fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 553 مشترک است و جایگاه 8 406 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 161 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 553 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 19 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -3 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -5 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 26.69% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.00% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 150 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 332 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 20 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 553
مشترکین
-524 ساعت
+97 روز
-330 روز
آرشیو پست ها
photo content
+9

photo content

የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ስጋቶችን መቆጣጠር ይገባል ተባለ ….....///…...... በዓለም ባንክ ፋይናንስ ተደርገው በሚሰሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፕራይም-1 ፕሮጀክቶች ላይ የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖ ስጋቶችን መቆጣጠር እንደሚገባ ተገለጸ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከዓለም ባንክ የኢትዮጵያ የአካባቢ እና ማህበራዊ ስጋት አስተዳደር ቡድን ጋር በመተባበር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከደቡብ ሱዳን ለተውጣጡ ባለሙያዎች በአካባቢ እና ማህበራዊ ስጋት አስተዳደር ዙሪያ በዩኒቨርስቲው ቅጥር ግቢ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል፡፡ በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ከፍተኛ ማህበራዊ ልማት ስፔሻሊስት ሚስተር ፓረታፐሪያ ጎሽ እንደገለጹት በፕሮጀክቶች ላይ ከማህበራዊና አካባቢያዊ ስጋት አስተዳደር ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ የባለሙያዎችን አቅም ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የባለሙያዎችን አቅም በማጎልበት በፕሮጀክቶች ውስጥ የሚያጋጥሙ የአካባቢ እና ማህበራዊ ስጋቶችን በመቆጣጠር ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን የሚያሟሉ እንዲሆኑ ሥልጠናው ትልቅ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ የሚከናወኑ የፕራይም-1 ፕሮጀክቶችን በመወከል የተገኙት አቶ እውነቱ ጌትነት እንደተናገሩት በዓለም ባንክ ፋይናንስ ተደርገው 15 የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመሮች እንደሚገነቡ ገልፀዋል፡፡    ፕሮጀክቶቹም የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖን በመቀነስ መልኩ በባንኩ የአካባቢ እና ማህበራዊ ጥበቃ መስፈርት መሠረት ግንባታቸውን ለማከናወን ለፕራይም ፕሮጀክቶች የተቀጠሩ የአካባቢ፣ የማህበራዊ እና ጤና እና ደህንነት ባለሙያዎች የአቅም ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ እንደተቋም የሚከናወኑ ሥራዎች ማህበረሰብ አቀፍ በመሆናቸው ሥልጠናው በፕሮጀክቶች ትግበራ ላይ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ይረዳል የሚል እምነት መኖሩንም ተናግረዋል፡፡ በተቋሙ የአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሪት ሜሮን ዮሐንስ በበኩላቸው የዓለም ባንክ ፋይናንስ በሚያደርገው ፕራይም -1 ኮምፖነት- 2 ስር ከሚገኙ 15 ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ፕሮጀክቶች ውስጥ ለ10 ፕሮጀክቶች የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖ ግምገማ እንዲሁም ለ 4 ፐሮጀክቶች የመልሶ ማስፈር መርሃ ግብር ጥናቶች ተጠናቀው በአበዳሪወ ይሁንታን በማግኘት በአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በኩል መጽደቻቸውን  አብራርተዋል፡፡ ቢሮው አሁን ላይ የ2 ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶችን የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖዎችን ግምገማ እና የመልሶ ማቋቋም ጥናቶችን እየተከታተለ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ በቀጣይም በኮፖነንት 3 ሥር ለሚገኙ  የጂኦተርማል ፕሮጀክቶች ጥናቶችን ለማስጠናት በዝግጅት ላይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በዓለም ባንክ መካከል ባለው የአካባቢያዊና ማህበራዊ የቁርጠኝነት ዕቅድ መሰረት 11 የአካባቢያዊ፣ የማህበራዊ እና የጤና ባለሙያዎች መቀጠራቸውን ያስታወሱት ወ/ሪት ሜሮን  ሠራተኞቹ ወደ ሥራ ከመግባታቸው በፊት አቅማቸውን ለማጎልበት ሥልጠናው መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡፡ ሥልጠናው በተቋሙ የተሰሩ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖ ግምገማ ሰነዶች ተግባራዊ በሚደረጉበት መንገድ እና በሥራ ላይ በሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች ዙሪያ ትኩረት አድርጎ ለቀጣዮች 5 ቀናት የሚሰጥ ይሆናል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

የቀደሙት አባቶቻንን የሀገራችንን ነፃነት ለማስጠበቅ መስዋዕትነት ከፍለዋል። በዱር በገደሉ ያቀጣጠሉት የነፃነት ፋና ዛሬም ለሀገራዊ ብልጽግናችን ትልቅ ጉልበት እንደሆነ እናምናለን። ትናንት አባቶቻችን
የቀደሙት አባቶቻንን የሀገራችንን ነፃነት ለማስጠበቅ መስዋዕትነት ከፍለዋል። በዱር በገደሉ ያቀጣጠሉት የነፃነት ፋና ዛሬም ለሀገራዊ ብልጽግናችን ትልቅ ጉልበት እንደሆነ እናምናለን። ትናንት አባቶቻችን በጠላት ላይ ድል ተቀዳጅተው ዳር ድንበሯ የተከበረች ሀገር እንዳስረከቡን ሁሉ እኛም ከአባቶቻችን የተረከብነውን ሀገራዊ አደራ በልማት ለማጽናትና መላ ኢትዮጵያን በታዳሽ ኃይል ብርሃን ለማድመቅ በቁርጠኝነት እየሰራን እንገኛለን። የአርበኞቻችን ጽናትና ተጋድሎ ለተቋማችን ግዙፍ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች መጠናከርና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥ ለምናደርገው ጥረት ትልቅ ስንቅ ነው። የጀግኖች አርበኞቻችን የድል ብርሃን በዛሬው የልማት ብርሃን ተደምሮ ለተሻለች ኢትዮጵያ በጋራ እንተጋለን። መላው የሀገራችን ሕዝቦች፣ የተቋማችን አመራሮችና ሠራተኞች፣ እንዲሁም ለባለድርሻና አጋር አካላት በሙሉ በድጋሜ እንኳን  ለአርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ። ወራሪዎችን ያሳፈረው አኩሪ ድል በድህነትና ጨለማ ላይም ይደገማል! ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ

በፕሮጀክቱ ዓለም አቀፍ የሥራ ቦታ ደህንነት እና ጤና ቀን ተከበረ ........///........ ​የዓለም የሥራ ደህንነት እና ጤና ቀን በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት “ጤናማ የሆነ ስነ-ልቦናዊ እና ማህበራዊ የሥራ አካባቢን ማረጋገጥ” በሚል ዓለም አቀፋዊ መሪ ቃል በድምቀት ተከብሯል። ​በዝግጅቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የሥራ ተቋራጩ ሠራተኞች የሥራ ቦታ ደህንነት እንዲከበር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። በበዓሉ ላይ አካላዊ፣ ሥነ-ልቦናዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች በሥራ ቦታ ደህንነት ላይ ያላቸውን ወሳኝ ሚና የሚያጎላ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ ተካሂዷል። የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራቱ ተሾመ እንደተናገሩት የሥራ ላይ ደህንነት በሥራ ቦታ መከበሩ የሠራተኛውን ግንዛቤ ለማሳደግና አደጋን ተከላክሎ ለመሥራት ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል። በፕሮጀክቱ ያለው የሥራ ቦታ ደህንነት መልካም ተሞክሮ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና እንደ አንድ ዐቢይ ተግባር ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው አረጋግጠዋል። ​የሥራ ተቋራጩ ዊ ቢዩልድ የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ሲልቪ ስቲፋኖ በበኩላቸው ለሰራተኞች ባስተላለፉት መልዕክት ኩባንያቸው ያለውን የሥራ ቦታ ደህንነት ባህል ለማስቀጠል ጽኑ ቁርጠኝነት እንዳለው ገልጸዋል። የሥራ ቦታ ደህንነት የኩባንያው ዋነኛ እሴት መሆኑን በመግለጽ የዊ ቢዩልድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መልዕክት በንባብ አቅርበዋል። ​በፕሮጀክቱ የአካባቢ እና ማህበራዊ እቅድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንደገለጹት የሠራተኞችን ጤና እና ደህንነት መጠበቅ ምርታማነትን ለማስቀጠል እና የፕሮጀክቱን ግቦች ለማሳካት መሰረት ነው። ደህንነቱ የተጠበቀ የሰው ኃይል በተፈጥሮው ምርታማ መሆኑን በመጥቀስ የሥራ ቦታ ደህንነት በሁሉም ደረጃዎች ቀዳሚ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባና የሁሉም አካላት ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል። ሚዛናዊ እና ውጤታማ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር ሥነ ልቦናዊ እና ማህበራዊ ደህንነት እንደ አካላዊ ደህንነት ሁሉ እኩል አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። በግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብሩ ላይ የተገኙ ሠራተኞች አካላዊ አደጋዎችን ከመከላከል ባለፈ ለሥራ አካባቢው አእምሯዊ እና ማህበራዊ ገጽታዎች ትኩረት መስጠት ስላለው አስፈላጊነት በመወያየት፣ አጠቃላይ የደህንነት አስተዳደር ስርዓትን ለማጠናከር በሚረዱ ሃሳቦች ላይ ተወያይተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

ሠራተኞች በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ላይ ያላቸውን አስተሳሰብና እውቀት ለማጎልበት እየተሰራ ነው ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘ
+9
ሠራተኞች በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ላይ ያላቸውን አስተሳሰብና እውቀት ለማጎልበት እየተሰራ ነው ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ለተውጣጡ የኦፕሬሽን ባለሙያዎች የዲጂታል መሣሪያዎችን የመጠቀም ልምምድንና እውቀትን (Digital Mindset and Literacy) ለማሳደግ ለአስር ቀናት ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ የዲጅታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ጽዮን በቀለ እንደገለጹት በተቋሙ ከተለዩ የለውጥ አጀንዳዎች መካከል አንዱ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በመሆኑ በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ሠራተኞች በዲጅታል ትራንስፎርሜሽን ላይ ያላቸው አስተሳሰብና እውቀት አነስተኛ መሆን ተቋሙ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶች በአግባቡ በመተግበር ውጤት ለማስመዝገብ አዳጋች እንዳደረገበት በጥናት መለየቱን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ለሥራ-ላይ-ደህንነትና-ጤና-ትኩረት-መስጠት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 22 ቀን 2018 ዓ.ም

ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በሙሉ የተቋማችን ግስጋሴና ስኬት በእናንተ ብርቱ ክንድና ትጋት ላይ የተመሠረተ ነው። ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን በሀገራችንና በመላው ዓለም በሚከበር
ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በሙሉ የተቋማችን ግስጋሴና ስኬት በእናንተ ብርቱ ክንድና ትጋት ላይ የተመሠረተ ነው። ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን በሀገራችንና በመላው ዓለም በሚከበርበት ዕለት በሥራ ላይ ሆናችሁ ለተቋማችንና ለሀገራችን ብርሃን ለመፈንጠቅ ለምታበረክቱት አስተዋጽኦ ምስጋናዬን እያቀረብኩ እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡ ላባችሁ ክብር ነው! ጥረታችሁም ለውጤታችን መሠረት በመሆኑ ዛሬም እንደ ትላንቱ ለሀገራዊ ዕድገታችን በጋራ እንቁም! መልካም የሠራተኞች ቀን በዓል! ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኢሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ

ለሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ …….///……… የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን "ጤናማ የሥነ-ልቦናና ማህበራዊ የሥራ አካባቢን እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል
+7
ለሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ …….///……… የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን "ጤናማ የሥነ-ልቦናና ማህበራዊ የሥራ አካባቢን እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ትናንት በውይይት ተከብሯል። በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ በውይይቱ መድረኩ መክፈቻ ላይ እንደገለፁት ሠራተኞች የደህንነትና የጤና ጥበቃ መመሪያዎችን ባለመከተላቸው ለተለያዩ የአካል ጉዳቶችና ለሕይወት ማጣት ሊጋለጡ ይችላሉ፡፡ በመሆኑም ሁሉም ሠራተኞች ለራሳቸውና ለሥራ ባልደረቦቻቸው ደህንነት ትኩረት በመስጠት ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ይኖርባቸዋል ብለዋል። በኮርፖሬት ፕላኒንግ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ኮርሳ ታሬሳ በበኩላቸው በሥራ ቦታ ከሥራ ይዘት ሁኔታና አደረጃጀት ጋር ተያይዞ የሚከሰት ከፍተኛ የሥራ ጫና፣ የሥራ መብዛት፣ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ለሥራ-ላይ-ደህንነትና-ጤና-ትኩረት-መስጠት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም

ግንባታውን በበጀት ዓመቱ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …….///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በደሴ ከተማ እያስገነባ የሚገኘውን የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት እስከ ሰ
+4
ግንባታውን በበጀት ዓመቱ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …….///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በደሴ ከተማ እያስገነባ የሚገኘውን የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ለማጠናቀቅ እየሰራ መሆኑን በተቋሙ የኢንጂነሪንግ እና ኮንስትራክሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ከፈለኝ እንደገለፁት ተቋሙ ለስድስት አቅመ ደካማ አባወራዎች መኖሪያ የሚውል ባለ አንድ ፎቅ (ጂ+1) ህንፃ በ28 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ወጪ እያስገነባ ይገኛል። መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረውን የቤት ግንባታ የመሠረት ሥራ በማጠናቀቅ ኮለኖችን የማቆም ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በግንባታው ሂደት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተው ወቅታዊ የነዳጅ እጥረት የግንባታ ግብአቶችን ለማጓጓዝ ተግዳሮት የፈጠረ መሆኑን የገለፁት አቶ ቴዎድሮስ የተለያዩ የመፍትሔ እርምጃዎችን በመውሰድ እስከ በጀት ዓመቱ መጠናቀቂያ ድረስ ቤቶቹን ገንብቶ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ተቋሙ ከተሰጠው ተልዕኮ ባሻገር በመላ ሀገሪቱ የማህበራዊ አገልግሎት ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም

ፓርኩ ያልተቆራረጠ ኃይል እያገኘ መሆኑን ገለፀ ………///……… የደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ ያልተቆራረጠ የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኘ መሆኑን አስታወቀ። የፓርኩ ስራ አስኪያጅ አቶ የሺጥላ ሙሉጌታ እ
+5
ፓርኩ ያልተቆራረጠ ኃይል እያገኘ መሆኑን ገለፀ ………///……… የደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ ያልተቆራረጠ የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኘ መሆኑን አስታወቀ። የፓርኩ ስራ አስኪያጅ አቶ የሺጥላ ሙሉጌታ እንደገለፁት ያልተቆራረጠ የኃይል አቅርቦት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርታቸውን ለተጠቃሚው ለማቅረብ በእጅጉ አግዟቸዋል። በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚገኘው የሶላር ፓነል አምራች ኩባንያ በደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ ሥራ ለመጀመር የቦታ መረጣ ማከናወኑን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ኩባንያው እስከ 40 ሜጋ ዋት ኃይል ሊጠቀም እንደሚችል ጠቁመዋል። በቀጣይም በርካታ አምራች ኩባንያዎች በኢንዱስትሪ ፓርኩ ሥራ ለመጀመር ፍላጎት እያሳዩ መሆኑን ገልፀው ለዚህም በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። የደብረብርሃን ቁጥር 2 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳኜ ይታገሱ በበኩላቸው ጣቢያው 33 እና 15 ኪሎ ቮልት አቅም ባላቸው 15 ወጪ መስመሮች ለኢንዱስትሪዎች፣ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፓርኩ-ያልተቆራረጠ-ኃይል-እያገኘ-መሆኑን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን እየተከበረ ይገኛል …….///……… የዘንድሮው የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን "ጤናማ የሥነ-ልቦናና ማህበራዊ የሥራ አካባቢን እናረ
+5
በተቋሙ የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን እየተከበረ ይገኛል …….///……… የዘንድሮው የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን "ጤናማ የሥነ-ልቦናና ማህበራዊ የሥራ አካባቢን እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል በተቋም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት በውይይት እየተከበረ በሚገኘው የሥራ ደህንነትና ጤና ቀን በዋናነት በሥራ ገበታ ላይ እያሉ በተለያዩ አደጋዎች ሕይወታቸውን ላጡና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ሠራተኞች መታሰቢያ እንዲሆን ታስቦ የተሰናዳ ነው። ማንኛውም ሠራተኛ የዕለት ተግባሩን አከናውኖ ወደ ቤቱ በሠላምና በጤና የመመለስ ሙሉ መብት ቢኖረውም አሁንም ድረስ የሥራ ቦታዎች ላይ ተግዳሮቶች እንደሚታዩ በመድረኩ ተገልጿል። በተለይም ደህንነቱና ጤንነቱ ያልተጠበቀ የሥራ አካባቢ፣ የእውቀትና የክህሎት ክፍተት እንዲሁም ደካማ የሙያ ደህንነት አጠባበቅ ባህል ለሠራተኞች ጤና ጉድለት፣ ለአካል ጉዳትና ለሞት መጋለጥ በምክንያትነት ተጠቃሽ ናቸው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-የዓለም-አቀፍ-የሥራ-ላይ-ደህንነት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

ከሚያዚያ 30 በፊት ሀብታቸውን ያላስመዘግቡ የተቋሙ ሠራተኞች ቅጣት ይጠብቃቸዋል ‎........///…….. ‎እስከ ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ የተቋሙ ሠራተኞች ለቅ
ከሚያዚያ 30 በፊት ሀብታቸውን ያላስመዘግቡ የተቋሙ ሠራተኞች ቅጣት ይጠብቃቸዋል ‎........///…….. ‎እስከ ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ የተቋሙ ሠራተኞች ለቅጣት የሚዳረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታትያ መምሪያ ገለጸ። ‎ ‎በመምሪያው የሙስና ተጋላጭነትና ሥልጠና ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግሥቱ አባይነህ እንደገለጹት በሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 መሠረት ሁሉም የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ሀብታቸውን የማስመዝገብ ግዴታ አለባቸው። ‎ ‎ሠራተኛው የራሱን እና የትዳር ጓደኛውን እንዲሁም ከ18 ዓመት በታች የሆነ ልጁን ጨምሮ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረት፣ የገቢ ምንጭና ዕዳ ማስመዝገብ ይኖርበታል ብለዋል። ‎ ‎ሆኖም በውርስ የተገኘ የጋራ ንብረት፣ የቤት ዕቃዎች፣ የግል መገልገያዎችና የጡረታ ገቢ በአዋጁ ከምዝገባ ነጻ መሆናቸውን አብራርተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከሚያዚያ-30-በፊት-ሀብታቸውን-ያላስመዘግቡ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ በተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ላይ ከተናገሯቸው ታሪካዊ ስኬቶችና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል:- ዋና ዋና ስኬቶች 1. የኃይል ማመንጨት አቅም ዕድገት፦ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ኩራት የሆነው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ፣ የአይሻ 2 እና የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች በስኬት ተጠናቅቀው ወደ ሥራ በመግባታቸው የሀገሪቱ የኃይል ማምረት አቅም ከ 9,730 ሜጋዋት በላይ ደርሷል። 2. የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫፕሮጀክት፦ ግዙፉ የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። 3. የፋይናንስ ስኬታማነት፦ ተቋሙ ካለበት ከፍተኛ የዕዳ ጫና ወጥቶ ወደ "ምንዳ" ተሸጋግሯል። የሀገር ውስጥ ዕዳ ወደ መንግሥት መዛወሩ፣ አዳዲስ ማመንጫዎች ሥራ መጀመራቸውና የኢነርጂ ምርት መጨመሩ፣ የታሪፍ ማሻሻያ መደረጉ እና የዳታ ማይኒንግ ሽያጭ በዶላር መከናወኑ የተቋሙን ገቢ አሳድጎታል። ይህም ደግሞ እንደ ኮይሻ እና አይሻ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በራስ የፋይናንስ አቅም እንዲገነቡ አስችሏል። የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች 1. የፕሮጀክት መዘግየት ባህልን መቅረፍ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት ማጠናቀቅ የተቋሙ ዋነኛ ባህል ሊሆን ይገባል። አላስፈላጊ ወጪንና የሥራ መጓተትን ለማስቀረት፣ በአሠራርና በአመለካከት ረገድ ራስን ወደ ውስጥ መመልከትና መለወጥ ያስፈልጋል። 2. የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞ "የተቋሙ አምባሳደሮች ሆኖ መስራት ይጠበቃል በየክልሉ (ሪጅን) የምትገኙ አመራሮችና ሠራተኞች የተቋሙ አምባሳደሮች ናችሁ። በተለይ ከመስተዳድር አካላት ጋር በመቀናጀት የተቋሙን መሠረተ ልማት ከጥቃት የመከላከልና የተቋሙን ጥቅም የማስከበር ኃላፊነታችሁን በላቀ ሁኔታ እንድትወጡ አደራ እላለሁ። 3. የስትራቴጂካዊ ዕቅድ ቀጣይነት ከ2016-2018 ዓ.ም በመተግበር ላይ ያለው የሦስት ዓመት የግሪድ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በዚህ ዓመት ቢጠናቀቅም የጎደሉትን በመሙላትና አዳዲስ ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ እንዲሁም ተቋማዊ ሁኔታዎችን በማካተት በቀጣይም መሪ ዕቅድ ሆኖ ያገለግላል። 4. የኢነርጂ ሽግግርና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EV) ዓለም አቀፍ የነዳጅ እጥረት ተፅዕኖ ለመቋቋም ነዳጅን በቁጠባ መጠቀምና ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መሸጋገር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። በተለይ ተቋማችን የኃይል አምራች እንደመሆኑ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በስፋት በመጠቀም ለሌሎች ተቋማት አርአያ መሆን ይጠበቅበታል። በዚህ ጉዳይ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። 5. ለብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ ኩነቶች ዝግጁ መሆን ሀገራዊ ምርጫ፦ በቴክኖሎጂ ለሚደገፈው ምርጫ አስተማማኝና ያልተቋረጠ የኃይል አቅርቦት ማረጋገጥ፣ ኮፕ 32 (COP32)፦ በ2020 ዓ.ም እስከ 100 ሺህ ሰዎች ይታደሙበታል ተብሎ በሚጠበቀውና ሀገራችን በምታስተናግደው ዓለም አቀፍ ጉባዔ ላይ የተቋማችን አረንጓዴ ኢነርጂ አሻራችን የማሳየት ከፍተኛ ኃላፊነት አለበት። ለእነዚህ ሥራዎች ከወዲሁ አሮጌ መስመሮችን የማደስና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ሥራ በከፍተኛ ፍጥነት መከናወን ይኖርበታል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030፦ መንግሥት ላቀደው የዲጂታል ኢትዮጵያ ስኬት ተቋማችን የጀርባ አጥንት በመሆኑ ሌት ተቀን መስራት ይጠበቅብናል። 6. የእውቅናና ሽልማት ሥርዓት በበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ ላይ በሥራቸው የተሻለ አፈጻጸም ላሳዩ የተቋማችን አመራሮችና ሠራተኞች ተገቢው የእውቅናና የሽልማት ሥርዓት ተግባራዊ ይደረጋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የፕሮጀክት ክትትል የሚታይ ለውጥ ሊያመጣ ይገባል - ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ‎.......///....... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቶች ክትትል የሚታይ የአፈፃፀም ለውጥ እንዲኖራቸው የክትትል ሥርዓቱን ማጠናከር እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለጹ። ‎ ‎ዋና ሥራ አስፈጻሚው በተቋሙ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት በፕሮጀክት ክትትል ረገድ ከሪፖርት ያለፈ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ክትትልና ድጋፍ የሚደረግላቸው ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ፣ በጀትና የጥራት ደረጃ እንደሚጠናቀቁ ሁሉ የተቋሙ ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ወደዚህ ደረጃ ማምጣት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ ‎ ‎የተቋሙ ከፍተኛው በጀት የሚውለው ለፕሮጀክቶች በመሆኑ የኃይል መሠረተ ልማቶች ፕሮጀክቶች ላይ የሚታይ ለውጥ ለማስመዝገብ የክትትልና የድጋፍ ሥርዓቱን በማጠናከር ሁሉም ኃላፊነቱን በእኔነት ስሜት መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

‎ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተገኙት ውጤቶች ተቋሙን ከዕዳ ወደ ምንዳ ያሸጋገሩ ናቸው - ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ‎.......///....... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ሥራዎች እና የተገኙት ውጤቶች ተቋሙን ከዕዳ ወደ ምንዳ ያሸጋገሩ መሆናቸውን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ። ‎ ‎ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በተቋሙ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የተቋሙ ቦርድና ሥራ አመራር ባደረገው ስትራቴጂካዊ አመራርና መንግስት በሰጠው ትኩረት በበጀት ዓመቱ የተሻለ ውጤት ተመዝግቧል። ‎ ‎በዚህም የተቋሙ የፋይናንስ ቁመና ላይ መሠረታዊ በሆነ መልኩ አዎንታዊ ለውጥ መታየቱን አብራርተዋል። ‎ ‎ይህም በፋይናንስ እጥረት ምክንያት የቆሙ ፕሮጀክቶችን ግንባታ በራስ አቅም ወደ ሥራ ለማስገባት የጎላ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል። ‎ ‎የኦፕሬሽን ባለሙያዎች በማይመችና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው እንደሚሰሩ ያስታወሱት ኢንጂነር አሸብር ሥራዎችን ይበልጥ ማዘመንና ምቹ የሥራ ከባቢ መፍጠር እንደሚገባም ተናግረዋል። ‎ ‎ሆኖም ከፕሮጀክት አፈጻጸም ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮች በሌሎች ተቋሚዊ ሥራዎች ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳድሩ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ አንስተዋል። ‎ ‎የተቋሙ ትልቁ በጀት የሚውለው ለፕሮጀክቶች በመሆኑ የኃይል መሠረተ ልማቶች ፕሮጀክቶች ላይ የሚታይ ለውጥ ለማስመዝገብ የክትትልና የድጋፍ ሥርዓቱን በማጠናከር ሁሉም ኃላፊነቱን በእኔነት ስሜት መወጣት አለበት ብለዋል። ‎ ‎ባለፉት ሦስት ዓመታት ሲተገበር የቆየው የተቋሙ የግሪድ ስትራቴጅ በዚህ በጀት ዓመት የሚጠናቀቅ በመሆኑ አፈጻጸሙን በመገምገም ለአዲሱ ስትራቴጂ እንደ ግብዓት መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ‎ ‎ተቋማዊ ሥራዎች ወጪን በቀነሰ እንዲሁም ከሙስናና ብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ ሊከናወኑ ይገባል ብለዋል። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ለተመዘገበው ውጤት የበኩላቸውን ሚና ለተወጡ የተቋሙ የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞችም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ‎ ‎በቀሪ ሦስት ወራት በበጀት ዓመቱ ያልተከናወኑ ተግባራትን በመለየት እንዲሁም የነበሩ እጥረቶችን በማስወገድ እና ቅንጅታዊ አሠራርን በማጎልበት በተለዬ እይታ ለተሻለ ውጤት ሁሉም እንዲረባረብ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ‎ የኮፕ 32 ዝግጅት እና 7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በተሳካ መልኩ የሀገርን ሁለንተናዊ ገጽታ በሚገነባ መልኩ እንዲከናወን እንዲሁም ዲጅታል 2030 እንዲሳለጥ እንደ ተቋም የሚጠበቁ ኃላፊነቶችን በአግባቡ ለመወጣት ሁሉም በትኩረት መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4