ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 572 подписчиков, занимая 8 384 место в категории Технологии и приложения и 2 165 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 572 подписчиков.

Согласно последним данным от 23 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 0, а за последние 24 часа — -2, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.89%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.48% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 026 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 408 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 9.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 24 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 572
Подписчики
-224 часа
-37 дней
Нет данных30 день
Архив постов
መምሪያው በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ደህንነትና ጥበቃ የተከናወኑ ሥራዎችን እየገመገመ ነው ….....///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ደህንነትና አስተዳደራዊ ጉዳዮች መምሪያ የዘጠ
+4
መምሪያው በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ደህንነትና ጥበቃ የተከናወኑ ሥራዎችን እየገመገመ ነው ….....///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ደህንነትና አስተዳደራዊ ጉዳዮች መምሪያ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በሀዋሳ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሺፋ እንደገለጹት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማው በተቋሙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ የሚፈጸሙ ሥርቆቶችን በመከላከል ረገድ ባለፈው ዘጠኝ ወራት በሪጅኖች የተከናወኑ ሥራዎችን፣ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በዝርዝር ይመለከታል። የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማው በተቋሙ ንብረት ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን ለመከላከል በተከናወኑ ሥራዎች የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ሪጅኖችን ተሞክሮ በማስፋት ልምድ የሚወሰድበት መሆኑንም ገልጸዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=መምሪያው-በኤሌክትሪክ-መሠረተ-ልማት-ደህ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም

ፕሮጀክቱ የአካባቢውን ማህበረሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ነው ……….////……… በኦሞ ወንዝ ላይ እየተገነባ የሚገኘው የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ከኃይል ማመንጫነት ባለፈ
+9
ፕሮጀክቱ የአካባቢውን ማህበረሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ነው ……….////……… በኦሞ ወንዝ ላይ እየተገነባ የሚገኘው የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ከኃይል ማመንጫነት ባለፈ ለዜጎች ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እያበረከተ መሆኑን የአካባቢው መስተዳድር አካላት እና የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ገለፁ፡፡ ከመሎኮዛ ወረዳ፣ ከጋሞ ዞን እና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስትና ከምክር ቤት የተውጣጡ አመራሮች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በፕሮጀክቱ በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ዙሪያ ምክክር አድርገዋል፡፡ በውይይቱ ላይ የመሎ ኮዛ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሉነህ አውሳቶ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ ለሀገር ብርሃን ከመሆን ባለፈ ለመሎ ኮዛ ሕዝብ አዲስ ተስፋን የፈነጠቀ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱ-የአካባቢውን-ማህበረሰብ-ማህበ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም

በፕሮጀክት የሚከናወኑ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ለአካባቢው ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽዖ እያበረከቱ ነው .......///....... የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከግድቡ ግንባታ ጎን ለጎ
+8
በፕሮጀክት የሚከናወኑ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ለአካባቢው ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽዖ እያበረከቱ ነው .......///....... የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከግድቡ ግንባታ ጎን ለጎን ያከናወናቸው የማህበራዊ ኃላፊነት ተግባራት የህብረተሰቡን አኗኗር ዘይቤ ማሻሻላቸውን የፕሮጀክቱ የአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንደገለጹት ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከሠራቸው ሥራዎች መካከል በፕሮጀክቱ ዙሪያ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ከ120 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የጠጠር መንገድ ግንባታ በዋነኝነት ይጠቀሳል። በፕሮጀክቱ አቅራቢያ ከተገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ባሻገር  በኦሞ ወንዝ ላይ የተገነባው 175 ሜትር ርዝማኔ ያለው ድልድይ ቀደም ሲል በአካባቢው የነበረውን ከፍተኛ የትራንስፖርት ችግር የቀረፉና የጎፋ እና ኮንታ ዞኖች ህዝቦችን ማገናኘታቸውን ገልፀዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በፕሮጀክት-የሚከናወኑ-የማህበራዊ-ኃላፊ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ የተዘረጋው የመሠረተ ልማት ደህንነት አስተዳደር አሰራር ውጤት እያስገኘ ነው …….///….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አዲስ የተዘረጋው የተቀናጀ የመሠረተ ልማት ደህንነት አስተዳደር አሰራር
ተቋሙ የተዘረጋው የመሠረተ ልማት ደህንነት አስተዳደር አሰራር ውጤት እያስገኘ ነው …….///….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አዲስ የተዘረጋው የተቀናጀ የመሠረተ ልማት ደህንነት አስተዳደር አሰራር ውጤት እያስገኘ መሆኑን በዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የተቋማዊ የመስረተ ልማት ደህንነት አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ፍራፊስ በቀለ እንደገለጹት ተቋሙ በመሠረተ ልማቶቹ ላይ የሚፈጸሙ ስርቆቶችን ለመከላከል የተቋማዊ የመስረተ ልማት ደህንነት አስተዳደር ቢሮ በመክፈት ወደ ሥራ ገብቷል። ቢሮው በ13ቱም የተቋሙ ሪጅኖች ከመከላከያ የተውጣጡ ከፍተኛ መኮንኖችን በመመደብ የጥበቃ ሥራውን በቅርበት እንዲመራና ከፌዴራልና ከክልል የፀጥታ አካላት እንዲሁም በየደረጃው ከሚገኙ የመስተዳድር አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር እንዲኖር እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-የተዘረጋው-የመሠረተ-ልማት-ደህን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ የሚወጡ ፖሊሲዎች ጥራት ያላቸውና የተናበቡ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው ‎…....///…... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚወጡ ፖሊሲዎች ጥራት ያላቸው፣ አሰራርን የሚያቀላጥፉ እና የተናበቡ እ
+8
በተቋሙ የሚወጡ ፖሊሲዎች ጥራት ያላቸውና የተናበቡ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው ‎…....///…... ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚወጡ ፖሊሲዎች ጥራት ያላቸው፣ አሰራርን የሚያቀላጥፉ እና የተናበቡ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የፖሊሲ፣ ፕሮሰስና የለውጥ ሥራ አመራር መምሪያ ገለጸ። ‎ ‎መምሪያው ከተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ የሙያ ደህንነት እና ጤንነት ቢሮ ጋር በሥራ ላይ ጤናና ደህንነት ረቂቅ ፖሊሲ ዙሪያ ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት ተካሂዷል። ‎ ‎የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አንዱዓለም ኪዳኔ እንደገለጹት ተቋሙ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ያለውን አቋምና አቅጣጫ የሚያመላክቱ እንዲሁም አሰራርን ውጤታማ የሚያደርጉ የተለያዩ ፖሊሲዎች በዝግጅት ሂደት ላይ ይገኛሉ፡፡ በዛሬው ዕለት የተካሄደው ውይይት በሥራ ላይ ጤናና ደህንነት ረቂቅ ፖሊሲ ዙሪያ በተቋሙ ውስጥ ካሉ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር በመወያየት ግብዓት ለማሰባሰብ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-የሚወጡ-ፖሊሲዎች-ጥራት-ያላቸውና&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን የብርሃን ጉዞ እየመራ ነው! 🇪🇹 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት 9 ወራት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የኃይል ማመንጨት አፈጻጸም አ
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን የብርሃን ጉዞ እየመራ ነው! 🇪🇹 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት 9 ወራት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የኃይል ማመንጨት አፈጻጸም አስመዝግቧል። የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ከማል አህመድ እንደገለጹት ግድቡ በዘጠኝ ወራት ውስጥ 13 ሺህ 778 ነጥብ 37 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት የዕቅዱን 95.7 በመቶ አሳክቷል! ይህ ስኬት በቁጥር ሲታይ፦ ✅ የ122% ብልጫ፦ የዘንድሮው የማመንጨት አቅም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ122 በመቶ ታላቅ ብልጫ አሳይቷል። (ባለፈው ዓመት 6 ሺህ 213 ጊጋ ዋት ሰዓት ነበር)። ✅ የ51% የሀገር ድርሻ፦ በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ እንደ ሀገር ከመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ብቻውን 51 በመቶ ድርሻ አለው! ✅ የተርባይኖች መጨመር፦ ለዚህ ከፍተኛ ስኬት ዋነኛው ምክንያት ወደ ሥራ የገቡ ተርባይኖች ቁጥር መጨመር ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ታላቁ-የኢትዮጵያ-ህዳሴ-ግድብ-የኢትዮጵያ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም

Yetewesesenu netboch bichemeru

⚡️ ለአስተማማኝ እና ጥራት ያለው የኃይል አቅርቦት ያልተቋረጠ ትጋት! 💡🇪🇹 በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ውስጥ የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝነት ለማሻሻል በርካታ ተግባራዊ ሥራዎች አከናውኗል። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ ሙሐመድ እንደገለጹት፣ በዚህ ወቅት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ማዘመን፣ የሠራተኞችን አቅም ማሳደግ እና መደበኛና ድንገተኛ የጥገና እና ፍተሻ ሥራዎችን በተስፋፋ መልኩ ማከናወን ተችሏል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ለአስተማማኝ-እና-ጥራት-ያለው-የኃይል-አቅ&lang=am

⚡️ ለአስተማማኝ እና ጥራት ያለው የኃይል አቅርቦት ያልተቋረጠ ትጋት! 💡🇪🇹 በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ውስጥ የኃይል አቅርቦትን አስተ
+7
⚡️ ለአስተማማኝ እና ጥራት ያለው የኃይል አቅርቦት ያልተቋረጠ ትጋት! 💡🇪🇹 በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ውስጥ የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝነት ለማሻሻል በርካታ ተግባራዊ ሥራዎች አከናውኗል። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ ሙሐመድ እንደገለጹት፣ በዚህ ወቅት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ማዘመን፣ የሠራተኞችን አቅም ማሳደግ እና መደበኛና ድንገተኛ የጥገና እና ፍተሻ ሥራዎችን በተስፋፋ መልኩ ማከናወን ተችሏል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ለአስተማማኝ-እና-ጥራት-ያለው-የኃይል-አቅ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በማበረታታት የውጭ ጥገኝነትን ለመቀነስ እየሰራ ነው ....…///…....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለዘርፉ የሚያስፈልጉ የቴክኖሎጂ ግብዓቶች በሀገር ውስጥ እንዲመረቱ በማበረታታት የውጭ ጥገኝነትን ለመቀነስ እየሰራ መሆኑን ገለጸ፡፡ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያዘጋጀውን የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ በአዲስ ዓለምአቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በመገኘት ጉብኝተዋል፡፡ በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኽኝ እንደገለጹት የጉብኝቱ ዓላማ የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች በሀገሪቱ እየተከናወኑ የሚገኙ የኢንዱስትሪ ልማት እንቅስቃሴዎችን በመረዳት ተቋሙ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስችለውን ግንዛቤ እንዲጨብጡ ለማድረግ ነው፡፡ በኤግዚቢሺኑ ላይ ምርታቸውን ያቀረቡ አምራች ኢንዱስትሪዎች ህልውናቸው የተመሰረተው በአስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ላይ በመሆኑ ተቋሙ ለኢንዱስትሪው ዕድገት አስፈላጊውን የኃይል አቅርቦትና ድጋፍ በማድረግ ረገድ ያለውን ከፍተኛ ሚናም ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ በበኩላቸው የሀገር ውስጥ ምርቶች በየዓመቱ በጥራትና በብዛት እያደጉ ለመምጣታቸው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አስተማማኝ መሆን ትልቁን ድርሻ እንደሚወስድ ገልጸዋል፡፡ እንደ ኢንጂነር ውድነህ ገለጻ ሀገሪቱ ቀደም ሲል ስታመርታቸው ከነበሩ ምርቶች በተጨማሪ ማዕድን ማቀነባበርን ጨምሮ ወደ ከባድ ኢንዱስትሪዎች የተሸጋገሩ ተቋማት መበራከታቸው እጅግ ከፍተኛ ኃይል የሚጠይቅ በመሆኑ ተቋሙ ይህንን ፍላጎት ለማሟላት በሰፊው እየሰራ ይገኛል። በሀገሪቱ እያደገ የመጣውን የኢንዱስትሪ ዕድገት ተከትሎ የኃይል አቅርቦት ጥያቄዎችን ለመመለስ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶች ተጠናቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ቀደም ሲል እስከ 80 በመቶ የሚሆነው የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት የግንባታ ግብዐቶች ከውጭ የሚገቡ የነበረ ሲሆን አሁን ግን በከፍተኛ ቮልቴጅ ደረጃ ኬብሎችን ጨምሮ ሌሎች ግብዓቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለማስቀረትና በራስ አቅም ለመመራት የሚያስችል ዕድል እየተፈጠረ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ተቋሙ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ ከባለሀብቶች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለዘርፉ የሚያስፈልጉ የቴክኖሎጂ ግብዓቶች በሃገር ውስጥ እንዲመረቱ በማበረታታት የውጭ ምንዛሬና ጥገኝነትን ለመቀነስ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል፡፡ በጉብኝቱ የተሳተፉ ሠራተኞች በ"ኢትዮጵያ ታምርት" የቀረቡ ምርቶች የኢነርጂና የኢንዱስትሪ ዘርፎች የማይነጣጠሉ መሆናቸውን የተገነዘቡበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ስጋቶችን መቆጣጠር ይገባል ተባለ ….....///…...... በዓለም ባንክ ፋይናንስ ተደርገው በሚሰሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፕራይም-1 ፕሮጀክቶች ላይ የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖ ስጋቶችን መቆጣጠር እንደሚገባ ተገለጸ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከዓለም ባንክ የኢትዮጵያ የአካባቢ እና ማህበራዊ ስጋት አስተዳደር ቡድን ጋር በመተባበር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከደቡብ ሱዳን ለተውጣጡ ባለሙያዎች በአካባቢ እና ማህበራዊ ስጋት አስተዳደር ዙሪያ በዩኒቨርስቲው ቅጥር ግቢ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል፡፡ በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ከፍተኛ ማህበራዊ ልማት ስፔሻሊስት ሚስተር ፓረታፐሪያ ጎሽ እንደገለጹት በፕሮጀክቶች ላይ ከማህበራዊና አካባቢያዊ ስጋት አስተዳደር ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ የባለሙያዎችን አቅም ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የባለሙያዎችን አቅም በማጎልበት በፕሮጀክቶች ውስጥ የሚያጋጥሙ የአካባቢ እና ማህበራዊ ስጋቶችን በመቆጣጠር ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን የሚያሟሉ እንዲሆኑ ሥልጠናው ትልቅ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ የሚከናወኑ የፕራይም-1 ፕሮጀክቶችን በመወከል የተገኙት አቶ እውነቱ ጌትነት እንደተናገሩት በዓለም ባንክ ፋይናንስ ተደርገው 15 የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመሮች እንደሚገነቡ ገልፀዋል፡፡    ፕሮጀክቶቹም የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖን በመቀነስ መልኩ በባንኩ የአካባቢ እና ማህበራዊ ጥበቃ መስፈርት መሠረት ግንባታቸውን ለማከናወን ለፕራይም ፕሮጀክቶች የተቀጠሩ የአካባቢ፣ የማህበራዊ እና ጤና እና ደህንነት ባለሙያዎች የአቅም ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ እንደተቋም የሚከናወኑ ሥራዎች ማህበረሰብ አቀፍ በመሆናቸው ሥልጠናው በፕሮጀክቶች ትግበራ ላይ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ይረዳል የሚል እምነት መኖሩንም ተናግረዋል፡፡ በተቋሙ የአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሪት ሜሮን ዮሐንስ በበኩላቸው የዓለም ባንክ ፋይናንስ በሚያደርገው ፕራይም -1 ኮምፖነት- 2 ስር ከሚገኙ 15 ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ፕሮጀክቶች ውስጥ ለ10 ፕሮጀክቶች የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖ ግምገማ እንዲሁም ለ 4 ፐሮጀክቶች የመልሶ ማስፈር መርሃ ግብር ጥናቶች ተጠናቀው በአበዳሪወ ይሁንታን በማግኘት በአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በኩል መጽደቻቸውን  አብራርተዋል፡፡ ቢሮው አሁን ላይ የ2 ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶችን የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖዎችን ግምገማ እና የመልሶ ማቋቋም ጥናቶችን እየተከታተለ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ በቀጣይም በኮፖነንት 3 ሥር ለሚገኙ  የጂኦተርማል ፕሮጀክቶች ጥናቶችን ለማስጠናት በዝግጅት ላይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በዓለም ባንክ መካከል ባለው የአካባቢያዊና ማህበራዊ የቁርጠኝነት ዕቅድ መሰረት 11 የአካባቢያዊ፣ የማህበራዊ እና የጤና ባለሙያዎች መቀጠራቸውን ያስታወሱት ወ/ሪት ሜሮን  ሠራተኞቹ ወደ ሥራ ከመግባታቸው በፊት አቅማቸውን ለማጎልበት ሥልጠናው መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡፡ ሥልጠናው በተቋሙ የተሰሩ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖ ግምገማ ሰነዶች ተግባራዊ በሚደረጉበት መንገድ እና በሥራ ላይ በሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች ዙሪያ ትኩረት አድርጎ ለቀጣዮች 5 ቀናት የሚሰጥ ይሆናል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

የቀደሙት አባቶቻንን የሀገራችንን ነፃነት ለማስጠበቅ መስዋዕትነት ከፍለዋል። በዱር በገደሉ ያቀጣጠሉት የነፃነት ፋና ዛሬም ለሀገራዊ ብልጽግናችን ትልቅ ጉልበት እንደሆነ እናምናለን። ትናንት አባቶቻችን
የቀደሙት አባቶቻንን የሀገራችንን ነፃነት ለማስጠበቅ መስዋዕትነት ከፍለዋል። በዱር በገደሉ ያቀጣጠሉት የነፃነት ፋና ዛሬም ለሀገራዊ ብልጽግናችን ትልቅ ጉልበት እንደሆነ እናምናለን። ትናንት አባቶቻችን በጠላት ላይ ድል ተቀዳጅተው ዳር ድንበሯ የተከበረች ሀገር እንዳስረከቡን ሁሉ እኛም ከአባቶቻችን የተረከብነውን ሀገራዊ አደራ በልማት ለማጽናትና መላ ኢትዮጵያን በታዳሽ ኃይል ብርሃን ለማድመቅ በቁርጠኝነት እየሰራን እንገኛለን። የአርበኞቻችን ጽናትና ተጋድሎ ለተቋማችን ግዙፍ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች መጠናከርና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥ ለምናደርገው ጥረት ትልቅ ስንቅ ነው። የጀግኖች አርበኞቻችን የድል ብርሃን በዛሬው የልማት ብርሃን ተደምሮ ለተሻለች ኢትዮጵያ በጋራ እንተጋለን። መላው የሀገራችን ሕዝቦች፣ የተቋማችን አመራሮችና ሠራተኞች፣ እንዲሁም ለባለድርሻና አጋር አካላት በሙሉ በድጋሜ እንኳን  ለአርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ። ወራሪዎችን ያሳፈረው አኩሪ ድል በድህነትና ጨለማ ላይም ይደገማል! ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ

በፕሮጀክቱ ዓለም አቀፍ የሥራ ቦታ ደህንነት እና ጤና ቀን ተከበረ ........///........ ​የዓለም የሥራ ደህንነት እና ጤና ቀን በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት “ጤናማ የሆነ ስነ-ልቦናዊ እና ማህበራዊ የሥራ አካባቢን ማረጋገጥ” በሚል ዓለም አቀፋዊ መሪ ቃል በድምቀት ተከብሯል። ​በዝግጅቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የሥራ ተቋራጩ ሠራተኞች የሥራ ቦታ ደህንነት እንዲከበር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። በበዓሉ ላይ አካላዊ፣ ሥነ-ልቦናዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች በሥራ ቦታ ደህንነት ላይ ያላቸውን ወሳኝ ሚና የሚያጎላ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ ተካሂዷል። የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራቱ ተሾመ እንደተናገሩት የሥራ ላይ ደህንነት በሥራ ቦታ መከበሩ የሠራተኛውን ግንዛቤ ለማሳደግና አደጋን ተከላክሎ ለመሥራት ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል። በፕሮጀክቱ ያለው የሥራ ቦታ ደህንነት መልካም ተሞክሮ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና እንደ አንድ ዐቢይ ተግባር ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው አረጋግጠዋል። ​የሥራ ተቋራጩ ዊ ቢዩልድ የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ሲልቪ ስቲፋኖ በበኩላቸው ለሰራተኞች ባስተላለፉት መልዕክት ኩባንያቸው ያለውን የሥራ ቦታ ደህንነት ባህል ለማስቀጠል ጽኑ ቁርጠኝነት እንዳለው ገልጸዋል። የሥራ ቦታ ደህንነት የኩባንያው ዋነኛ እሴት መሆኑን በመግለጽ የዊ ቢዩልድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መልዕክት በንባብ አቅርበዋል። ​በፕሮጀክቱ የአካባቢ እና ማህበራዊ እቅድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንደገለጹት የሠራተኞችን ጤና እና ደህንነት መጠበቅ ምርታማነትን ለማስቀጠል እና የፕሮጀክቱን ግቦች ለማሳካት መሰረት ነው። ደህንነቱ የተጠበቀ የሰው ኃይል በተፈጥሮው ምርታማ መሆኑን በመጥቀስ የሥራ ቦታ ደህንነት በሁሉም ደረጃዎች ቀዳሚ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባና የሁሉም አካላት ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል። ሚዛናዊ እና ውጤታማ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር ሥነ ልቦናዊ እና ማህበራዊ ደህንነት እንደ አካላዊ ደህንነት ሁሉ እኩል አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። በግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብሩ ላይ የተገኙ ሠራተኞች አካላዊ አደጋዎችን ከመከላከል ባለፈ ለሥራ አካባቢው አእምሯዊ እና ማህበራዊ ገጽታዎች ትኩረት መስጠት ስላለው አስፈላጊነት በመወያየት፣ አጠቃላይ የደህንነት አስተዳደር ስርዓትን ለማጠናከር በሚረዱ ሃሳቦች ላይ ተወያይተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

ሠራተኞች በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ላይ ያላቸውን አስተሳሰብና እውቀት ለማጎልበት እየተሰራ ነው ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘ
+9
ሠራተኞች በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ላይ ያላቸውን አስተሳሰብና እውቀት ለማጎልበት እየተሰራ ነው ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ለተውጣጡ የኦፕሬሽን ባለሙያዎች የዲጂታል መሣሪያዎችን የመጠቀም ልምምድንና እውቀትን (Digital Mindset and Literacy) ለማሳደግ ለአስር ቀናት ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ የዲጅታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ጽዮን በቀለ እንደገለጹት በተቋሙ ከተለዩ የለውጥ አጀንዳዎች መካከል አንዱ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በመሆኑ በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ሠራተኞች በዲጅታል ትራንስፎርሜሽን ላይ ያላቸው አስተሳሰብና እውቀት አነስተኛ መሆን ተቋሙ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶች በአግባቡ በመተግበር ውጤት ለማስመዝገብ አዳጋች እንዳደረገበት በጥናት መለየቱን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ለሥራ-ላይ-ደህንነትና-ጤና-ትኩረት-መስጠት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 22 ቀን 2018 ዓ.ም

ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በሙሉ የተቋማችን ግስጋሴና ስኬት በእናንተ ብርቱ ክንድና ትጋት ላይ የተመሠረተ ነው። ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን በሀገራችንና በመላው ዓለም በሚከበር
ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በሙሉ የተቋማችን ግስጋሴና ስኬት በእናንተ ብርቱ ክንድና ትጋት ላይ የተመሠረተ ነው። ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን በሀገራችንና በመላው ዓለም በሚከበርበት ዕለት በሥራ ላይ ሆናችሁ ለተቋማችንና ለሀገራችን ብርሃን ለመፈንጠቅ ለምታበረክቱት አስተዋጽኦ ምስጋናዬን እያቀረብኩ እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡ ላባችሁ ክብር ነው! ጥረታችሁም ለውጤታችን መሠረት በመሆኑ ዛሬም እንደ ትላንቱ ለሀገራዊ ዕድገታችን በጋራ እንቁም! መልካም የሠራተኞች ቀን በዓል! ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኢሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ

ለሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ …….///……… የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን "ጤናማ የሥነ-ልቦናና ማህበራዊ የሥራ አካባቢን እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል
+7
ለሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ …….///……… የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን "ጤናማ የሥነ-ልቦናና ማህበራዊ የሥራ አካባቢን እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ትናንት በውይይት ተከብሯል። በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ በውይይቱ መድረኩ መክፈቻ ላይ እንደገለፁት ሠራተኞች የደህንነትና የጤና ጥበቃ መመሪያዎችን ባለመከተላቸው ለተለያዩ የአካል ጉዳቶችና ለሕይወት ማጣት ሊጋለጡ ይችላሉ፡፡ በመሆኑም ሁሉም ሠራተኞች ለራሳቸውና ለሥራ ባልደረቦቻቸው ደህንነት ትኩረት በመስጠት ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ይኖርባቸዋል ብለዋል። በኮርፖሬት ፕላኒንግ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ኮርሳ ታሬሳ በበኩላቸው በሥራ ቦታ ከሥራ ይዘት ሁኔታና አደረጃጀት ጋር ተያይዞ የሚከሰት ከፍተኛ የሥራ ጫና፣ የሥራ መብዛት፣ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ለሥራ-ላይ-ደህንነትና-ጤና-ትኩረት-መስጠት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም