Egziabher Meslene እግዚአብሔር ምስሌነ
ይህ ይፋዊ የደብረ ገሊላ ዐማኑኤል ካቴድራል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ት/ቤት ገጽ ነው፡፡ በዚህ ገጽ - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት የጠበቁ ትምህርቶችን እናሰራጫለን፡፡ - የቅድስት ቤተክስቲያናችን እና የሰንበት ት/ቤቱን እንቅስቃሴ ወቅታዊ መረጃ እናደርስበታለን፡፡ ገጹን ለሌሎችም እያጋራችሁ የቤተክርስቲያናችንን አገልግሎት እናፋጥን፡፡ @EMeslene
Больше- Подписчики
- Просмотры постов
- ER - коэффициент вовлеченности
Загрузка данных...
Загрузка данных...
ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምእመናን ስለ ጌታ ትንሣኤ ማስረጃ እያቀረበ ነው:: በዚያን ዘመን ለጌታ ትንሣኤ ማስረጃ ስትጠቅስ በማቴዎስ ወንጌል እንዲህ ይላል ብለህ እንዳትጠቅስ ገና ወንጌላት አልተጻፉም:: ቢጻፉም ማቴዎስ በሕይወት እያለ በቃሉ መመስከር ሲችል ጽሑፉን ማስረጃ ማድረግ አያስፈልግህም:: ስለዚህ ለመነሣቱ ማስረጃዎች ከተነሣ በኋላ ያዩት ሰዎች ነበሩ:: በሕይወት ያሉትን የዓይን ምስክሮችን መጥቀስ ይቻላል:: የዓይን እማኞች ምስክርነት ከጽሑፍ በላይ የታሪክ ማስረጃ ነው:: ስለዚህ ጳውሎስ ስለ ጌታ ትንሣኤ “እነ እገሌ አይተውታል” እያለ መዘርዘርን መረጠ::
በሌሊት ማለፍና በፀሐይ መውጣት መካከል ገና ጨለማ ሳለ ሁለቱ ማርያሞች ማርያም መግደላዊትና የያዕቆብ እናት ማርያም ከሰሎሜ ጋር ሽቱ ሊቀቡት ወደ መቃብሩ ሄዱ። በዚህ ግርማ ሌሊቱ ባልተለየው ድምፀ አራዊቱ በሚሰማበት ሌሊት የአይሁዳውያን ዛቻና የኃያላኑን የሮማ ወታደሮች ቁጣ ተጋፍጠው የክርስቶስን ክቡር ሥጋ ሽቶ ይቀቡ ዘንድ ወደ መቃብሩ ገሰገሱ። እነኚህ ሴቶች የክርስቶስን ሞት ሰምተው መቃብሩን ሊያዩ ከሩቅ የመጡ እንግዶች አልነበሩም ይልቁንም በዕለተ አርብ እየተላጋ ሲወሰድ፣ በየመንገዱ ሲጎተትና መስቀል ተሸክሞ ሲሄድ እያለቀሱ በደም የተዋበ የመስቀሉን መንገድ በእንባ ያጠቡ ሴቶች ናቸው።
የክርስቶስን መከራና ሕመም ኬርኤላይሶን ብለን ያሰብንበት ዕለተ ስቀለት ካለፈ አንድ ሳምንት ሞላው። በስግደትና በሐዘን ያሰብነው ሕማሙ መዳረሻው ለእኛ ካጠላብን የሐዘን ቀንበር ነፃ መሆን ነውና የከፈለልንን ፍፁም ፍቅር ለማሰብ ቅድስት ቤተክርስቲያን የሰሙነ ትንሳዔውን የመጀመሪያ አርብ ቅድስት ቤተክርስቲያን ብላ ትሰይመዋለች።