ማስጠበቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከኦሮሚያ ክልል እና ከምዕራብ አርሲ የዞን የመስተዳድር አካላት  ጋር በሻሸመኔ ከተማ ውይይት ማካሄድ ጀምሯል። በተቋሙ የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ኮምፒሊያንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደጉማ ነዳ  እንደገለጹት ውይይቱ በግድቡ ጥብቅ ወሰን ውስጥ በሚከናወን እርሻ  ምክንያት በግድቡ ላይ እየደረሰ ባለው ጉዳት፣ ከግድብ ውሃ አጠቃቀም፣ ከይዞታ ማረጋገጫ እና ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ ነው። የማመንጫ ጣቢያው የይዞታ ማረጋገጫ ባለማግኘቱ በበጋ ወራት የጣቢያውን ጥብቅ ወሰን በማለፍ እርሻዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም ጣቢያው በደለል እንዲሞላ ከማድረጉም በላይ የግብርና ተረፈ ምረቱ ወደ ጣቢያው በመግባት ውሃ ወደ ተርባይኖቹ እንዳያልፍ በማድረግ የጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራ እና ደህንነት ላይ ስጋት መደቀኑን ተናግረዋል። ተቋሙ በጣቢያው ላይ እያጋጠሙት ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ከአካባቢው የመስተዳድር አካላት እና ማህበረሰቡ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም አብራርተዋል። ከዚሁ በተጨማሪም ተቋሙ እያከናወናቸው ባሉ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች እና ለአካባቢው ማህበረሰብ  በሠራቸው የልማት ሥራዎች ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ነው። በውይይቱ ላይ የተቋሙና የጣቢያው ኃላፊዎችን ጨምሮ የኦሮሚያ የገጠር ልማት ክላስተር፣ የዞንና ወረዳ መስተዳድር አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ባለፉት ስድስት ወራት በሰባት ማከፋፈያ ጣቢያዎች የመቆጣጠሪያ ቅየራ ተከናወኗል …....///….…. በ2017 የመጀመሪያ ግማሽ በጀት ዓመት በሰባት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ዘመናዊ ስዊች ጊር ወይም መቆጣጠሪያ የመቀየር ሥራ መከናወኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ገለጸ፡፡ በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለፁት በ2017 በጀት ዓመት የ37 ማከፋፈያ ጣቢያዎች የመቆጣጠሪያ ሥርዓት በዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ለመቀየር ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት የሰባት ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የባለ 15 እና 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች በዘመናዊ መቆጣጠሪያዎች የመቀየር ሥራ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን በ21 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ደግሞ የሲቪል ሥራና የዕቃ ማጓጓዝ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በአሸጎዳ፣ በድሬድዋ ሦስት፣ በጅጅጋ፣ በባህርዳር ሁለት፣ በዲላ እና በጋሸና ማከፋፈያ ጣቢያዎች በግማሽ በጀት ዓመቱ የቅየራ ሥራው መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ የሚቀየረው ስዊች ጊር በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ያጋጥም የነበረውን የጥገና ስራ በማስቀረት እና የኃይል መቆራረጥን በመቀነስ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት እንደሚያሳድግ ገልጸዋል፡፡ የመቆጣጠሪያ ብሬከሩ ሙሉ በሙሉ ዝግ ሆኖ የሚሰራ በመሆኑ ከአቧራ፣ ከእርጥበት ብሎም ከውጫዊ አየር ተጠብቆ ረጅም ጊዜ እንደሚያገለግል ገልጸው ከአሁን ቀደም ኋላ ቀር በሆነ ቴክኖሎጂ ሲሰራበት የነበረውን አሰራር በማስወገድ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የሚያሳድግ እና አሰራሩን የሚያዘምን ነው ብለዋል፡፡ በተቋሙ የማከፋፈያ ጣቢያዎች የጥገና ባለሙያና የማዘመን ሥራው አስተባባሪ አቶ ሚሊዮን በለጠ በበኩላቸው የስዊች ጊር ቅየራው በጊዜያዊ ሌሎች የመቆጣጠሪያ ሥርዓት በመዘርጋት ኃይል ሳይቋረጥ እየተከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ የቅየራ ስራው በተቋሙ ባለሙያዎች መከናወኑን የገለጹት አቶ ሚሊዮን ይህም የባለሙያዎችን አቅም ከማሳደግ በተጨማሪ ለውጭ ኩባንያ ይከፈል የነበረውን ወጭ ከ50 በመቶ በላይ ያስቀረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አስተባባሪው እንዳሉት የዘመናዊ መቆጣጠሪ ብሬከሩን ከሚያቀርበው ኩባንያ ጋር በመተባበር የባለሙያዎች አቅም ግንባታ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ብሬከሮች በሚቀየሩባቸው ማከፋፈያ ጣቢዎች አካባቢ የክሬን አገልግሎት የሚሰጡ ድጅቶች አለመኖር፣ ለሲቪል ግንባታ የሚያገለግሉ ግብዓቶች እጥረት እና ዕቃዎችን ወደ ጣቢያ ለማድረስ የመንገድ ችግር በሥራው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደራቸውን ገልጸዋል፡፡ ተቋሙ በሦስት ምዕራፎች በ75 ማከፋፈያ ጣቢዎች ላይ የማዘመን ሥራ ለማከናወን አቅዶ እየሰራ ሲሆን እስከ አሁን የ25 ማከፋፈያ ጣቢዎች ሥራ ተጠናቋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9