ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 533 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 338,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 162

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 533 名订阅者。

根据 29 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 6,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.10%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.85% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 901 次浏览,首日通常累积 2 619 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 30 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 533
订阅者
-124 小时
-167
+630
帖子存档
photo content
+6

ባለፉት 21 ቀናት ብቻ በሦስት የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ስርቆት ተፈጽሟል ........///........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን አንድ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ በሚያስተዳድራቸው የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ላይ በተፈጸመ ስርቆት አራት ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ኪሳራ መድረሱን መምሪያው አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመርና ኦፕቲካል ፋይበር ኦፕሬሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ በፍቃዱ በቀለ እንደተናገሩት ባለፉት ሦስት ሳምንታት በሱሉልታ-ገርበጉራቻ- ደብረ ማርቆስ ባለ 400 ኪሎ ቮልት፣ በጌዶ-ገፈርሳ ባለ 230 ኪሎ ቮልት እና በቃሊቲ-ኮተቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ስርቆት ተፈጽሟል፡፡ በሱሉልታ-ገርበጉራቻ- ደብረ ማርቆስ ባለ 400 ኪ.ቮ እና በጊዶ-ገፈርሳ ባለ 230 ኪ.ቮ መስመሮች ላይ በተፈጸመው ስርቆት 338 የታወር ብረቶች፣ 678 ብሎኖች እና 1 ሺህ 290 የብሎን ማሰሪያዎች በዘራፊዎች መወሰዱን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ከቃሊቲ - ኮተቤ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የማስተላለፊያ መስመር ላይ አንድ የመስመሩ ተሸካሚ ምሶሶ መውደቁንም አመልክተዋል፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በተፈጸሙ ስርቆቶች በአስር የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶችች ላይ ጉዳት እንደደረሰ ያነሱት ሥራ አስኪያጁ ጉዳት የደረሰባቸውን የምሰሶ አካላት መልሶ ለመተካት ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የምሶሶዎችን የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚያፈልጉ የኤሌክትሮድ፣ የጉልበት ሠራተኛ፣ የነዳጅ እና ሌሎች ግብዓቶችን ለማሟላት የሚወጣውን ወጪ ጨምሮ በአጠቃላይ ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚያፈልግ አቶ በፍቃዱ ተናግረዋል። በመስመሮቹ ላይ በተፈጸመው ስርቆት ምክንያት ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ባይኖሩም ችግሩ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በሚሰራው ሥራ ላይ እንቅፋት እየሆነ ይገኛል ብለዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ለችግሩ አፋጣኝ መፍትሔ ካልተሰጠው በቀጣይ ጊዜያት ስርቆት በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የኃይል መቋረጥ ሊያጋጥም ይችላል፡፡ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የብረት ማቅለጫ ፋብሪካዎች የተሰረቁ እና ቁርጥራጭ ብረታብረቶችን በግብዓትነት መጠቀማቸው በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ በተደጋጋሚ ለሚፈጸመው ስርቆት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡ በስርቆቱ ላይ የተሳተፉ አምስት ተጠርጣሪዎች በህብረተሰቡ ጥቆማና ትብብር በጸጥታ አካላት በቁጥጥር ስር እንደዋሉና እና ቀሪ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል በአካባቢው የሚገኙ የጸጥታ አካላት ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ የጸጥታ አካላት ያደረጉትን ጥረት አመስግነው በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ስርቆቶችን ለመከላከል ሁሉም የመስተዳድርና የፀጥታ አካላት ንብረቶችን በኃላፊነት መጠበቅ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ የማዕከላዊ ሪጅን አንድ የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው 1 ሺህ 404 ነጥብ 39 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር እና 22 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እያስተዳደረ ይገኛል፡፡ ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ላይ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በተፈጸመ ስርቆት በተቋሙ ላይ ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ኪሳራ መድረሱን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ የሥራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጳጉሜ 01 ቀን 2015 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ እና የተግባር ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከጥቅምት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት በሚገኘው የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡

photo content
+4

የሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ ግሪዱን በማረጋጋት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው .........///.......... የሆለታ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ የሀገሪቱ የኃይል ቋት እንዲረጋጋ በማድረግ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጥላሁን አዘዘው እንደገለፁት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ከተገነቡት ጣቢያዎች መካከል ትልቁና የኤሌክትሪክ መዋዠቅ እንዳይከሰት የሚደርግ ስታቲክ ቫር ኮምፐንሴተር የተባለ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት የማከፋፈያ ጣቢያ ነው። የተገጠመለት ቴክኖሎጂ ኃይል በሚዋዥቅበት ጊዜ ቮልቴጁን በማረጋጋት የጣቢያውን ደህንነት ከማስጠበቁ በተጨማሪ ብሔራዊ የኃይል ቋት ወይም ግሪዱ እንዳይረበሽ በማድረግ በሀገሪቱ ጤናማ የኤሌክትሪክ ፍሰት እንዲኖር እንደሚያግዝ ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ማከፋፈያ ጣቢያው ከህዳሴ ግድብ በደዴሳ አድርጎ የሚመጣውን 500 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ ወደ 400 ኪሎ ቮልት በመቀየር ለሱልልታ፣ ሰበታ እና ገላን ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚልክ ነው። ማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢው መገንባቱ ከግሪዱ ኃይል ለመስጠትና ለመቀበል አማራጮችን እንደሚያሰፋ ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። ጣቢያው ለሆለታ ከተማና አካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም በዙሪያው እየተገነቡ ላሉት ኢንዱስትሪዎች ያልቆራረጠ ኃይል የሚያቀርቡ ከ6 በላይ ወጪ መስመሮች እንዲኖሩት የማስፋፊያ ሥራዎች መከናወናቸውን ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የመቱ - ማሻ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታ በቅርቡ ዳግም ይጀመራል ...///… በተለያዩ ምክንያቶች ግንባታው ተቋርጦ የቆየው የሙቱ - ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት በቅርቡ እንደሚጀመር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የፕሮግራም 1 ፕሮጀክት አስተዳደር 1 ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ሙሉብርሃን እንዳስታወቁት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቱ በሚያልፍባቸው ቦታዎች ላይ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ጥናት ተካሂዶ ሥራው ሲሰራ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ በአካባቢው በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የተመዘገበ ደን በመኖሩ ምክንያት ፕሮጀክቱን ፋይናንስ የሚያደርገው የዓለም ባንክ ተጨማሪ ጥናት መደረግ አለበት የሚል ምክረ ሀሳብ በማቅረቡ የግንባታ ሥራው መቋረጡን ተናግረዋል፡፡ ይኼን ተከትሎ በውጭ አማካሪ ድርጅት ተጨማሪ የአካባቢያዊ ተጽዕኖ ጥናት ተካሂዶ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ የሚዘረጋበትን አቅጣጫ በመቀየር ለችግሩ መፍትሔ መስጠቱን ገልፀዋል፡፡ ከአካባቢያዊ ተፅዕኖ ጥናት ጋር በተያያዘ ባንኩ ያነሳው ጥያቄ መፍትሄ እስኪያገኝ ድረስ ፕሮጀክቱ ከሁለት ዓመት በላይ ተቋርጦ መቆየቱንም ነው ሥራ አስኪያጁ የጠቆሙት፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የመስመር ዝርጋታው 68 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት የነበረው ቢሆንም የዲዛይን ለውጥ በመደረጉ ምክንያት 3 ኪሎ ሜትር ጨምሯል፡፡ የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ተቋርጦ እንዲቆይ በመደረጉ ምክንያት ሥራ ተቋራጩ የተጨማሪ በጀት ጥያቄ አቅርቦ እንደነበር የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ችግሩ መፍትሔ እስኪያገኝ ድረስ ወደ ግንባታ ቦታው ለመግባት ፈቃደኛ ሳይሆን መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ በዋጋ ጭማሪው ዙሪያ ከግንባታ ተቋራጩ ጋር መግባባት ላይ በመደረሱ ግንባታው በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ እንደሚጀምር ሥራ አስኪያጁ አረጋግጠዋል፡፡ የማስተላለፊያ መስመሩ ከሚኖሩት 174 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች መካከል የ50 ምሶሶዎች መትከያ የመሰረት ሥራ መከናወኑንና የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ 75 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ሲኖ ሀይድሮ በተባለ የቻይና ኩባንያ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በማማከር ሥራው ላይ ደግሞ ኢ ኤል ሲ የተሰኘ የጣሊያን ኩባንያ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 20 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1