EEP Communication
الذهاب إلى القناة على Telegram
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication
تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 696 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 049 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 173 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 696 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 02 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 141، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 0، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 28.59%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.37% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 487 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 569 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“EEP Communication”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 03 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.
15 696
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+147 أيام
+14130 أيام
أرشيف المشاركات
15 696
ተመራቂዎች ችግር የሚያብራሩ ሳይሆን ለመፍትሔ የሚቆሙ መሆን እንዳለባቸው ተገለፀ
ተመራቂዎች በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ እና ለችግሮች በጋራ መፍትሔ በማስቀመጥ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳሰቡ።
ይህን መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ የኃይል ማመንጫዎች ማስተባበሪያ አንድ ዳይሬክተር አቶ አብዱ ይማም ናቸው።
ዳይሬክተሩ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ሲከታተሉ ቆይተው ለተመረቁ የጊቤ 1 እና 2 ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በወቅቱም ተቋሙ የያዘውን ርዕይና ተልዕኮ ለማሳካት ብቃት ያለው የሰው ኃይል እንደሚያስፈልገው ጠቁመው ከዚህ አኳያ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ ከዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ሠራተኞች ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን ትምህርታቸውን በሥራ ቦታቸው ሆነው እንዲከታተሉ በማድረግ ማስመረቅ መቻሉን አቶ አብዱ ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው የተቋሙን ሠራተኞች አቅም ለማሳደግ እያደረገ ላለው ጥረት እና ለተመራቂዎች ስኬት ላበረከተው አስተዋፅኦም ምስጋና አቅርበዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም በቀጣይ ሠራተኞችን ከማስተማር ባለፈ የኃይል ማመንጫዎችን የምርምር ማዕከል ለማድረግ የሚደረገው የጋራ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ተመራቂዎቹም ችግር የሚያብራሩ ሳይሆን ለመፍትሔ በጋራ በመቆም እና ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ለተሻለ የኃይል አቅርቦት ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ተወካይ እና የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶክተር አዳነ ወልደመድህን በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ሀገሪቱ የምትከተለውን የአረንጓዴና ዘላቂ ልማት ግብ እውን ለማድረግ የታዳሽ ኃይልን የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ እየሠራ ይገኛል።
ይህንን ስትራቴጂ መነሻ በማድረግ በዘርፉ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአብነት ያህልም ላለፉት አምስት ዓመታት ከሥራቸው ጎን ለጎን በፅናትና በቁርጠኝነት በኤሌክትሪካል እና ኮምፒውተር ኢንጅነሪንግ መስክ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው የተመረቁትን የጊቤ 1 እና 2 ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞችን ጠቅሰዋል።
ምርቃት የትምህርት ማብቂያ ሳይሆን የምርምር መጀመሪያ መሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር አዳነ ተመራቂዎች በታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂዎች ላይ የፈጠራና የማሻሻያ ሥራዎችን በማከናወን እንዲሁም አዳዲስ አሰራሮችን በማምጣት የሀገሪቱን የኃይል ሽፋን ማሳደግ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
የተፈጥሮ ታዳሽ ሀብት ወደ ኤሌክትሪክ ተቀይሮ ሀገር እንደሚያበራ ሁሉ ተመራቂዎችም ንድፈ-ሐሳባዊ እውቀቸውን ከሥራ ልምዳቸው ጋር በማቀናጀት ለሀገሪቱን ሁለንተናዊ ዕድገት ብርሃን ሰጪ መሆን እንዳለባቸው ዶ/ር አዳነ ገልጸዋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከዩኒቨርሲቲው የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ 3.84 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው የተቋሙ ሠራተኛ ሳሙኤል ንጉሴ የሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተወካይ ተቀብሏል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
15 696
ተመራቂዎች ችግር የሚያብራሩ ሳይሆን ለመፍትሔ የሚቆሙ መሆን እንዳለባቸው ተገለፀ
ተመራቂዎች በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ እና ለችግሮች በጋራ መፍትሔ በማስቀመጥ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳሰቡ።
ይህን መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ የኃይል ማመንጫዎች ማስተባበሪያ አንድ ዳይሬክተር አቶ አብዱ ይማም ናቸው።
ዳይሬክተሩ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ሲከታተሉ ቆይተው ለተመረቁ የጊቤ 1 እና 2 ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በወቅቱም ተቋሙ የያዘውን ርዕይና ተልዕኮ ለማሳካት ብቃት ያለው የሰው ኃይል እንደሚያስፈልገው ጠቁመው ከዚህ አኳያ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ ከዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ሠራተኞች ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን ትምህርታቸውን በሥራ ቦታቸው ሆነው እንዲከታተሉ በማድረግ ማስመረቅ መቻሉን አቶ አብዱ ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው የተቋሙን ሠራተኞች አቅም ለማሳደግ እያደረገ ላለው ጥረት እና ለተመራቂዎች ስኬት ላበረከተው አስተዋፅኦም ምስጋና አቅርበዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም በቀጣይ ሠራተኞችን ከማስተማር ባለፈ የኃይል ማመንጫዎችን የምርምር ማዕከል ለማድረግ የሚደረገው የጋራ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ተመራቂዎቹም ችግር የሚያብራሩ ሳይሆን ለመፍትሔ በጋራ በመቆም እና ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ለተሻለ የኃይል አቅርቦት ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ተወካይ እና የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶክተር አዳነ ወልደመድህን በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ሀገሪቱ የምትከተለውን የአረንጓዴና ዘላቂ ልማት ግብ እውን ለማድረግ የታዳሽ ኃይልን የትኩረት አቅጣጫው አድርጎ እየሠራ ይገኛል።
ይህንን ስትራቴጂ መነሻ በማድረግ በዘርፉ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአብነት ያህልም ላለፉት አምስት ዓመታት ከሥራቸው ጎን ለጎን በፅናትና በቁርጠኝነት በኤሌክትሪካል እና ኮምፒውተር ኢንጅነሪንግ መስክ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው የተመረቁትን የጊቤ 1 እና 2 ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞችን ጠቅሰዋል።
ምርቃት የትምህርት ማብቂያ ሳይሆን የምርምር መጀመሪያ መሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር አዳነ ተመራቂዎች በታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂዎች ላይ የፈጠራና የማሻሻያ ሥራዎችን በማከናወን እንዲሁም አዳዲስ አሰራሮችን በማምጣት የሀገሪቱን የኃይል ሽፋን ማሳደግ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
የተፈጥሮ ታዳሽ ሀብት ወደ ኤሌክትሪክ ተቀይሮ ሀገር እንደሚያበራ ሁሉ ተመራቂዎችም ንድፈ-ሐሳባዊ እውቀቸውን ከሥራ ልምዳቸው ጋር በማቀናጀት ለሀገሪቱን ሁለንተናዊ ዕድገት ብርሃን ሰጪ መሆን እንዳለባቸው ዶ/ር አዳነ ገልጸዋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከዩኒቨርሲቲው የኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ 3.84 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው የተቋሙ ሠራተኛ ሳሙኤል ንጉሴ የሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተወካይ ተቀብሏል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
15 696
በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የተቋሙ ሠራተኞች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ነው።
......///......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በመጀመሪያ ዲግሪ ያስተማራቸውን 47 የጊቤ አንድ እና ሁለት ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሠራተኞች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በጊቤ አንድ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግቢ ውስጥ እየተከናወነ ይገኛል።
ከተመራቂዎቹ መካከል 29 የሚሆኑት ከጊቤ አንድ፣ ዘጠኝ ከጊቤ ሁለት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ እንዲሁም 9 ደግሞ ከደቡብ ምዕራብ ሪጅን የተውጣጡ ሲሆኑ ከአጠቃላይ ተመራቂዎች ውስጥ 11 ሴቶች ናቸው።
ዩኒቨርሲቲው ሠራተኞችን ሲያስመርቅ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን የዛሬ ተመራቂ ሠራተኞች በኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጅነሪንግ የትምህርት መስክ ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው ትምህርታቸውን በተከታታይ የትምህርት ፕሮግራም ለአምስት ዓመታት ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ የኃይል ማመንጫዎች ማስተባበሪያ አንድ ዳይሬክተር አቶ አብዱ ይማም፣ የዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ተወካይ እና የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር አዳነ ወ/መድህን (ዶ/ር)፣ የጣቢያዎቹና የሪጅኑ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው የሴኔት አባላት፣ የተመራቂ ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ በቦታው ተገኝቶ የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱን እየተከታተለ የሚገኝ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን በቀጣይ የሚያደርስ ይሆናል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
15 696
ተቋሙ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ያከናወናቸው የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራዎች ዘመን ተሻጋሪ መሆናቸውን የዞኖቹ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ገለፁ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ያከናወናቸው የክረምት የችግኝ ተከላ፣ የትምህርት ቤት እና የአቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታ እንዲሁም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ሥራዎች ዘመን ተሻጋሪና በትውልድ ቅብብሎሽ የሚታወሱ መሆናቸውን የአሪ እና የደቡብ ኦሞ ዞኖች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ገልጸዋል።
በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር በሁለቱም ዞኖች ሰባት ትምህርት ቤቶችን እና ሰባት የአቅመ-ደካሞች መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓት የተከናወነ ሲሆን በተጨማሪም ለ120 የገንዘብ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍና የችግኝ የመትከል ስራ ተከናውኗል።
የአሪ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ገረመው ኃይሌ እንደገለፁት በአካባቢው ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶች ባለመኖራቸው ተማሪዎች በልጅነት ዘመናቸው በቤት ውስጥ ለመዋል ይገደዱ ስለነበር በእድገታቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሲያሳድር ቆይቷል።
ተቋሙ ከመደበኛ የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታ ጎን ለጎን ያከናወናቸው የበጎ ፈቃድና የአረንጓዴ አሻራ ሥራዎች ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በተጨባጭ የተወጣበት መሆኑን ያስረዱት ምክትል አስተዳዳሪው በተለይም የተደረገው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተማሪዎች ያለምንም ችግር ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የሚያስችልና የትምህርት ጥራትን የሚያሰፋ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በተመሳሳይ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ተቋሙ በማሊ ወረዳ ሊሞ ጌንቶ ቀበሌ ያከናወናቸው የትምህርት ቤትና የመኖሪያ ቤት ግንባታዎች እንዲሁም የቁሳቁስ ድጋፎች ዘመን የማይሽራቸው መሆናቸውን ገልፀዋል።
አቶ ማዕከል አክለውም ዝቅተኛው የማኅበረሰብ ክፍል የዕለት ፍጆታውን ለማሟላት በሚቸገርበት ወቅት ለትምህርት ቁሳቁስ የሚወጣው ወጪ ተጨማሪ ከባድ ጫና እንደሚፈጥር አብራርተዋል።
በመሆኑም የተደረገው ድጋፍ የቤተሰቦችን የኢኮኖሚ ሸክም በማቃለል ወላጆች ትኩረታቸውን ወደ መተዳደሪያቸው እንዲያደርጉ ዕድል እንደሚፈጥር ያስገነዘቡት ዋና አስተዳዳሪው ዛሬ ድጋፍ አግኝተው የሚማሩ ሕፃናት ነገ ሀገርን የሚረከቡ ብቁ ዜጎችና መሪዎች እንደሚሆኑ ጠቁመው እንቅስቃሴው የትውልድ ግንባታ መሠረት መሆኑን ገልፀዋል።
በመጨረሻም የሥራ ኃላፊዎቹ ተቋሙ ያከናወናቸው ሥራዎች በማኅበረሰቡ እና በመንግሥት መካከል የመረዳዳት የወንድማማችነት እና የባለቤትነት ስሜት እንዲጎለብት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን በመግለጽ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
15 696
+9
የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ አመራር አባላት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ
በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን "በጎነት ለኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ባለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ እና በደቡብ ኦሞ ዞኖች ተገኝቶ ችግኝ ተክሏል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት ተቋሙ የሚያከናውናቸው የማኅበራዊ ኃላፊነት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና የአረንጓዴ አሻራ ሥራዎች ብሔራዊ አንድነትንና ወንድማማችነትን ለማጠናከር ትልቅ ድርሻ አላቸው።
በሁለቱ ዞኖች የተከናወኑት የቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፎች ተቋሙን ከማስተዋወቅ ባሻገር ነገ የተቋሙ ተረካቢ በሚሆኑ ተማሪዎችና በህብረተሰቡ ዘንድ የባለቤትነት ስሜት የሚፈጥሩ መሆኑን ገልጸው በጎ አድራጎቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙ-ከፍተኛ-የሥራ-አመራር-አባላት-በደ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
15 696
+9
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኣሪ ዞን ያከናወናቸው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎች በምስል
.....///......
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
15 696
+9
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኣሪ ዞን ያከናወናቸው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በምስል
.....///......
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
15 696
+6
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኣሪ ዞን ያከናወናቸው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎች በምስል
.....///......
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
15 696
ተቋሙ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የልማትና የበጎ አድራጎት ሥራዎችን አስጀመረ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣትና የልማት ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር አካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በአሪ ዞን ሦስት ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶችን እና አራት የአቅመ-ደካማ መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ባደረጉት ንግግር ተቋሙ ከኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግንባታ ጎን ለጎን የኃይል ማመንጫዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሚገኙበት አካባቢ የሚኖሩ ማህበረሰቦችን ቀጥተኛ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶችን እያከናወነ ይገኛል።
ቀደም ሲል በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ከተማ ከ28 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን ወጪ ለስድስት አቅመ-ደካማ ዜጎች ደረጃው የጠበቀ ባለአንድ ወለል ህንፃ ገንብቶ ለማስረከብ በዝግጅት ላይ እንደሚገኝና ለ250 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ማከፋፈሉን እንደማሳያ ጠቅሰዋል።
በዛሬው ዕለትም በአሪ ዞን ጆንካ ከተማ በተካሄደው መሰረት ድንጋይ በተጨማሪ ለ60 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶች ድጋፍና የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርም ተካሂዷል።
እነዚህ የልማት ሥራዎች ብሔራዊ አንድነትን፣ ወንድማማችነትንና አካታችነትን ለማጠናከር ያለሙ መሆናቸውን የገለጹት ኢንጂነር አሸብር በአሪ ዞን የተጀመረው የበጎ አገልግሎት መርሃ ግብር በተመሳሳይ በነገው ዕለት በደቡብ ኦሞ ዞንም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
15 696
+9
በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ጂንካ ገብቷል
.....///......
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ ከፍተኛ የተቋሙ ልዑክ የክረምት በጎ ሥራውችን እና የአረንጓዷ አሻራን ለማስመር ጂንካ ከተማ ገብቷል።
የልዑካን ቡድኑ ጂንካ ሲገባ የአሪ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ገረመው ኃይሌን ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በጂንካ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ልዑኩ ዛሬና ነገ በሚኖረው ቆይታ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ እና ደቡብ ኦሞ ዞኖች ደረጃቸውን የጠበቁ የመዋለ ህፃናት ትምህርት ቤት እና የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥ፣ የ2018 የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ማካሄድ፣ ከአሪ ዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የጋራ ውይይት፣ ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ እና የደም ልገሳ ፕሮግራሞች እንደሚከናወኑ ይጠበቃል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
