en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 696 subscribers, ranking 8 049 in the Technologies & Applications category and 2 173 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 696 subscribers.

According to the latest data from 02 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 141 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 28.59%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.37% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 487 views. Within the first day, a publication typically gains 2 569 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 696
Subscribers
No data24 hours
+147 days
+14130 days
Posts Archive
አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በመኖሩ የፋብሪካው ምርታማነት ጨምሯል ....///..... አስተማማኝ ኃይል እየቀረበ በመሆኑ ምርታማነቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የሲ ኤንድ ኢ ወንድማማቾች ብረታ ብረት ፋብሪካ ፋብሪካ አስታወቀ። የፋብሪካው ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ሙሉጌታ እንዳስታወቁት ፋብሪካው በቢሾፍቱ ከተማ የሚገኝና በአርማታ የብረት ምርት በሀገሪቱ ከቀዳሚዎቹ ተርታ የሚሰለፍ ነው። በ2003 ዓ.ም ሥራ የጀመረው ፋብሪካው በአሁኑ ወቅት ከ650 በላይ ቋሚ፣ ከ45 በላይ ጊዜያዊ እና የተለያየ ሙያዊ ድጋፍ የሚሰጡ የውጭ አገር ሠራተኞችን መያዙን ተናግረዋል። የብረት ፋብሪካ ከፍተኛ ኃይል የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከአሁን ቀደም በምርት ሥራው ላይ እንቅፋት የሚፈጥር የኃይል መቆራረጥ እንደነበር አስታውሰዋል። የኃይል መቆራረጡ በፋብሪካው ላይ የሚያደርሰውን ኪሳራ ለማስቀረት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በመነጋገር ከቆቃና ከገላን በሁለት አቅጣጫ ኃይል የሚያገኝ የራሱን ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ገንብቶ ወደ ሥራ ማስገባቱን ገልጸዋል። ይህም የኃይል መቆራረጡን በማስወገድ የፋብሪካውን ምርታማነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዳሳደገው ነው ምክትል ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት። ከተቋሙ ጋር በተደረገ የአገልግሎት ሥምምነት (service level agreement) መሠረት የማከፋፈያ ጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራ እና ሌሎች ሙያዊ ድጋፎች በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች እየተከናወነ እንደሚገኝም አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት ፋብሪካው እስከ 10 ሜጋ ዋት የሚደርስ ኃይል እየተጠቀመ ሲሆን አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት መኖሩን ታሳቢ በማድረግ 10 ሺ ሄክታር ከከተማ አስተዳደሩ ተቀብሎ የማስፋፊያ ሥራ እያከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል። በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈጸም ስርቆት የፋብሪካውን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን እንገነዘባለን ያሉት አቶ ዮሴፍ እንደ ድርጅት ችግሩን ለመከላከል ወደ ፋብሪካው የሚመጡ ቁርጥራጭ ብረቶችን የሚረከብበት ጠንካራ የቅበላ መመሪያ እንዳለው ተናግረዋል። ድርጅቱ የሚመጡ ቁርጥራጭ ብረቶች ከመሰረተ ልማቱ ጋር ግንኙነት የሌላቸውና ከስርቆት የጸዱ መሆኑን እያረጋገጠ ከመቀበል በተጨማሪ አጠራጣሪ ነገሮች በሚስተዋልበት ጊዜ ከጸጥታ አካላት ጋር በመነጋገር ጭምር እንደሚሰራ አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሲ ኤንድ ኢ ወንድማማቾች ብረታ ብረት ፍብሪካ ባለ132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ጣሰው ተክሌ በበኩላቸው ጣቢያው ከቆቃና ከገላን በሁለት አቅጣጫ ኃይል የሚያገኝ በመሆኑ ያልተቋረጠ የኃይል አማራጭ ለማግኘት አስችሎታል ብለዋል። ተቋሙ እስከ 40 ሜጋ ዋት ለማቅረብ ዝግጁ ቢሆንም እስከ አሁን ፋብሪካው እየተጠቀመ ያለው ከ10 ሜጋ ዋት ያልበለጠውን መሆኑን አቶ ጣሰው ተናግረዋል። ፋብሪካው አሁን ላይ ከሚያከናውነው ማስፋፊያ በተጨማሪ ሌሎች የማስፋፊያ ሥራዎችን ቢሰራም አስተማማኝ ኃይል የማቅረብ አቅም መኖሩን አስረድተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ቅንጅታዊ አሰራርን በመዘርጋት የኃይል መቆራረጡን መቀነስ ተችሏል ....///.... ቅንጅታዊ አሰራር በመዘርጋት የኃይል መቆራረጥን መቀነስ መቻላቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አዳማ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አዳማ ሪጅን የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። የአዳማ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ብርሃኑ ቦንገር እንደገለጹት ሁለቱ ተቋማት የሚሰጡት አገልግሎት ተያያዥነት ያለው በመሆኑ በማህበረሰቡ የሚቀርቡ የኃይል ጥያቄዎችን ለመመለስ እንዲሁም የኃይል ተደራሽነቱን ለማሳደግ ተቋማዊ አሰራሩን በጠበቀ መልኩ ተናበው እየሰሩ ነው፡፡ በከተማዋ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ላላቸው ፋብሪካዎች አስተማማኝ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ የኃይል መቆራረጥ መንስኤዎችን በትብብር ለመቅረፍ እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከተማዋንናና የኢንዱስትሪዎችን ቀጣይ የኃይል ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ በቅርቡ አዳማ ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ገንብቶ ወደ ሥራ ማስግባቱንም አውስተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአዳማ ሪጅን የኔትወርክ መሰረተ ልማት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተሬሳ ዓለሙ በበኩላቸው ከማከፋፈያ ጣቢያው 80 ሜጋ ዋት አካባቢ ኃይል እንደሚወስዱና ከጣቢያው ጋር የዕለት ተዕለት ግንኙነት እንዳላቸው አብራርተዋል። በከተማዋ ያለውን የኃይል ተደራሽነትና የአገልግሎት ጥራቱን ለማሳደግ እንዲሁም በአገልግሎቱ በኩል ምንም የኃይል መቆራረጥ እንዳይኖር በቅንጅት እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። አሁን ላይ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ያለ ኤሌክትሪክ ማግኘት የማይታሰብበት ጊዜ ላይ በመደረሱ የሚመጡ የኃይል ጥያቄዎችን ለመመለስ ቅንጅታዊ አሰራሩን ማጠናከር አማራጭ የሌለው  መሆኑን ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት። የኃይል መቆራረጡ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካ እና ደህንነት ላይ ተጽዕኖ እንዳለው በመረዳት ችግሩን በዘላቂነት በመቅረፍ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖር በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

#News Update በጣቢያው ሲከናወን የቆየው የትራንስፎርመር ቅየራ ተጠናቋል ....///.... በወልቂጤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሲከናወን የቆየው የ63 ሜጋ ቮልት አምፔር የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራ መጠናቀቁን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙጀረብ የኑስ እንደገለፁት የትራንፎርመር ቅየራ ሥራው በመጠናቀቁ በፈረቃ ኃይል ሲያገኙ ለነበሩ አካባቢዎች ማምሻውን አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ማቅረብ ይጀመራል። በዚህም በ66 ኪሎ ቮልት የወሊሶ፣ ቱሉቦሎ፣ ጎሮ፣ አመያ እና አጨበር እንዲሁም ቁሳ ከተሞች ያለ ፈረቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት እንደሚጀምሩ ገልፀዋል። በጉራጌ ዞን ሥር ለሚገኙ አካባቢዎች በ15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር  ኃይል እንደሚያገኙም ነው የተናገሩት። በወልቂጤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አንድ ትራንስፎርመር ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር ምክንያት አካባቢዎቹ ላለፉት 3 ሳምንታት የተወሰኑ አካባቢዎች ኃይል በፈረቃ ሲያገኙ መቆየታቸው ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የክረምቱን ወራት ታሳቢ ያደረገ የግድብ ደህንነትና ክትትል ሥራ እየተከናወነ ነው .....///..... በቆቃ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ መጪውን የክረምት ወራት ታሳቢ ያደረገ የግድብ ደህንነት ክትትል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ ያፌት ተስፋዬ እንዳስታወቁት በክረምት ወራት ሊኖር የሚችለው ዝናብ ለኃይል ማመንጫዎች አስፈላጊ ቢሆንም በግድቦች ላይ ተገቢው የቅድመ ጥንቃቄ ሥራ ካልተከናወነ ለአደጋ ሊያጋልጥ  ይችላል ። በክረምት ወራት በእድሜ ምክንያት እያጋጠሙ ያሉ ስንጥቆች እንዲሁም የእንቦጭ አረምና ደለል በግድቡ ደህንነትና ኦፕሬሽን ሥራ ላይ አሉታዊ ጫና እንደሚያሳድሩ ጠቁመዋል። በመሆኑም መጪውን የክረምት ወራት ታሳቢ በማድረግ እነዚህን ችግሮች ለመከላከል አጠቃላይ የግድብ ፍተሻ እና የቅድመ መከላከል የጥገና እንዲሁም የክትትል ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን አብራርተዋል። የክትትልና ቁጥጥር ሥራው በውኃ መግቢያው፣ በውኃ ማስተንፈሻ (Spillways) እና በግድቡ የተለያዩ ክፍሎች ላይ  እንደሚከናወን ገልፀዋል። በዚህም የግድቡን የውኃ ማስተንፈሻ እና መቆጣጠሪያ በሮች በመጠገንና ብረቶቹን ከዝገት በመከላከል ለሥራ ዝግጁ እንዲሆኑ ለማድረግ እንደሚያስችል ገልጸዋል። በግድቡ የላይኛው ክፍል ላይ የሚገኙ ስንጥቆች እየሰፉ እንዳይሄዱ ክፍተቶቹን የሙሙላት ሥራ መከናወኑንም አብራርተዋል። እንደ አቶ ያፌት ገለፃ የግድብ ደህንነት ሥራው በክረምት ወራት ወደ ግድቡ የሚገባውን ክፍተኛ ውኃ ለማስተንፈስ በሮቹ በትክክል አንደሚከፈቱ፣ እንደሚዘጉ እና ብሬከሩ በትክክል እንደሚስራ አስቀድሞ ለመለየት ይጠቅማል። የቅድመ ፍተሻና እና ጥገና ሥራው ግድቡ ውኃ ከሞላ በኋላ የተበላሹ በሮች፣ ሞተሮች፣ ብሬከሮች እና የተለያዩ መሣሪያዎችን ለመጠገን የሚፈጥረውን የሥራ ጫና እንደሚያቀል አብራርተዋል። የክትትልና ቁጥጥር ሥራው የግድቡን ደህንነት በመጠበቅና የኦፕሬሽን ሥራውን በማቀላጠፍ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው የሚጠበቅበትን ኃይል በአግባቡ እንዲያመርት ከማድረጉም ባሻገር በታችኛው ተፋሰስ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ከጎርፍ አደጋ ለመከላከል የሚያስችል መሆኑንም አቶ ያፌት ገልጸዋል፡፡ በግድቡ አካላት ላይ ከሚከናወኑ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች በተጨማሪ በግድቡ ሠው ሰራሽ ሀይቅ ላይ በፍጥነት እየተስፋፋ የሚገኝውን የእንቦጭ አረም ክረምቱ ከመግባቱ በፊት ለማስወገድ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ባሳተፍ መልኩ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። የቆቃ የውኃ ኃይል ማመንጫ ከ1952 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥጌ/ሞመ ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ የሚሆኑባቸው በሀገርአቀፍ ደረጃ ተከብረው የሚውሉ ብሔራዊ በዓላት ፡- 1. መስከረም 1 ቀን የዘመን መለወጫ (እንቁጣጣሽ) በዓል 2. የካቲት 23 ቀን የአድዋ ድል በዓል 3. ሚያዚያ  23 ቀን የዓለም የሠራተኞች (የላብአደሮች) ቀን 4. ሚያዚያ  27 ሰባት ቀን የአርበኞች (የድል) ቀን በዓል የሚከተሉት በዓላት በሀገርአቀፍ ደረጃ ታስበው የሚውሉ ብሔራዊ በዓላት ናቸው ፡- 1. የካቲት 12 ቀን የሰማዕታት ቀን 2. ሕዳር 29 ቀን የኢትዮጵያ ህብረ-ብሄራዊነት (የብሔር ብሔረሰቦች) ቀን በተጠቀሱት ብሔራዊ በዓላት የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት ይሆናሉ፡፡ የሚከተሉት በዓላት በሀገርአቀፍ ደረጃ የሚከበሩ ሃይማኖታዊ በዓላት ናቸው :: 1. መስከረም 17 ቀን የመስቀል በዓል 2. በየአራት ዓመቱ የሚመጣው ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ ታህሳስ 29 ቀን የሚውለው የገና ወይም የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል 3. ጥር 11 ቀን የጥምቀት በዓል 4. የስቅለት በዓል 5. የትንሳኤ (ፋሲካ) በዓል 6. የኢድ-አልአድሃ (አረፋ) በዓል 7. የመውሊድ በዓል 8. የኢድ አልፈጥር በዓል በተጠቀሱት ሃይማኖታዊ በዓላት የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ ይሆናሉ። ግንቦት 20 ግን የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ውስጥ አልተካተተም። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

#ExamResult የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡
+1
#ExamResult የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-4ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል በተሰጠው የተግባር ፈተና ከተራ ቁጥር 1 እስከ ተራ ቁጥር 10 ስማችሁ የተገለጸው ተወዳዳሪዎች ከግንቦት 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ፣ የስራ ልምድ ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ ቀርባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦቱ የከተሞችን ሁለንተናዊ ዕድገት እያፋጠነ ነው .......///........ የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት የከተሞችን ሁለንተናዊ ዕድገት እያፋጠነ መሆኑን የአዳማ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የሞጆ ከተማ ከንቲባ ገለጹ። የአዳማ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ንጋቱ ሞቱማ እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የገነባቸውና የሚያስተዳድራቸው የንፋስና የውኃ ኃይል ማመንጫዎች እንዲሁም የተለያየ የቮልቴጅ መጠን ያላቸው ማከፋፈያ ጣቢያዎች በከተማዋ ዙሪያ ይገኛሉ። ተቋሙ የገነባቸው እነዚህ የኃይል መሰረተ ልማቶች የአካባቢውን የኃይል አቅርቦት በማሳደግ አዳማ ከተማን የኢንዱስትሪና የኮንፈረንስ ማዕከል እንዳደረጋት ተናግረዋል። እንደ ምክትል ከንቲባው ገለፃ አሁን ላይ በከተማዋ አስተማማኝ ኃይል በመኖሩ በርካታ ዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርጉና ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ፋብሪካዎችን ጨምሮ ትልልቅ ኢንቨስትመንቶች ወደ ሥራ እየገቡ ነው። ለአዳማ ከተማ ነዋሪዎች ለመጠጥ እየዋለ ያለውን ውኃ ከቆቃ የኃይል ማመንጫ ግድብ እንደሚያገኙ የተናገሩት ምክትል ከንቲባው የኃይል መሰረተ ልማቶቹ ንጹህ የመጠጥ ውኃን ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ የማህበረሰቡን የአኗኗር ዘይቤ በማዘመን በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑንም አብራርተዋል። አስተዳደራቸው በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን ከተቋሙ ጋር ያለውን ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር ለመከላከል እንደሚሰራ በመግለፅ ቀጣይ የከተማዋን ዕድገት ታሳቢ ያደረገ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ተቋሙ በትኩረት እንዲሰራም ጠይቀዋል። የሞጆ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ገዛሊ ሀሹ በበኩላቸው ከተማዋ የሎጅስቲክስና የኢንዱስትሪ ማዕከል በመሆኗ እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በመኖሩ የኢንቨስትመንት ፍሰቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል ብለዋል። ቀደም ሲል በከተማዋ ላይ ኢንቨስት ያደረጉ ከ300 በላይ ባለሃብቶች ከ30 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ነው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው በርካታ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ለከተማ አስተዳደሩ ቀርበው በሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በከተማዋ አቅራቢያ እየተገነባ መሆኑን የጠቆሙት ከንቲባው በቀጣይም የከተማዋን ፈጣን እድገት የሚያስቀጥል የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። የከተማው ነዋሪ፣ የፋብሪካ ባለቤቶች እንዲሁም ከተማ አስተዳደሩ ለሚያቀርበው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ተቋሙ እየሰጠ ላለው ምላሽ ምስጋና አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥጌ/ሞመ ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

#ዜናእረፍት! ዜና እረፍት! በተቋሙ የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ሥራ ባልደረባ የነበሩት አቶ ጌትነት በቀለ ባደረባቸው ህመም በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ህክምና ሲከታተሉ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ተቋሙ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል፡፡ አቶ ጌትነት በቀለ ከአባታቸው ከአቶ በቀለ ወልደአማኑኤል እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ሲደልለኝ ተመቸ በአዲስ አበባ ጉለሌ ክ/ከተማ መስከረም 21 ቀን 1968 ዓ.ም ተወለዱ። ከ1972 እስከ 1985 ዓ.ም ድረስ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ቀጨኔ ደብረ ሠላም፣ ወ/ሮ ቀለመወርቅ ጥሩነህ፣ ኢትዮጵያ ትቅደም እና ጀኔራል ዊንጌት ት/ቤቶች ተከታትለዋል። በ1990 ዓ.ም በተቋሙ ማሰልጠኛ ለ6 ወራት በኤሌክትሮ ሜካኒክ የሙያ መስክ ሥልጠና ወስደው ታህሳስ 18 ቀን 1990 ዓ.ም በቆቃ ኃይል ማመንጫ ሥራ መጀመራቸውን የግል ማህደራቸው ያስረዳል፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል (ኤሌክትሮኒክስ) ቴክኖሎጂ በ1999 ዓ.ም ያገኙት አቶ ጌትነት ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በ2014 ዓ.ም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ፓወር ምህንድስና አጠናቀዋል። አቶ ጌትነት ላለፉት 27 ዓመታት በባለሙያነትና በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች ተቋሙን በቅንነት፣ በታማኝነት፣ በታታሪነት ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን በባህሪያቸውም እጅግ በጣም ትሁት፣ ሰው አክባሪ፣ ጥሩ ሥነ-ምግባርን የተላበሱ ትጉህ ሠራተኛ ነበሩ። አቶ ጌትነት በተቋሙ የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ የክላስተር አንድ የኃይል ማመንጫዎች መምሪያ ዳይሬክተር ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል። አቶ ጌነትነት ባደረባቸው ህመም ምክንያት በተወለዱ በ49 ዓመታቸው ግንቦት 17 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ ሲሆን የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸውም በዛሬው ዕለት ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት በአቃቂ ቃሊቲ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን ይፈፀማል፡፡ አቶ ጌትነት ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበሩ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአቶ ጌትነት በቀለ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በድጋሜ እየገለፀ ለቤተሰቦቹ እና ወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን ይመኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥጌ/ሞመ ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የኃይል አቅርቦት ያልተዳረሰባቸውን አካባቢዎች ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ነው ….....///….... የኃይል አቅርቦቱ ያልተዳረሰባቸውን አካባቢዎች ተደራሽ የሚያደርጉ የኃይል መሰረተ ልማቶች ግንባታ እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት እስከ አሁን ምንም ዓይነት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ያልተገነባባቸውና የኃይል አቅርቦቱ ያልተዳረሰባቸው አካባቢዎች አሉ። የተደራሽነት ችግርን ለመቅረፍ የሚገነቡት የማከፋፈያ ጣቢያዎችና የማስተላለፊያ መስመሮች እስከ አሁን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ያልነበሩ አካባቢዎችን ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የደብባዊ ግሪድ ማስፋፈያ ፕሮጀክት አካል የሆኑት የሺግዳን እና ቲርጋ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ የተደራሽነት ሽፉኑን የሚያሳድጉ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። እንደ ሀገር ያለውን 54 በመቶ የኤሌክትሪክ ሽፋን ወደ 78 በመቶ ለማሳደግ ተቋሙ ዕቅድ ነድፎ እየሰራ ስለመሆኑ አብራርተዋል። ቀሪ አካባቢዎች ከግሪድ ጋር ባልተገናኘ መንገድ ኃይል የሚያገኙበትን አቅጣጫ መቀመጡንም ተናግረዋል። እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ሽፋንን የሚያሰፉ አዳዲስ የማከፋፈያ ጣቢያዎችንና ማስተላለፊያ መስመሮችን ከመገንባት በተጓዳኝ ተጨማሪ የኃይል ፍላጎት ባለባቸው አካባቢዎች የአቅም ማሳደግ እና የማዘመን ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ20 ሺ 650 ሰርኪዩት ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው 307 የማስተላለፊያ መስመሮችን እንዲሁም 194 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ያስተዳድራል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥጌ/ሞመ ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ማከፋፈያ ጣቢያው የኃይል ብክነትን በማስወገድ አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ  ነው .....///...... የአዳማ አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የኃይል ብክነትን በማስወገድ አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ብርሃኑ ቦንገር እንደገለፁት ጣቢያው ለአዳማ ከተማ እንዲሁም የአዳማ ቆርቆሮን ጨምሮ በዙሪያዋ ለሚገኙ በርካታ ፋብሪካዎች ኃይል እያቀረበ ይገኛል። ከከተማዋ መስፋፋትና ከኢንዱስትሪዎች ፍሰት መጨመር ጋር ተያይዞ እየቀረበ ያለውን የኃይል ጥያቄ ለመመለስ ተጨማሪ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያ  እንደተተከለለት ተናግረዋል። በዚህም ከ80 ሜጋ ዋት በላይ በመጫን ቀደም ሲል ጣቢያው የነበሩትን ሰባት ወጭ መስመሮች ወደ 13 በማሳደግ ለአዳዲስ እና ተጨማሪ ኃይል ለሚጠይቁ ነባር ደንበኞች አስተማማኝ ኃይል ማቅረብ እንደተቻለ  ጠቁመዋል። ለደንበኞች ያልተቆራረጠ ኃይል ለማቅረብ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አዳማ ዲስትሪክት ጋር በመተባበር የስካዳ ሥርዓት መተግበሩንም ገልጸዋል። ቀደም ሲል ጣቢያው ከ90 በመቶ በላይ የአዳማን የኃይል ፍላጎት ሲያሟላ መቆየቱን ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ አሁን ላይ የአዳማ ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተገንብቶ ወደ ሥራ በመግባቱ በጣቢያው ላይ የነበረውን ጫና እንዲቀንስ አድርጎታል ብለዋል። የጣቢያውን ኃይል ጭነት እና ፍሰት የሚቆጣጠሩና ብክነትን የሚቀንሱ ሦስት "ፓወር ሪአክተሮች" መተከላቸውን አቶ ብርሃኑ አስረድተዋል። የማከፋፈያ ጣቢያውን ደህንነት ለማረጋገጥ የመቆጣጠሪያ ክፍሉን የማሻሻልና የማዘመን ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል። የመቆጣጠሪያ ቅየራው ክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች አስተባባሪ አቶ ክብሮም በረኼ በበኩላቸው የጣቢያው የመቆጣጠሪያ ሥርዓቶች ረጅም ዓመት ያገለገሉ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ ሲ ዋይ ጂ በተባለ የቻይና ኩባንያ አማካኝነት በአዲስ መልክ የመቀየር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል። ይህም በተለያየ ምክንያት ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን በመከላከል የኃይል መቆራረጡን ለማስወገድ እና የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማዘመን እንደሚያስችል አስረድተዋል፡፡ አዳማ አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ከአዋሽ ሰባት፣ ከቆቃ እና ከአዳማ 2 ንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ኃይል ይቀበላል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥጌ/ሞመ ግንቦት 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ፆታ ተኮር ጥቃትን መከላከል የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ……////……. ፆታ ተኮር ጥቃትን መከላከል የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ አስታወቀ፡፡ መምሪያው ከሪጅኖች፣ ከኃይል ማመንጫዎች  እና ከዋናው መስሪያ ቤት ለተውጣጡ ሠራተኞች በሥርዓተ ፆታ እና ልማት እንዲሁም በፆታ ተኮር ጥቃት ላይ ያተኮረ ሥልጠና በተቋሙ መሰብሰቢያ አዳራሽ ሰጥቷል። ሥልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደገለፁት ፆታ ተኮር ጥቃቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ናቸው፡፡ የሴቶችን መብት ለማስከበር በርካታ የህግና የፖሊሲ ማዕቀፎች በሥራ ላይ እንደዋሉ የጠቆሙት ዳይሬክተሯ ይሁን እንጂ ከጊዜ ወደ ጊዜ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ፆታዊ ጥቃቶችን በሚፈለገው ደረጃ ማስቆም እንዳልተቻለ ተናግረዋል፡፡ የሥልጠናው ተሳታፊዎች በአካባቢያቸውና በሥራ ቦታቸው ላይ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብ ፆታ ተኮር ጥቃቶችን እንዲከላከሉና የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን እንዲያከናውኑ ዕድል ይሰጣል ብለዋል፡፡ ሥልጠናው ፆታ ተኮር ጥቃት የሚደርስባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የህግ፣ የሥነ-ልቦና እና ጤና ነክ ድጋፎችን እንዲያገኙ የማመቻቸት ሥራ እንዲሰሩ እንደሚያግዛቸውም ነው ያብራሩት፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ የሥልጠናው ተሳታፊዎች ሥርዓተ ፆታ ከልማት ጋር ያለውን ትስስርና የሚያመጣውን ሁለተናዊ ዕድገት በመረዳት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን ይሰራሉ፡፡ በተቋሙ የካሳ ጉዳዮች አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ አቶ ደረጄ አጥናፌ በሥልጠናው ላይ እንደገለፁት ጥቃት ሰዎች ሰው በመሆናቸው ብቻ የተጎናፀፏቸውን እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ሰነዶች እውቅና የተሰጣቸውን ሰብዓዊ መብቶች የሚጥስ ድርጊት ነው፡፡ ፆታ ተኮር ጥቃት በሰዎች ላይ አካላዊ፣ ወሲባዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ችግሮችን የሚያስከትል ፆታን መሰረት አድርጎ የሚፈፀም የኃይል ድርጊት መሆኑንም ነው የገለፁት፡፡ እንደ አቶ ደረጄ ገለፃ ያልተፈለገ እርግዝና፣ የአባላዘር በሽታ፣  የቤተሰብ ግጭት፣ አካላዊ እና ሥነ ልቦናዊ ጉዳቶች እንዲሁም ሞት የፆታ ተኮር ጥቃት ውጤቶች ናቸው፡፡ መንግሥትም ሆነ ተቋማት ፆታ ተኮር ጥቃቶች ላይ የተደነገጉ ህጎችን ወደ ተግባር በመቀየር ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚጠብቅባቸው አፅዕኖት ሰጥተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም