ru
Feedback
UoG CMHS students union

UoG CMHS students union

Открыть в Telegram

ይህ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የህ/ጤ/ሳ/ኮ ተማሪዎች የቴሌግራም ቻናል ነው። ማንኛውንም ተማሪን👷👨‍🏫 👩‍🏫 የሚመለከት ጥያቄ እንዲሁም አስተያየት ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ማቅረብ ይችላሉ። @samuelgetinet @ghoo3e 👉 ትኩረት ለተማሪዎች 👈

Больше
5 182
Подписчики
+1824 часа
+627 дней
+20630 день
Архив постов
📢 አስቸኳይ የጉዞ ማስታወቂያ❗️‼️ ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ካምፓስ (ህ.ጤ.ሳ.ኮ) መደበኛ እና ተመራቂ ተማሪ እና የቴዲ፤ ማራኪ፤ ፋሲል ካምፓሶች ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ፤ በመጀመሪያ ሰላምታችን ይድረሳችሁ እያልን፣ የአመቱ ማጠናቀቂያ ላይ በመድረሳችንና አብዛኛው ተማሪ በሰኔ 20 ቀን ከግቢ እንደሚወጣ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ከጎንደር ወደ ደሴ፣ ወልዲያ እና ጋሻና መጓዝ ለምትፈልጉ፤ እንዲሁም በደሴ መስመር ለምሳሌ ወደ  "ደብረ ብርሃን"  እና "አዲስ አበባ" የምትሄዱ (እስከ ደሴ በዚህ መኪና ተጉዛችሁ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በሌላ መኪና መገናኘት ለምትፈልጉ ጭምር) ምዝገባ መጀመሩን እንገልጻለን። 📌 የጉዞው ዝርዝር መረጃ መነሻ ቦታ፦ከጤና ሳይንስ ካምፓስ እና የቴዲ  :  ማራኪ ካምፓስ (ግቢው ድረስ መኪናው ይመጣል) መነሻ ቀን እና ሰዓት፦ሰኔ 20 ቀን፣ ማለዳ (በጠዋት) መድረሻዎች፦ ደሴ፣ ወልዲያ፣ ጋሻና (እና በደሴ መስመር ያሉ ከተሞች) ✨ የዚህ የጉዞ መርሃ ግብር ልዩ ጥቅሞች 🛑 የፍተሻ መጉላላትን መቀነስ፦ ጉዞው በተደራጀ መልኩ ስለሚያስተባብር መንገዶች ላይ የሚኖሩትን አላስፈላጊ ፍተሻዎችና እንግልቶች በእጅጉ ይቀንሳል። ⏱️ በሰዓቱ መድረስ፦ ያለምንም መዘግየት ጉዞው በቀጥታ ከግቢ በመነሳት ፈጣንና ቀልጣፋ በሆነ መንገድ መድረሻችሁ ያደርሳችኋል። 🚷 ከእንግልት መራቅ፦ ወደ አዘዞ መናኸሪያ በመሄድ ተጨማሪ ድካምና የትራንስፖርት ወጪ ማውጣት አይጠበቅባችሁም። መኪናው እዚሁ የጤና ግቢ ድረስ በመምጣት በቀጥታ ይጭናችኋል። 📝 የምዝገባና የግንኙነት አድራሻዎች መጓዝ የምትፈልጉ ተማሪዎች ከታች በተጠቀሱት ስልክ ቁጥሮች በመደወል ወይም አጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS) በመላክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳስባለን። 📞 የመመዝገቢያ ስልኮች፦ 0933243896 => ደሴ ለመመዠገብ 0946256365 => ወልድያ ለመመዠገብ 0953820014 => ጋሻና እና አቅራቢ ለመመዠገብ > 💡 ማሳሰቢያ፦ የመመዝገቢያ ቀን ከዛሬ ጀምሮ እስከ እሮብ ማታ ድረስ መመዝገብ ትችላላችሁ::  ከጉዞው ጋር በተያያዘ ማንኛውንም አይነት ቅሬታ፣ አስተያየት ወይም ጥያቄ ካላችሁ ከላይ በተጠቀሱት ስልኮች በመደወልም ሆነ በቴክስት ወይም ከታች ባለው telegram link መጠየቅ ትችላላችሁ። ▶️  https://t.me/+yI4efbRFQ7xhYWZk >  በያላችሁበት ሰላማችሁ ይብዛ፤ መልካም የፈተና እና የትርኢት ጊዜ፣ እንዲሁም ደህንነቱ የተጠበቀ መልካም ጉዞ ይመኝላችኋል! ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

‼️❗️ማስታወቂያ❗️‼️ ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህ.ሴ.ጣ.ኮ ግቢ ተመራቂ እና መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ፤ ለሁሉም ተመራቂ እና መደበኛ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች የዘንድሮው የትምህርት ዘመን እየተጠናቀቀ ስለሆነ፣ ተመራቂ ተማሪዎች በሪጅስትራል ኦፊስ በተገለፀው ቀን ፤ ተመራቂ ያልሆናችሁ ደግሞ ከነገ ጀምሮ እስከ "ሰኔ 19/2018 ዓ.ም" ድረስ የክሊራንስ ሂደታችሁን በአግባቡ አጠናቃችሁ ከወዲሁ ሻንጣችሁን እና ጉዟችሁን እንድታመቻቹ በታላቅ አክብሮት እናሳስባለን። ይህንን አስቀድመን ለማሳወቅ የወደድነው፣ ከ "ሰኔ 21/2018 ዓ.ም" ጀምሮ ግቢው ለተማሪዎች የሚሰጠውን ማንኛውንም አይነት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ የሚያቋርጥ ስለሆነ፣ ተማሪዎች ይህንን ተረድታችሁ ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ፣ ከካፌ ውጪ (Non-Cafe) ለሆናችሁ ተማሪዎች ወርሃዊ የኑሮ መደጎሚያ (Cost-sharing) ገንዘባችሁን በተመለከተ፤ ምናልባትም በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት (ቢበዛ በሁለት ቀናት ውስጥ) ወደ የባንክ ሂሳባችሁ ገቢ የሚደረግ መሆኑን እንገልጻለን። ከህ.ጤ.ሳ.ኮ ተማሪዎች አገልግሎት ዲን ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

ግልፅ ለማድረግ ያህል ዋናው በር ክፍት የሚሆነው ከጠዋቱ 12:00 እስከ ምሽቱ 2:00 ብቻ ነው። በዚህ ሰአት ግን የፈለገው ተማሪ መውጣትም መግባትም ይችላል። ለዛሬ ጥበቃዎች ስላልሰሙ ነበር ዝግ የነበረው።

ለተወዳጅ ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ፤ እንኳን ለዚህ ታላቅ እና ታሪካዊ የህይወት ምዕራፍ በሰላም አደረሳችሁ! ላለፉት ዓመታት በታላቁ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቆይታችሁ ብዙ ውጣ ውረዶችን፣ እንቅልፍ አልባ ሌሊቶችን፣ የናፍቆት ጊዜያትን እና እልህ አስጨራሽ ፈተናዎችን በፅናት አልፋችሁ ዛሬ ለዚህ ክብር በቅታችኋል። ይህ እስካሁን ያሳለፋችሁት ያልተቋረጠ ጥረት፣ ትዕግስት እና ትጋት የውስጣዊ ጥንካሬያችሁ እና የዓላማችሁ ፅናት ህያው ምስክር ነው። ከነገ ጀምሮ የምትቀመጡበት አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና እስካሁን በግቢያችን የገነባችሁትን ጥልቅ እውቀት፣ ክህሎት እና ብቃት በተግባር የምታሳዩበት የመጨረሻው ማረጋገጫ እንጂ የሚያስፈራ እንቅፋት አይደለም። እናንተ ይህንን ፈተና በብቃት ለማለፍ እና አሸናፊ ሆናችሁ ለመውጣት የሚያስችል ሙሉ አቅም፣ እውቀት እና በቂ ዝግጅት እንዳላችሁ ፅኑ እምነት አለን። በፈተናው ወቅት መረጋጋትን፣ በራስ መተማመንን እና ሙሉ ትኩረትን እንድትላበሱ አደራ እላለሁ። የተማራችሁትን አስታውሱ፣ በራሳችሁ እመኑ፣ እንዲሁም የድካማችሁን ፍሬ የምትበሉበት ጊዜ አሁን መሆኑን አትዘንጉ። እኛ የተማሪዎች ህብረት አባላት እና አመራሮች ሁልጊዜም ከጎናችሁ ነን፤ በውጤታማነታችሁም ሙሉ እምነት አለን። ፈጣሪ መልካም የፈተና ጊዜ፣ የጠራ እና ብሩህ አእምሮ፣ እንዲሁም ታላቅ ስኬት እንዲያድላችሁ ከልብ እመኛለሁ። በድል እንደምንገናኝ አልጠራጠርም፤ በርቱ፣ ከእናንተ ጋር ነን! መልካም እድል! ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

‼️❗️ማስታወቂያ‼️❗️ ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ የህ.ሴ.ጣ.ኮ ግቢ ተማሪዎች በሙሉ፤ የተማሪዎቻችንን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ የተሻለ፣ ቀልጣፋ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ለማድረግ ሲሰራ የነበረው የእግረኛ ድልድይ ዝግጅቱ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ከነገ ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑን በታላቅ ደስታ እናሳውቃለን። በመሆኑም ማንኛውም የካምፓሳችን ተማሪ ከነገ ጀምሮ ይህንን የእግረኛ ድልድይ በመጠቀም የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴውን ማድረግ የሚችል መሆኑን እንገልፃለን። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የካምፓሳችንን ዋና በር አጠቃቀም በተመለከተ አዲስ የሰዓት ገደብ የወጣ መሆኑን እያሳወቅን፤ ተማሪዎች ዋናውን በር መጠቀም የሚችሉት "በምሽት ክፍለ ጊዜ ከ12፡00 እስከ 2፡00 ሰዓት" (በሀገር ውስጥ/በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር) ብቻ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን። ከተጠቀሰው ሰዓት ውጪ በዋናው በር መጠቀም የማይቻል መሆኑን ተገንዝባችሁ፣ እንቅስቃሴያችሁን በተፈቀደው ሰዓት ብቻ እንድታደርጉ እና በሌሎች ሰዓታት አዲሱን የእግረኛ ድልድይ እንድትጠቀሙ በአክብሮት እንጠይቃለን። ትብብራችሁ ለጋራ ደህንነታችን እና ለግቢያችን ሰላማዊ እንቅስቃሴ እጅግ ወሳኝ ነው። ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

የተማሪዎች ላውንጅ ቁልፍ የጣልክ/ሽ ተማሪ ከተማሪዎች ህብረት ቢሮ መጥተህ/ሽ መውሰድ ትችላለህ/ያለሽ:: ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

ተማሪ Samuel Amere የATM ካርድ ስለተገኘልህ ከተማሪዎች ህብረት ቢሮ መጥተህ መውሰድ ትችላለህ:: ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

"New Announcement" ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለ
"New Announcement"
  ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️

የተማሪዎች ፑል ቤት ላይ አንድ ጆሮ airpod የጣልክ ተማሪ ከተማሪዎች ህብረት ቢሮ መጥተህ መውሰድ ትችላለህ ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️

"New Urgent Announcement"
ውድ የ2018 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ! ከዚህ ቀደም ለExit Exam 750 ብር ክፍያ መክፈላችሁ ይታወቃል። በመሆኑም ዮኒቨርሲቲው ይህንን ክፍያ በራሱ የሚሸፍን በመሆኑ ምክንያት እናንተ የከፈላችሁት ገንዘብ ለሁላችሁም ተመላሽ እንዲሆን የተወሰነ መሆኑን እያሳወቅን። ገንዘባችሁን ለመውሰድ በመጀመሪያ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ ሬጅስትራል ካሉት የየዲፓርትመንቱ ኦፊሰሮች በመቀበል ካሽ ገንዘቡን በመጀመሪያ ከከፈላችሁበት የፋይናንስ ቢሮ በመስኮት በኩል ሄዳችሁ ደረሰኛችሁን መልሳችሁ በመስጠት በተጨማሪም ሙሉ ስማችሁን እና የራሳችሁ የሆነ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር እንድታስመዘግቡ ለማሳወቅ እንወዳለን።
ማሳሰቢያ:- የምዝገባው ቀን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ሰዓት ጀምሮ እስከ ነገ ማለትም አርብ ቀን: 5/10/2018 ዓ.ም ቀኑን ሙሉ ብቻ ስለሆነ በቶሎ ፈጥናችሁ እንድትመዘገቡ ስንል እናሳስባለን።
  ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

ማስታወቂያ
እንደምን አደራችሁ? የመውጫ ፈተና ከሰኔ 4-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በዩኒቨርሲቲያችን ካሉና ከምናስፈትናቸው 1873 ተፈታኞች መካከል 1794 (95.8%) የፋይዳ ቁጥራቸውን ከመረጃቸው ጋር አስተሳስረው ፈተናውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይሁን እንጂ 79 ተፈታኞች እስካሁን ያላስተሳሰሩ በመሆኑ ፈተናውን ለመውሰድ Username እና Password ስለማይሰጣቸው ፈተናውን የማይወስዱ መሆኑ ታውቆ ነገ እንዲያስተሳስሩ በትምህርት ክፍሎች በኩል እንዲደርሳቸው እያሳሰብን፤ ፈተናውን ሳይወስዱ ቢቀሩ ኃላፊነቱን የሚወስዱት ራሳቸው ተፈታኞቹ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ #From: የሕ.ጤ.ሳ.ኮ እና አጠ.እስ.ሆ የጤና ትምህርት ምክትል ኮርፖሬት ዲያሬክተር   ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

❗️ማሳሰብያ‼️❗️ "ለውድ የካምፓሳችን ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ፤" ለመውጫ ፈተና የከፈላችሁትን ገንዘብ ከማዕከል ፋይናንስ ቢሮ እንድትቀበሉ የወጣውን ማሳሰቢያ ተመልክተናል። ሆኖም ግን የተማሪዎች ህብረት ወደ ማዕከል ካምፓስ መሄድ ሳያስፈልጋችሁ የከፈላችሁትን ገንዘብ በራሳችን ካምፓስ ውስጥ መውሰድ እንድትችሉ ውሳኔውን ለማስቀየር ከማኔጅመንቱ ጋር በከፍተኛ ሁኔታ እየተወያየና ጥረት እያደረገ ይገኛል። ስለሆነም ከማኔጅመንቱ የመጨረሻውን ፈቃድ አግኝተን ምላሽ እስክናሳውቃችሁ ድረስ ሁላችሁም በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እናሳስባለን። ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

ዛሬ ከCH-20 Ground ላይ የሽንት ቤቱ በር አካበቢ ብር የጣልክ ተማሪ ከተማሪዎች ህብረት ቢሮ መጥተህ የገንዘቡን መጠን ተናግረህ መውሰድ ትችላለህ። ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

ዛሬ lounge አካበቢ ብር የጣልክ/ሽ ተማሪ ከተማሪዎች ህብረት ቢሮ መጥተህ/ሽ መውሰድ ትችላለህ/ያለሽ። ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

ተማሪ Betelhem Alemye የተማሪ መታወቂያ ካርድ(ID) ስለተገኘልሽ ከተማሪዎች ህብረት ቢሮ መጥተሽ መውሰድ ትችያለሽ:: ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

የ2018 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መርሐግብር (Exit Exam Schedule) (Tentative). የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

Repost from Tikvah-University
የ2018 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መርሐግብር (Exit Exam Schedule) (Tentative) የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። @tikvahuniversity

ማስታወቂያ ለመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች የአመቱን ትምህርት የጨረሳችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ስትመጡ የፋይዳ መታወቂያና የቲን ቁጥር  /TIN Number/ ይዛችሁ እንድትመጡ እያሳሰብን ምዝገባ ያለፋይዳ መታወቂያና የቲን ቁጥር  /TIN Number/ እንደማይደረግ እናሳውቃለን። ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

ተማሪ Gethahun Fantaw ID No. 02128/15 የመመገቢያ ካርድ(Meal Card) ስለተገኘ ከተማሪዎች ሕብረት ቢሮ መጥተህ መውሰድ ትችላለህ። ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e

❗️‼️ Announcement‼️❗️📢 To All Campus Students Dear Respected Students, We are pleased to announce that the new pedestrian walking bridge, designed to improve campus security and student convenience, is fully open for service starting today. Accordingly, we urge all students to strictly follow these operational changes and guidelines: ▶️ Starting today, any student entering or leaving the campus must exclusively use this new pedestrian bridge. ▶️ Please be informed that the main entrance and exit gate of the campus, which we have been using until now, will be completely closed starting today and onwards. ▶️ It is strictly mandatory to carry your "Student ID Card" at all times whenever you enter or exit the campus using the new walking bridge. Please be aware that no service or passage will be granted to any student without an ID card. We strongly advise you not to forget your ID card to avoid any inconvenience. We politely request that you contribute to the peace and security of our campus by properly implementing this new campus directive. Thank You! ❗️‎ትኩረት ለተማሪዎች❗️ 📌 የሕ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት ‎ 👨‍🏫 @uogcmhsstudentunion 👩‍🏫 ‎#ለወዳጅዎ_ያጋሩ! ‎ሀሳብዎን በነጻነት ይግለጹ ⤵️                 ‎👉 @Blessed2018102 ‎👉 @ghoo3e