ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 572 подписчиков, занимая 8 384 место в категории Технологии и приложения и 2 165 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 572 подписчиков.

Согласно последним данным от 23 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 0, а за последние 24 часа — -2, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.89%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.48% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 026 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 408 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 9.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 24 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 572
Подписчики
-224 часа
-37 дней
Нет данных30 день
Архив постов
photo content
+8

በብልሽት ምክንያት የተቋረጠውን ኃይል መልሶ የማገናኘት ሥራ እየተሰራ ነው   ………..///……… አዲስ ዌስት ተብሎ በሚጠራው የኮልፌ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ትናንት ምሽት ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር የተነሳ ኃይል የተቋረጠባቸውን መስመሮች ለማናኘት ርብርብ እተካሄደ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ዘላለም ጌታነህ እንደገለፁት በጣቢያው አንድ ወጪ መስመር ላይ ባጋጠመ ችግር ከጣቢያው ኃይል ሲያገኙ የነበሩት ዘጠኝ መስመሮች በሙሉ ትናንት ለሊቱን አገልግሎት መስጠት አቋርጠው ነበር፡፡ ይሁንና ኃይል ከተቋረጠ ጊዜ ጀምሮ በተሰራው ሥራ ሰባቱ መስመሮች መልሰው ኃይል እንዲያገኙ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ቀሪዎቹን ሁለት መስመሮች ለማገናኘት ርብርቡ መቀጠሉን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ወደ ወይራ፣ ጦር ኃይሎችና ኮካ እንዲሁም ወደ አማኑኤል መሳለሚያ እህል በረንዳ እና መርካቶ የሚሄዱት መስመሮች የሚኖራቸውን ጭነት በማየት ለማገናኘት አልያም በአቅራቢያ ወደሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች መስመሮቹን በጊዜያዊነት የማዛወር ቴክኒካዊ መፍትሔዎች ጎን ለጎን እየታዩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ የኢፍጣር መርሃ ግብር አካሄደ .......////.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል 1446ኛውን የረመዳን ፆምን ምክንያት በማድረግ የእስልምና እምነት ተከታይ ለሆኑ የተቋሙ ሠራተኞች፣ ደንበኞች እና ባለድርሻ አካላት  በራማዳ ሆቴል የኢፍጣር ወይም  የእራት ግብዣ መርሃ ግብር አካሄደ። በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትላቅ ትርጉም ከሚሠጣቸው ሃይማኖታዊ ትዕዛዛት መካከል ታላቁ የረመዳን ፆም አንዱ መሆኑን አንስተዋል። በዚህ የጾም ወር የኢፍጣር መርሃ ግብር ለሙስሊም ሠራተኞች እና ባለድርሻ አካላት መደረጉ በተቋሙ መተሳሰብን እና መተዛዘንን በማዳበር የጋራ ተቋማዊ እሴትን ለመገንባት ያግዛል ብለዋል። የፕሮግራሙ አስተባባሪ አቶ መሐመድ አለው በበኩላቸው የረመዳን ወር በጾምና በስግደት እንዲሁም የተቸገሩትን በመርዳት ከፈጣሪ ምህረት የሚጠየቅበት መሆኑን ገልጸዋል። ስለሆነም የተቋሙ ሙስሊም ሠራተኞች ከኃጢያት በመራቅ፣ የፈጣሪን ፍራቻ በማጽናት እና የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ቀሪ ጾሙን እንዲያሳልፉ ጥሪ አቅርበዋል። በተቋሙ የኃይል ማስተላለፍ ዘርፍ የሠው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል በበኩላቸው እንደዚህ ዓይነት መርሃ ግብሮች መዘጋጀታቸው የእርስ በርስ ግንኙነትን ከማጠናከር ባሻገር በተቋሙ ላይ የእኔነት ስሜትን ያሳድጋል  ብለዋል። መርሃ ግብሩ እንደ ተቋም ለሁለተኛ ጊዜ መደረጉን ያስታውሱት ዳይሬክተሩ በቀጣይም ሠራተኛውን  በማስተባበር አቅም የሌላቸውን ማገዝ እንደሚገባ አመልክተዋል። ለመርሃ ግብሩ  መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራቸውን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የሥራ ኃላፊዎችን፣ሠራተኞችን እና የፕሮግራሙ አስተባባሪዎችን አመስግነዋል።   💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የሀገሪቱን ዕድገት የሚመጥን የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታ በመከናወን  ላይ ነው ........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሀገራዊ የኢኮኖሚ እድገቱን የሚመጥን የኃይል መሰረተ ልማቶችን ግንባታ እያካሄደ መሆኑን የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር ገለጹ። ዳይሬክተሩ አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት ያለ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢኮኖሚያዊ እድገትንም ሆነ ማህበራዊ ልማት  ፈጽሞ ማሰብ የማይቻልበት ጊዜ ሆኗል። ተቋሙም ይህን ታሳቢ ያደረጉ የኃይል መሰረተ ልማቶችን ግንባታ በመላ ሀገሪቱ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። አሁን ላይ ያለውን ሀገራዊ ኃይል የማመንጨት አቅም ከእጥፍ በላይ ለማሳደግ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ አምስት የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ በመከናወን ላይ ነው ብለዋል። ተቋሙ ተጨማሪ የኃይል ፍላጎት ባለባቸው አካባቢዎች የማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያና የማዘመን ሥራ ከማከናወን ጎን ለጎን ተደራሽነቱንና ፍትሐዊነቱን የሚያሰፉ አዳዲስ የማከፋፈያ ጣቢያዎችንና ማስተላለፊያ መስመሮችን እየገነባ እንደሆነም ተናግረዋል። የሚገነቡ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና የማስተላለፊያ መስመሮች እስከ አሁን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ያልነበሩትን አካባቢዎች ተደራሽ ማድረግን ትኩረት ያደረጉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል። በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የኃይል ተደራሽነት ሽፋኑን አሁን ካለበት 54 በመቶ ወደ 78 በመቶ ለማድረስ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አቶ ሞገስ ገልፀዋል። ከዋናው ግሪድ ኃይል የማያገኙ አካባቢዎችም ኦፍ ግሪድ በሆነ ወይም ከግሪድ ጋር ባልተገናኘ መንገድ ኃይል የሚያገኙበትን መንገድ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል። የሀገር ውስጥ የኃይል ፍላጎትን ከማሟላት ባሻገርም በቀጣናው የሚገኙ የጎረቤት ሀገራትን በኃይል ለማስተሳሰር በርካታ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል። በዚህም ለጅቡቲ፣ ለኬኒያና ለሱዳን ኃይል እየቀረበ መሆኑንና በቅርቡም ለታንዛኒያ ማቅረብ እንደሚጀመር ጠቁመዋል። እንደ አቶ ሞገስ ገለጻ ለጎረቤት ሀገራት እየቀረበ ያለው ኃይል ከሚመነጨው ከ10 በመቶ በታች ድርሻ ቢኖረውም የተቋሙን ከ30 በመቶ በላይ ገቢ እየሸፈነና ለቀጣናዊ ትስስር አስተዋጽዖ እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል። እየተገነቡ ያሉ የኃይል መሰረተ ልማቶች የአፍሪካ ህብረት በአጀንዳ 2063 የቀረፀውን አህጉሩን በመሰረተ ልማት የማስተሳሰር ዕቅድ ለማሳካት ጉልህ ድርሻ እንደሚያበረክቱ ነው ያብራሩት። ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በኦፕሬሽን ላይ ብቻ የሚገኙ 194 የማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ 20 ሺ 673 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመሮች እና 17 የማመንጫ ጣቢያዎችን ያስተዳድራል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የህብረተሰቡን የኃይል ጥያቄ የሚመልስ የጋራ አሰራር መዘርጋት ይገባል …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ የሚተገብሯቸው አሰራሮች የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞችን ጥያቄ የሚመልሱ እንዲሆን የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ አሳሰበ፡፡ በዘርፉ የማዕከላዊ 3 ሪጅን እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአዲስ አባባና የሸገር ከተማ የዲስትሪዩቢሽን ኃላፊዎች የ100 ቀናት ዕቅዶቻቸዉ ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ የሪጅኑ የጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ  ታደሰ  ገብሬ  እንደገለፁት የውይይቱ ዓላማ በኦፕሬሽን እና ጥገና ሥራዎች የአፈፃፀም መሥፈርት /SOP/ ላይ የጋራ ግንዛቤ ለመያዝ፣ ደንበኞችን ማዕከል ያደረገ የተቀላጠፈ ሥራ ለመስራት እና የኃይል  ጭነትን ለማሻሻል ነው፡፡ በውይይቱ ላይ በሪጅኑ ውስጥ በሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በ15 እና በ33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች በአዲስ አባባና በሸገር ከተማ ላይ የሚታዩ የኃይል መቆራረጥ ችግሮችን በጋራ መፍታት እና የጋራ አሰራሮችን ማበልፀግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ሃሳቦች ቀርበዋል፡፡ በ100 ቀናት ዕቅዱ ላይ የተካተቱ ችግሮችን ለመቅረፍ የጋራ መግባባት ፈጥሮ መንቀሳቀስ እንደሚገባ አቶ ታደሰ አሳስበዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የምዕራብ አዲስ አበባ ሪጅን የፕላኒንግ ኃላፊ የሆኑት አቶ አለነ ወልዴ በበኩላቸው የመለዋወጫ ዕቃዎች እጥረትና ከአቅም በላይ ጭነት ያለባቸው መስመሮች መኖራቸውን ለሥራቸው እክል እንደሆነ ተናግረዋል። የውይይት መድረከ  ፈጣን የማስተካከያ እርምጃዎችን ለመውሰድ እንደሚያስችል ገልፀዋል፡፡      እንደ አቶ አለነ ገለፃ ተቋማቱ በጋራ የሚሰሯቸዉን ሥራዎች ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል አሰራር ሊዘረጉ ይገባል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ሥራ 63 በመቶ ደርሷል …......///…...... የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የወላይታ ሶዶ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ሥራ 63 በመቶ መድረሱን ፕሮጀክቱ አስታወቀ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወላይታ ሶዶ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሲቪል መሐንዲስ አቶ አበበ ሚጀና እንደገለጹት የእሳት መከላከያ ግድግዳን ጨምሮ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎችን ለማስቀመጥ የሚያግዙ የመሰረት ሥራዎች ተጠናቀዋል። በአሁኑ ሰዓት የትራንስፎርመር ዘይት የማጣራት ስራ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል። የፍሳሽ ማስወገጃ እና ገመዶች የሚዘረጉበት ቦይ (ኬብል ትሬንች) ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙ ገልጸው የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ የአጥር ግንባታ እና መሬቱን ጠጠር የማልበስ ተግባራት ደግሞ በቀጣይ እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል። ቀሪ ሥራዎችን ክረምት ከመግባቱ በፊት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነም ተናግረዋል። በሥራ ተቋራጩ ሃዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን የማስፋፊያው የሳይት ኢንጂነር አቶ ቁምላቸው ግርማ እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ሥራ እያንዳንዳቸው ባለ 250 ሜጋ ቮልት አምፔር የመጫን አቅም ያላቸው ሁለት ባለ400/230 ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመሮች ተከላ ሥራን ያካትታል፡፡ ሥራውን በተያዘለት የጊዜ ገደብ እስከ ህዳር 2018 ዓ.ም ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውንም አብራርተዋል። የፕሮጀክቱ ምዕራፍ አንድ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዷለም መላኩ በበኩላቸው ከ14 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በሆነ በጀት የተጀመረው የወላይታ-ሶዶ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ሥራ ሲጠናቀቅ ለአርባምንጭ እና ለኦሞ ኩራዝ አካባቢ አስተማማኝ ኃይል ለማስተላለፍ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራ 69 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮሜካኒካል ሥራው ደግሞ 25 በመቶ መድረሱን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ አጠቃላይ አፈጻጸሙ 63 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል። ለማስፋፊያ ሥራው አስፈላጊ የሆኑ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች በአብዛኛው ሳይት በመድረሳቸው ሥራውን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ የሳይት ሥራ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 15 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

photo content

የተቋረጠው ከቀናት በኋላ ኃይል መልሶ ተገናኝቷል .......///...... የቆቃ ሁርሶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በዘራፊዎች በመውደቃቸው ም
የተቋረጠው ከቀናት በኋላ ኃይል መልሶ  ተገናኝቷል .......///...... የቆቃ ሁርሶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በዘራፊዎች በመውደቃቸው ምክንያት በምስራቅ ኢትዮጵያ ተቋርጦ የቆየውን ኃይል መልሶ ማገናኘት መቻሉን  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት ምሽት 2፡19 ሰዓት ላይ የወደቁትን ታወሮች መልሶ የመትከልና የተበጠሰውን የኃይል ማስተላለፊያ የማገናኘት ሥራ ተጠናቆ በአንደኛው ሰርኪዩት የተቋረጠው ኃይል ማገናኘት ተችሏል፡፡ በተከናወነው ሥራ ኃይል ተቋርጦባቸው የቆዩት የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተሞች በሙሉ ኃይል ማግኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡ የተቋረጠው ኃይል መልሶ እስኪገናኝ ድረስ በትዕግስት የጠበቁ  ደንበኞችን ዳይሬክተሩ አመስግነው ህብረተሰቡ የመሰረተ ልማቱን ከስርቆት እንዲከላከል ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

የተቋረጠውን ኃይል መልሶ ለማገናኘት ርብርብ እየተደረገ ነው .......///...... በአፋር ክልል አዋሽ 7 ከተማ አቅራቢያ በዘራፊዎች ተቆርጠው የወደቁትን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብ
የተቋረጠውን ኃይል መልሶ ለማገናኘት ርብርብ እየተደረገ ነው .......///...... በአፋር ክልል አዋሽ 7 ከተማ አቅራቢያ በዘራፊዎች ተቆርጠው የወደቁትን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች መልሶ ለመትከል ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት የወደቁትን ታወሮች የማለያየት እና የጎደሉትን ብረቶች በመተካት ታወሮቹን መልሶ የማቆም ሥራ ተጀምሯል። በነገው ዕለት ታወሩን መልሶ የማቆም ሥራ በማጠናቀቅ የማስተላለፊያ መስመሩን የማገናኘት እና ኃይል መልሶ የማስተላለፍ ሥራ ሊጀመር እንደሚችል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ኃይል በትዕግስት እንዲጠብቁ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 13 ቀን 2017 ዓ.ም

ጣቢያው ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ........///........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ-ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ኮንቨርተር ጣቢያ ምስራቅ አፍሪካን በኃይል ለማስተሳሰር ከፍተኛ ሚና እየተጨወተ መሆኑ ተገለጸ። በጣቢያው የጥገናና የኦፕሬሽን ባለሙያ አቶ መኮንን ካሴ እንደተናገሩት የኮንቨርተር ጣቢያው በዲዛይን፣ በቴክኖሎጂ እና በዓይነቱ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያው በመሆን በ2014 ዓ.ም ነው ሥራ የጀመረው። ኮንቨርተር ጣቢያው ከወላይታ ሶዶ ቁጥር ሁለት የማከፋፈያ ጣቢያ በአራት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመሮች ተቀብሎ፣ 12 ኮንቨርተር ትራንስፎርመሮችን እና 1 ሺ 680 ታሪስተሮች(thyristors) ተጠቅሞ ኃይል የሚያስተላልፍ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ጣቢያው 2 ሺ ሜጋ ዋት ኃይል የመሸከም አቅም ባላቸው በሁለት ፖሎች  እና ከኢትዮጵያ እስከ ኬኒያ በተዘረጋ 1 ሺ 60 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር አማካይነት ኃይል እያስተላለፍ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ከኬኒያ ጋር ባለው የኃይል ሽያጭ ስምምነት መሰረት በአሁኑ ወቅት በቀን 18 ስዓት ማለትም እስከ ምሽት 6 ስዓት ድረስ በሰዓት 200 ሜጋ ዋት እንዲሁም ከዚያ በኋላ በሚኖረው ቀሪ 6 ስዓት ደግሞ በሰዓት 65 ሜጋ ዋት ኃይል እየቀረበ ይገኛል ብለዋል። ጣቢያው በስምምነቱ መሠረት እየጨመረ የሚሄደውን የኃይል አቅርቦት እና ወደ ታንዛኒያ ኃይል ለማስተላለፍ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል አቅም እንዳለውም ገልጸዋል፡፡ በቀጣይ ከሌሎች ሀገራት ጋር የሚደረጉ የኃይል ሽያጭ ስምምነቶችን ተከትሎ አስተማማኝና ኃይል በማስተላለፍ ለአህጉራዊ የኃይል ትስስር መሳለጥ የሚያደርገውን አስተዋጽዖ ለማስቀጠል እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ጣቢያው የኃይል ኤክስፖርቱን ለማሳደግ የተያዘውን ጥረት ለመደገፍ ተለዋጭ ዥረት (Alternative Current) ወደ ቀጥተኛ ዥረት (Direct current) የቴክኖሎጅ ዓይነት ለመለወጥ የተገነባ ማከፋፈያ ጣቢያ በመሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው አስታውሰዋል። ቀጥተኛ ዥረት መሆኑ ከ1 ሺ ኪሎ ሜትር በላይ ያለምንም ተጨማሪ ማከፋፈያ ጣቢያ በሁለት መስመር ብቻ ኃይል ለማስተላለፍ ማስቻሉን የተናገሩት ባለሙያው መስመሩ በተለዋጭ ዥረት ዘዴ የተገነባ ቢሆን ኖሮ ምንአልባትም አራት አካባቢ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን መገንባት ያስገድድ ነበር ብለዋል።   በተጨማሪም በፍሪኩየንሲ ልዩነት ምክንያት ግሪድ እንዳይረበሽ፣ የኃይል ብክነት እንዳይኖር፣ ከስምምነት ውጭ ኃይል ከግሪድ እንዳይሄድ እንዲሁም ኃይል መላክ ብቻ ሳይሆን ከኬኒያ ኃይል መቀበል ካስፈለገ ለመቀበል የሚያስችል መሆኑንም አብራርተዋል። የኃይል ሽያጩን ላይ መተማመን እንዲኖር ለማድረግም በኮንቨርተር ጣቢያው እና ሱስዋ ናሮክ ግዛት በሚገኘው የኬንያው ኬትራኮ ኮንቨርተር ጣቢያ ላይ የሁለቱ ተቋማት የኢነርጂ ሜትሮች መተከላቸውንም ጠቁመዋል። ተቋሙ የጣቢያውን የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራውን አስተማማኝ ለማድረግ ወደ 20 የሚደርሱ መሐንዲሶችን ሕንድ አገር ድረስ በመላክ ሥልጠና እንዲወስዱ ማድረጉን የጠቆሙት ባለሞያው ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ ችግር እንዳያጋጥም የደቡብ 1 እና 2 ሪጅኖች በሚያዋስኑት አከባቢ መሰረት ተከፋፍለው የጥገና ቡድን በማዋቀር ክትትል እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

በጣቢያው በራስ አቅም የሚከናወኑ የጥገና ሥራዎች እያደጉ ነው …….///…….. በጊቤ ሦስት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በራስ አቅም የሚከናወኑ የጥገና ሥራዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ሀብታሙ ሰሙ እንደገለጹት ማመንጫ ጣቢያው ሥራ በጀመረበት የመጀመሪያው ዓመት ቻይኖችን በማስገባት የዕውቀት ሽግግር ከተደረገ በኋላ ርክክብ በመፈጸም የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም ማከናወን ጀምሯል። የኃይል ማመንጫ ጣቢያው 1 ሺ 870 ሜጋ ዋት በማመንጨት ለብሔራዊ የኃይል ቋት ከፍተኛውን ድርሻ የሚያበረክት መሆኑን የተናገሩት አቶ ሀብታሙ ይኼን ከግምት ያስገባ የቅድመ መከላከል፣ የትንበያ እና የፍተሻ ጥገና ሥራዎች በጣቢያው ባለሙያዎች እንደሚከናወኑ ገልጸዋል፡፡ በጣቢያው የሚከናወኑ የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም በአግባቡ ለማከናወን ለባለሙያዎቹ አጫጭርና የሥራ ላይ ሥልጠናዎችን እንደሚሰጡ እና እርስ በእርስ የሚማማሩበት ሥርዓት መዘርጋቱንም ጠቁመዋል፡፡ ተርባይኖች እንዳይቆሙ የተበላሹ ዕቃዎች ላይ ማሻሽያ በመስራት ጭምር በርካታ የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም የመስራቱ ልምምድ እያደገ መምጣቱን አብራርተዋል፡፡ ይህም የባለሙያዎችን አቅም በመጠቀም ወጪና ጊዜን በቆጠበ መልኩ አስተማማኝ ኃይል ለማምረት ምቹ መደላድል መፍጠሩን አብራርተዋል። ከኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ ተቋራጩ የቻይናው ዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ ጋር በተደረገ ስምምነት መሰረት የመለዋወጫ ዕቃዎች በወቅቱ እየቀረቡ ነው ያሉት ሥራ አስኪያጁ በስምምነቱ ያልተካተቱት ዕቃዎች ደግሞ በግልጽ ጨረታ እየተገዙ ነው ብለዋል። የጣቢያው የጥገና ባለሙያ አቶ እሸቱ አበራ በበኩላቸው የኃይል ምርቱን በአስተማማኝነት ለመጨመር የሚያስችሉ የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም በጣቢያው የጥገና ወርክሾፕ እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ብሬከሮችን ጨምሮ የማቀዝቀዣ ፓምፖች እና ሌሎች የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። የማቀዝቀዣ ፓምፖች የጥገና ሥራ በውጭ ባለሙያ ቢከናወን ኖሮ ጥገና የሚያስፈልጋቸውን ዕቃዎች ከመጠገን ይልቅ ወደ መቀየር በመግባት ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ ይዳርገው እንደነበር ገልፀዋል። ዕቃዎቹን በጣቢያው ባለሙያዎች በመስራት ወደ አገልግሎት እንዲገቡ መደረጉ ወጪና ጊዜን ከመቆጠቡም በላይ የጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራ የሚያቀላጥፍ ነው ብለዋል። ሠራተኛው አቅሙን አሟጦ እንዲጠቀም እና ሙያዊ ክህሎቱን በማሳደግ ትልልቅ የጥገና ሥራዎችን መስራት እንችላለን የሚል የራስ መተማመን እንዲኖራቸው ዕድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። አቶ እሸቱ የሠራተኛውን አቅም ቀጣይነት ባለው መልኩ የመገንባት፣ የመልዋወጫ እቃ አቅርቦት እና  የክትትልና ድጋፍ ሥራዎች ትኩረት ሊሰጥባቸው እንደሚገባ አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ለኢንዱስትሪው ፍላጉት በቂ የኃይል አቅርቦት መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፁ ........///......... በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚፈልገውን የኃይል አቅርቦት ለማሟላት የሚያስችል በቂ ኃይል መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለፁ፡፡ ጠቅላይ ሚንስትሩ የፌደራል መንግስት የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምን አስመልክቶ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሲሰጡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለፁት በፋብሪካዎችና ኢንዱስትሪዎች በተደረገ ጥናት ቀደም ሲል ሲነሳ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር ሙሉ በሙሉ ተፈቷል፡፡ እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ በበጀት ዓመቱ 8 ወራት ለኢንዱስትሪ ሴክተሩ የቀረበው የኤሌክትሪክ ኃይል ምርት 50 በመቶ ዕድገት ሲያሳይ በሀገር ደረጃ ደግሞ 47 በመቶ የኃይል ፍላጎት ዕድገት ተመዝግቧል፡፡ የሚታየው የፍላጎት ዕድገት ከፍተኛ ዝግጅት እንደሚጠይቅ ያሳየ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ታሳቢ ያደረገ የኤሌክትሪከ መሰረተ ልማት ግንባታ አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1