uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 687 підписників, посідаючи 7 990 місце в категорії Технології та додатки та 2 177 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 687 підписників.

За останніми даними від 16 вересня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 61, а за останні 24 години на 8, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 23.13%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.11% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 629 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 527 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 9.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 17 вересня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 687
Підписники
+824 години
-47 днів
+6130 днів
Архів дописів
ስነ-ምግባርን በተላበሰ መንገድ ሥራን ማከናወን እንደሚገባ ተገለፀ …..////…… የሀገሪቱን ብሎም የተቋሙን ህግና መመሪያ ባከበረ እና ስነ-ምግባርን በተላበሰ መንገድ የዕለት ከዕለት ሥራዎችን ማከና
+6
ስነ-ምግባርን በተላበሰ መንገድ ሥራን ማከናወን እንደሚገባ ተገለፀ …..////…… የሀገሪቱን ብሎም የተቋሙን ህግና መመሪያ ባከበረ እና ስነ-ምግባርን በተላበሰ መንገድ የዕለት ከዕለት ሥራዎችን ማከናወን እንደሚገባ ተገለፀ። የኮርፖሬት ፋይናንስ እና ሰው ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ ለፕሮጀክት ሠራተኞች እየተሰጠ በሚገኘው ስልጠና ላይ እንደገለፁት የስራ ላይ ስነ-ምግባር መርሆዎችን በውል በመገንዘብ እና ተግባራዊ በማድረግ የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ማሳደግ ይገባል። ስነ-ምግባር የተቋሙን ተወዳዳሪነት የሚወስን ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ ሰራተኛ ስራውን በታማኝነት፣ በቁርጠኝነትና በከፍተኛ የስራ ተነሳሽነት በማከናወን ለተቋሙ ስኬት የበኩሉን አሻራ ማሳረፍ እንዳለበት በአፅንኦት ገልፀዋል። ስልጠናውን የሰጡት የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ አጥናፌ በበኩላቸው ሰራተኞች የስራ ሰዓትን በማክበርና ሥራው የሚጠይቀውን ዲሲፕሊን በመላበስ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ስነ-ምግባርን-በተላበሰ-መንገድ-ሥራን-ማከ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://x.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም

ሪጅኑ ለሰበታ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ሠራተኞች እውቅና ሰጠ ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 3 ሪጅን በሰበታ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የተከሰተው የእሳት አደጋ ወደ ፓወር
+9
ሪጅኑ ለሰበታ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ሠራተኞች እውቅና ሰጠ ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 3 ሪጅን በሰበታ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የተከሰተው የእሳት አደጋ ወደ ፓወር ትራንስፎርመሩ ሳይሸጋገር አደጋውን ለተቆጣጠሩ የጣቢያው ሠራተኞች እውቅና ሰጥቷል፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ እስማኤል ሙዘይን በእውቅና ሥነ- ስርዓቱ ወቅት እንደገለጹት ሪጅኑ በማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ላይ የሚከሰቱ አደጋዎችን ለመከላክል  ባለፉት ሁለት ዓመታት ለሠራተኞች ተከታታይ የእሳት አደጋ መከላከያ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡ የሰበታ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ሠራተኞች ነሐሴ 18 ቀን 2018  ዓ.ም ምሽት ሦስት ሠዓት አካባቢ  በጣቢያው እሳት ሲነሳ አደጋውን ለመቆጣጠር የወሰዱት ስልጠና አስተዋጽኦ ማድረጉንና በቀጣይ የእሳት አደጋ መከላከያና የመጀመሪያ እርዳት ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግውረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሪጅኑ-ለሰበታ-1-ማከፋፈያ-ጣቢያ-ሠራተኞች-እ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://x.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም

የኦፕሬሽን ወጪን መመለስ እና ማህበራዊ ደህንነትን ማመጣጠን፡ የታሪፍ ማዕቀፍ ዲዛይን መርሆዎች ⚡️ የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማዕቀፋችንን ለማዘመን በምንሰራበት ወቅት አካሄዳችን የፋይናንስ ጽ
የኦፕሬሽን ወጪን መመለስ እና ማህበራዊ ደህንነትን ማመጣጠን፡ የታሪፍ ማዕቀፍ ዲዛይን መርሆዎች ⚡️ የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማዕቀፋችንን ለማዘመን በምንሰራበት ወቅት አካሄዳችን የፋይናንስ ጽኑነትን ከደንበኞች ማኅበራዊ ደህንነት ጋር ለማጣጣም አራት ዋና ዋና የዲዛይን መርሆዎች ታሳቢ ተደርገዋል። 1️⃣ የኦፕሬሽን ወጪንመሸፈን (Cost Reflectivity): የገቢ ፍላጎት እና የኦፕሬሽን ወጪዎችን መሸፈን እንደ መነሻ ተወስዷል። 2️⃣ ማህበራዊ ጥበቃ (Social Protection): ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የታሪፍ ተጠቃሚ ደንበኞች(Lifeline tariffs) ታሳቢ ያደረጉ የሽግግር ድጋፍ ማእቀፎች ግልጽነት ባለው መልኩ ይተገበራሉ። 3️⃣ የፋይናንስ ጤናማነት (Financial Health): ተራማጅ በሆነ እና ወጪን የሚሸፍን አሰራር በመተግበር የኃይል አቅራቢ ተቋማትን የፋይናንስ ጤናማነት እና የኢንቨስትመንት አቅም ማጠናከር እንደ አንድ መርህ ታሳቢ ተደርጓል። 4️⃣ የግልጽነት ፍተሻ (Transparency Test): የተጠናው የታሪፍ  ማዕቀፍ ለኢትዮጵያ ኢነርጂ ዘርፍ ቀጣይነት ያለው፣ ፍትሃዊ እና ጽኑ የኃይል ዘርፍ መሰረት መሆንን በማረጋገጥ የፖሊሲውን ውጤታማነት መፈተሽ ላይ ትኩረት ያደርጋል። 🌍🔌 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለማሳደግ የታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ማዘመን ወሳኝ ነው ….///…. በኢትዮጵያ ጠንካራ የፋይናንስ አቅም በመፍጠር የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለማሳደግ የኤሌክትሪ
+6
የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለማሳደግ የታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ማዘመን ወሳኝ ነው ….///…. በኢትዮጵያ ጠንካራ የፋይናንስ አቅም በመፍጠር የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለማሳደግ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ማዘመን ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ። የደቡብ ኮሪያ መንግሥት የባለሙያ ድጋፍ በማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ለማዘመን ያከናወነውን ጥናት ለተቋሙ አመራሮች በስካይ ላይት ሆቴል አቅርቧል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚን በመወከል የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ተወካይ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ደስታዓለም ኃይሉ እንደገለጹት ተቋሙ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥ የፋይናንስ አቅሙን ማጠናከርና የእውቀት ሽግግር ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-አቅርቦቱን-አስተማማኝነት-ለማሳ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም

የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ለማዘመን የተከናወነው ጥናት እየቀረበ ነው ….///…. የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ለማዘመን የተከናወነው ጥናት ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በዛሬው ዕለት በስካይ ላይት ሆቴል እየቀረበ ነው፡፡ የደቡብ ኮሪያ መንግሥት የባለሙያ ድጋፍ በማድረግ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ለማዘመን በሚያስችል እና የዕውቀት ሽግግርን ባረጋገጠ አግባብ የተካሄደ ጥናት ነው፡፡ ጥናቱ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድርድር ማዕቀፍ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን በማድረግ የተቋሙን የፋይናንስ ቁመና በማጎልበት፣ የግል ኢንቨስትመንቶችን በማበረታታት እና ስጋትን በመቀነስ በኩል ለተቋሙ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል። በጥናቱ የመክፈቻ መርሀ ግብር ላይ በኮሪያ የንግድና ኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን ኤጀንሲ  የኢትዮጵያ ከፍተኛ አማካሪ ጥናቱ ሳይንሳዊ መርሆዎችን ባረጋገጠ መልኩ መከናወኑን ገልፀዋል። በኢትዮጵያ የደቡብ ኮርያ ቻርጅ ዲ አፌር ሚስ ያንግ ሚ ካንግ ከስድስት አስር ዓመታት በላይ የዘለቀውን የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አንስተው በኃይል ዘርፍ የተጀመረው ግንኙነት የሀገራቱን የወደፊት ግንኙነት ያሳያል ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ ኢንጂነር ደስታለም ኃይሉ በበኩላቸው የሀገራቱ ግንኙነት አሁን ለተከናወነው የታሪፍ ድርድር ማዕቀፍ ወሳኝ እንደነበር አንስተዋል። ማዕቀፉ ሙያዊ በሆነ መንገድ በመዘጋጀቱ በዋና ሥራ አስፈፃሚው ስም አመስግነዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም

photo content
+9

ኢትዮጵያ ለኬንያ የምታቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ልታሳድግ ነው ...….///….... ኢትዮጵያ ለኬንያ የምታቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል በእጥፍ ለማሳደግ የሚያስችላትን ቅድመ ዝግጅት እያጠናቀቀች መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ያለውን የኃይል ትስስር የበለጠ ለማጠናከርና የኃይል ኤክስፖርት አቅሟን ለማሳደግ ከቀጣናው ሀገራት ጋር በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል ስታካሂድ የነበረው የምክክር መድረክ ተጠናቋል፡፡ በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ተወካይ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ደስታለም ኃይሉ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 200 ሜጋ ዋት ኃይል ለኬንያ እያቀረበች ነው። በሁለቱ ሀገራት መካከል እየተከናወኑ ያሉ የቴክኒክና መሰል ሥራዎችን በማጠናቀቅ ከመጪው ታህሳስ ወር ጀምሮ የሚቀርበው የኃይል መጠን ወደ 400 ሜጋ ዋት ያድጋል። ይሁንና ተጨማሪ ኃይል ከመላኩ በፊት የሙከራ ሥራውን የሚያከታተል የጋራ የቴክኒክ ቡድን ወደ ሥራ መግባቱን ኢንጂነር ደስታለም ጠቁመዋል። የኬንያ ኤሌክትሪክ ግሪድ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተያያዘ በመሆኑ የግሪድ አለመረጋጋት እንዳይከሰት የጋራ ጥንቃቄ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በሙከራ ደረጃ 100 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለታንዛኒያ እያቀረበች በመሆኑ በኬንያና ታንዛኒያ መካከል ያለው የመሠረተ ልማት ማሻሻያ ሲጠናቀቅ መደበኛ የኃይል ሽያጭ እንደሚጀመር ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም አዳዲስ የማስተላለፊያ መስመሮችን በመዘርጋትና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመገንባት ከቀጣናው ሀገራት ጋር የሚደረገውን የኃይል ኤክስፖርት  ትስስር ለማሳደግ ዕቅድ ተይዞ ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል፡፡ በምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል የሚደረገው የኃይል ትስስርና ትብብር የቀጣናውን የኤሌክትሪክ አቅርቦትና ተዳራሽነት ለማሻሻል እንዲሁም የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትልቅ መሠረት እንደሆነ አስረድተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም

photo content
+4

ኢትዮጵያ በኃይል ኤክስፖርት  ዕድገት  እያሳየች ነው ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት አስር ዓመታት ለጎረቤት ሀገራት ኤክስፖርት ያደረገው ኃይል የ31 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡን የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር አባል ሀገራት መካከል ያለውን የኃይል አቅርቦትና የገበያን ትስስር ለማጠናከር እንዲሁም በቀጣናው በሚጠበቀው የኢል ኒኖ ስጋት መከላከል ዙሪያ ለመምከር የተዘጋጀው የምክክር ጉባኤ ተጠናቋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ዳይሬክተር ኢንጂነር ሚኪያስ ወንድሙ ስለሀገሪቱ የኃይል ማምረት አቅም እና የኃይል ኤክስፖርት ዕድገት ለቀጣናው ሀገራት ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት እንደገለጹት ኢትዮጵያ ካላት አጠቃላይ የኃይል ምርት ውስጥ የኤክስፖርት ድርሻው ከ6.5 እስከ 10 በመቶ ይደርሳል። የምስራቅ አፍሪካን የኃይል ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ሰፊ ዕቅዶች መያዛቸውን ያብራሩት ኢንጂነር ሚኪያስ እ.ኤ.አ እስከ 2030 ድረስ የኃይል ኤክስፖርት አቅምን ወደ 5 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት ለማሳደግ ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በቀጣይም የኃይል ሽያጭ ንግድን ለማስፋት ከደቡብ ሱዳን፣ ከሶማሊያ እና ከሶማሊላንድ ጋር አዳዲስ የማስተላለፊያ መስመሮችን የመዘርጋት እንዲሁም ከጂቡቲና ከሱዳን ጋር ሁለተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የመገንባት ዕቅድ ተይዞ ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል። የሀገሪቱ የኃይል ማመንጨት ሥርዓት ከ95 በመቶ በላይ በውሃ ላይ የተመሠረተ በመሆኑ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚከሰቱ ተጽዕኖዎችን ለመቋቋም የኃይል ስብጥርን ለማስፋት የሚያስችሉ ዕቅዶች ተቀርፀው እየተተገበሩ መሆናቸውን ኢንጂነር ሚኪያስ ገልፀዋል። የሀገሪቱ የኃይል ማመንጨት ሥርዓቱ በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ውስጥ እንዳይገባ የኃይል ስብጥርን ለማስፋት የሚያስችሉ ዕቅዶች ተቀርፀው እየተተገበሩ መሆናቸውንም ኢንጂነር ሚኪያስ አክለው ገልፀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም

photo content
+3

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፡ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የቀጣይ ዕቅዶች ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የቀጣይ ዕቅዶች አስመልክቶ ያደረጉት ማብራሪያ፡ ኢንጂነር አሸብር ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦ ✅ የኃይል ማመንጨት አቅም ግንባታ እና ኤክስፖርት አፈጻጸም ✅ የ2030 የዲጂታል ስትራቴጂ ትግበራ ✅ በቀጣይ ዓመት የሚከናወኑ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ሙሉ መረጃውን በዩቲዩብ ቻናላችን ይከታተሉ፡ 👉 https://youtu.be/g6GyPt8qZKw 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም

በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የሚገኘውን ዕምቅ የኤሌክትሪክ ሀብት አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል የጋራ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ....///.... በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ያለውን እምቅ የኤሌክትሪክ ሀብት በስፋት
+9
በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የሚገኘውን ዕምቅ የኤሌክትሪክ ሀብት አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል የጋራ ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ....///.... በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ያለውን እምቅ የኤሌክትሪክ ሀብት በስፋት በማልማትና የሀገራትን የኤሌክትሪክ ግሪድ በማስተሳሰር ለቀጣናው ልማት ማዋል እንዲቻል የሀገራት የጋራ ቁርጠኝነትና ትብብር ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ። በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር አባል ሀገራት መካከል ያለውን የኃይል አቅርቦት፣ ፍጆታ እና ትስስር ለማጠናከር የተዘጋጀው የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ስቲሪንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢንጂነር አሸብር ባልቻን ወክለው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ኢንጂነር ያለውአይቀር ማንደፍሮ እንደገለፁት የሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) የኤሌክትሪክ ኃይል እና የዘመናዊ ዕድገት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ሞተር እየሆነ መጥቷል፡፡ ይሁንና በቀጣናው በሚገኙ ማህበረሰቦችና ኢንዱስትሪዎች ዘንድ የኃይል እጥረትና የአስተማማኝነት ችግር አሁንም ከባድ ፈተና እንደሆነ ቀጥሏል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በምስራቅ-አፍሪካ-ቀጣና-የሚገኘውን-ዕምቅ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 4 ቀን 2018 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኃይል አቅርቦቱን በእጥፍ አሳድጓል ....///... የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ከእጥፍ በላይ በማሳደግ የቀጣናውን የኃይል
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኃይል አቅርቦቱን በእጥፍ አሳድጓል ....///... የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ከእጥፍ በላይ በማሳደግ የቀጣናውን የኃይል ትስስር እያጠናከረ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ። ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ  ለኢዚአ እንደገለጹት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን ጽናት፣ አንድነትና ቁርጠኝነት በተግባር የተገለጠበት «ዳግማዊ ዓድዋ» ነው። የግድቡ ግንባታ ኢትዮጵያ በራሷ አቅም የላቀ ስኬት ማስመዝገብ እንደምትችል ለዓለም ያስመሰከረችበትና አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የከፈተችበት ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑንም ጠቁመዋል።   ተጨማሪ ያንብቡ.… https://www.eep.com.et/?amh-news=ታላቁ-የኢትዮጵያ-ህዳሴ-ግድብ-የኃይል-አቅ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 4 ቀን 2018 ዓ.ም

ሪጅኑ በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የሥራ ክፍሎች፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ሠራተኞች እውቅና ሰጠ .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን በ2018 በ
+9
ሪጅኑ በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የሥራ ክፍሎች፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ሠራተኞች እውቅና ሰጠ .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የሥራ ክፍሎች፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ሠራተኞች በዛሬው እለት እውቅና ሰጠ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንዳስታወቁት በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ የጥገና ሠራተኞች፣ ለማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎች፣ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ተቋቁመው ሥራቸውን እያከናወኑ ላሉ ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ሌሎች በሪጅኑ ሥር ለሚገኙ የሥራ ክፍሎች እውቅና ተሰጥቷል፡፡ በዚህም መሠረት በሪጅኑ በስርቆት ምክንያት ወድቀው በነበሩ  የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች መልሶ ግንባታ እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያ ሥራዎች ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ላበረከቱ  ሠራተኞች የምስክር ወረቀት እና የማበረታቻ ሽልማት መበርከቱን ተናግረዋል።   ተጨማሪ ያንብቡ.… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሪጅኑ-በ2018-በጀት-ዓመት-የተሻለ-አፈፃፀም-ላስ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም

እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ! አዲስ ዓመት ሁሌም ተስፋ ይዞ የሚመጣ የበዓላት ሁሉ መጀመሪያ ነው፡፡ የዘመን መቀየር ተስፋችንን የሚያለመልም እና ነገን አልመን ወደፊት እንድንጓዝ
እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ! አዲስ ዓመት ሁሌም ተስፋ ይዞ የሚመጣ የበዓላት ሁሉ መጀመሪያ ነው፡፡ የዘመን መቀየር ተስፋችንን የሚያለመልም እና ነገን አልመን ወደፊት እንድንጓዝ የሚያደርግ እንዲሆን ዛሬን በአግባቡ ማቀድና ዕለት ዕለት በትጋት መሥራት ይጠይቃል፡፡ እንደ ተቋም በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ የያዝነውን ዕቅድ ለማሳካት የምንተጋበት፤ በ2018 በጀት ዓመት ያስመዘግብናቸውን የኦፕሬሽን፣ የፕሮጀክት አፈፃፀምና የፋይናንስ ድሎች የምናስቀጥልበት፣ "የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል" የመሆን ራዕያችንን እውን ለማድረግ የምንሠራበት፣ ሁለንተናዊ ተቋማዊ ስኬት የምናስመዘግብበት እንዲሁም በግል ያቀድናቸውን ውጥኖች ከግብ የምናደርስበት የሠላም፣ የደስታና የስኬት ዘመን እንዲሆን እመኛለሁ!! መልካም አዲስ ዓመት! አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር)፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ

ጳጉሜን 5 — የነገው ቀን   ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ላለፉት 3 ዓመታት ሲተገብረው በቆየው «G.R.I.D» ስትራቴጂ ውስጥ በ«D» የተወከለው «Digital Transformation» (ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን) የተቋሙን አሠራርና የመሠረተ ልማት አያያዝ ወደ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሥርዓት በማሸጋገር ረገድ ትልቅ ምዕራፍ ተሻግሯል። የዲጂታል ትራንስፎርሜሽኑ ዋና ዓላማዎች ✅   አስተማማኝነት፦ በኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ መስመሮች ላይ የሚያጋጥሙ ብልሽቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ቀድሞ መለየትና በፍጥነት ማስተካከል፤ ✅   ውጤታማነት፦ የኃይል ብክነትን በዘመናዊ የመለኪያና የመቆጣጠሪያ መሣሪያዎች መቀነስ፤ ✅   ደህንነት፦ የብሔራዊ የኃይል መረብ (National Grid) ደህንነትንና ሳይበር ጥቃቶችን መከላከል የሚያስችል አስተማማኝ የሳይበር ደኅንነት ሥርዓት መገንባት፤ በዚህ በጳጉሜን 5 «የነገው ቀን» መታሰቢያነት ተቋሙ አገልግሎቱን ፈጣን፣ ዘመናዊና አስተማማኝ ለማድረግ ያስቻሉ ዋና ዋና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትግበራዎች ምን እንደሆኑ ከብዙ በጥቂቱ ለማሳየት እንሞክራለን፡፡ ዋና ዋና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ስኬቶች SCADA/EMS (ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ሥርዓት) በሀገር አቀፍ ደረጃ የኃይል ማመንጫዎችንና ከፍተኛ የቮልቴጅ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን (Substations) በእውነተኛ ጊዜ (Real-time) በዲጂታል መንገድ ለመቆጣጠርና የኃይል መቆራረጥ ሲያጋጥም ወዲያውኑ ምላሽ ለመስጠት የሚያግዝ አውቶሜትድ ሥርዓት ነው፡፡   የማከፋፈያ ጣቢያዎች ዲጂታላይዜሽን የነበሩትን አሮጌ የዘይት ሰርኪዩት ብሬከሮች በዘመናዊ የዲጂታል የጋዝ መቆጣጠሪያዎች በመተካትና የደህንነት ሥርዓቶችን በማዘመን የቴክኒክ ብልሽቶችንና የኃይል ማቋረጥ ጊዜን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ተችሏል።   የውስጥ አሠራርና የፋይናንስ ዲጂታላይዜሽን የተቋሙን የበጀት፣ የንብረት አያያዝ፣ የሰው ሀብትና የግዥ አሠራሮች እንዲሁም የውስጥ ኮሙዩኒኬሽንን ከወረቀት ነፃ ወደሆነ ዲጂታል ሥርዓት በመቀየር ግልጽነትና ቀልጣፋ አሠራር እንዲሰፍን ተደርጓል።   የቴሌኮም መሠረተ ልማት አጠቃቀም በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የተዘረጉ የፋይበር ኦፕቲክስ (OPGW) መስመሮችን ለዲጂታል ዳታ ማስተላለፊያ በመጠቀም የተቋሙን መረጃ መለዋወጥ ከማፈጠኑ ባሻገር አዳዲስ የገቢ አማራጮችን ፈጥሯል።   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዛሬ የሚገነባቸው የዲጂታል መሠረተ ልማቶች «የነገዋን ኢትዮጵያ» በበለጸገ፣ በዘመናዊና በተሳሰረ አረንጓዴ ኤነርጂ ለመምራት የሚያስችሉ ጠንካራ መሠረቶች ናቸው!   #የነገውቀን #ጳጉሜን5 #ኢትዮጵያኤሌክትሪክኃይል #EEP #GRIDStrategy #DigitalTransformation #SmartGrid #Ethiopia 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ከወረቀት ወደ ዲጂታል! ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት! ትናንትን በመማርና በማረም ዛሬን በላቀ ትጋት በመገንባት ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አ
ከወረቀት ወደ ዲጂታል! ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት! ትናንትን በመማርና በማረም ዛሬን በላቀ ትጋት በመገንባት ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የአሶሳ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ ……..///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ኖሪንኮ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን ጋር የጉባ-አ
+7
የአሶሳ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ ……..///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ኖሪንኮ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን ጋር የጉባ-አሶሳ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የአሶሳ 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ፡፡ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የኖሪንኮ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ሚስተር ዱ ዢኦዶግ ናቸው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደገለጹት ተቋሙ ከተከዜ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ጀምሮ በተለያዩ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታዎች ላይ ከኩባንያው ጋር አብሮ ሲሰራ ቆይቷል። ስምምነቱ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለውን የኃይል አቅርቦት አስተማማኝ የሚያደርግና ኢንቨስትመንትን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ መሆኑን ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአሶሳ-2-ባለ-400-ኪሎ-ቮልት-ማከፋፈያ-ጣቢያ-ግ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም

#የተቋምቀን ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ቀን በዓል አከባበር
+8
#የተቋምቀን ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ቀን በዓል አከባበር