ru
Feedback
Injibara University

Injibara University

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Injibara University

Канал Injibara University (@injiuniversity) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 19 226 подписчиков, занимая 10 377 место в категории Образование и 1 775 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 19 226 подписчиков.

Согласно последним данным от 01 августа, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 146, а за последние 24 часа — 8, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 28.68%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 14.02% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 512 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 695 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 0.

📝 Описание и контентная политика

Описание канала не предоставлено.

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 02 августа, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Образование.

19 226
Подписчики
+824 часа
+387 дней
+14630 день
Архив постов
photo content

photo content
+9

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የድንች ምርጥ ዘር  ብዜት የመስክ ምልከታ ተካሄደ። ============================ ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አግልግሎት የምርምር ካውንስል አባላት በልደታ ቀበሌ እየለማ የሚገኘውን የድንች ዘር ብዜትን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ዲን ሀብታሙ አድማስ (ዶ/ር) እንደገለፁት ከዚህ በፊት ዩኒቨርሲቲው በለጠና ጉደኔ የሚባሉ ሁለት የድንች ዝርያዎችን ከሶስት እስከ አራት ዓመታት አምርቶ የተሻለ ምርት በማግኘት ለአርሶ-አደሩና ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ዘሩን ማሰራጨቱን ገልፀው የዚህ ሜጋ ፕሮጀክት ምርምር ዓላማም በክረምት ወቅት በሽታን ተቋቁሞ የተሻለ ምርት የሚሰጠውን የድንች ዝርያ በመምረጥ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለአርሶ-አደሩ የማስተዋወቅ ስራ መሆኑን ተናግረዋል። በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ሀገር-በቀል እውቀት አስተባባሪ የሆኑት ወዳጄ አዲስ (ዶ/ር)  እንደገለፁት በ2018 ዓ.ም ከተመደቡት 33 ፕሮጀክቶች ውስጥ የድንች ዘር ብዜት አንዱና ለወደፊት የማህበረሰቡን ችግር ይፈታል ተብሎ የሚታሰብበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቅሰው ለአርሶ-አደሩ የምርጥ ዘር ፍላጎት እንዲሟላ ለማድረግ  በእንደዚህ ዓይነት የምርምር ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት ተደርጎ  እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የዩኒቨርስቲው የሆርቲ ካልቸር መምህርና ተመራማሪ የሆኑት አቶ ንብረት እሽቱ በበኩላቸው ከተለያዩ የግብርና ምርምር ማዕከላት (ደብረ-ብርሃንና አዴት) የመጡ 12 አይነት አዳዲስ የድንች ዝርያዎች በ697 ካ.ሜ ቦታ ላይ በጥሩ ቁመና እየለሙ እንደሚገኙ ገልፀው  ለአርሶ-አደሩ ድንችን በክረምት ወራት  ማምረት አስቸጋሪ ወቅት ስለሆነ በክረምቱ ሳቢያ የሚመጡ በሽታዎችን ተቋቁሞ የተሻለ ምርትና ውጤት መስጠት የሚያስችለውን ዝርያ ለይቶ በቀጣይ ለአርሶ-አደሩ የተሻለ የዘር ብዜት ለማሰራጨት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

photo content
+9

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ተጀመረ፡፡ ======================================== ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር  የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተጀምሯል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) በየዓመቱ በሚካሄደው የተቀናጀ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የአረንጓዴ ልማት እንቅስቃሴ በርካታ ቁጥር ያላቸው የተለያዩ የችግኝ ዝርያዎች መተከላቸውን ገልፀው በቀጣይ ለሚከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሮች ለምግብነት የሚውሉና በገቢ ምንጭነታቸው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው  እንደ አፕል ፣ አቦካዶ፣ ዘይቱን፣ የደጋ ቡና እና መሰል የአትክልትና ፍራፍሬ ዝርያዎችን በስፋት ለመትከል ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ አክለውም ዩኒቨርሲቲው ለግቢው ውበትና አረንጓዴነት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ እ.ኤ.አ በ2025  በሀገር አቀፍ ደረጃ እውቅና የተሰጠው መሆኑን በማስታወስ ለዚከ ታላቅ ስኬት መድረስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላትና  ሰራተኞች  ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል፡፡  የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ እና የምርምር እና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ግብርና እና አረንጓዴ ልማትን የትኩረት መስክ በማድረግ እየሰራ እንደደሚገኝ ገልጸው ከዚህ በፊት ባደረጋቸው  የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሮች በሊዊ ተራራ ላይ ከ167 ሺህ በላይ ችግኖች ተተክለው በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡  በዛሬው ዕለትም የዩኒቨርሲቲው የ2018 ዓ.ም አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በግቢው ውስጥ የተዘጋጁ የዘይቱን ችግኞችን በመትከል በይፋ ተጀምሮ በቀጣይ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሮች ሌሎች በርካታ ቁጥር ያላቸው የችግኝ ዝርያዎች የሚተከሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው የግብርና ኮሌጅ ዲን የሆኑት ሀብታሙ አድማስ (ዶ/ር) በበኩላቸው በእንጅባራ ዩኒቨርሰቲ ግቢ ውስጥ ከ7 ሺህ በላይ የአፕል ችግኝ መተከሉን ገልጸው ባለፉት ዓመታት በዩኒቨርሲቲው የሊዊ ተራራ ከተተከሉ ችግኞች 99 በመቶ በላይ መፅደቃቸውን ተናግረዋል፡፡ የችግኞችን የመጽደቅ ምጣኔ ለማሳደግ እንክብካቤ አስፈላጊ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ሀብታሙ ለዚህም  የሊዊ ተራራ ልማት አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረው በአረንጓዴ ልማት ዘርፉ ለምግብነት የሚውሉና እና ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ሊሆኑ የሚችሉ ችግኞች ለቀጣይ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሮች ለተከላ እየተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በአረንጓዴ አሻራ የአጀማመር መርሃ-ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ዲኖች፣ ሥራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም የአስተዳደር እና አውትሶርስ ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡ ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

photo content

photo content

4_5992178422502136968.pdf2.51 KB

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ መሰረት በኦንላይን ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ ተወዳዳሪዎች ከዚህ በታች በተገለፀላችሁ ዝርዝር መሰ
+2
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ መሰረት በኦንላይን ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ ተወዳዳሪዎች ከዚህ በታች በተገለፀላችሁ ዝርዝር መሰረት ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ብቃትና ሰው ኃብት አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ ቢሮ ተገኝታችሁ ፈተናውን በኦንላይን እንድትፈተኑ እናሳስባለን።

photo content
+9

photo content
+9

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ተጠናቀቀ። ሐምሌ16 /2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ6ዙሮች በበይነ መረብ (Online) እና በወረቀት ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም ድረስ  ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ዛሬ በሰላም ተጠናቋል።   የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በርካታ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች የተሰተናገዱበት  ዓመት መሆኑን ገልፀው የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንትና የፈተና አስፈፃሚ ግብረ-ሀይሉ ተማሪዎች  ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ  አስቻይ ሁኔታዎችን በመፍጠር በሰሩት የተቀናጀ ሥራ ፈተናው በሀገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የፈታና መርሃ-ግብር መሰረት ያለምንም ችግር በሰላም መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች  ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት (ዶ/ር) አእምሮ ታደሰ እንደገለፁት ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ  እስከ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም ድረስ ከአማራ ክልል አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር እና ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የ12ኛ  ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በበይነ መረብ (Online) እና በወረቀት ለመውሰድ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ 10389 የሚሆኑ የተፈጥሮና የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎች ፈተናቸውን በ6ዙር ያለምንም ችግር ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ  መውሰዳቸውን ገልፀው በፈተና ወቅት ከቅድመ ዝግጅት እስከ ፈተናው ማጠቃለያ ድረስ በየደረጃው የራሳቸውን አስተዋፅኦ ላበረከቱ የዩኒቨርሲቲው የፈተና አስፈፃሚ ግብረ ሀይል አባላት ምስጋና አቅርበዋል። በትምህርት ሚኒስቴር የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የበይነ-መረብ (online) ፈተና ማዕከል ሀላፊ የሆኑት አቶ ጌትነት ታመነ በበኩላቸው  2376  የሚሆኑ ተማሪዎች ፈተናቸውን በበይነ መረብ (online) እንዲሁም  8013 የሚሆኑት ደግሞ በወረቀት በአጠቃላይ 10389 የሚሆኑ የተፈጥሮና የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎች ፈተናውን ያለምንም ችግር መውሰዳቸውን ገልፀው ፈተናው ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከተው ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል። ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

የ6ኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የበይነመረብ (online) ፈተና መሰጠት ተጀመረ፡፡ ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራዩኒቨርሲቲ ከሐምሌ 14/2018 እስከ ሐምሌ16/2018 በበይነመረብ (on
+6
የ6ኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ  የበይነመረብ (online) ፈተና መሰጠት ተጀመረ፡፡ ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራዩኒቨርሲቲ ከሐምሌ 14/2018 እስከ ሐምሌ16/2018 በበይነመረብ (online) የሚሰጠው የ6ኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ የ12ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የጥኋት መርሀ ግብር በእንግሊዘኛ ቋንቋ ፈተና ተጀምሯል ። ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

ለ6ኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ገለፃ ተደረገ። በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፈተናቸውን በበይነ መረብ (online) ለሚወስዱ የመጨረሻ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ
+4
ለ6ኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ገለፃ ተደረገ። በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፈተናቸውን በበይነ መረብ (online) ለሚወስዱ የመጨረሻ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ  ተፈታኝ ተማሪዎች  በዛሬው ዕለት ገለፃ ተደርጎላቸዋል። የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር የፈተና ክፍል ሀላፊ የሆኑት አቶ አማረ ታደሰ እንደገለፁት በዚህ ዙር 190 የሚሆኑ  የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ  መልቀቂያ ፈተናቸውን በበይነ መረብ (online) የሚወስዱ መሆናቸውን ገልፀው ተማሪዎች በቆይታቸው ጊዜ የዩኒቨርሲቲውን ህግና ደንብ አክብረው ፈተናቸውን በአግባቡ እንዲፈተኑ አሳስበዋል። በትምህርት ሚኒስትር የእንጅባራ ዪኒቨርሲቲ የበይነ-መረብ (online) ፈተና ማዕከል ሀላፊ  የሆኑት አቶ ጌትነት ታመነ በበኩላቸው በፈተናው ወቅት ስለተፈቀዱና ስለተከለከሉ ነገሮች ለተፈታኞች ያብራሩ ሲሆን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ አዱኛ አልበል ደግሞ በፈተና ወቅት የሚያጋጥሙ ማንኛውም የቴክኒክ ችግሮች ካሉ ስራ ክፍሉ ዝግጁ መሆኑን ለተፈታኞች አስረድተዋል ። ፈተናውም ከነገ ሐምሌ14/2018 ዓ.ም  ጀምሮ እስከ ሐምሌ16/2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ ለሶስት ቀናት የሚሰጥ ይሆናል። ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የቆየው 5ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተጠናቀቀ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው በበይነ-መረብ (Online) ሲሰጥ የቆየው የ5
+7
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የቆየው 5ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተጠናቀቀ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው  በበይነ-መረብ (Online) ሲሰጥ የቆየው የ5ኛው ዙር የማህበራዊ ዘርፍ ተፈታኝ ተማሪዎች ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዛሬ በሠላም ተጠናቋል። የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር ሀብታሙ ዘገየ (ዶ/ር) እንደገለፁት በዩኒቨርሲቲው  ከሐምሌ 9/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ613 ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online)  ሲሰጥ የቆየው   የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና  ምንም አይነት ችግር ሳያጋጥም በሰላም መጠናቀቁን ተናግረዋል ። ዶክተር ሀብታሙ አያይዘውም እንጅባራ ዩኒቨርስቲ ከነበሩት የኮምፒውተር ቤተ-ሙከራ ክፍሎች በተጨማሪ 2 የኮምፒውተር ቤተ-ሙከራ ክፍሎችን 80 ዘመናዊ ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን ተጠቅሞ በማዘጋጀት የፈተና ሂደቱ ስኬታማ እንዲሆን ማድረጉን ገልፀዋል። በትምህርት ሚኒስቴር የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የበየነ መረብ  የፈተና ማዕከል ኃላፊ የሆኑት አቶ ጌትነት ታመነ እንደገለፁት ዩኒቨርሲቲው ለፈተናው አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረጉ ምንም አይነት የኢንተርኔትም ሆነ የመብራት መቆራረጥ ሳያጋጥም 5ኛው ዙር ማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተና መጠናቀቁን ተናግረው  ለፈተና ሂደቱ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ለነበራቸው የዩኒቨርቲው ማኔጅመንት እና የፈተና ግብረ-ሀይል አባላት ምስጋና አቅርበዋል ። በ6ኛው  ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና 191  ተማሪዎች ከነገ ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ16/2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ 3 ቀናት ፈተናውን በዩኒቨርሲቲው እንደሚወስዱ ተገልጿል። ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

Check out A.T.M's video! #TikTok https://vm.tiktok.com/ZSXUcHaJe/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

photo content
+9

photo content

photo content
+9

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ፈታኝ መምህራን እና አስተባባሪዎች የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲን ግቢ እና ዘንገና ሀይቅን  ጎበኙ።   ሐምሌ 9/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ   በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ   በተለያዩ ዙሮች ሲሰጥ የነበረውን ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ሲያስፈትኑና ሲያስተባብሩ የነበሩ መምህራን እና ፈተና ማዕከል አስተባባሪዎች የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ እና ዘንገና ሀይቅን ጎብኝተዋል።   በጉብኝቱ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር፣ ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት በተጨማሪ ግብርና እና አረንጓዴ ልማት፣ የማህበረሰብ ጤና፣ ቱሪዝም እና ኢንተርፕራይዝ ልማት እንዲሁም የአገው ባህል ቋንቋና ታሪክ ላይ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል የመጡ ፈታኝ መምህራን የአገውን ባህል እና አካባቢውን እንዲያውቁ  የጉብኝት መርሃ-ግብሩ መዘጋጀቱን ገልፀዋል።  ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈታኝ መምህራን እና የፈተና ማዕከል ኃላፊዎች በዩኒቨርሲቲው እየተሰሩ ያሉ የሁለገብ አዳራሽ፣ መማሪያ ክፍል፣ የመምህራን መኖሪያ አፓርታማ ግንባታዎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን አረንጓዴ ልማት ሥራዎችንና  ዘንገና ሀይቅን ጎብኝተው  ፕሬዝዳንቱ አክለውም እንጅባራ ዩኒቨርስቲ ወደ ልህቀት ምዕራፍ በመሸጋገር እና ራስ ገዝ ለመሆን ሱታና ንግድና ማማከር ሥራዎች ኢንተርፕራይዝን በማቋቋም በህትመት፣ በኢንዱስትሪ እና ግብርና ሜካናይዜሽን ላይ በመሳተፍ ራሱን እያጠናከረ እንደሚገኝም ተናግረዋል።  የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት ኃላፊ እና የምርምር እና ማህበረሰብና አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በግብርና እና አረንጓዴ ልማት ትኩረት መስክ  ከለምርምር ከመማሪያነት ባለፈ ለገቢ ምንጭ የሆኑ በርካታ ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በጉብኝት መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ሃሳብና አስተያየት የሰጡት ፈታኝ መምህራንና አስተባባሪዎች ዩኒቨርሲቲው እያከናወናቸው ባሉ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችና ለአካባባቢው ማህበረሰብ የእንግዳ ተቀባይነት ባህል ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በጉብኝቱ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የፈተና ማዕከል አስተባባሪዎች እና ፈታኝ መምህራን ተሳትፈዋል። ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!