fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 688 مشترک است و جایگاه 7 994 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 178 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 688 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 15 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 68 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -5 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 23.41% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.17% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 670 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 536 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 16 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 688
مشترکین
-524 ساعت
-27 روز
+6830 روز
آرشیو پست ها
ኢትዮጵያ ለኬንያ የምታቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ልታሳድግ ነው ...….///….... ኢትዮጵያ ለኬንያ የምታቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል በእጥፍ ለማሳደግ የሚያስችላትን ቅድመ ዝግጅት እያጠናቀቀች መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ያለውን የኃይል ትስስር የበለጠ ለማጠናከርና የኃይል ኤክስፖርት አቅሟን ለማሳደግ ከቀጣናው ሀገራት ጋር በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል ስታካሂድ የነበረው የምክክር መድረክ ተጠናቋል፡፡ በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ተወካይ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ደስታለም ኃይሉ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 200 ሜጋ ዋት ኃይል ለኬንያ እያቀረበች ነው። በሁለቱ ሀገራት መካከል እየተከናወኑ ያሉ የቴክኒክና መሰል ሥራዎችን በማጠናቀቅ ከመጪው ታህሳስ ወር ጀምሮ የሚቀርበው የኃይል መጠን ወደ 400 ሜጋ ዋት ያድጋል። ይሁንና ተጨማሪ ኃይል ከመላኩ በፊት የሙከራ ሥራውን የሚያከታተል የጋራ የቴክኒክ ቡድን ወደ ሥራ መግባቱን ኢንጂነር ደስታለም ጠቁመዋል። የኬንያ ኤሌክትሪክ ግሪድ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተያያዘ በመሆኑ የግሪድ አለመረጋጋት እንዳይከሰት የጋራ ጥንቃቄ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በሙከራ ደረጃ 100 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለታንዛኒያ እያቀረበች በመሆኑ በኬንያና ታንዛኒያ መካከል ያለው የመሠረተ ልማት ማሻሻያ ሲጠናቀቅ መደበኛ የኃይል ሽያጭ እንደሚጀመር ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም አዳዲስ የማስተላለፊያ መስመሮችን በመዘርጋትና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመገንባት ከቀጣናው ሀገራት ጋር የሚደረገውን የኃይል ኤክስፖርት  ትስስር ለማሳደግ ዕቅድ ተይዞ ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል፡፡ በምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል የሚደረገው የኃይል ትስስርና ትብብር የቀጣናውን የኤሌክትሪክ አቅርቦትና ተዳራሽነት ለማሻሻል እንዲሁም የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትልቅ መሠረት እንደሆነ አስረድተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም

photo content
+4

ኢትዮጵያ በኃይል ኤክስፖርት  ዕድገት  እያሳየች ነው ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት አስር ዓመታት ለጎረቤት ሀገራት ኤክስፖርት ያደረገው ኃይል የ31 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡን የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር አባል ሀገራት መካከል ያለውን የኃይል አቅርቦትና የገበያን ትስስር ለማጠናከር እንዲሁም በቀጣናው በሚጠበቀው የኢል ኒኖ ስጋት መከላከል ዙሪያ ለመምከር የተዘጋጀው የምክክር ጉባኤ ተጠናቋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ዳይሬክተር ኢንጂነር ሚኪያስ ወንድሙ ስለሀገሪቱ የኃይል ማምረት አቅም እና የኃይል ኤክስፖርት ዕድገት ለቀጣናው ሀገራት ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት እንደገለጹት ኢትዮጵያ ካላት አጠቃላይ የኃይል ምርት ውስጥ የኤክስፖርት ድርሻው ከ6.5 እስከ 10 በመቶ ይደርሳል። የምስራቅ አፍሪካን የኃይል ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ሰፊ ዕቅዶች መያዛቸውን ያብራሩት ኢንጂነር ሚኪያስ እ.ኤ.አ እስከ 2030 ድረስ የኃይል ኤክስፖርት አቅምን ወደ 5 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት ለማሳደግ ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በቀጣይም የኃይል ሽያጭ ንግድን ለማስፋት ከደቡብ ሱዳን፣ ከሶማሊያ እና ከሶማሊላንድ ጋር አዳዲስ የማስተላለፊያ መስመሮችን የመዘርጋት እንዲሁም ከጂቡቲና ከሱዳን ጋር ሁለተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የመገንባት ዕቅድ ተይዞ ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል። የሀገሪቱ የኃይል ማመንጨት ሥርዓት ከ95 በመቶ በላይ በውሃ ላይ የተመሠረተ በመሆኑ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚከሰቱ ተጽዕኖዎችን ለመቋቋም የኃይል ስብጥርን ለማስፋት የሚያስችሉ ዕቅዶች ተቀርፀው እየተተገበሩ መሆናቸውን ኢንጂነር ሚኪያስ ገልፀዋል። የሀገሪቱ የኃይል ማመንጨት ሥርዓቱ በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ውስጥ እንዳይገባ የኃይል ስብጥርን ለማስፋት የሚያስችሉ ዕቅዶች ተቀርፀው እየተተገበሩ መሆናቸውንም ኢንጂነር ሚኪያስ አክለው ገልፀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም

photo content
+3

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፡ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የቀጣይ ዕቅዶች ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የቀጣይ ዕቅዶች አስመልክቶ ያደረጉት ማብራሪያ፡ ኢንጂነር አሸብር ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦ ✅ የኃይል ማመንጨት አቅም ግንባታ እና ኤክስፖርት አፈጻጸም ✅ የ2030 የዲጂታል ስትራቴጂ ትግበራ ✅ በቀጣይ ዓመት የሚከናወኑ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ሙሉ መረጃውን በዩቲዩብ ቻናላችን ይከታተሉ፡ 👉 https://youtu.be/g6GyPt8qZKw 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም

በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የሚገኘውን ዕምቅ የኤሌክትሪክ ሀብት አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል የጋራ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ....///.... በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ያለውን እምቅ የኤሌክትሪክ ሀብት በስፋት
+9
በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የሚገኘውን ዕምቅ የኤሌክትሪክ ሀብት አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል የጋራ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ....///.... በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ያለውን እምቅ የኤሌክትሪክ ሀብት በስፋት በማልማትና የሀገራትን የኤሌክትሪክ ግሪድ በማስተሳሰር ለቀጣናው ልማት ማዋል እንዲቻል የሀገራት የጋራ ቁርጠኝነትና ትብብር ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ። በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር አባል ሀገራት መካከል ያለውን የኃይል አቅርቦት፣ ፍጆታ እና ትስስር ለማጠናከር የተዘጋጀው የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ስቲሪንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢንጂነር አሸብር ባልቻን ወክለው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ኢንጂነር ያለውአይቀር ማንደፍሮ እንደገለፁት የሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) የኤሌክትሪክ ኃይል እና የዘመናዊ ዕድገት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ሞተር እየሆነ መጥቷል፡፡ ይሁንና በቀጣናው በሚገኙ ማህበረሰቦችና ኢንዱስትሪዎች ዘንድ የኃይል እጥረትና የአስተማማኝነት ችግር አሁንም ከባድ ፈተና እንደሆነ ቀጥሏል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በምስራቅ-አፍሪካ-ቀጣና-የሚገኘውን-ዕምቅ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 4 ቀን 2018 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኃይል አቅርቦቱን በእጥፍ አሳድጓል ....///... የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ከእጥፍ በላይ በማሳደግ የቀጣናውን የኃይል
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኃይል አቅርቦቱን በእጥፍ አሳድጓል ....///... የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ከእጥፍ በላይ በማሳደግ የቀጣናውን የኃይል ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ። ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ  ለኢዚአ እንደገለጹት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን ጽናት፣ አንድነትና ቁርጠኝነት በተግባር የተገለጠበት «ዳግማዊ ዓድዋ» ነው። የግድቡ ግንባታ ኢትዮጵያ በራሷ አቅም የላቀ ስኬት ማስመዝገብ እንደምትችል ለዓለም ያስመሰከረችበትና አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የከፈተችበት ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑንም ጠቁመዋል።   ተጨማሪ ያንብቡ.… https://www.eep.com.et/?amh-news=ታላቁ-የኢትዮጵያ-ህዳሴ-ግድብ-የኃይል-አቅ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 4 ቀን 2018 ዓ.ም

ሪጅኑ በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የሥራ ክፍሎች፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ሠራተኞች እውቅና ሰጠ .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን በ2018 በ
+9
ሪጅኑ በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የሥራ ክፍሎች፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ሠራተኞች እውቅና ሰጠ .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የሥራ ክፍሎች፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ሠራተኞች በዛሬው እለት እውቅና ሰጠ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንዳስታወቁት በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ የጥገና ሠራተኞች፣ ለማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎች፣ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ተቋቁመው ሥራቸውን እያከናወኑ ላሉ ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ሌሎች በሪጅኑ ሥር ለሚገኙ የሥራ ክፍሎች እውቅና ተሰጥቷል፡፡ በዚህም መሠረት በሪጅኑ በስርቆት ምክንያት ወድቀው በነበሩ  የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች መልሶ ግንባታ እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያ ሥራዎች ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ላበረከቱ  ሠራተኞች የምስክር ወረቀት እና የማበረታቻ ሽልማት መበርከቱን ተናግረዋል።   ተጨማሪ ያንብቡ.… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሪጅኑ-በ2018-በጀት-ዓመት-የተሻለ-አፈፃፀም-ላስ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም

እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ! አዲስ ዓመት ሁሌም ተስፋ ይዞ የሚመጣ የበዓላት ሁሉ መጀመሪያ ነው፡፡ የዘመን መቀየር ተስፋችንን የሚያለመልም እና ነገን አልመን ወደፊት እንድንጓዝ
እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ! አዲስ ዓመት ሁሌም ተስፋ ይዞ የሚመጣ የበዓላት ሁሉ መጀመሪያ ነው፡፡ የዘመን መቀየር ተስፋችንን የሚያለመልም እና ነገን አልመን ወደፊት እንድንጓዝ የሚያደርግ እንዲሆን ዛሬን በአግባቡ ማቀድና ዕለት ዕለት በትጋት መሥራት ይጠይቃል፡፡ እንደ ተቋም በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ የያዝነውን ዕቅድ ለማሳካት የምንተጋበት፤ በ2018 በጀት ዓመት ያስመዘግብናቸውን የኦፕሬሽን፣ የፕሮጀክት አፈፃፀምና የፋይናንስ ድሎች የምናስቀጥልበት፣ "የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል" የመሆን ራዕያችንን እውን ለማድረግ የምንሠራበት፣ ሁለንተናዊ ተቋማዊ ስኬት የምናስመዘግብበት እንዲሁም በግል ያቀድናቸውን ውጥኖች ከግብ የምናደርስበት የሠላም፣ የደስታና የስኬት ዘመን እንዲሆን እመኛለሁ!! መልካም አዲስ ዓመት! አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር)፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ

ጳጉሜን 5 — የነገው ቀን   ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ላለፉት 3 ዓመታት ሲተገብረው በቆየው «G.R.I.D» ስትራቴጂ ውስጥ በ«D» የተወከለው «Digital Transformation» (ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን) የተቋሙን አሠራርና የመሠረተ ልማት አያያዝ ወደ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሥርዓት በማሸጋገር ረገድ ትልቅ ምዕራፍ ተሻግሯል። የዲጂታል ትራንስፎርሜሽኑ ዋና ዓላማዎች ✅   አስተማማኝነት፦ በኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ መስመሮች ላይ የሚያጋጥሙ ብልሽቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ቀድሞ መለየትና በፍጥነት ማስተካከል፤ ✅   ውጤታማነት፦ የኃይል ብክነትን በዘመናዊ የመለኪያና የመቆጣጠሪያ መሣሪያዎች መቀነስ፤ ✅   ደህንነት፦ የብሔራዊ የኃይል መረብ (National Grid) ደህንነትንና ሳይበር ጥቃቶችን መከላከል የሚያስችል አስተማማኝ የሳይበር ደኅንነት ሥርዓት መገንባት፤ በዚህ በጳጉሜን 5 «የነገው ቀን» መታሰቢያነት ተቋሙ አገልግሎቱን ፈጣን፣ ዘመናዊና አስተማማኝ ለማድረግ ያስቻሉ ዋና ዋና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትግበራዎች ምን እንደሆኑ ከብዙ በጥቂቱ ለማሳየት እንሞክራለን፡፡ ዋና ዋና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ስኬቶች SCADA/EMS (ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ሥርዓት) በሀገር አቀፍ ደረጃ የኃይል ማመንጫዎችንና ከፍተኛ የቮልቴጅ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን (Substations) በእውነተኛ ጊዜ (Real-time) በዲጂታል መንገድ ለመቆጣጠርና የኃይል መቆራረጥ ሲያጋጥም ወዲያውኑ ምላሽ ለመስጠት የሚያግዝ አውቶሜትድ ሥርዓት ነው፡፡   የማከፋፈያ ጣቢያዎች ዲጂታላይዜሽን የነበሩትን አሮጌ የዘይት ሰርኪዩት ብሬከሮች በዘመናዊ የዲጂታል የጋዝ መቆጣጠሪያዎች በመተካትና የደህንነት ሥርዓቶችን በማዘመን የቴክኒክ ብልሽቶችንና የኃይል ማቋረጥ ጊዜን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ተችሏል።   የውስጥ አሠራርና የፋይናንስ ዲጂታላይዜሽን የተቋሙን የበጀት፣ የንብረት አያያዝ፣ የሰው ሀብትና የግዥ አሠራሮች እንዲሁም የውስጥ ኮሙዩኒኬሽንን ከወረቀት ነፃ ወደሆነ ዲጂታል ሥርዓት በመቀየር ግልጽነትና ቀልጣፋ አሠራር እንዲሰፍን ተደርጓል።   የቴሌኮም መሠረተ ልማት አጠቃቀም በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የተዘረጉ የፋይበር ኦፕቲክስ (OPGW) መስመሮችን ለዲጂታል ዳታ ማስተላለፊያ በመጠቀም የተቋሙን መረጃ መለዋወጥ ከማፈጠኑ ባሻገር አዳዲስ የገቢ አማራጮችን ፈጥሯል።   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዛሬ የሚገነባቸው የዲጂታል መሠረተ ልማቶች «የነገዋን ኢትዮጵያ» በበለጸገ፣ በዘመናዊና በተሳሰረ አረንጓዴ ኤነርጂ ለመምራት የሚያስችሉ ጠንካራ መሠረቶች ናቸው!   #የነገውቀን #ጳጉሜን5 #ኢትዮጵያኤሌክትሪክኃይል #EEP #GRIDStrategy #DigitalTransformation #SmartGrid #Ethiopia 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ከወረቀት ወደ ዲጂታል! ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት! ትናንትን በመማርና በማረም ዛሬን በላቀ ትጋት በመገንባት ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አ
ከወረቀት ወደ ዲጂታል! ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት! ትናንትን በመማርና በማረም ዛሬን በላቀ ትጋት በመገንባት ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የአሶሳ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ ……..///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ኖሪንኮ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን ጋር የጉባ-አ
+7
የአሶሳ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ ……..///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ኖሪንኮ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን ጋር የጉባ-አሶሳ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የአሶሳ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ፡፡ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የኖሪንኮ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ሚስተር ዱ ዢኦዶግ ናቸው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደገለጹት ተቋሙ ከተከዜ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ጀምሮ በተለያዩ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታዎች ላይ ከኩባንያው ጋር አብሮ ሲሰራ ቆይቷል። ስምምነቱ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለውን የኃይል አቅርቦት አስተማማኝ የሚያደርግና ኢንቨስትመንትን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ መሆኑን ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአሶሳ-2-ባለ-400-ኪሎ-ቮልት-ማከፋፈያ-ጣቢያ-ግ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም

#የተቋምቀን ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ቀን በዓል አከባበር
+8
#የተቋምቀን ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ቀን በዓል አከባበር

በየዓመቱ ጳጉሜን 4 የተቋም ቀን ሆኖ ይከበራል - ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ……..///……… በየዓመቱ ጳጉሜን 4 የተቋም ቀን (Company Day) ሆኖ እንደሚከበር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና
+8
በየዓመቱ ጳጉሜን 4 የተቋም ቀን ሆኖ ይከበራል - ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ……..///……… በየዓመቱ ጳጉሜን 4 የተቋም ቀን (Company Day) ሆኖ እንደሚከበር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አስታወቁ። ኢንጂነር አሸብር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሚከበርበት ሥነስርዓት ላይ እንደገለፁት ጳጉሜን 4 የሀገራችን ብሔራዊ አርማ የሆነው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለምረቃ የበቃበት ቀን በመሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም በዚሁ ዕለት በየዓመቱ የተቋም ቀን ሆኖ እንዲከበር ወስኗል። በርካታ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ከትንሽ ተነስተው ለታላቅነት የበቁት ባላቸው ፋይናንስ ሳይሆን በሠራተኞቻቸው የዘወትር ትጋትና ጥረት መሆኑን ገልፀው የተቋሙ ሠራተኞችም ለተቋሙ ስኬት ላበረከቱት ጉልህ አሰተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በየዓመቱ-ጳጉሜን-4-የተቋም-ቀን-ሆኖ-ይከበራ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2018 ዓ.ም

በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች፣ ሪጅኖችና ፕሮጀክቶች ዕውቅና ተሰጠ  .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዛሬው ዕለት ባከበረው የተቋም ቀን በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ማመንጫ ጣቢያዎች፣ ሪጂኖችና ፕሮጀክቶች እንዲሁም አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ተቋቁመው ኃይል የማመንጨት ሥራቸውን እያከናወኑ ለሚገኙ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዕውቅና ሰጥቷል። በዚሁ መሰረት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ ጊቤ 3 እና ገናሌ ዳዋ 3  የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም የሰሜን ምሰራቅ 1፣ መካከለኛ 2 እና ምስራቅ 2 ሪጅኖች በኃይል ማመንጨት፣ማስተላለፍ እና ማከፋፈል የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገባቸው የተሽከርካሪ፣ የዋንጫና የምስክር ወረቀት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በተመሳሳይ በለስ፣ ጢስ ዐባይ፣ ፊንጫ እና አመርቲ ነሼ የውሃ ኃይል ማመንጫ  ጣቢያዎች በአካባቢያቸው ያለውን  አስቸጋሪ ሁኔታ ተቋቁመው  ኃይል የማመንጨት ሥራቸውን በብቃት በመወጣታቸው በልዩ ሁኔታ የዋንጫ፣ የምስክር ወረቀትና የተሽከርካሪ ሽልማት ተሰጥቷቸዋል።   በፕሮጀክት  አፈፃፀም በኩልም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ ኮይሻ የውሃናአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች እውቅና  ተሰጥቷቸዋል። በተጨማሪም ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፣ ገንዳ አርባ አግሮ ኢንዱስትሪ፣ ለገጣፎ ኮምቦልቻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የሽቦ ቅየራ ሥራ፣ በቆጂ እና ደብረ ታቦር ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ  ፕሮጀክቶች  የዋንጫና የምሽክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+9

ተቋሙ የፈጠራ ሥራዎችን በማከናወን አስተዋፅኦ ላበረከቱ ባለሙያዎች ዕውቅና ሰጠ .......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዛሬው እለት ባከበረው የተቋም ቀን የተለያዩ የፈጠራና አሰራርን
+9
ተቋሙ የፈጠራ ሥራዎችን በማከናወን አስተዋፅኦ ላበረከቱ ባለሙያዎች ዕውቅና ሰጠ .......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዛሬው እለት ባከበረው የተቋም ቀን የተለያዩ የፈጠራና አሰራርን የሚያዘምኑ ሥራዎችን በማከናወን አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር እና ተቋሙን ከተጨማሪ ወጭ በመታደግ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ባለሙያዎች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡ በዚህም ባለሙያዎቹ ባከናወኑት ሥራ ተቋሙን ከ374 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማዳን የምስክር ወረቀትና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በዚሁም መሠረት ፍቅረዮሐንስ ታደሰ - በኖዝል ፊክስ  የፈጠራ ሥራ በማከናወንና 2 ሚሊዮን ብር  በማዳን፤ ፋንታሁን እስከዚያው - በጀኔሬተር የላይኛውና ታችኛው ጋይድ ቢሪን ላይ የማሻሻያ ሥራ በማከናወንና 2 ሚሊዮን ብር ተጨማሪ  ወጪ በማስቀረት፤ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የፈጠራ-ሥራዎችን-በማከናወን-አስተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2018 ዓ.ም

ጳጉሜን 4 — የሕብር ቀን ሰብአዊ እርዳታ እና የማህበራዊ ድጋፍ ስራዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አቅመ-ደካማ ዜጎችን መደገፍ፣ በአደጋ የተጎዱ አካባቢዎችን ማቋቋም እና የመማር-ማስተማር ሂደትን
ጳጉሜን 4 — የሕብር ቀን   ሰብአዊ እርዳታ እና የማህበራዊ ድጋፍ ስራዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አቅመ-ደካማ ዜጎችን መደገፍ፣ በአደጋ የተጎዱ አካባቢዎችን ማቋቋም እና የመማር-ማስተማር ሂደትን ማጠናከር ሰብአዊ ክብርን የመጠበቅና ነገን የመገንባት ታላቅ ኃላፊነት እንደሆነ ያምናል፡፡ በዚህ መርህ የተሰሩ ሥራዎች፡- የአደጋ ጊዜ ሰብአዊ እርዳታ በደቡብ ኦሞ ዞን (ሐመር፣ ዳሰነች፣ ኛንጋቶም እና ሳላማጎ ወረዳዎች) በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት አጋጥሞ በነበረው የምግብ እጥረት ወደ 260 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የሰብአዊ እርዳታ ድጋፍ ተደርጓል።   የመኖሪያ ቤትና ትምህርት ድጋፍ (ደሴ) በደሴ ከተማ ከ28 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ለ6 አቅመ-ደካማ ዜጎች ባለአንድ ወለል ህንፃ (G+1) ተገንብቶ ለርክክብ ዝግጁ የሆነ ሲሆን፣ ለ250 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ተበርክቷል።   በትምህርት ዘርፍ አበይት ድጋፎች በየም ዞን ለፎፋ አዳሪ ትምህርት ቤት የ10 ሚሊዮን ብር የግብዓት ድጋፍ የተደረገ ሲሆን በአሪ እና ደቡብ ኦሞ ዞኖችም የትምህርት ቤቶችና የአቅመ-ደካሞች መኖሪያ ቤት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተጥሏል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2018 ዓ.ም