ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 537 подписчиков, занимая 8 368 место в категории Технологии и приложения и 2 174 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 537 подписчиков.

Согласно последним данным от 30 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 10, а за последние 24 часа — -6, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 24.86%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.87% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 862 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 620 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 9.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 01 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 537
Подписчики
-624 часа
-207 дней
+1030 день
Архив постов
አስተዳደሩ የተቋሙን የሦስት ወራት አፈፃፀም ገመገመ ………///……… የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሦስት ወራት አፈፃፀም በፈተና ውስጥ ውጤት የተመዘገበበት ነው ሲል ገለፀ፡፡ ለአስተዳደሩ በቀረበው የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርት እንደተገለፀው በሩብ ዓመቱ 5 ሺህ 526 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማምረት ታቅዶ 4 ሺህ 760 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የዕቅዱን 86 ነጥብ 1 በመቶ ኃይል ማምረት ተችሏል፡፡ ከተመረተው ኃይል ውስጥ ከውሃ የመነጨው 4 ሺህ 639 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 97 ነጥብ 5 በመቶ፣ ከንፋስ 106 ነጥብ 3 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 2 ነጥብ 2 በመቶ እና ከተርማል 14 ነጥብ 3 ወይም 0 ነጥብ 3 በመቶ ድርሻ እንደነበራቸው ተነስቷል፡፡ የኃይል ሽያጭ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ጭማሪ ቢታይበትም ከዕቅድ አንፃር ግን መጠነኛ ልዩነት መታየቱን ሪፖርቱ አመልክቶ ለጎረቤት ሀገራት 21 ነጥብ 4 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ሽያጭ መከናወኑ ተገልጿል። በራስ አቅም የሚሰሩ ፕሮጀክቶች በመልካም አፈፃፀም ላይ ስለመሆናቸው የተነሳ ሲሆን 7 ፕሮጀክቶች በአማካይ 83 በመቶ አፈፃፀም እንዳላቸው በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡ ለመሠረተ ልማት ግንባታ የሚወጣውን ወጪ ለመመለስ የሚያስችል ታሪፍ እንደሌለ፣ እያደገ የሄደው የውጭ ምንዛሬ ለውጥ በተቋሙ የፋይናንስ አቋም ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑ፣ የመሰረተ ልማት ስርቆት፣ የካሳ ክፍያና የጸጥታ ችግር የተቋሙ ዋንኛ የስጋት ምንጮች መሆናቸውና ስጋቱን ለመቀነስ የሚያስችል ሥራ እየተሰራ መሆኑም በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡ ተቋሙ የቀጣዮቹን ሶስት ዓመታት ስትራቴጂክ ዕቅድ ማዘጋጀቱ፣ ከቢሮ ኪራይ ወጥቶ በራሱ ህንፃ ውስጥ መግባቱ፣ ዕዳና ወጪን ተመጣጣኝ ለማድረግ እየሰራ መሆኑ፣ የብሔራዊ የኃይል ቋት ማዕከል ግንባታ መጀመሩ፣ የተተኪ አመራሮች ዕቅድ መኖሩ፣ የግብ ቋት ለመፍጠር ከተቋም እስከ ግለሰብ ፈፃሚ ድረስ እየተሰራ መሆኑ በሪፖርቱ ተነስቷል፡፡ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር በበኩሉ በዋና ዋና መመዘኛዎች ተቋሙ ያለበትን ደረጃ የተመለከተ ዝርዝር ሪፖርት አቅርቧል፡፡ የአስተዳደሩ የግምገማ ሪፖርት የኢነርጂ ምርት በ11 በመቶ ማደጉንና የሩብ ዓመቱ አፈፃፀም 86 በመቶ መሆኑ፤ የኃይል ሽያጩ የዕቅዱን 81 በመቶ ቢከናወንም የውጭ ኃይል ሽያጭ ማነሱን፣ ተቋማዊ ስጋቶች ተለይተው የድርጊት መርሃግብር መዘጋጀቱን በዝርዝር ተመልክቷል፡፡ የተጠቃሚን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ኃይል ማምረት መቻሉ፣ ለአሰላ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የተገዛው ዕቃ ወደሀገር ውስጥ እየገባ መሆኑ፤ አሰራርን ለማዘመን የተዘረጋው ሳፕ የተባለው መተግበሪያ በመርሀ ግብሩ መሰረት መከናወኑ፣ በራስ አቅም ፕሮጀክቶች መገንባታቸው፣ የሶስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ መዘጋጀቱ በጥንካሬ ተነስቷል፡፡ የውጭ ሀገር ሽያጭ መቀነሱ፣ የገቢ አሰባሰብ ከዕቅዱ አንፃር ሲታይ ማነሱ፣ ፕሮጀክቶች በጊዜና በወጪ ልዩነት የታየባቸው መሆኑ፣ የሩብ ዓመቱ ፋይናንስ መግለጫ አለመዘጋጀቱ፣ በተያዘው ዕቅድ መሰረት የብድር ክፍያ አለመፈፀሙ በክፍተትነት ተነስቷል፡፡ በሪፖርቱ ላይ ጥያቄዎች ቀርበው በሚመለከታቸው ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በግምገማው ማጠቃለያ ላይ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃ/ሚካኤል እንደተናገሩት ተቋሙ ስጋቶቹን በመለየት መፍትሔ ለመስጠት የጀመረው ሥራ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል፡፡ ገቢውን እና የውስጥ አቅሙን ለማጠናከር ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ ያሳሰቡት ዋና ዳይሬክተሩ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡ እንደ አቶ ሀብታሙ አስተያየት ተቋሙ በፈተና ውስጥም ሆኖ ውጤት ማስመዝገብ ችሏል፤ ለዚህም የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

በአፍሪካ ቀንድ የተከሰተው ድርቅ ለኬንያ በሚቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል  መጠን ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል በሚል የተሰራጨው መረጃ የተሳሳተ ነው .........////........ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የተከሰተው ድርቅ ለኬንያ በሚቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል  መጠን ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል በሚል የተሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ኢትዮጵያ ካላት የኃይል ምርት ለጎረቤቶቿ በፍላጎታቸው መጠን እያቀረበች ትገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ የተሻለ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል ከፍተኛ የውሃ ሀብት ባለቤት የሆነችና ከውሃ ኤሌክትሪክ ኃይልን ለማመንጨት ተስማሚ መልክዐ ምድር ያላት አገር መሆኗን ሚኒስትሩ በመግለጫቸው አንስተዋል፡፡   በሀገሪቱ ያለውን ከፍተኛ የውሃ ሀብት በመጠቀም የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻሉ ለኢትዮጵያና ለጎረቤት ሀገሮች ትልቅ በረከት ነው ያሉት ሚኒስትሩ ይህም በቀጠናው ያለውን አንድነትና ትብብር ለማጠናከር እንደሚያግዝ  ገልፀዋል፡፡ እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ ኬንያ፣ ጅቡቲና ሱዳን የኃይል ፍላጎት መጠናቸው እያደገ በመምጣቱ በኢትዮጵያ በኩል ፍላጎታቸውን ማሟላት የሚያስችል ሰፊ የኤሌክትሪክ ምርት አቅም አለ፡፡ ኢትዮጵያ ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች በአብዛኛው በቂ ውሃ እንዲይዙ በመደረጉ ምንም ዓይነት የኃይል እጥረት አለመኖሩን ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል፡፡ ሚኒስትሩ እንደገለፁት ባለፉት ሁለት ዓመታት በዝናብ መዛባት የተነሳ ግድቦች በሚፈለገው መጠን ባይሞሉም በኃይል አቅርቦትና የሽያጭ ገቢ ላይ ግን ምንም ዓይነት ተፅዕኖ አላሳደረም፡፡ ስለሆነም በአፍሪካ ቀንድ ያለው የአየር መዛባት ኢትዮጵያ ለኬንያ በምታቀርበው ኃይል ላይ ተፅዕኖ እንዳሳደረ ተደርጎ እየተሰራጨ ያለው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ሚኒስትሩ በመግለጫቸው አብራርተዋል፡፡ ሰሞኑን ኬንያ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት የኃይል ማመንጫ ግድቦች የውሃ መጠን ክፉኛ በመቀነሱ ከኢትዮጵያ ማግኘት ከሚገባኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ ግማሹ ብቻ እያገኘሁ ነው ስትል በሀገሪቱ የኃይል እና የነዳጅ ሚኒስትር ዴቪስ ቺርቺር በኩል መግለጫ መስጠቷን ቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ የተሰኘው ድረ-ገፅ ማስነበቡ ይታወሳል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በማሰራጫ መስመር ላይ በተፈጠረ ችግር ምክንያት በአዲስ ሰፈር እና በወረገኑ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተቋርጦ የነበረው ኃይል ተመልሷል .........////......... ከቃሊቲ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል በሚቀበሉት የወረገኑ እና የአዲስ ሰፈር ማከፋፈያ ጣቢያዎች ተቋርጦ የነበረውን ኃይል ማገናኘት መቻሉን የቃሊቲ አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ ገለጹ፡፡ የጣቢያው ኃላፊ አቶ እጅጉ ማሬ እንደገለጹት በጣቢያዎቹ ላይ የተቋረጠው ኃይል በዝቅተኛ የማሰራጫ መስመር ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት ነው፡፡ የኃይል መቋረጥ ችግሩ የተፈጠረው የኃይል ማሰራጫ መስመሩ ተበጥሶ ከቃሊቲ አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ አዲስ ሰፈር እና ሜክሲኮ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ከተዘረጋው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጋር በመገናኘቱ ነው፡፡ ለንክኪው ምክንያት የነበረው የስርጭት መስመር ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ በተዘረጋበት መስመር አቅራቢያ የተዘረጋ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡ በቃሊቲ አንድ- አዲስ ሰፈር ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር ላይ የተፈጠረው ችግር ከቃሊቲ አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል የሚያገኘውን የወረገኑ ማከፋፈያ ጣቢያን ኃይል አቋርጦ እንደነበርም አቶ እጅጉ ተናግረዋል፡፡ ችግሩ በዛሬው ዕለት ከቀኑ 5:57 ደቂቃ ላይ እንደተከሰተ ያነሱት የጣቢያው ኃላፊ በዚህም የአዲስ ሰፈር ማከፋፈያ ጣቢያ ለ17 ደቂቃ እንዲሁም ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያቀርበው የወረገኑ ማከፋፈያ ጣቢያ ደግሞ ለ23 ደቂዎች ያህል ኃይል ተቋርጦባቸው መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመቀናጀት የተቋረጠውን ኃይል በአጭር ጊዜ ውስጥ ማገናኘት መቻሉንም አቶ እጅጉ ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ተቋሙ ባከናወነው የኮንትራት አስተዳደርና የቁጥጥር ሥራ የተገነባው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ………...///……... ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ኃይል ማቅረብ የሚችል ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የሱፐርቪዥን እና ኮንትራት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ግርማ ዘለቀ እንደገለፁት የተቋሙ የማማከር ሥራዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደጉ መጥተዋል። ተቋሙ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ በተጨማሪ ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን፣ ለደርባ ሲሚንቶ፣ ለለሚ ሲሚንቶ፣ ለሲ ኤንድ ኢ የብረት ማቅለጫ እና ለአባይ ሲሚንቶ የማማከር ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ገልፀዋል። ለአየር መንገዱ ለተገነባው የማከፋፈያ ጣቢያ የአዋጭነት ጥናት፣ ዲዛይን የማፅደቅ፣ የጨረታ ዝግጅት፣ የሳይት ቁጥጥር እና የኮንትራት አስተዳደር ሥራዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማከናወኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ አየር መንገዱ የራሱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲኖረው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቀረበ ምክረ ሃሳብን ተከትሎ ነው ፕሮጀክቱ የተገነባው። አዲሱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከቃሊቲ አንድ ወደ ኮተቤ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በሁለት በኩል ኤሌክትሪክ እንዲያገኝ ታስቦ የ7 ኪሎ ሜትር ግንባታ እንደተከናወነለት ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተደጋጋሚ ያጋጥሙት የነበሩትን የኃይል ማነስ እና የመቆራረጥ ችግሮች በዘላቂነት መፍታት እንደሚያስችለው ገልፀዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር የኃይል ተጠቃሚ በመሆኑ ምክንያት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ደንበኛ ሆኗልም ብለዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን የኦፕሬሽን እና የጥገና ሥራዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንደሚያከናውን የገለፁት ዳይሬክተሩ ለዚህም የአገልግሎት አሰጣጥ ስምምነት ( Service Level Agreement) ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር መፈራሩሙን ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ በ18 ወራት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉን፣ ለግንባታው 7 ነጥብ 9 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በጀት ተይዞለት መከናወኑን ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ የፋይናንስ ወጪ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተሸፈነ ሲሆን ጀኔራል ኤሌክትሪክ እና ሲ.ሲ.ሲ.ኤስ የተባሉ ሥራ ተቋራጮች ግንባታውን በጋራ አከናውነዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ፕሮጀክት ግንባታ 35 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል ………..///…….... የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ፕሮጀክት ግንባታ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሠረት እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የዲጂታላይዜሽን እና አቅም ማሻሻል ፕሮጀክት አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ በኃይሉ ወ/ ጊዮርጊስ እንደተናገሩት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ ሥራ 35 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል። በአሁኑ ወቅት በፕሮጀክቱ የሁለት የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከላት እና አንድ የመኖሪያ ቤት ህንፃ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የጠቀሱት አቶ በኃይሉ በ2016 በጀት ዓመት መጨረሻ የፕሮጀክቱን ግንባታ 70 በመቶ ለማድረስ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ከሁሉም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለኦፕሬሽን ሥራዎች የሚያስፈልጉ መረጃዎችን ወደ አንድ ማዕከል መሰብሰብ የሚያስችሉ የኮሙዩኒኬሽን እና የኔትወርክ መሳሪያዎች ፍብረካ መጀመሩንም ነው ሥራ አስኪያጁ የገለፁት። በመቆጣጠሪያ ማዕከላቱ ውስጥ የሚተከሉ ሰርቨሮች ፍብረካ መጠናቀቁን የጠቆሙት አቶ በኃይሉ የፍተሻና ሙከራ ሥራዎች ከተከናወኑ በኃላ ማጓጓዝ እንደሚጀመር ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የመረጃ ልውውጥና የግሪድ ክትትል ሥርዓቱን የሚያጠናክሩ የተለያዩ ሶፍትዌሮች እየበለፀጉ ይገኛሉ። ከሁሉም የኃይል ማመንጫዎች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት የሚላኩ መረጃዎችን ከሳይበር ጥቃት ለመከላከል የሚረዱ የደህንነት መሳሪያዎች እንደሚኖራቸውም ነው አቶ በኃይሉ ያስታወቁት። የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ፕሮጀክቱ በአሁኑ ሰዓት አገልግሎት እየሰጠ ከሚገኘው የመቆጣጠሪያ ማዕከል በተሻለ የኦፕሬሽን ሥራዎችን የሚያቀላጥፉ ዘመናዊ ሶፍትዌሮችና የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች ይኖራቸዋል ብለዋል። ፕሮጀክቱ በሥራ ላይ ካሉት የኃይል ማመንጫዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች በተጨማሪ ወደፊት የሚገነቡትን የኃይል መሰረተልማቶች ታሳቢ በማድረግ እየተገነባ እንደሚገኝ ገልፀዋል። የፕሮጀክቱን ግንባታ የፈረንሳዩ ጀኔራል ኤሌክትሪክ እና የቻይናው ሲኖ ሃይድሮ ኩባንያ በጋራ እያከናወኑ ሲሆን የማማከር ሥራውን ደግሞ ሒፋብ የተባለ የፊንላንድ ኩባንያ እያከናወነ ይገኛል። ፕሮጀክቱ 57 ነጥብ 67 ሚሊዮን ዩሮ እና ከ102 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለታል፡፡ የፕሮጀክቱ የፋይናንስ ወጪ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ የሚሸፈን ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ ያለአግባብ ሲከፈል የነበረ የኢንሹራንስ ክፍያ ማስቀረት ችሏል ---///--- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2015 በጀት ዓመት የመድን ዋስትና የማያስፈልጋቸውን ንብረቶች በመለየት ያለአግባብ ሲከፈል የነበረ የኢንሹራንስ ክፍያ ማስቀረቱን በተቋሙ የንብረት አስተዳደርና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የንብረት፣ ሪስክ እና ኢንሹራንስ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሣህሌ ደግፍ እንዳስታወቁት በበጀት ዓመቱ ለኢንሹራንስ ሽፋን ሊከፈል የነበረ ንብረትን የሥጋት ደረጃ በመለየት ከ 59 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል፡፡ ተቋሙ ወጪውን ማዳን የቻለው በኮንትራክተሮችና አማካሪ ድርጅቶች ስም ለሚገኙ እንዲሁም በሰነድ አለመሟላት የተነሳ ጉዳት ቢደርስባቸው የካሳ ክፍያ ለመጠየቅ አስቸጋሪ ለሆኑ ተሸከርካሪዎችና የግንባታ ማሽነሪዎች የሚከፈለውን የኢንሹራንስ ክፍያ በማስቀረት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ለንብረት ኢንሹራንስ ሽፋን የሚከፈለውን ክፍያ ለመቀነስ በተከናወነው ሥራ በ2014 በጀት ዓመት ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን መቻሉን አስታውሰዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በኢትዮጵያ መድን ድርጅት ጠቅላላ ውድመት ደርሶባቸዋል ተብለው የተለዩ ተሽከርካሪዎች አዋጭነታቸው ታይቶ በተቋሙ ጋራዥና በራሱ በመድን ድርጅት በኩል እንዲጠገኑ ተደርገዋል፡፡ በተያያዘ ዜና ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ ከተሸከርካሪዎች የጉዳት ኢንሹራንስ ሽፋንና ከኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ንብረቶች ጉዳት ተቋሙ ከ79 ሚሊዮን ብር በላይ የካሳ ክፍያ ማግኘቱን ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል፡፡ በኢንሹራንስ አሰራርና አፈፃፀም ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዲኖር ለማድረግ በኢትዮጵያ መድን ድርጅት በኩል ሥልጠና መሰጠቱንና ለተቋሙ ንብረቶች የስጋት ጥናት ለማከናወን የአማካሪ ቅጥር ለማከናወን እየተሰራ መሆኑንም ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት (Child Caregivers) የሥራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 22 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ አውጥቶ የጽሁፍ ፈተና ጥቅምት 21 ቀን 2016 ዓ.ም መስጠቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ከህዳር 03 ቀን 2016 ዓ.ም እሰከ ህዳር 05 ቀን 2016 ዓ.ም በወጣላችሁ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በተቋሙ ዋና መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ የቃል ፈተና የሚሰጥ መሆኑን አውቃችሁ ለቃል ፈተና ተዘጋጅታችሁ እንድትቀርቡ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1