cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ዜናዎች

ይኼ ገጽ የአመቱ ስንክሳር በየቀኑ የሚቀርብበት ማብራሪያው ላልቀረበበትም የበለጠ እንድናነብ የሚረዳን መማማሪያ ነው። " ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ:: በዓለም ያለው ሁሉ: እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት: ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ: ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም:: ዓለሙም: ምኞቱም ያልፋሉ::" 1ዮሐ. 2:15 # ያጋሩ

Больше
Рекламные посты
2 175
Подписчики
-124 часа
-47 дней
+1430 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

መንጋውን ሲመቱ በጎቹ ይበተናሉና ሞዴል፣ ፊት አውራሪ ተብለው በዚህም በዛም ይቦተልኩና ብዙ ተከታይ ብዙ አድናቂ ሲያገኙ የሚያደርጉትን ያጣሉ። ደስታ የሚገኘው ከታዋቂነት ስለሚመስላቸውና ስለሚያስቡ ሳያውቁ ታውቀው ሲታወቁ ይጠፋሉ። እውቀት መታወቅ አይደለም! እውቀትን ለመግዛት ዝቅ ማለት፣ ጥበብን መሻት መገደም መንበርከክ ያስፈልጋል። በአለም ጠቢባን የሆኑ እውቆች በታሪካቸው ከሕዝብ አይን የጠፉበት ምክንያት በጓዳ ብዙ የቤት ሥራቸውን እየሰሩ በመሆናቸው ነው። መናፍቃን ንፁሀንን ለማጥመድና ዓለምን ለማስናፈቅ ከሚጠቀሙበት የማጥመጃ መንገድ አንዱ ተከታይ አለን፣ ብዙ ሰው ያደንቀናል ብለው የሚታሰብባቸው መንጋዎችን ማጥመድ ነው። ከዛ የመንጋው ተከታይ እንዴ? እሱማ እንዲህ ከሆነ የሆነ የገባው ነገር አለ ማለት ነው ይልና ጭፍኑ ይኖግዳል። ይኼም በዚህ ብቻ አይበቃም ጭር ሲል አይወዱምና ታክቲክ ወይም በየጊዜው አዲስ ስልት እየዘየዱ ድራማቸውን ይቀጥላሉ። ከተራ አማኙ እስከ ክህነት ያለው፣ ከአገልጋዩ እስከ ተገልጋይ ምዕመኑ እንዲህና እንዲያ እያወዛገቡ በአጀንዳ ያጣድፉታል። ነገሩ እንዲያ ሆኖ የማኅበራዊ ሚዲያውን አጀንዳ ለማጰንጠጥ የተያዘው ትልቅ ዘመቻ በችርቻሮ ብቅ ብቅ እያለ ነው ሳሜንት ምን እንጠብቅ? ሁሉም ቢሆን ድራማው በጥሩ ደራሲ ዳጎስ ባለ በጀት በታለመለት ዓላማ የሚሄድ ይመስላል
Показать все...
👍 4
† ስንክሳር ግንቦት 16 † በስመ አብ: ወወልድ: ወመንፈስ ቅዱስ: አሐዱ አምላክ። †  ግንቦት 16 † ✝ ቅዱስ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ ✝ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌሉ እንደነገረን በመንግስተ ሰማያት ታላቁ ሰው ወንጌላዊው ዮሐንስ ነው:: ቅዱሱ ሐዋርያ ከዘብዴዎስና ከማርያም ባውፍልያ ተወልዶ: በገሊላ አካባቢ አድጐ: ገና በወጣትነቱ መድኃኔ ዓለምን ተከትሎታል:: ቅዱስ ዮሐንስ ከሐዋርያት ቀድሞ ጌታን ከመከተሉ ባሻገር በምንም ምክንያት ከጐኑ አይጠፋም ነበር:: ስለ ንጽሕናውና በጐ የፍቅር ሕሊናው ሕጻን ሳለ በወንድሞቹ ሐዋርያት ዘንድ ሞገሱ ከፍ ያለ ነው:: ጌታችንን እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ በመከተሉ ድንግል እመቤታችንን ተቀብሏል:: ከእርሷ ጋር ለ15 ዓመታት ቢቀመጥ መዝገበ ምሥጢር ሆነ:: ስንኩዋን ከሰው ልጆች ይቅርና ከልዑላኑ መላዕክትም ማዕረጉ ከፍ አለ:: ሰው ቢበቃ መላእክትን ሊያይ ይቻለዋል:: ቅዱስ ዮሐንስን ግን መላእክት ሊያዩት ይከብዳቸዋል:: ከፍጥረት ወገን ከእመ ብርሃን ቀጥሎ ክቡር እርሱ ነው:: ቅዱስ ዮሐንስ በታናሽ እስያ ለ7ቱ አብያተ ክርስቲያናት መስበኩ ይታሰባል:: ቅዱሱ ከጌታችን ዕርገት በሁዋላ ለ70 ዓመታት በዚህ ምድር ሲኖር አብዛኛውን ጊዜውን ያሳለፈው በኤፌሶን አካባቢ ነው:: ሕዝቡን ወደ ክርስትና ለማምጣት በአፍም በመጽሐፍም ደክሟል:: 3 መልዕክታት: ራዕዩንና ወንጌልን ጽፎላቸዋል:: ሕይወትን ስለ ሰበከላቸው በፈንታው ብዙ አሰቃይተውታል:: ከእሳት እስከ ስለት: እስከ መጋዝም በስተእርጅና ደርሶበታል:: እርሱ ግን በትእግስቱ ገንዘብ አድርጉዋቸዋል:: ††† ቅዱሱ በኤፌሶን ††† =>ይህቺ ኤፌሶን የሚሏት ሃገር መገኛዋ በቀድሞው ታናሽ እስያ (አሁን ቱርክ አካባቢ) ሲሆን ብዙ ሐዋርያት አስተምረውባታል:: ያም ሆኖ የሚፈለገውን ያህል ለውጥ ያመጣች አልነበረችምና ቅዱስ ዮሐንስ ሊሔድ ተነሳ:: ከደቀ መዛሙርቱ መካከልም ቅዱስ አብሮኮሮስን (ከ72ቱ አርድእት አንዱ ነው) አስከትሎ እየጸለዩ በመርከብ ላይ ተሳፈሩ:: ሐዋርያት አበው መከረኞች ናቸውና ማዕበል ተነሳባቸው:: በጥቂት አፍታም መርከባቸው በማዕበሉ ተበታተነች:: ቅዱስ አብሮኮሮስ በስባሪ ላይ ተሳፍሮ ወደ አንዲት ደሴት ደረሰ:: ከንጹሑ መምሕሩ ቅዱስ ዮሐንስ ተለይቷልና አለቀሰ:: ፍቁረ እግዚእ ግን ያለ ምግብና ውሃ ማዕበለ ባሕር እያማታው ለ40 ቀናት ቆየ:: እርሱ በፈጣሪው ፍቅር የተመሰጠ ነበርና አለመመገቡ አልጐዳውም:: በ40ኛው ቀን ግን ደቀ መዝሙሩ ወዳለበት ደሴት ማዕበሉ አደረሰው:: 2ቱ ቅዱሳን ተፈላልገው ተገናኙ:: እጅግም ደስ ብሏቸው ፈጣሪን አመሰገኑ:: አምላካቸው ወደዚህች ደሴት ያመጣቸው በጥበቡ ነውና ሲዘዋወሩ 2 ነገርን አስተዋሉ:: 1ኛ የደሴቷ ሁሉም ነዋሪ የሚያመልኩት ጣዖትን ነው:: 2ኛ አብዛኞቹ የቤተ መንግስት ውላጆች ናቸው:: ሮምና የሚሏት አንዲት ሴት ደግሞ እነዚህን ሁሉ እየመገበች ታስተዳድራለች:: ቅዱሳኑ በቦታው በቀጥታ ትምሕርተ ወንጌልን ቢናገሩ እንደ ማይቀበሏቸው ስለ ተረዱ ሌላ ፈሊጥን አሰቡ:: እንዳሰቡትም ወደ እመቤት ሮምና ቤት ሒደው በባርነት ተቀጠሩ:: ለእርሷም "ድሮ የአባትሽ ባሮች የነበርን ሰዎች ነን" ስላሏት 2ቱን ቅዱሳን እሳት አንዳጅና ገንዳ አጣቢ አደረገቻቸው:: ለሰማይ ለምድሩ የከበዱ እነዚህ ቅዱሳን የካዱትን ይመልሱ ዘንድ በባርነት ግፍን ተቀበሉ:: የመከር (የማሳመኛ) ጊዜ ሲደርስም አንዳች አጋጣሚ ተፈጠረ:: ቅዱሳኑ ዮሐንስና አብሮኮሮስ ወደ መታጠቢያ ቤቱ ሲገቡ ሰይጣን በውስጥ ኖሮ ደንግጧልና እወጣለሁ ብሎ ሲሮጥ የንጉሡን ልጅ ረግጦ ገደለው:: ሮምናና የአካባቢው ሰዎች ከበው ሲላቀሱ ቅዱሳኑ ቀረቡ:: ሮምና ግን በቁጣ "ልትሣለቁ ነው የመጣችሁ?" በሚል ቅዱስ ዮሐንስን በጥፊ መታችው:: መላእክት እንኩዋ ቀና ብለው ሊያዩት የሚከብዳቸው ሐዋርያ ይህንን ታገሰ:: በጥፊ ወደ መታችው ሴት ቀረብ ብሎም "አትዘኚ! ልጁ ይነሳል" አላትና ጸለየ:: ወደ ሞተውም ቀረብ ብሎ በጌታችን ስም አስነሳው:: በዚህ ጊዜም ሮምናን ጨምሮ በሥፍራው የነበሩ ሰዎች ለቅዱስ ዮሐንስ ሰገዱ:: እርሱ ግን ሁሉንም አስነስቶ ትምሕርተ ሃይማኖትን: ፍቅረ ክርስቶስን ሰበከላቸው:: በስመ ሥላሴ አጥምቆ: ካህናትን ሹሞ: ቤተ ክርስቲያንም አንጾላቸው ወጥቷል:: በሁዋላም ለሮምናና ለደሴቷ ሰዎች ክታብ (መልዕክትን) ጽፎላቸዋል:: ይህች መልዕክት ዛሬ 2ኛዋ የዮሐንስ መልዕክት ተብላ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ትታወቃለች:: ቅዱስ ዮሐንስ ቀጥሎ የተጉዋዘው ወደ ኤፌሶን ነው:: በዚህች ከተማ የምትመለክ አርጤምስ (አርጢሞስ) የሚሏት ጣዖት ነበረች:: አርጤምስ ማለት መልክ የነበራት ትዕቢተኛ ሴት ስትሆን አስማተኛ ባሏ ነው እንድትመለክ ያደረጋት:: ቅዱስ ዻውሎስ ብዙ ምዕመናን ከእርሷ እንዲርቁ ማድረግ ችሏል:: ጨርሶ ያጠፋት ግን ቅዱስ ዮሐንስ ነው:: በቦታውም ብዙ ግፍ ደርሶበት: በርካታ ተአምራትን አድርጉዋል:: ቤተ ጣዖቱንም በተአምራት አፍርሶታል:: =>ግንቦት 16 ቀን የሚከበሩ          ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ (ስብከቱና ቅዳሴ ቤቱ) 2.ቅዱስ ኢያሱ ሲራክ ነቢይና ጠቢብ (መጽሐፈ ሲራክን የጻፈ) 3.ቅድስት እናታችን ዐስበ ሚካኤል (ኢትዮዽያዊት) =>ወርኀዊ በዓላት 1.ኪዳነ ምሕረት (የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም) 2.ቅድስት ኤልሳቤጥ (የመጥምቁ ዮሐንስ እናት) 3.ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ (የቅ/ላሊበላ ወንድም) 4.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ ጻድቅ 5.አባ አቡናፍር ገዳማዊ 6.አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ 7.አባ ዳንኤል ጻድቅ " በጌታ ኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ: የእናቱም እህት: የቀለዮዻም ሚስት ማርያም: መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር:: ጌታ ኢየሱስም እናቱን: ይወደው የነበረውንም ደቀ መዝሙር በአጠገቡ ቆሞ ባየ ጊዜ እናቱን 'አንቺ ሆይ! እነሆ ልጅሽ' አላት:: ከዚህ በሁዋላ ደቀ መዝሙሩን 'እናትህ እነሁዋት' አለው:: ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት:: " (ዮሐ. 19:25) 🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹                    👇👇👇 (ይህ የቴሌግራም ቻናላችን ነው ይቀላቀሉን)     🕊 https://t.me/Sinksar 🕊      🕊 https://t.me/Sinksar 🕊      🕊 https://t.me/Sinksar 🕊
Показать все...
ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ዜናዎች

ይኼ ገጽ የአመቱ ስንክሳር በየቀኑ የሚቀርብበት ማብራሪያው ላልቀረበበትም የበለጠ እንድናነብ የሚረዳን መማማሪያ ነው። " ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ:: በዓለም ያለው ሁሉ: እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት: ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ: ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም:: ዓለሙም: ምኞቱም ያልፋሉ::" 1ዮሐ. 2:15 # ያጋሩ

🙏 4
✞ ስንክሳር ግንቦት 15 ✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ:: አሜን ፡፡ ✞ ❖ ግንቦት 1 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 🌿" ቅዱስ ናትናኤል "🌿 በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ከቅዱሳን ሐዋርያት መካከል ዘግይቶ ሰማዕትነትን የተቀበለ ይህ ቅዱስ ሐዋርያ ነው:: ቅዱሱ ሐዋርያ የተወለደው ከእሥራኤላውያን ወላጆቹ ጌታችን በተወለደበት ዘመን አካባቢ ነው:: ይህ በምን ይታወቃል ቢሉ እርሱ ሕጻን እያለ ሔሮድስ 144,000 ሕጻናትን ሲፈጅ እርሱ ግን በእግዚአብሔር ጥበብ ተርፏል:: እናቱ በቅርጫት ውስጥ አድርጋ የበለስ ዛፍ ላይ አስቀምጣው ተደብቃ ታጠባው ነበር:: +ለሐዋርያው ወላጆቹ ያወጡለት ስም ስምዖን ሲሆን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ናትናኤል ብሎታል:: በባልንጀሮቹ ሐዋርያት ደግሞ የቃናው ስምዖን (ገሊላ ቃና አካባቢ ስላደገ): አንዳንዴም ቀናተኛው ስምዖን ይሉት ነበር:: ምሑረ ኦሪት ነበርና ዘወትር ለሕግ ይቀና ነበር:: +በገሊላ ቃና ሰርግ የደገሰው ዶኪማስ የቅዱስ ናትናኤል የአጎት ልጅ ነው:: ጌታና ደቀ መዛሙርቱን ዶኪማስ የጠራበት አንዱ ምክንያትም ይሔው ነው:: +ቅዱስ ናትናኤል ኦሪትን ከገማልያል ተምሮ: ከበለስ ቁጭ ብሎ ይተክዝ ነበር:: "መሲሕ ምነው ቀረህ" እያለም ይተክዝ ነበር:: ማዕምረ ኅቡዓት አምላካችን ክርስቶስ ይህንን አውቆ በፊልዾስ አማካኝነት ጠርቶታል:: +ናትናኤል ለጊዜው ተከራክሮ ነበር:: በኋላ ግን የጌታችንን ማንነት በደቂቃዎች ተረድቶ አምኗል:: ጌታችንም "ክዳት ሽንገላ በልቡ ውስጥ የሌለበት ንጹሕ እሥራኤላዊ" ሲል አመስግኖታል:: +ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ከጌታችን እግር ሥር ምስጢረ መንግስተ ሰማያትን ተምሮ: በጸጋ መንፈስ ቅዱስም ሰክሮ ብዙ አሕዛብን ከጨለማ (ጣኦት አምልኮ) ወደ ብርሃን (አሚነ ክርስቶስ) መልሷል:: እጅግ ብዙ መከራንም ተቀብሏል:: +የጌታችን ወንድም የተባለ ቅዱስ ያዕቆብ በአይሁድ ከተገደለ በኋላም ቅዱስ ናትናኤል የኢየሩሳሌም 2ኛ ኤዺስ ቆዾስ ሆኖ አገልግሏል:: ከአይሁድም ዘንድ ብዙ መከራ ደርሶበታል:: በመጨረሻም በዚህች ዕለት በሰማዕትነት አልፏል:: በገድለ ሐዋርያት ላይ እንደተጠቀሰው ቅዱሱ ሰማዕት የሆነው በ150 ዓመቱ ነው:: ያ ማለት ደግሞ ከሐዋርያት አባቶች በመጨረሻ ያረፈው እርሱ ነው ያሰኛል:: ❖እግዚአብሔር በቅዱስ ናትናኤል ምልጃ ሃገራችንን ከጥፋት: ሕዝቦቿንም ከመቅሰፍት ይሰውርልን:: ከበረከቱም አይለየን:: =>ግንቦት 15 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት= 1.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ (ቀናተኛው ስምዖን) 2.ቅዱስ ሚናስ ባሕታዊ 3.ቅዱስ ቀርጢኖስ ሰማዕት 4."400" ቅዱሳን ሰማዕታት =>ወርሐዊ በዓላት 1.ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ 2.ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (አፈ በረከት) 3.ቅዱስ ሚናስ ግብፃዊ 4.ቅድስት እንባ መሪና 5.ቅድስት ክርስጢና 🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹                    👇👇👇 (ይህ የቴሌግራም ቻናላችን ነው ይቀላቀሉን)     🕊 https://t.me/Sinksar 🕊      🕊 https://t.me/Sinksar 🕊      🕊 https://t.me/Sinksar 🕊
Показать все...
ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ዜናዎች

ይኼ ገጽ የአመቱ ስንክሳር በየቀኑ የሚቀርብበት ማብራሪያው ላልቀረበበትም የበለጠ እንድናነብ የሚረዳን መማማሪያ ነው። " ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ:: በዓለም ያለው ሁሉ: እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት: ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ: ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም:: ዓለሙም: ምኞቱም ያልፋሉ::" 1ዮሐ. 2:15 # ያጋሩ

🙏 4
🙏  ስንክሳር ግንቦት 14  🙏 እንኩዋን የመነኮሳት አባት ለተባለው "ቅዱስ ዻኩሚስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ✍" ቅዱስ ዻኩሚስ (አባ ባኹም) "✍ ዛሬን አያድርገውና ምንኩስና ማለት መላእክትን መስሎ የሚኖርበት ሕይወት ነበር:: ምንኩስና በእግዚአብሔር ፈቃድ በአባ እንጦንስ ቢመሠረትም ሕይወቱን በማስፋፋት ደረጃ የቅዱስ ዻኩሚስን ያሕል የደከመና የተሳካለት ግን የለም:: ቅዱሱ በትውልዱ ግብፃዊ እንደሆነ የሚነገር ሲሆን ከቀደመ ሕይወቱ ጋር በተያያዘ የሚተረክ ነገር በመጽሐፈ ገድሉ ላይ አለ:: ዻኩሚስ ወደ ምንኩስናው ዓለም የመጣ በታላቁ አባ ዸላሞን አማካኝነት ነው:: ለተወሰነ ጊዜም መንፈሳዊ አባቱን እየረዳ ሕይወተ መነኮሳትን አጥንቷል:: በመንፈሳዊ ሕይወቱና በተጋድሎ እየበረታና እየደረጀ ሲሔድ ከአባ ዸላሞን ተለይቶ : ማሕበር መስርቶ ለመኖር አምላኩን ጠይቆ ፈቃድ በማግኘቱ በሕግ የሚመራ የመጀመሪያውን ገዳም መሥርቷል:: ቅዱስ ዻኩሚስ ጸሎቱ አጋንንትን ከአካባቢው አያስቀርባቸውም ነበር:: አካሉ አልቆ በአጥንቶቹ እስኪቆም ድረስ ጾሟል:: ዓርብ ዓርብ የጌታችንን ሕማማት እያሰበ ከእንባ ጋር ይሰግዳል:: እንባውና ላበቱ ከፊቱ እየወረደ አካባቢው ጭቃ ይሆን ነበር:: ጌታችንም መስቀል ተሸክሞ ይታየው ነበር:: ስለ ክብሩም መላእክት ወደ ሰማይ ወስደው ገነትና ሲዖልን አሳይተውታል:: አባታችን ቅዱስ ዻኩሚስ ከርሕራሔው የተነሳ አጋንንት ያደሩባቸውን ሰዎች ሲያገኝ በቀጥታ ከመፈወስ ይልቅ ደዌውን : ርኩሳን መናፍስቱንም ወደ እርሱ እንዲገለበጡ ያዛቸው ነበር:: ከዚያም በጾም : በጸሎትና በስግደት ያማስናቸዋል:: ያኔ በግዳቸው እየጮሁ ሲወጡ ደጉ አባት "ምነው ትንሽ ቆዩ እንጂ" ይላቸዋል:: አጋንንቱም እያደነቁ "ከገነት ካስወጣነው ከአዳም በቀር እንዲህ ዓይነት ፍጡርስ ዓይተን አናውቅም" ብለው እንደ ጢስ በነዋል:: አጋንንት ስለሚፈሩት "አርበኛው መነኩሴ" ይሉታል:: 👏< የቅዱስ ዻኩሚስ ፍሬዎች >👏 1.በግብፅ በርካታ ገዳማትን አቁዋቁሟል:: 2.ለሁሉም ገዳማት አበ ምኔቶችን ሹሞ እየዞረ ይጠብቃቸው ነበር:: 3.የመጀመሪያውን ሥርዓተ መነኮሳት አዘጋጅቷል:: 4.መነኮሳት ሥጋዊም ሆነ መንፈሳዊ ሹመት እንዳይሾሙ ከልክሏል:: 5.መነኮሳት ከገዳማቸው በፍፁም እንዳይወጡ ከልክሏል:: 6.ከግብፅ ውጪ ምንኩስናን ያስፋፉ አባቶችን አስተምሮ አመንኩሷል:: (ለምሳሌ በኢትዮዽያ ምንኩስናን ያስፋፉት አቡነ አረጋዊ የዚህ አባት ደቀ መዝሙር ናቸው) ከዚሕም ባለፈ በርካታ ሥራዎችን ሠርቷል:: ቅዱስ ዻኩሚስ ጫማ ሳይጫማ: እሾህን ሳይሰቀቅ ይረግጥም ነበር:: የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ እጥፍ ሆኖ የበዛለት ቅዱሱ መነኮስ ወደ ወደደው እግዚአብሔር በዚህች ቀን ሔዷል:: =>የጻድቁ መነኮስ ጸጋና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን:: =>ግንቦት 14 ቀን የሚከበሩ       ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ አባ ዻኩሚስ (አበ መነኮሳት ሣልሳዊ) 2.አባ ሲማኮስ ሰማዕት =>ወርሐዊ በዓላት 1.አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል) 2.ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ 3.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ 4.ቅዱስ ሙሴ (የእግዚአብሔር ሰው) 5.አባ ስምዖን ገዳማዊ 6.አባ ዮሐንስ ጻድቅ 7.እናታችን ቅድስት ነሣሒት " ይህ ነገር ለተሰጣቸው ነው እንጂ ለሁሉ አይደለም:: በእናት ማሕጸን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ:: ሰውም የሰለባቸው ጃንደረቦች አሉ:: ስለ መንግስተ ሰማያትም ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ:: ሊቀበለው የሚችል ይቀበለው:: " (ማቴ. 19:11) 🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹                    👇👇👇 (ይህ የቴሌግራም ቻናላችን ነው ይቀላቀሉን)     🕊 https://t.me/Sinksar 🕊      🕊 https://t.me/Sinksar 🕊      🕊 https://t.me/Sinksar 🕊
Показать все...
ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ዜናዎች

ይኼ ገጽ የአመቱ ስንክሳር በየቀኑ የሚቀርብበት ማብራሪያው ላልቀረበበትም የበለጠ እንድናነብ የሚረዳን መማማሪያ ነው። " ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ:: በዓለም ያለው ሁሉ: እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት: ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ: ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም:: ዓለሙም: ምኞቱም ያልፋሉ::" 1ዮሐ. 2:15 # ያጋሩ

👍 4🙏 3
ኑ በመልካም እንተባበር ለባለ ውለታችን ውለታ እንመልስ ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ መታመማቸውን እና ለህክምና ብር እንደሚያስፈልግ ሰምተናል። ቀርቤ እንደተረዳሁት ሊቀ መዘምራን በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ አልፈዋል። እናም ብንተባበር ከህክምናም በላይ ለአባታችን ብዙ ማድረግ እንችላለን። Account 1000481007287 KINETIBEB W/KIRKOS W/MESKEL CBE 👉እንደ ቸርነትህ 👉ይህ ቁርባን 👉ሰው ለሰው 👉አልፋ እና ኦሜጋ 👉እኔስ በመግባሬ 👉አንድ እምነት ነው 👉የአንተ ስራ 👉እመ አምላክ 👉ፀምር ዘጌድዮን 👉እናምናለን 👉ድንግል ወላዲተ ቃል 👉በስራዬ የት ይሄን መግቢያዬ 👉ድንግል ሆይ ስለ አንቺ 👉የሲና ሐመልማል 👉አቤት የዛን ግዜ 👉መፅሐፍ ቅዱስን 👉ዘጠኝ ሰአት ሲሆን 👉በአርእያው ፈጥሮናል እናመስግነው 👉አምነናል በልጅሽ በአንቺ አናምንም አሉ 👉ሞትን አትፍሩ 👉ወይ እኔ ወይ እኔ 👉ኧረ ሰው መሆኔ 👉ተነሽ ኢትዮጵያ.........ሌሎችም እነኚህ ዝማሬዎች ሰምተን ልባችን ወደ እግዚአብሔር የተመለሰ፣ለንሰሃ የበቃን የት ነን?
Показать все...
🙏 4
✞ ስንክሳር ግንቦት 13 ✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ❖ ግንቦት 13 ቀን የሚከበሩ       ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 🌿" ቅዱስ አርሳኒ "🌿 =>ቅድስት ሃይማኖት እዚህ ዛሬ እኛ ጋር የደረሰችው በበርካታ ሰማዕታትና ጻድቃን ደም ነው:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ግድግዳዎቿ እንጨትና ድንጋይ እንዳይመስሏችሁ:: አጽመ ቅዱሳን ነው እንጂ:: ቅዱሳን ልዑለ ባሕርይ ክርስቶስን እንደ እኔ እና እንደ ዘመኑ ትውልድ በከንፈራቸው የሚሸነግሉ አልነበሩም:: እነርሱ በፍጹም ልባቸው ስለ ፍቅሩ ሕይወታቸውን አሳልፈው ሰጡ እንጂ:: በቅድስናቸው ከተመሰከረላቸው ቀደምት ቅዱሳን አንዱ ደግም ቅዱስ አርሳንዮስ ነው:: ቅዱሱ የተወለደው በ345 ዓ/ም ሮም ውስጥ ነው:: በወጣትነቱ ይሕ ቀረህ የማይሉት የጥበብና የፍልስፍና ሰው ነበር:: በተለይ በትልቁ የሮም ቄሳር ቴዎዶስዮስ ዘመን በቤተ መንግስት አካባቢ የተከበረና የንጉሡ ልጆች መምሕር ነበር:: አኖሬዎስና አርቃዴዎስን ቀጥቶ ያሳደጋቸውም እርሱ ነበር:: በድንግልና እስከ 40 ዓመቱ ድረስ ሮም ውስጥ ቆየ:: ከዚህ በኋላ ግን ስለ ሰማያዊ ነገሮች ሲያስብ መልዐኩ በሕልም ወደ ግብፅ ሒድ አለው:: በመጀመሪያ ወደ እስክንድርያ ቀጥሎ ወደ ገዳመ አስቄጥስ ሒዶ መነኮሰ:: በቆይታ ግን ብሕትውና ምርጫው ሆነ:: ቅዱስ አርሳኒ በእነዚሕ ነገሮቹ ይታወቃል:- 1.በምንም ምክንያት ከማንም ጋር አያወራም:: (ለ60 ዓመታት በአርምሞ ኑሯል) 2.በቤተ መቅደሱ ግድግዳ ተጠግቶ እንባውን ሲያፈስ የርሱን አካል አርሶ በመሬት ላይ ሲፈስ ይታይ ነበር:: ከእንባው ብዛት ቅንድቦቹ ተላልጠው አልቀው ነበር:: 3.በርካታ ድርሳናትን ደርሷል:: ብዙዎቹ ዛሬም ግብጽ ውስጥ አሉ:: 4.ሸንጎበቱን ወደ ደረቱ አዘንብሎ ስለሚቆም ማንንም ቀና ብሎ አያይም ነበር:: 5.ለጸሎት አመሻሽ 11:00 አካባቢ ላይ ይቆምና ጸሎቱን የሚጨርስ ፀሐይ ግንባሩን ስትመታው ነው:: 6.ሁል ጊዜ ራሱን "አንተ ሰነፍ (ሐካይ) እያለ ይገስጽ ነበር:: 7.በገዳማውያን ታሪክ የርሱን ያሕል በቁመቱ ረዥም አልተገኘም ይባላል:: የራሱ ጸጉር በጀርባው የወረደ ሲሆን ጽሕሙን በስዕሉ ላይ እንደምታዩት ነጭና እስከ መታጠቂያው የወረደ ነበር:: እነዚህ ግን በጣም ጥቂቶቹ ናቸው:: ቅዱስ አርሳንዮስ አካሉ በተጋድሎ ደቆ: ለ60 ዓመታት በግሩም መንፈሳዊነት ኑሮ በ100 ዓመቱ በዚሕች ዕለት ዐርፏል:: ❖አምላካችን እግዚአብሔር ከታላቁ የቅድስና ሰው አርሳኒ በረከት አይለየን:: =>ግንቦት 13 ቀን የሚከበሩ         ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት= 1.ቅዱስ አርሳንዮስ - አርሳኒ (ጠቢብ ገዳማዊ) =>ወርኀዊ በዓላት 1.እግዚአብሔር አብ 2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላዕክት 3."99ኙ" ነገደ መላዕክት 4.ቅዱስ አስከናፍር 5."13ቱ" ግኁሳን አባቶች 6.አቡነ ዘርዐ ቡሩክ =>+"+ የፍጥረት ወገን ሁሉ በሰው ይገራል:: ደግሞ ተገርቷል:: ነገር ግን አንደበትን ሊገራ ማንም ሰው አይችልም:: የሚገድል መርዝ የሞላበት ወላዋይ ክፋት ነው:: በእርሱ ጌታንና አብን እንባርካለን:: በእርሱም እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠሩትን ሰዎች እንረግማለን:: ከአንድ አፍ በረከትና መርገም ይወጣሉ:: ወንድሞቼ ሆይ ይህ እንዲህ ሊሆን አይገባም:: " (ያዕ. 3:7-11) †🌹 ወስብሐት ለእግዚአብሔር 🌹†   👇👇👇 Join. በዚህ የቴሌግራም ቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ። 🌹ወስብሐት ለእግዚአብሔር  🌹                    👇👇👇 (ይህ የቴሌግራም ቻናላችን ነው ይቀላቀሉን) 🕊 https://t.me/Sinksar 🕊  🕊 https://t.me/Sinksar 🕊   🕊 https://t.me/Sinksar 🕊
Показать все...
ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ዜናዎች

ይኼ ገጽ የአመቱ ስንክሳር በየቀኑ የሚቀርብበት ማብራሪያው ላልቀረበበትም የበለጠ እንድናነብ የሚረዳን መማማሪያ ነው። " ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ:: በዓለም ያለው ሁሉ: እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት: ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ: ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም:: ዓለሙም: ምኞቱም ያልፋሉ::" 1ዮሐ. 2:15 # ያጋሩ

🔥 2🙏 1
✍ሥንክሳር ግንቦት 12✍ ✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞           ❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖ ግንቦት 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✍ ✝ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ✝°+ =>ለቤተ ክርስቲያን የብርሃን ምሰሶ ስለሆነላት ስለ ታላቁ ሐዋርያዊ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? እንደ እኔ ያለ ኃጥእ: ለባሴ ሥጋና ገባሬ ንስሃ ስለሱ ሊናገር አይቻለውምና:: አባቶቻችን እንደ ነገሩን ስለ አፈ ወርቅ ለመናገር አፈ ወርቅ መሆን ያስፈልጋል:: ግን እስኪ በቅዱሱ አባት ምልጃ ጥቂት ልሞክር:: 👉<< ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ማን ነው? >> ነገዱ ከሶርያ: የተወለደው በ347 ዓ/ም በእስክንድርያ ሲሆን አባቱ አስፋኒዶስ እናቱ ደግሞ አትናስያ ይባላሉ:: እነርሱ ደግ ቢሆኑ ይህንን እንቁ ልጅ እግዚአብሔር ሰጣቸው:: ዮሐንስ ለክርስቲያን እንደሚገባ በትምሕርትና በጥበብ አደገ:: ገና በሕጻንነቱ ወደ ግሪክ ሔዶ የዘመኑን ሳይንስ (ፍልስፍና) ከአፉ እስከ ገደፉ ተምሮ ተመልሷል:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን ለየት ከሚያደርጉት ነገሮችም አንዱ ይሔው ነው:: በዘመናዊም ሆነ በመንፈሳዊ ትምሕርት ይህ ቀረህ የማይሉት ሊቅ የሆነው ገና በ15 ዓመቱ ነበር:: በ2 ወገን የተሳለ ሰይፍ በመሆኑ ስንኳን በሕይወተ ሥጋ እያለ ዛሬም ለንፉቃን ትልቅ የራስ ምታት ነው:: 👉ቅዱሱ ገና በ16 ዓመቱ ሃብት: ንብረት: ውበት: ክብርና እውቀት የሞላለት ቢሆንም ያለውን ሁሉ ለነዳያን ሰጥቶ መጻሕፍትን ብቻ ሰብስቦ ከባልንጀራው ቅዱስ ባስልዮስ ጋር በርሃ ገባ:: ሰውነቱን በጾምና በጸሎት እየቀጣ በበርሃ ሲኖር ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ወደ እርሱ መጡ:: ሊቀ ሐዋርያት የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ ስልጣን ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ ወንጌሉን ሰጥተው ተሰወሩት:: 👉ከዚህች እለት በኋላ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ባሕረ ምስጢራት ሆነ:: ብሉይ ከሐዲስ: ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ራዕየ ዮሐንስ ድረስ በአንድምታ ትርጉዋሜ ተነተናቸው:: በተለይ ሐዲስ ኪዳንን እየመላለሰ አመሰጠረው:: ቅዱስ ሕሊናው ሳይታክት: ንጹሕ እጆቹ ሳይዝሉ የጻፋቸው ድርሳናት: መልዕክታትና ትርጉዋሜያት ቢቆጠሩ አሥር ሺህ ሞሉ:: በእውነት ለዚህ አንክሮ ይገባል! የሚገርመው ይህን ሁሉ ሲሰራ እድሜው ገና ለጋ: ማዕርጉም ዲቁና ነበር:: ከዚህ በኋላ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ቅስና ተሹሞ በስብከተ ወንጌል ብዙ ቦታዎችን አዳረሰ:: በቅድስናው ወደውታልና የቁስጥንጥንያ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት:: አፈ ወርቅ ሲናገርም ሆነ ሲያስተምር እንኳን የሚያወራ ኮሽ የሚል የለም:: ከጣዕመ ትምሕርቱ የተነሳ ሕዝቡ በተደሞ ይሰሙት ነበር:: 👉ሲያስተምር ምድራዊው ሰው ይቅርና ልዑላኑ መላእክት ተሰብስበው ያደንቁት ነበር:: አንዴም እመቤታችን በሕዝብ መካከል " አፈ-ወርቅ" ብላ ጠርታዋለች:: ለዛም ነው አፈ-ወርቅ የሚባለው:: ቅዱሱ በሥልጣነ ቃሉ መልዐከ ሞትን ገስፆ 10 ዓመት አቁሞታል:: +"ድንግል ማርያም ንጹሕ ብርሌን ትመስላለች:: ብርሌ የተለያየ ቀለም ያለው ፈሳሽ ቢያስገቡበት ቀለሙ አብሮ ይቀያየራል:: እመቤታችንም ጌታን ጸንሳለችና ሕብረ መለኮቱ ሲለዋወጥ መልኳ አብሮ ሲለዋወጥ እያየ ዮሴፍ ይደነግጥ ነበር:: 'እርሷ ማን ናት? በማሕጸኗ ያለውስ ማን ነው' እያለ ይጨነቅ ነበር:: ጌታን ከወለደች በኋላ ግን አንድ ሕብረመልክ ሆናለችና:: አስቀድሞ ማን እንደ ነበረች አላወቀም:: አሁን ግን እርሷም ወላዲተ አምላክ: ልጇም አምላክ ዘበአማን መሆኗን አወቀ ማለት ነው" እያለ ሲተረጉም ሰምተው ሁሉም ሲያደንቁ: በዚያ የነበረች ስዕለ አድኅኖ  "አፈ ወርቅ! ልሳነ ወርቅ! አፈ በረከት!" ስትል ተናገረች:: ያን ጊዜ አርቃድዮስ የወርቅ ልሳን በሊቁና በስዕሏ ላይ አደረገ:: አፈ ወርቅ ግን ባጭር ታጥቆ "እሰግድ ለኪ! እሰግድ ለኪ! ወእዌድሰኪ . . ." ብሎ ዛሬ በተአምረ ማርያም የምናውቀውን ምስጋና ሰተት አድርጐ አደረሰላት:: ይህንን ምስጋናም ሊቃነ መላእክቱ ሰምተው እያደነቁ ወደ ሰማይ ወጥተዋል:: ሊቁ ባረፈ በ35 ዓመቱ: በትንሹ ቴዎዶስዮስ ዘመን: ሥጋው ፈልሷል:: ወደ ቁስጥንጥንያ ሲደርስም ከናፍቆት የተነሳ ታላቅ ዝማሬና እንባ ተደርጓል:: አፈ ወርቅም ቀና ብሎ ሕዝቡን ባርኳል::   🌿 አቡነ ተክለሃይማኖት🌿 ዳግመኛ በዚህ ቀን ታላቁ ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሥጋቸው ፈልሷል:: ይሕ የተደረገው ጻድቁ ከረፉ ከ56 ዓመታት በኋላ ነው:: በዕለቱም ድንቅ ድንቅ ተአምራት ተፈጽመዋል::              ❣✍❣ ❖ግንቦት 12 ቀን የሚከበሩ 🌹ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት🌹 👉1.ቅ.ዮሐንስ አፈ ወርቅ (የዓለም ሁሉ መምሕር) 👉2. አቡነ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ጻድቅ (ፍልሠታቸው) 👉3.ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ (ቃል ኪዳን የተቀበለችበት) 👉4.አባ አብርሃም ዘደብረ ሊባኖስ 👉5.ቅዱስ ዕንባቆም ነቢይ 👉6.እስክንድር ንጉሠ ኢትዮዽያ 👉7.ቅዱስ መስቀል (የተአምር በዓሉ) 👉8.አባታችን ያሬድ (የማቱሳላ አባት) 👉9.ቅዱስ ሚናስ ዲያቆን 🌹ወርኃዊ በዓላት🌹 1፡ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት 2፡ ቅዱስ ድሜጥሮስ 3፡ ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ 4፡ ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ 5፡ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ 6፡ ቅዱስ ላሊበላ 7፡ ቅድስት መስቀል ክብራ
Показать все...
🙏 3
የእንዳልካቸው ዘነበ ሳል እና ኒሞኒያ ******** ከስነልቦና ባለሙያዋ ትዕግሥት ዋልተንጉሥ ጋር በቅርቡ ለአንባቢያን የሚደርስ መጽሐፍ እዘጋጅተናል ። ቲጂ በመጽሐፉ ውስጥ ደጋግማ የምትጠቀምበት ቃል ነው " ሳሉ እና ኒሞኒያው " ። የሚታይ እና የማይታየው ( የተደበቀው ) ማንነታችን ማለት ነው ። እንዳልካቸው ዘነበን ገና በJTV ላይ ስናየው ጀምሮ በፈጣን ንግግሩ ነው ። መደበኛ አነጋገሩ እንደሱ አይመስለኝም ። በጣም ይፈጥናል ፤ ይጮሀል ። እንድንሰማው የቻለውን ሁሉ ይናገራል ። የሆነ ነገር ሳያመልጠው የሚሽቀዳደም ነው የሚመስለው ። በግሌ ያ አቀራረቡ ሳይረብሸኝ የማደምጠው የሬዲዮ ቅርጽ ያለው አቀራረቡ ነው ። ተደምጧልም ደግሞ ። ከዚያን ጊዜ ( የቴሌቪዥን ፕሮግራሙ ከተቋረጠ ) በኋላም እንዳልካቸው መረጋጋት አላይበትም ። ብዙ ነገር የሚነካካ ነው ። ፖለቲካው ውስጥ ይገባል ፣ ሀይማኖት ውስጥ ሁሉም ጋ ያለ መስሎ መታየት ይፈልጋል ። አሁንም ጮክ ብሎ መናገር ያበዛል ። ከብዙሀን ጋር ይላተማል ። ጩኸት ሲበረክት ደስ ይለዋል ። ሲመስለኝ እንደሚናገረው አድማጮችም ጮክ ብለው መስማት ያለባቸው ይመስለዋል ። እንዳልካቸው በጣም ይጮሀል ። አንዳንዴ በተለይ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ወንጌላውያን ሀይማኖቶች መሀል ጉዳይ ሆኖ ሲቀርብ በጩኸት ጩኸት እንዲነሳ ታትሮ ይሰራል ። ብዙሀንን ይተነኩሳል ። ሲመስለኝ ዝም እንዲባል አይፈልግም ። ጮሆ ያስጮሀል ። በዚያ የሚደሰት ይመስለኛል ። ብዙ ጊዜ ለምን እንደማይረጋጋ ፣ ለምን እንደሚጮህ ፣ ተቃውሞና ጩኸትን ለምን እንደሚጠራ ግራ ይገባኛል ። አዚህች የ3:16 ደቂቃ ቪዲዮ ውስጥ የእንዳልካቸው ኒሞኒያ የታየኝ ይመስለኛል ። በዚህ ቪዲዮ ላይ ዓመተ ምህረቱ የተጠቀሰም ባይሆን በትውልድ መንደሩ አንዲት ሴት ፀበል ስትጠመቅ የእንዳልክን እናት በስም ጠርታ በቡዳ እንደበላቻት በመለፍለፏ በእናቱ ላይ የደረሰውን ሰቆቃ ይናገራል ። ይህ ልጅ በንግግር ያበሳጫችሁን ፣ ሀይማኖታችሁን ሊነካ መሞከሩን ፣ ፖለቲካውን ተጠግቶ በሚያደርገው ያስቀየማችሁን ሁሉ ለአፍታ እርሱትና የልጁን የስነልቦና ጉዳት አስቡት ። " ኤልዛቤል " ከተሰኘው የአዳም ረታ አጭር ልቦለድ ተወስዶ በሜጋ የኪነጥበባት ማዕከል የተሰራውን የቴሌቪዥን ድራማ አስታወሰኝ ። ዓለማየሁ ታደሰ የሚተውነው አባወራ በሚስቱ ፣ በጓደኛው ፣ በማህበረሰቡ ላይ ያለውን ጥርጣሬና ጥላቻ ምክንያት በአንዲት አነስተኛ ትዕይንት ተከውና እናገኛታለን ። ከሙሉ ድራማው ያቺን አጭር አይረሴ ትዕይንት አልረሳትም ። ትንሹ ጳውሎስ ( ስሙ እንደዚያ ይመስለኛል ) አንድ ጊዜ ወደ ሰፈራቸው ሲመለስ እናቱ ቡዳ ናት ተብላ " የበላችውን ለማስተፋት " የአካባቢው ማህበረሰብ ተሰብስቦ እናቱን ባገኘው ነገር ሁሉ ሲቀጠቅጣት ያያል ። ጳውሎስ በዚያች ትንሽ እድሜው ማህበረቡ ላይ ያቄማል ። ያ ቂም በሚስቱም ፣ በጓደኛውም ፣ በዙሪያው ባሉ ሰዎች ላይ ሁሉ ይገለጻል ። ይህች ትዕይንት በእኔ የሆነች ያህል አልረሳትም ። እንዳልካቸው ዘነበም የሆነው እንዲህ ነው ። ከጳውሎስ እናቱ ስትደበደብ አለማየት ነው የቀረለት ። ይህ በቀላሉ የሚወጣ ትውስታ አይደለም ። " በቃ አልቻልኩም ። ማዘር እያየሁ ጠቆረች ። እዚያ አካባቢ ለቅሶ መጥራት አቆሙ እሷን ። የሆነ ቦታ ስትሄድ ' አው ! ' [ እንደ ጅብ ] እያሉ ይጠሯታል ። ከባድ ነገር ነበር ያሳለፍኩት ። በማዘሬ የመጣው ከባድ ነበር ። እኔን ሲያዩ ያማትቡ ነበር ፤ ቄሶቹም አገልጋዮቹም ። ካዱን ። ቤተሰብ ሁሉ ተካደ ። ዘመቻው ሰፋና ማዘር መንቀሳቀስ አቃታት ። አንጀቴን በላቺኝ ። ጠቆረች ፤ ከሳች ። ይሄን ማየት አልፈልግም አልኩ ። ወጣሁ ። ያንን ምድር ረገምኩት ። " ይላል ። የዚህን ስቃይ ለመረዳት የግድ እዚያ ቦታ ላይ መቆም አያስፈልግም ። በእውነት ልብ የሚሰብር ገጠመኝ ነው ። እናት ናት በሀሰት ተወንጅላና አካባቢው አድሞባት እንዲህ የምትለበለበው ። ልብ ይሰብራል ። ካልበረቱና እግዚአብሔር ካልረዳ ራስን ያስጠፋል ። ህብረተሰብ ላይ ፣ ሀይማኖት ላይ ቂም ያሲዛል ። ለብቀላ ያስነሳል ። ብቀላው አባቱ ሞክረውት እንደነበረው ሀይማኖት በመቀየር የሚገለጥ ይሆናል ። እንዳልክ ጩኸት ውስጥ ፣ " ኢየሱስ ብቻ ያድናል " ውስጥ እነዚህ ሁሉ የኋላ ታሪኮች አሉ ። " አለፈ ያ ጊዜ " ይላል ባለታሪኩ ። ጊዜ ግን እንዲሁ በዋዛ አያልፍም ። በምን አለፈ ? ያ ቁስለት በምን ታከመ ? ተዳፈነ እንጂ አላለፈም ። ያለፈ ሊመስለው ይችላል ራሱ ባለ ታሪኩም ። ግን አያልፍም ። ይኸው ያ ጊዜ " ካለፈ " ከብዙ ዓመት በኋላም ከማህበረሰብ ሲያጋጨውና ሀይማኖቱን ሲያስጥለው እየታየ ነው ። " ነገሩ ተጋለጠ ። ሰዉ ገባው ። ማዘር ደግሞ አንድም የጎደለባት የለም ። ወተቱ ፣ እርጎው " ይላል ። ይህ ቀርቶ እናቱ የዚያች ከተማ ከንቲባ ፣ ባለሀብት ፣ ተሰሚ ሊሆኑ ይችላሉ ። በምንም አይነት ያን ቁስለት አያጠፉትም ። የአዕምሮ ቁስለት ( Trauma ) እንዲህ " በቃ ! " ተብሎ የሚበቃ አይደለም ። ህክምና ይፈልጋል ። " ይቅርታ አድርጌላቸዋለሁ " ሊባል ይችላል ። ቁስሉ ግን አልታከመም ። የስነልቦና ህክምና ይፈልጋል ። ሀይማኖት መቀየር ፣ " አሁን ሰላምን አገኘሁ " ማለት እሱ ሳሉ ነው ። ኒሞኒያው ግን ውስጥ አለ ። እሱ መውጣት አለበት ። እኔ እንዲህ ይታየኛል ። እንደውም መጮህ ፣ ከመጠን በላይ መፍጠን ፣ ሀይማኖት መለወጥ ፣ ደም ስር እየተገታተረ " እውነቱ ይህ ብቻ ነው " ማለት ፣ እዚህም እዚያም ለመሆን መሞከር ከሆነበት አንጻር ይህ ቀላል ነገር ነው ። ይቺ አጭር ቪዲዮ ከበቂ በላይ ትናገራለች ። የሄዱት ይመጣሉ ያለነው እንፀናለን! 🙏
Показать все...
👍 5
† ስንክሳር ግንቦት 11 † እንኳን ለታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ††† ††† ቅዱስ ያሬድ:- ከእግዚአብሔር ያገኘነው አባታችን : ክብራችን : ሞገሳችን ነውና በምን እንመስለዋለን? *አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም):: *ልቡናው የቅድስና ማሕደር:: *ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ ነው:: *እስከ አርያም ተነጥቆ የማይፈጸም ምሥጢርን የተመገበ ማን እንደርሱ! ሊቀ ሊቃውንት እዝራ ሐዲስ እንደሚሉት:- "ቅዱስ ያሬድ ለኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከራስ ጸጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ : ሙሉ አካሏ ነው::" ††† የሊቁ ዜና ሕይወት በጥቂቱ ††† ††† ቅዱስ ያሬድ የተወለደው በ505 ዓ/ም አክሱም አካባቢ ሲሆን እናቱ ክርስቲና (ታኡክልያ) አባቱ ደግሞ ይስሐቅ (አብድዩ) ይባላሉ:: ሊቁ በሕጻንነቱ ምሥጢር (ትምሕርት) አልገባው ብሎ ይቸገር ነበር:: ትምሕርት እንቢ ያለው ሰነፍ ስለ ነበር አይደለም:: በጥበበ እግዚአብሔር እንጂ:: ምን ትምሕርት ባይገባው ጾምና ጸሎትን ያዘወትር ነበር:: ልቡናው ደግሞ በእመቤታችንና በልጇ ፍቅር የታሠረ ነበር:: አንድ ቀን ግን መምሕሩ የነገሩት ቀለም አልያዝሕ አለው:: ሲፈትኑትም ባለመመለሱ ተገረፈ:: ዱላው በጣም ስለ ተሰማው ቅዱሱ ከመምሕሩ ኮብልሎ ማይ ኪራሕ አካባቢ ሲደርስ ደክሞት አርፎ እግዚአብሔር ትጋትንና ተስፋ አለመቁረጥን ከትል አስተማረው:: ትሏ ስድስት ጊዜ ወድቃ በሰባተኛው ፍሬዋን ስትበላት ተመልክቷልና:: ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ መምሕሩ ተመልሶ : ይቅርታ ጠይቆ ትምሕርት ጀመረ:: ሊቁም ትጋትንና ጸሎትን ከሰጊድ ጋር አበዛ:: እግዚአብሔር ደግሞ በድንግል እናቱ አማካኝነት የምሥጢር ጽዋን አጠጣው:: ካህኑ ያሬድ እንዲያ አልገባህ ያለው ምስጢር ተገልጦለት በጥቂት ጊዜ ብሉይ ከሐዲስ ወሰነ:: በምሥጢር ባሕርም ይዋኝ ጀመር:: ያን ጊዜ ሰማያዊ ዜማ አልተገለጠም ነበርና በጸሎት ላይ ሳለ ተደሞ መጣበት:: ሦስት መላእክት በሦስት ወፎች አምሳል መጥተው አነጋገሩት:: ድንገትም ነጥቀው ወደ ሰማያት : ወደ ልዑላኑ መላእክት ዘንድ አደረሱት:: ሊቁ በሰማያት ልዩ ምሥጢር : ልዩ ምስጋናና ልዩ ዜማን አዳመጠ:: ይሕንን ምስጋና ብዙ ቅዱሳን ቢሰሙትም ቅዱስ ያሬድ ግን ይዞት እንዲወርድ ተፈቀደለት:: ሊቁ ወደ ምድር ተመልሶ በታላቅ ተመስጦ አክሱም ጽዮን ውስጥ በሃሌታ አመሰገነ:: ሕዝቡና ንጉሡም ከጣዕሙ የተነሳ አደነቁ:: ቅዱስ ያሬድ ለተወሰነ ጊዜ በአክሱምና ደብረ ዳሞ ሲያገለግል ቆይቶ : ከመሬት ክንድ ከስንዝር ከፍ ብሎ ለእመቤታችን አንቀጸ ብርሃንን ደርሶላት ከሃገሩ ወጣ:: ††† ቅዱስ ያሬድ በቀሪ የሕይወቱ ዘመናት:- 1. አምስት ያሕል መጻሕፍትን ጽፏል:: 2. በጣና ቂርቆስ : በዙር አባና በሌሎችም ቦታዎች ወንበር ዘርግቶ ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርቷል:: 3.በሰሜን ተራሮች አካባቢ በትጋሃ መላእክትና በተባሕትዎ ኑሯል:: ††† በ576 (571) ዓ/ም በተወለደ በ71 ዓመቱ በዚህች ቀን ተሰውሯል:: ††† አባቶቻችን:- *ጥዑመ ልሳን *ንሕብ *ሊቀ ሊቃውንት *የሱራፌል አምሳያ *የቤተ ክርስቲያን እንዚራ *ካህነ ስብሐት *መዘምር ዘበድርሳን *ማኅሌታይ *ልዑለ ስብከት እያሉ ይጠሩታል:: ††† የቅዱሱ ጸሎትና በረከት ሃገራችንን ከክፉው ሁሉ ይጠብቅልን:: ††† ግንቦት 11 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ያሬድ ካህን ወማኅሌታይ 2.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ 3.ቅዱሳን ክርስቲናና ይስሐቅ (የቅዱስ ያሬድ ወላጆች) 4.ቅድስት ታውክልያ እናታችን (ንግሥናን ንቃ ሰማዕት የሆነች) 5.ቅድስት አፎምያ ሰማዕት 6.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት 7.ቅድስት አናሲማ ገዳማዊት 8.አባ በፍኑትዮስ ገዳማዊ 9.አባ አሴር ሰማዕት (ኢትዮዽያዊ) 10.አባ በኪሞስ ጻድቅ ††† ወርሐዊ በዓላት 1.ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት 2.ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት 3.ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና 🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹                    👇👇👇 (ይህ የቴሌግራም ቻናላችን ነው ይቀላቀሉን)     🕊 https://t.me/Sinksar 🕊      🕊 https://t.me/Sinksar 🕊      🕊 https://t.me/Sinksar 🕊
Показать все...
ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ዜናዎች

ይኼ ገጽ የአመቱ ስንክሳር በየቀኑ የሚቀርብበት ማብራሪያው ላልቀረበበትም የበለጠ እንድናነብ የሚረዳን መማማሪያ ነው። " ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ:: በዓለም ያለው ሁሉ: እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት: ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ: ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም:: ዓለሙም: ምኞቱም ያልፋሉ::" 1ዮሐ. 2:15 # ያጋሩ

👍 4
Фото недоступноПоказать в Telegram
ጥብቅ ማስታወቂያ ለሰባክያነ ወንጌል +++++++++++++++++++++ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥር በሚገኙ ገዳማት አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ፡ በስብከተ ወንጌል አገልግሎት ተመድባችሁ የምታገለግሉ ሰባክያን በሙሉ ከግንቦት 7 ቀን ጀምሮ እስከ ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ጽ/ቤት በስብከተ ወንጌል ዋና ክፍል በአካል እየቀረባችሁ ያላችሁን የትምህርት ማስረጃ ዋናውን እና ኮፒውን በመያዝ እንድትመዘገቡ እናስታውቃለን ፡፡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት
Показать все...
👍 2