ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 668 подписчиков, занимая 8 097 место в категории Технологии и приложения и 2 185 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 668 подписчиков.

Согласно последним данным от 25 августа, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 134, а за последние 24 часа — -3, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 31.40%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 17.80% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 920 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 790 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 11.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 26 августа, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 668
Подписчики
-324 часа
+87 дней
+13430 день
Архив постов
የተግባር ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ......///...... ተጨማሪ ያንብቡ.… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተግባር-ፈተና-ጥሪ-ማስታወቂያ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻ
+4
የተግባር ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ  ......///...... ተጨማሪ ያንብቡ.… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተግባር-ፈተና-ጥሪ-ማስታወቂያ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

ማከፋፈያ ጣቢያው የሰሜናዊ ግሪድን በማረጋጋት ረገድ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል ……..///…….. የሱሉልታ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የኢትዮጵያ ሰሜናዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ሲስተ
+4
ማከፋፈያ ጣቢያው የሰሜናዊ ግሪድን በማረጋጋት ረገድ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል ……..///…….. የሱሉልታ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የኢትዮጵያ ሰሜናዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ሲስተምን በማረጋጋት ረገድ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ተናገሩ። ኃላፊው አቶ ዳንኤል አደኔ እንደገለፁት ጣቢያው ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና ከበለስ የኃይል ማመንጫዎች የሚመረተውን ኃይል በመቀበል ወደተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በማስተላለፍ የድርሻውን እየተወጣ ይገኛል። ማከፋፈያ ጣቢያው የሚጠቀማቸው ሪአክተሮች የቮልቴጅ መዛባት በሚያጋጥምበት ወቅት የግሪድ ሲስተሙን ከድንገተኛ የኃይል መቋረጥ ለመጠበቅ እና የተረጋጋ ኃይል ለማቅረብ እገዛ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል። እንደ ጣቢያው ኃላፊ ገለጻ ጣቢያው ባለ 400፣ 230፣ 132 እና 33 ኪሎ ቮልት አቅም ያላቸው የተለያዩ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በማስተናገድ ላይ ይገኛል፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ.… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማከፋፈያ-ጣቢያው-የሰሜናዊ-ግሪድን-በማረ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ ደርሷል …….///……... የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራ
+4
የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ ደርሷል …….///……... የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራቱ ተሾመ ገለጹ። 201 ሜትር ርዝመት ያለው የግድብ ግንባታው 6 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የአፈር ቁፋሮ በማካሄድ አጠቃላይ ግድቡ ከሚፈልገው 7 ነጥብ 72 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሊት ውስጥ 81 ነጥብ 2 በመቶው ማለትም 6 ነጥብ 27 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሊት (RCC) ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል። የኃይል ማመንጫ ቤቱ የቁፋሮ ሥራ እንዲሁም የሲቪል ሥራው የመጀመሪያ ደረጃ የኮንክሪት ሙሌት ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁንም ተናግረዋል። ተጨማሪ ያንብቡ.… https://www.eep.com.et/?amh-news=የፕሮጀክቱ-አጠቃላይ-አፈጻጸም-ከ77-በመቶ-በ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

በኮይሻ የፕሮጀክት አመራር የታዩ ምርጥ ተሞክሮዎችን በአግባቡ ቀምሮ ማስፋት ይገባል ....///... በኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከዕውቀት ሽግግርና አቅም ግንባታ፣ ምቹ የሥራ ከባቢን ከመፍ
+8
በኮይሻ የፕሮጀክት አመራር የታዩ ምርጥ ተሞክሮዎችን በአግባቡ ቀምሮ ማስፋት ይገባል ....///... በኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከዕውቀት ሽግግርና አቅም ግንባታ፣ ምቹ የሥራ ከባቢን ከመፍጠር እንዲሁም ከፕሮጀክትና ከኮንትራት አስተዳደር ጋር ተያይዞ የታዩ ምርጥ ተሞክሮዎችን በአግባቡ ቀምሮ በቀጣይ በሚከናወኑ ፕሮጀክቶች መተግበር እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለጹ። በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የተመራው የሥራ አመራር ቡድን በኮይሻ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ አድርጓል። የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራቱ ተሾመ ለልዑኩ ባደረጉት ገለፃ ፕሮጀክቱን እስከ ግንቦት 2021 ዓ.ም ድረስ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ የዋናው ግድብ፣ የኃይል ማመንጫ ቤት፣ የውሃ ማስተንፈሻና ሌሎች ተጓዳኝ ሥራዎች በፍጥነት እየተከናወኑ መሆናቸውን አብራርተዋል። ተጨማሪ ያንብቡ.… https://www.eep.com.et/?amh-news=በኮይሻ-የፕሮጀክት-አመራር-የታዩ-ምርጥ-ተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፡ በራስ የመልማት እና የኃይል ዘርፍ መሪነት ማሳያ ......///...... የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን ራዕይ፣ ቁርጠኝነት እና የራስ አቅም ቅንጅት
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፡ በራስ የመልማት እና የኃይል ዘርፍ መሪነት ማሳያ  ......///...... የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን ራዕይ፣ ቁርጠኝነት እና የራስ አቅም ቅንጅት ምን ውጤት ማምጣት እንደሚችል የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው። በአባይ ወንዝ ላይ የተገነባው ይህ ግድብ በአፍሪካ ትልቁ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሲሆን በመላው አህጉሪቱ ለሚካሄዱ ግዙፍ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችም እንደ ምርጥ ሞዴል የሚወሰድ ነው።   📊 የፕሮጀክቱ ጥቅል መረጃ ⚡️ የኃይል ማመንጨት አቅም፡ 5,150 ሜጋ ዋት 🔋 አማካይ ዓመታዊ የኃይል ምርት፡ 15,700 ጊጋ ዋት ሰዓት   ተጨማሪ ያንብቡ.… https://www.eep.com.et/?amh-news=የታላቁ-የኢትዮጵያ-ህዳሴ-ግድብ-በራስ-የመ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

እንኳን ለነቢዩ መሐመድ የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላም አደረሳችሁ! የብርሃን ጉዞ አያከትምም! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማህበረሰባችንን ህይወት የሚያበራ፣ የአኗኗር ዘይቤ የሚለውጥ፣ የተጀመረው
እንኳን ለነቢዩ መሐመድ የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላም አደረሳችሁ!   የብርሃን ጉዞ አያከትምም!   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማህበረሰባችንን ህይወት የሚያበራ፣ የአኗኗር ዘይቤ የሚለውጥ፣ የተጀመረውን ኢኮኖሚያዊ ለውጥ የሚያሳልጥና የዲጂታል 2030 ግቦችን ለማሳካት የሚያስችል አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡   ከኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቻችን የሚመነጨውን ኃይል በሀገሪቱ ሁሉም አቅጣጫ በተዘረጉት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና በማከፋፈያ ጣቢያዎቻችን ጨለማን ገፈን በብርሃን ለመተካት ከመቼውም ጊዜ በላይ በትጋት እየሰራን እንገኛለን፡፡   ለእስልምና እምነት ተከታዮች የመውሊድ በዓል የሰላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ ስንመኝ የበዓሉ አስተምህሮ የሆነውን የመተሳሰብ፣ የፍቅርና የመደጋገፍ ብርሃን ለሌሎች እንዲያበራ በጎነትና ትጋትን የዘወትር መመሪያችን በማድረግ ነው፡፡   ኢድ ሙባረክ!   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም

የወደቁ የብረት ምሰሶዎችን ወደ አገልግሎት ለመመለስ እየተሰራ ነው ....///.... ከለገጣፎ - ቃሊቲ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የወደቁ አምስት የብረት ምሰ
+9
የወደቁ የብረት ምሰሶዎችን ወደ አገልግሎት ለመመለስ እየተሰራ ነው ....///.... ከለገጣፎ - ቃሊቲ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የወደቁ አምስት የብረት ምሰሶዎችን ወደ አገልግሎት ለመመለስ እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ 1 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ደረጄ ገዛኸኝ እንደተናገሩት የታወር አካላትን ከተለያዩ ቦታዎች በማሰባሰብ እና ጥገናውን በማከናወን የሁለት ታዎሮችን ተከላ ሥራ ማከናዎን ተችሏል፡፡ ቀሪዎቹ ሶስት የወደቁ የብረት ምሰሶዎች የመሠረት ቁፋሮ የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ የመሠረት ቁፋሮ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለብረት ምሰሶዎች መሠረት ግንባታ የሚውሉ የአሸዋ፣የጠጠር እና የሲሚንቶ ግብአቶች ሳይት የማድረስ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ነው ዳይሬክተሩ ያስታወቁት፡፡ አምስቱ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊት 7 ሰዓት አካባቢ መውደቃቸው ይታወሳል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም

የጣቢያውን የኦፕሬሽን ባለሙያዎች አቅም ለማሳደግ ይሰራል ....///.... በኢትዮ ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታትና የባ
+9
የጣቢያውን የኦፕሬሽን ባለሙያዎች አቅም ለማሳደግ ይሰራል ....///.... በኢትዮ ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታትና የባለሙያዎችን አቅም ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ። በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የተመራው የሥራ አመራር ቡድን በኮንቨርተር ጣቢያው እና የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል በሆነው የወላይታ ሶዶ ማከፋፈያ ጣቢያ የመስክ ምልከታ አድርጓል። የኮንቨርተር የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ግርማ  ስለ ጣቢያው የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራ አስመልክቶ ባደረጉት ገለፃ እስከ ኬኒያ የተዘረጋው 1 ሺ 45 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር 2 ሺህ ሜጋ ዋት ኃይል የማስተላለፍ አቅም ይዞ 2014 ዓ.ም ላይ ወደ ኦፕሬሽን ገብቷል።‌‎ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የጣቢያውን-የኦፕሬሽን-ባለሙያዎች-አቅም&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም

የአየር ንብረት ለውጡ በኃይል አቅርቦቱ ላይ ችግር እንዳይፈጥር በትኩረት መስራት ይገባል .....///..... በምስራቅ አፍሪካ የተከሰተው የአየር ንብረት ለውጥ በኃይል አቅርቦቱ ላይ ችግር እንዳይፈ
+9
የአየር ንብረት ለውጡ በኃይል አቅርቦቱ ላይ ችግር እንዳይፈጥር በትኩረት መስራት ይገባል .....///..... በምስራቅ አፍሪካ የተከሰተው የአየር ንብረት ለውጥ በኃይል አቅርቦቱ ላይ ችግር እንዳይፈጥር በትኩረት መስራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የተመራው የከፍተኛ ሥራ አመራር ቡድን በጊቤ ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በመገኘት ውይይትና የመስክ ምልከታ አድርጓል። በዚህ ወቅት የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ሰሙ እንደገለጹት የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በዓመት እስከ 6 ሺህ 500 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማመንጨት ለብሔራዊ የኃይል ቋት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቀጥሎ ከፍተኛውን ድርሻ እያበረከተ ይገኛል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአየር-ንብረት-ለውጡ-በኃይል-አቅርቦቱ-ላ&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

ተቋሙ ከክልሉ ጋር ተቀራርቦ ለመሥራት ዝግጁ ነው ....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ የኃይል ኃይል መሠረተ ልማቶችን ደህንነት ለማረጋገጥና የፕሮጀክቶችን አፈጻጸም ለማሻሻል ከክልሉ ጋር ተቀራርቦ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ። የተቋሙ አመራር በኃይል መሠረተ ልማት ጥበቃ እና በካሣ ክፍያ ጉዳዮች ዙሪያ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት፣ ከዞን፤ ከወረዳና ከአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ከተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር በአርባምንጭ ከተማ ውይይት አካሂዷል። የውይይቱ ተሳታፊዎች መድረኩ ከከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆትና ከካሳ ክፍያ ጋር በተያያዘ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ሲሰሩ የቆዩ ሥራዎችን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ የሚረዳ ጉልህ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። የልማት ተነሽዎችን በፕሮጀክቶቹ ተጠቃሚ ከማድረግ፣ አጥፊዎችን ተከታትሎ ከማስቀጣት፣ እጅ ከፍንጅ የሚያዙ ንብረቶች ግምት ወጥ ከማድረግ፣ ከካሳ ክፍያ መዘግየት፣ ከግንዛቤ ፈጠራና ከቅንጅታዊ አሰራር ጋር በተያያዘ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከተሳታፊዎች ተነስተዋል። ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ የሰጡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ አቶ ተመስገን ጌታቸው ያለአስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በክልሉ ዘለቂ እድገትንና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ አይቻልም። በመሆኑም በክልሉ የሚገኙ የኃይል መሠረተ ልማቶችን ከመጠበቅ፣ ወሰን ከማስከበር፣ ከብረት ምሰሶ ስርቆት እና ከካሣ ጉዳዮች ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ከክልል ጀምሮ እስከ ቀበሌ ድረስ አመራሩና የጸጥታ መዋቅሩ አቅዶና ታች ወርዶ የመስራት ሙከራ መኖሩን አንስተዋል። አሁን ላይ በክልሉ የመስተዳድርና የጸጥታ አካላት ከተቋሙ እና ከማህበረሰቡ ጋር በቅንጅት በመሥራት የብረት ምሰሶ ስርቆት የመቀነስ ሁኔታ ቢኖርም ችግሩን በዘላቂት መቅረፍ አለመቻሉን አንስተዋል። በኃይል መሠረተ ልማት ላይ የሚፈጸም ስርቆት ተራ ወንጀል ሳይሆን ከሀገር ክደት ተለይቶ የማይታይ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካል ተቀናጅቶና ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባም ጠቁመዋል። በክልሉ የሚገኙ የኃይል መሠረተ ልማቶችን ደህንነት ለማስጠበቅና ከካሳ ክፍያ ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የክልሉ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ጊዜው የቴክኖሎጅና የሰው ሠራሽ አስተውሎት በመሆኑ ከዘመኑ ጋር ለመራመድና ሁሉንአቀፍ ሀገራዊ እድገት ለማስመዝገብ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም ተቋሙ በኦፕሬሽን ላይ ያሉትን የኃይል መሠረተ ልማቶች በመጠበቅና በማዘመን እንዲሁም አዳዲስ ሜጋ ፕሮጀክቶችን ደግሞ በስፋት በመገንባት ተደራሽነቱን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።   በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ የኃይል መሠረተ ልማቶችን ደህንነት ከማረጋገጥ እና ከካሳ ክፍያ እንዲሁም ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ተቋሙ ችግሮች እያጋጠሙት ሥለመሆኑም አንስተዋል። ችግሮቹን በዘላቂነት ለመፍታትም ከክልሉና በየደረጃው ከሚገኙ የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ተቋሙ ተቀራርቦና ተባብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። ቀጣናዊ ትስስርን ለማሳደግና ሁሉን አቀፍ ብልፅግና ለማረጋገጥ ወሳኝ የሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት መጠበቅ ለአንድ ተቋም ብቻ የሚተው ባለመሆኑ ሁሉም ኃላፊነቱን በእኔነት ስሜት ሊወጣ እንደሚገባም ተናግረዋል። ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በሚያልፉባቸውና ትልልቅ የኤሌክትሪክ ፕሮጀክቶች ባሉባቸው አካባቢዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተቋሙ ካሳ ከመክፈል በተጨማሪ ትልልቅ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። ተቋሙ በክልል የሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁና የኃይል መሠረተ ልማቶች ደህንነት እንዲረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ተባብረውና ተቀናጅተው እንዲሰሩም ጠይቀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

የኃይል መሠረተ ልማቶችን ደህንነትን በማስጠበቅ በኩል የመስተዳድር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው ....///..... በኦፕሬሽንና በግንባታ ላይ የሚገኙ የኃይል መሠረተ ልማቶችን ደህንነት በማስጠበቅ በኩል የመስተዳድር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ የሥራ አመራር ቡድን በኃይል መሠረተ ልማት ጥበቃ እና በካሳ ክፍያ ጉዳዮች ዙሪያ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት፣ ከዞንና ከአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ከተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር በአርባምንጭ ከተማ ውይይት እያካሄደ ይገኛል። ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሁፍ ያቀረቡት የደቡብ ሁለት ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ታዬ እንደገለጹት በክልሉ የጊቤ ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ እና የኢትዮ-ኬንያ ኮንቨርተር ጣቢያን ጨምሮ በርካታ የኃይል መሠረተ ልማቶች በኦፕሬሽን ይገኛሉ። ተቋሙ ከልማት አጋሮች በሚገኘው ብድርና ዕርዳታ እንዲሁም በራሱ ፋይናንስ በመመደብ የክልሉን የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት በዘላቂነት የሚያረጋግጡ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ሆኖም በክልሉ በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፍያ መስመሮች ላይ የሚፈጸመው የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት እንዲሁም ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች ለተቋሙ ከፍተኛ ፈተና መደቀናቸውን አንስተዋል። በተቋሙ የደቡብ ሁለት ሪጅን ከ2016 እስከ 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ የታወር ስርቆት እየቀነሰ ቢመጣም በሦስቱ ዓመት ብቻ 34 ሚሊዮን ብር ጉዳት መድረሱን የጠቆሙት አቶ ምትኩ ተጠርጣሪዎች ሲያዙ የሚመለከታቸዉ የመስተዳድርና የጸጥታ አካላት በቂ ትብብር አለማድረጋቸው ለችግሩ አንዱ ምክንያት መሆኑንም ተናግረዋል። በተጨማሪም በክልሉ በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሥር በሕግ የተቀመጠውን ወሰን በማለፍ የመኖሪያ ቤት በመገንባትና ሙዝና ማንጎ በኮሪደር ውስጥ በመትከል ለኃይል መቆራረጥ ስለመዳረጋቸውም ጠቅሰዋል። ተቋሙ የደቡብ ክልልን የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት ለማረጋገጥ የሚያከናውነው የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የተጀመረው የተሻሻለው የካሳ አዋጅ ከመውጣቱ በፊት በመሆኑ ከካሳ ጉዳዮች ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮችን በአፋጣኝ ለመፍታት የመስተዳድር አካላት ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባም ተገልጿል። በጎፋ፣ ባስኬቶ እና ደቡብ ኦሞ ዞኖች ውስጥ በግለሰቦች የሚደረጉ የፕሮጀክት መዳረሻ መንገዶችን የመዝጋት እንዲሁም የግንባታ ሥራዎችን የማስተጓጎል ችግሮች የፕሮጀክቱን አፈጻጸም እያዘገዩ በመሆኑ ክልሉ አፋጣኝ እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባም ገልጸዋል። የኃይል መሠረተ ልማቶችን ከጥቃትና ከስርቆት በማስጠበቅ እና ከካሳ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ በኩል የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በየደረጃው ያሉ የመስተዳድር አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። በቀረበው የመነሻ ጽሁፍ ላይ ውይይት እየተደረገም ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

የተቋሙ አመራሮችና የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች የማከፋፈያ ጣቢያውን የግንባታ አፈፃፀም ጎበኙ ...///.... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተመራ የተቋሙ የሥራ አመራር ቡድን እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና የዞን የሥራ ኃላፊዎች የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል በሆነው በአርባምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ላይ የመስክ  ምልከታ አድርጓል። የመስክ ምልከታው የተቋሙ አመራር እና የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች ፕሮጀክቱ የደረሰበትን የመጨረሻ ምዕራፍ የግንባታ አፈፃፀም በመጎብኘት እያጋጠሙ የሚገኙ ተግዳሮቶች ዙሪያ መፍትሄና ግብረ መልስ ለመስጠት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በመስክ ጉብኝቱ ወቅት ለከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድኑ ገለፃ ያደረጉት በፕሮጀክቱ የምዕራፍ አንድ የሣይት ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር አበበ ሚጀና እንደተናገሩት የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ቀደም ሲል የነበረውን የአርባ ምንጭ ቁጥር አንድን ኃይል የመስጠት አቅም በአራት እጥፍ የሚያሳድግ ነው፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ በ120 ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ለሚገኙ የአካባቢው ማህበረሰቦች እንዲሁም አርባ ምንጭ ላይ ለመገንባት ለታሰበው የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑንም አብራርተዋል። የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ከወላይታ ሶዶ 230 ኪሎ ቮልት፣ ከኦሞ ኩራዝ አንድ በ230 ኪሎ ቮልት መስመርና ከአርባ ምንጭ አንድ በ132 ኪሎ ቮልት መስመር የሚገናኝ ሲሆን በ33 ኪሎ ቮልት አስር እንዲሁም በ15 ኪሎ ቮልት አምስት በድምሩ 15 ወጭ መስመሮች እንዳሉትም ተናግረዋል፡፡ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶቹን በአጭር ጊዜ በመፍታት ፕሮጀክቱን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ በሚደረገው ጥረት የመስክ ምልከታው ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ኢንጂነር አበበ አስገንዝበዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ከክልሉ የመስተዳድር አካላት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር ለተነሱ ችግሮች አፋጣኝ እልባት ይሰጣል ብለዋል። ፕሮጀክቱ እያጋጠሙት ያሉትን ተግዳሮቶች በመፍታት በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ የተቋሙ አመራሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግዋል። የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ከ37 ነጥብ 09 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት ሃዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን በተባለ የደቡብ ኮሪያ ሥራ ተቋራጭ ግንባታው የተጀመረው ሕዳር 2016 ዓ.ም ነው። የተቋሙ የልዑካን ቡድኑ እስከ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በሚኖረው ቆይታ ከአርባምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በተጨማሪ በኢትዮ-ኬኒያ ኮንቨርተር ጣቢያ፣ በጊቤ ሦስት ኃይል ማመንጫና በኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

የሀገርን ማዕዘናት በንጹህ ኃይል የማብራት ጉዞ   ሀገራችን ኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ምንጮችን በጥቅም ላይ በማዋል የምስራቅ አፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን አበክራ እየሰራች ትገኛለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለፁት "የታዳሽ ኃይል አማራጮቻችንን በስፋት በማሳደግ፣ የሀገራችንን እያንዳንዱን ማዕዘን እያበራን እንገኛለን" የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ኤኮኖሚና በኃይል ዘርፍ የያዘችውን ሀገራዊ ራዕይና በተግባር ያሳካቻቸውን ስኬቶች ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።   ሀገርን በታዳሽ ኃይል ለማብራት ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል፡- 1. የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 5,150 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ግዙፍ የውሃ ኃይል ማመንጫ ሲሆን የሀገሪቱን ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ከእጥፍ በላይ አሳድጓል። ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች፣ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም ለዜጎች አስተማማኝ ኃይል ከማቅረቡ ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በመሸጥ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ ይገኛል።   2. የታዳሽ ኃይል ምንጮች አሰባጥሮ መጠቀም                 ኢትዮጵያ እንደሀገር ከውሃ ኃይል ማመንጫዎች በተጨማሪ እንደ አሸጎዳ፣ አዳማ 1 እና 2፣ አይሻ 2 እና አሰላ ያሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ሥራ መጀመር ከንፋስ የማመንጨት አቅምን 504 ሜጋ ዋት ያደረሱ ናቸው፡፡  ማሳደግ እንዲሁም የአይሻ የንፋስ ኃይል ፕሮጀክትን የመሳሰሉ አዳዲስ ግንባታዎችን በማጠናቀቅ የኃይል አማራጩን ማሰፋፋት ተችሏል። በአሉቶ ላንጋኖ እና በቱሉ ሞዬ እየተካሄዱ ያሉ የጂኦተርማል ፕሮጀክቶች የወደፊት የኃይል ዋስትና ስብጥርን ከሚያረጋግጡ የታዳሽ ኃይል አማራጮች መካከል ይጠቀሳሉ። ከዋናው ግሪድ ርቀው ለሚገኙ የገጠር አካባቢዎች የፀሐይ ኃይል አነስተኛ ግሪዶችን (Mini-grids) እና የቤት ውስጥ ሶላር ሲስተሞችን መስፋፋት የኃይል ተደራሽነትን lማሳደግ ተዐማሪ አቅም ፈጥሯል፡፡   3. የኃይል ተደራሽነትን ማፋጠን በገጠርና ከከተሞች ራቅ ባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት በሺዎች የሚቆጠሩ መንደሮችና አነስተኛ ከተሞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ጀምረዋል፡፡ የመኖሪያ ቤቶች፣ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ጣቢያዎችና የግብርና ምርት ማቀናበሪያዎች ኃይል እንዲያገኙ በማድረግ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶችን ጥራት ማሻሻል ተችሏል።   4. ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ኢትዮጵያ ከታዳሽ የኃይል ምንጮች የሚመነጭ ንፁህ ኢነርጂ ወደ ሱዳን፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ እና ታንዛኒያ በመላክ የኃይል ትስስር ፈጥራለች፡፡   5. የግል አልሚዎች ወደ ዘርፉ መግባት ዘርፉን ለማዘመን በተከናወኑ የፖሊሲ ማሻሻያዎች የሀገር ውስጥና የውጭ የግል አልሚዎች (Private Developers) በኃይል ማመንጨት ሥራ ላይ በር የሚከፍት የፖሊሲ ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል።   በአጠቃላይ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን ማስፋፋት የዜጎችን የዕለት ተዕለት ህይወት ከማሻሻሉም በላይ ሀገራችንን ወደ ተሻለ የኢንዱስትሪ እና የኢኮኖሚ እድገት የሚያሸጋግር የታሪካዊ ጉዞ አወንታዊ ማሳያ ነው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የኤሌክትሪክ አቅርቦት ጥራትን ማሻሻል ….///…. በአንድ ሀገር ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚጫወተው ሚና ወደር የለውም። የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢንዱስትሪዎች
የኤሌክትሪክ አቅርቦት ጥራትን ማሻሻል  ….///…. በአንድ ሀገር ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚጫወተው ሚና ወደር የለውም። የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢንዱስትሪዎች መንቀሳቀስ፣ ለንግድ ተቋማት መስፋፋት፣ ለጤና እና ትምህርት አገልግሎቶች መዘመን እንዲሁም ለዜጎች የዕለት ተዕለት ህይወት መሻሻል ዋነኛ መሰረት ነው። ይሁንና ዘላቂና ሁለንተናዊ እድገትን ለማረጋገጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ማስፋፋት እና የአገልግሎት ጥራትን ማሻሻል ትኩረት የሚፈልጉ ጉዳዮች ናቸው፡፡   የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ማለት አገልግሎቱ ያልደረሳቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በተለይም በገጠርና ከከተሞች ራቅ ባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን ከዋናው ግሪድ የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ ማለት ነው። ይህን ማድረግ ከተቻለ አገልግሎቱን ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በፍትሐዊነት በማድረስ ማህበራዊ ፍትህን ለማረጋገጥ ያስችላል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኤሌክትሪክ-አቅርቦት-ጥራትን-ማሻሻል&lang=am "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም