Injibara University
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Injibara University 的分析概览
频道 Injibara University (@injiuniversity) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 19 219 名订阅者,在 教育 类别中位列第 10 377,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 775 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 19 219 名订阅者。
根据 01 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 146,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 28.68%。内容发布后 24 小时内通常能获得 14.02% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 512 次浏览,首日通常累积 2 695 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 02 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。
19 219
订阅者
+824 小时
+387 天
+14630 天
帖子存档
19 219
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የድንች ምርጥ ዘር ብዜት የመስክ ምልከታ ተካሄደ።
============================
ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አግልግሎት የምርምር ካውንስል አባላት በልደታ ቀበሌ እየለማ የሚገኘውን የድንች ዘር ብዜትን ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ዲን ሀብታሙ አድማስ (ዶ/ር) እንደገለፁት ከዚህ በፊት ዩኒቨርሲቲው በለጠና ጉደኔ የሚባሉ ሁለት የድንች ዝርያዎችን ከሶስት እስከ አራት ዓመታት አምርቶ የተሻለ ምርት በማግኘት ለአርሶ-አደሩና ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ዘሩን ማሰራጨቱን ገልፀው የዚህ ሜጋ ፕሮጀክት ምርምር ዓላማም በክረምት ወቅት በሽታን ተቋቁሞ የተሻለ ምርት የሚሰጠውን የድንች ዝርያ በመምረጥ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለአርሶ-አደሩ የማስተዋወቅ ስራ መሆኑን ተናግረዋል።
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ሀገር-በቀል እውቀት አስተባባሪ የሆኑት ወዳጄ አዲስ (ዶ/ር) እንደገለፁት በ2018 ዓ.ም ከተመደቡት 33 ፕሮጀክቶች ውስጥ የድንች ዘር ብዜት አንዱና ለወደፊት የማህበረሰቡን ችግር ይፈታል ተብሎ የሚታሰብበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቅሰው ለአርሶ-አደሩ የምርጥ ዘር ፍላጎት እንዲሟላ ለማድረግ በእንደዚህ ዓይነት የምርምር ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የዩኒቨርስቲው የሆርቲ ካልቸር መምህርና ተመራማሪ የሆኑት አቶ ንብረት እሽቱ በበኩላቸው ከተለያዩ የግብርና ምርምር ማዕከላት (ደብረ-ብርሃንና አዴት) የመጡ 12 አይነት አዳዲስ የድንች ዝርያዎች በ697 ካ.ሜ ቦታ ላይ በጥሩ ቁመና እየለሙ እንደሚገኙ ገልፀው ለአርሶ-አደሩ ድንችን በክረምት ወራት ማምረት አስቸጋሪ ወቅት ስለሆነ በክረምቱ ሳቢያ የሚመጡ በሽታዎችን ተቋቁሞ የተሻለ ምርትና ውጤት መስጠት የሚያስችለውን ዝርያ ለይቶ በቀጣይ ለአርሶ-አደሩ የተሻለ የዘር ብዜት ለማሰራጨት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
19 219
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ተጀመረ፡፡
========================================
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተጀምሯል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) በየዓመቱ በሚካሄደው የተቀናጀ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የአረንጓዴ ልማት እንቅስቃሴ በርካታ ቁጥር ያላቸው የተለያዩ የችግኝ ዝርያዎች መተከላቸውን ገልፀው በቀጣይ ለሚከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሮች ለምግብነት የሚውሉና በገቢ ምንጭነታቸው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው እንደ አፕል ፣ አቦካዶ፣ ዘይቱን፣ የደጋ ቡና እና መሰል የአትክልትና ፍራፍሬ ዝርያዎችን በስፋት ለመትከል ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ዩኒቨርሲቲው ለግቢው ውበትና አረንጓዴነት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ እ.ኤ.አ በ2025 በሀገር አቀፍ ደረጃ እውቅና የተሰጠው መሆኑን በማስታወስ ለዚከ ታላቅ ስኬት መድረስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ እና የምርምር እና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ግብርና እና አረንጓዴ ልማትን የትኩረት መስክ በማድረግ እየሰራ እንደደሚገኝ ገልጸው ከዚህ በፊት ባደረጋቸው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሮች በሊዊ ተራራ ላይ ከ167 ሺህ በላይ ችግኖች ተተክለው በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡
በዛሬው ዕለትም የዩኒቨርሲቲው የ2018 ዓ.ም አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በግቢው ውስጥ የተዘጋጁ የዘይቱን ችግኞችን በመትከል በይፋ ተጀምሮ በቀጣይ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሮች ሌሎች በርካታ ቁጥር ያላቸው የችግኝ ዝርያዎች የሚተከሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የግብርና ኮሌጅ ዲን የሆኑት ሀብታሙ አድማስ (ዶ/ር) በበኩላቸው በእንጅባራ ዩኒቨርሰቲ ግቢ ውስጥ ከ7 ሺህ በላይ የአፕል ችግኝ መተከሉን ገልጸው ባለፉት ዓመታት በዩኒቨርሲቲው የሊዊ ተራራ ከተተከሉ ችግኞች 99 በመቶ በላይ መፅደቃቸውን ተናግረዋል፡፡
የችግኞችን የመጽደቅ ምጣኔ ለማሳደግ እንክብካቤ አስፈላጊ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ሀብታሙ ለዚህም የሊዊ ተራራ ልማት አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረው በአረንጓዴ ልማት ዘርፉ ለምግብነት የሚውሉና እና ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ሊሆኑ የሚችሉ ችግኞች ለቀጣይ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሮች ለተከላ እየተዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በአረንጓዴ አሻራ የአጀማመር መርሃ-ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ዲኖች፣ ሥራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም የአስተዳደር እና አውትሶርስ ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
19 219
+2
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ መሰረት በኦንላይን ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ ተወዳዳሪዎች ከዚህ በታች በተገለፀላችሁ ዝርዝር መሰረት ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ብቃትና ሰው ኃብት አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ ቢሮ ተገኝታችሁ ፈተናውን በኦንላይን እንድትፈተኑ እናሳስባለን።
19 219
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ተጠናቀቀ።
ሐምሌ16 /2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ6ዙሮች በበይነ መረብ (Online) እና በወረቀት ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም ድረስ ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ዛሬ በሰላም ተጠናቋል።
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በርካታ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች የተሰተናገዱበት ዓመት መሆኑን ገልፀው የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንትና የፈተና አስፈፃሚ ግብረ-ሀይሉ ተማሪዎች ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ አስቻይ ሁኔታዎችን በመፍጠር በሰሩት የተቀናጀ ሥራ ፈተናው በሀገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የፈታና መርሃ-ግብር መሰረት ያለምንም ችግር በሰላም መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት (ዶ/ር) አእምሮ ታደሰ እንደገለፁት ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም ድረስ ከአማራ ክልል አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር እና ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በበይነ መረብ (Online) እና በወረቀት ለመውሰድ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ 10389 የሚሆኑ የተፈጥሮና የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎች ፈተናቸውን በ6ዙር ያለምንም ችግር ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ መውሰዳቸውን ገልፀው በፈተና ወቅት ከቅድመ ዝግጅት እስከ ፈተናው ማጠቃለያ ድረስ በየደረጃው የራሳቸውን አስተዋፅኦ ላበረከቱ የዩኒቨርሲቲው የፈተና አስፈፃሚ ግብረ ሀይል አባላት ምስጋና አቅርበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የበይነ-መረብ (online) ፈተና ማዕከል ሀላፊ የሆኑት አቶ ጌትነት ታመነ በበኩላቸው 2376 የሚሆኑ ተማሪዎች ፈተናቸውን በበይነ መረብ (online) እንዲሁም 8013 የሚሆኑት ደግሞ በወረቀት በአጠቃላይ 10389 የሚሆኑ የተፈጥሮና የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎች ፈተናውን ያለምንም ችግር መውሰዳቸውን ገልፀው ፈተናው ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከተው ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
19 219
+6
የ6ኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የበይነመረብ (online) ፈተና መሰጠት ተጀመረ፡፡
ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራዩኒቨርሲቲ
ከሐምሌ 14/2018 እስከ ሐምሌ16/2018 በበይነመረብ (online) የሚሰጠው የ6ኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ የ12ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የጥኋት መርሀ ግብር በእንግሊዘኛ ቋንቋ ፈተና ተጀምሯል ።
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
19 219
+4
ለ6ኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ገለፃ ተደረገ።
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፈተናቸውን በበይነ መረብ (online) ለሚወስዱ የመጨረሻ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተፈታኝ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ገለፃ ተደርጎላቸዋል።
የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር የፈተና ክፍል ሀላፊ የሆኑት አቶ አማረ ታደሰ እንደገለፁት በዚህ ዙር 190 የሚሆኑ የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተናቸውን በበይነ መረብ (online) የሚወስዱ መሆናቸውን ገልፀው ተማሪዎች በቆይታቸው ጊዜ የዩኒቨርሲቲውን ህግና ደንብ አክብረው ፈተናቸውን በአግባቡ እንዲፈተኑ አሳስበዋል።
በትምህርት ሚኒስትር የእንጅባራ ዪኒቨርሲቲ የበይነ-መረብ (online) ፈተና ማዕከል ሀላፊ የሆኑት አቶ ጌትነት ታመነ በበኩላቸው በፈተናው ወቅት ስለተፈቀዱና ስለተከለከሉ ነገሮች ለተፈታኞች ያብራሩ ሲሆን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ አዱኛ አልበል ደግሞ በፈተና ወቅት የሚያጋጥሙ ማንኛውም የቴክኒክ ችግሮች ካሉ ስራ ክፍሉ ዝግጁ መሆኑን ለተፈታኞች አስረድተዋል ።
ፈተናውም ከነገ ሐምሌ14/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ16/2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ ለሶስት ቀናት የሚሰጥ ይሆናል።
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
19 219
+7
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የቆየው 5ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተጠናቀቀ
ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
በዩኒቨርሲቲው በበይነ-መረብ (Online) ሲሰጥ የቆየው የ5ኛው ዙር የማህበራዊ ዘርፍ ተፈታኝ ተማሪዎች ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዛሬ በሠላም ተጠናቋል።
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር ሀብታሙ ዘገየ (ዶ/ር) እንደገለፁት በዩኒቨርሲቲው ከሐምሌ 9/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ613 ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምንም አይነት ችግር ሳያጋጥም በሰላም መጠናቀቁን ተናግረዋል ።
ዶክተር ሀብታሙ አያይዘውም እንጅባራ ዩኒቨርስቲ ከነበሩት የኮምፒውተር ቤተ-ሙከራ ክፍሎች በተጨማሪ 2 የኮምፒውተር ቤተ-ሙከራ ክፍሎችን 80 ዘመናዊ ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን ተጠቅሞ በማዘጋጀት የፈተና ሂደቱ ስኬታማ እንዲሆን ማድረጉን ገልፀዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የበየነ መረብ የፈተና ማዕከል ኃላፊ የሆኑት አቶ ጌትነት ታመነ እንደገለፁት ዩኒቨርሲቲው ለፈተናው አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረጉ ምንም አይነት የኢንተርኔትም ሆነ የመብራት መቆራረጥ ሳያጋጥም 5ኛው ዙር ማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተና መጠናቀቁን ተናግረው ለፈተና ሂደቱ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ለነበራቸው የዩኒቨርቲው ማኔጅመንት እና የፈተና ግብረ-ሀይል አባላት ምስጋና አቅርበዋል ።
በ6ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና 191 ተማሪዎች ከነገ ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ16/2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ 3 ቀናት ፈተናውን በዩኒቨርሲቲው እንደሚወስዱ ተገልጿል።
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
19 219
Check out A.T.M's video! #TikTok https://vm.tiktok.com/ZSXUcHaJe/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite
19 219
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ፈታኝ መምህራን እና አስተባባሪዎች የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲን ግቢ እና ዘንገና ሀይቅን ጎበኙ።
ሐምሌ 9/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ዙሮች ሲሰጥ የነበረውን ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ሲያስፈትኑና ሲያስተባብሩ የነበሩ መምህራን እና ፈተና ማዕከል አስተባባሪዎች የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ እና ዘንገና ሀይቅን ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር፣ ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት በተጨማሪ ግብርና እና አረንጓዴ ልማት፣ የማህበረሰብ ጤና፣ ቱሪዝም እና ኢንተርፕራይዝ ልማት እንዲሁም የአገው ባህል ቋንቋና ታሪክ ላይ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል የመጡ ፈታኝ መምህራን የአገውን ባህል እና አካባቢውን እንዲያውቁ የጉብኝት መርሃ-ግብሩ መዘጋጀቱን ገልፀዋል።
ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈታኝ መምህራን እና የፈተና ማዕከል ኃላፊዎች በዩኒቨርሲቲው እየተሰሩ ያሉ የሁለገብ አዳራሽ፣ መማሪያ ክፍል፣ የመምህራን መኖሪያ አፓርታማ ግንባታዎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን አረንጓዴ ልማት ሥራዎችንና ዘንገና ሀይቅን ጎብኝተው
ፕሬዝዳንቱ አክለውም እንጅባራ ዩኒቨርስቲ ወደ ልህቀት ምዕራፍ በመሸጋገር እና ራስ ገዝ ለመሆን ሱታና ንግድና ማማከር ሥራዎች ኢንተርፕራይዝን በማቋቋም በህትመት፣ በኢንዱስትሪ እና ግብርና ሜካናይዜሽን ላይ በመሳተፍ ራሱን እያጠናከረ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት ኃላፊ እና የምርምር እና ማህበረሰብና አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በግብርና እና አረንጓዴ ልማት ትኩረት መስክ ከለምርምር ከመማሪያነት ባለፈ ለገቢ ምንጭ የሆኑ በርካታ ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በጉብኝት መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ሃሳብና አስተያየት የሰጡት ፈታኝ መምህራንና አስተባባሪዎች ዩኒቨርሲቲው እያከናወናቸው ባሉ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችና ለአካባባቢው ማህበረሰብ የእንግዳ ተቀባይነት ባህል ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በጉብኝቱ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የፈተና ማዕከል አስተባባሪዎች እና ፈታኝ መምህራን ተሳትፈዋል።
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
