ch
Feedback
ስንክሳርና ወቅታዊ የEOTC ጉዳዮች

ስንክሳርና ወቅታዊ የEOTC ጉዳዮች

前往频道在 Telegram

ይኼ ገጽ የአመቱ ስንክሳር በየቀኑ የሚቀርብበት ማብራሪያው ላልቀረበበትም የበለጠ እንድናነብ የሚረዳን መማማሪያ ነው። " ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ:: በዓለም ያለው ሁሉ: እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት: ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ: ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም:: ዓለሙም: ምኞቱም ያልፋሉ::" 1ዮሐ. 2:15 # ያጋሩ

显示更多
2 674
订阅者
无数据24 小时
+27
+630

数据加载中...

吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+80
在2个频道中
六月 '26
+73
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+34
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+34
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+32
在1个频道中
Get PRO
二月 '26
+39
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+47
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+93
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+73
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+56
在1个频道中
Get PRO
九月 '25
+43
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+43
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+30
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+53
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+66
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+73
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+42
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+70
在2个频道中
Get PRO
一月 '25
+104
在4个频道中
Get PRO
十二月 '24
+103
在1个频道中
Get PRO
十一月 '24
+116
在1个频道中
Get PRO
十月 '24
+101
在1个频道中
Get PRO
九月 '24
+135
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+115
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+97
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+60
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+56
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+68
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+64
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+96
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+84
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+66
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+35
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+48
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+57
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+132
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+195
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+142
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+75
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+58
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+85
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+114
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+137
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+93
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+89
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+74
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+71
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+58
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+110
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+86
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+71
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+59
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+102
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+46
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+63
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+62
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+47
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+38
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+47
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+65
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+101
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+72
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+26
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+58
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+51
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+46
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+388
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
29 七月+3
28 七月+3
27 七月+1
26 七月+5
25 七月+4
24 七月+2
23 七月+4
22 七月+4
21 七月+3
20 七月0
19 七月+4
18 七月+1
17 七月+2
16 七月0
15 七月+2
14 七月+1
13 七月+4
12 七月+4
11 七月+1
10 七月+3
09 七月+2
08 七月+3
07 七月+5
06 七月+1
05 七月+4
04 七月+2
03 七月+9
02 七月+3
01 七月0
频道帖子
#ሐምሌ_22 የታላላቅ አባቶቻችን የአቡነ ጎርጎሪዎስ ካልዕ እና የሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ የዕፈፍታቸው መታሰቢያ ነው። የአባቶቻችን በረከታቸው ይድረሰን: 👉 "ምንም ብትሉ:ምንም ብትሉ :ይህ ህዝብ አን
#ሐምሌ_22 የታላላቅ አባቶቻችን የአቡነ ጎርጎሪዎስ ካልዕ እና የሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ የዕፈፍታቸው መታሰቢያ ነው። የአባቶቻችን በረከታቸው ይድረሰን: 👉 "ምንም ብትሉ:ምንም ብትሉ :ይህ ህዝብ አንድ ህዝብ ነው: ዝም ብለህ ስራህን ስራ!" #አቡነ_ጎርጎሪዎስ_ካልዕ 👉 "አረማዊ የሆነው የፋሺስት መንግሥት ቤተ-ክርስቲያንን ለማቃጠል፣ ሕዝበ ክርስቲያንን ለመግደል፣ ሃይማኖትን ለማጥፋት፣ ታሪካችንን ለማበላሸት የመጣ ነው እንጂ በጎ ለመሥራት እውነተኛ ፍርድ ለመስጠት ስላልመጣ ለዚህ ለግፈኛ አትገዙ፡፡ ስለ ውድ ሀገራችሁ፣ ስለ ቀናች ሃይማኖታችሁ ተከላከሉ፡፡ ነፃነታችሁ ከሚረክስ ሙታችሁ ስማችሁ ቢቀደስ ታላቅ ዋጋ ያለው ክብር ታገኛላችሁ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዚህ ለጠላት እንዳይገዛ አውግዣለሁ፤ የኢትዮጵያ መሬት ጠላትን ብትቀበል የተረገመች ትሁን፡፡ በፈጣሪዬ  ክርስቶስ ስም የተገዘተች ትሁን፡፡” #ሰማዕቱ_አቡነ_ጴጥሮስ

2
🌿 ስንክሳር ሐምሌ 23 🌿 https://t.me/Sinksar ††† እንኳን ለእናታችን ቅድስት መሪና ሰማዕት እና ቅዱስ ለንጊኖስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† ታላቋ ቅድስት መሪና ሰማዕት (SAINT MARINA THE GREAT) ††† ††† እናታችን ቅድስት መሪና ስም አጠራራቸው ከከበረ : ተጋድሏቸው ካማረ ታላላቅ ሴት ሰማዕታት አንዷ ናት:: ተወልዳ ያደገችው ከዋናው ዘመነ ሰማዕታት በፊት በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን ሶርያ አካባቢ ነው:: አባቷ ዳኬዎስ የሚባል ጣዖት አምላኪ ቢሆንም እናቷ ግን ክርስቲያን ነበረች:: ነገር ግን እናቷ ገና በ5 ዓመቷ ሞተችባትና ለሞግዚት ተሰጠች:: የእግዚአብሔር ጥበብ ሆኖ ሞግዚቷ ደግ ክርስቲያን ነበረችና ለ10 ዓመታት ሃይማኖተ ክርስቶስን እና ምግባረ ጽድቅን አስተማረቻት:: ዕድሜዋ 15 ዓመት ሲሆን አባቷ ዳኬዎስ አረፈ:: በዘመኑ ዳኬዎስ የሚሉት (ቅዱስ መርቆሬዎስን የገደለው) ክፉ ንጉሥ ነበርና ክርስቲያኖችን አሳደዳቸው:: ይህን ዜና ቅድስት መሪና ስትሰማ ደስ አላት:: እጅግ ባማረ ንጽሕና እንደ ኖረች ሁሉ በክርስቶስ ስም ደሟን ለማፍሰስ አስባ ወደ ንጉሡ መኮንን ሔደች:: ††† አበው እንዳስተማሩን ከሴቶች ሰማዕታት በውበትና ደም ግባት እንደ ቅዱሳት:- *መሪና *አርሴማ እና *ጣጡስ የሚያክል የለም:: ዐይንን ማፍዘዝ የሚችል ውበት ነበራቸው:: መኮንኑ መልኩዋን ዐይቶ ሰውነቱ ተናወጠ:: "ጣዖት አምልኪና የእኔ ሚስት ሁኚ" አላት:: እርሷ ግን መኮንኑን ከነ ጣዖቱ አቃለለችው:: "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ" አለችው:: መኮንኑ ካነጋገሯ የተነሳ ተቆጥቶ ይገርፏት ዘንድ አዘዘ:: መሬት ላይ ጥለው በብረት ዘንግ ቢመቷት አካሏ እየተቆረጠ ብዙ ደም ፈሰሰ:: ወስደውም ጨለማ ውስጥ ጣሏት:: ቅዱስ ሚካኤል ከሰማይ ወርዶ አድኗት: አጽንቷትም ዐረገ:: በማግስቱ በመጋዝ አካሏን ቆራርጠው ጣሉ:: ዳግመኛ ሊቀ መላእክት አዳናት:: ወደ ጨለማ ክፍል ወስደው ሲጥሏት ትልቅ ዘንዶ መጣባት:: እጆቿ ተዘርግተው እጸለየች ዋጣት:: እርሷ ግን ጸሎቷን ቀጠለች:: ከደቂቃዎች በሁዋላ ግን ዘንዶው ለ2 ተሰነጠቀና እጆቿ እንደተዘረጉ ወጣች:: በሌላ ቀን ግን ሰይጣን ፊት ለፊት መጥቶ ታገላት:: ከሰማይ ነጭ ርግብና መስቀል ወርዶላታልና አልቻላትም:: ከእግሯ በታች ጥላ ደጋግማ ረገጠችው:: ሰይጣንም በሐፍረት እየጮኸ ሔደ:: "ለሰይጣን ኬደቶ ከመ አሣዕን በእግር" እንዲል:: (እንዲህ ነበሩ የቀደመው ዘመን እናቶቻችን) መኮንኑ ከክርስትና ያስወጣት ዘንድ በትልቅ ጋን ውሃ አስፈልቶ "በዚያ ላይ ቀቅሏት" አለ:: ድንገት ግን ከሰማይ ነጭ ርግብ ወርዳ: ውሃውን አቀዝቅዛ: 3 ጊዜ በውሃው አጠመቀቻት:: (እስከዚህ ሰዓት ድረስ አልጠመቀችም ነበርና) ርግቧ የብርሃን ልብስ አልብሳ: አክሊለ ክብር ደፋችላት:: መኮንኑ ተስፋ ስለ ቆረጠ "አንገቷን በሰይፍ ምቱ" አለ:: በዚያች ሰዓት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወርዶ "ብጽዕት መሪና ብጽዐን ይገባሻል" አላት:: "ስምሽ በሚጠራበት: መታሰቢያሽ በሚደረግበት ሁሉ በዚያ ረድኤት: በረከት ይበዛል:: አንቺን ያከበረውን አከብረዋለሁ:: ከርስትሺም አስገባዋለሁ" ብሏት ጌታችን ዐረገ:: ወታደሮቹ አንገቷን በሰየፉ ጊዜ ታላቅ መነዋወጽ ሆነ:: ድውያን ተፈወሱ: ዕውሮች አዩ: አንካሶች ረቱ: የማይሰሙትም ሰሙ:: ቅዱሳን መላእክትም ከሰማያት ወርደው የቅድስት መሪናን ነፍስ በዝማሬ አሳረጉ:: ††† ቅዱስ ለንጊኖስ ሰማዕት ††† ††† ለንጊኖስ ማለት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስብከት ዘመን የዺላጦስ ወታደር የነበረ ሰው ነው:: ስለ ጌታችን ተአምራት በየጊዜው ይሰማ ነበር:: ሔዶ እንዳያገኘው ግን አይሁድን ይፈራ ነበር:: እነርሱ "በክርስቶስ ያመነ ሁሉ ከምኩራብ ይባረር" ብለው ነበርና:: (ዮሐ. 9:22) ጌታችን በተሰቀለባት ዕለተ ዐርብ ግን ጭንቅ ሆነበት:: ጌታን እንዲሰቅሉ ከታዘዙ ወታደሮች እንደ አንዱ ተመርጦ ነበርና በዘዴ "አሞኛል" ብሎ እስከ 9 ሰዓት ድረስ ቆየ:: በሁዋላ ግን አይሁድ "በክርስቶስ ሞት ያልተባበረ ሁሉ ወንጀለኛ ነው" የሚል አዋጅ በማስነገራቸው እየፈራ ቀራንዮ ሲደርስ "ጐኑን ውጋው" ብለው ረዥምና ጥቁር ጦር ሰጡት:: ለንጊኖስ ወደ ጌታችን ዐይን ተመለከተ:: እያየው እንዳልሆነ ገመተ:: ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው በባሕርይ ሥልጣኑ ለይቷልና ጦሩን ጨብጦ ወደ ጌታ ጐን ልኮ ወጋው:: ከጌታ ቀኝ ጐንም በ"ለ" አምሳል ትኩስ ደምና ውሃ ፈሰሰ:: አንዷ ፍንጣቂ ሔዳ የታወረች ዐይኑ ላይ ዐርፋ ዐይኑን አበራች:: ለለንጊኖስ ታላቅ ደስታ ሆነ:: ለእኛ ግን ማየ ገቦና ደመ ገቦ ፈለቀልን:: የጌታችን ትእግስቱና ቸርነቱ ግን ይደንቃል:: "ከመ ኢየሐስብ ቦቱ ዘኩናተ እዱ ርግዘቶ:: በኃጣውኢሁ ለዘኢፈቀደ ሞቶ:: ምሕረቶ እሴብሕ ወዐዲ ትዕግስቶ::" እንዳሉ ሊቃውንት:: ጌታችን ከተነሳ በሁዋላ ለንጊኖስ ወደ ቅዱስ ዼጥሮስ ዘንድ ሒዶ ስለ እውነት : ስለ ሃይማኖትም ተማረ:: ተጠምቆ: ምድራዊ ወታደርነቱን ትቶ እየሰበከ ከኢየሩሳሌም ወደ ቀዸዶቅያ ወረደ:: ለዘመናትም ጌታችን ክርስቶስን በሥርዓተ ወንጌል አገለገለ:: በመጨረሻም በጢባርዮስ ቄሣር ዘመን አይሁድ አሳደዱት: አንገላቱት:: የነርሱ ወገን ስለነበረም መከራ አጸኑበት:: የጽድቅ አርበኛና የክርስቶስ ሐዋርያ ቅዱስ ለንጊኖስ ግን ጸና:: በዚህች ዕለትም አይሁድ አንገቱን ቆርጠውት ለሰማዕትነት በቃ:: ቅዱሱ በሕይወቱም በዕረፍቱም ተአምራትን ሠርቷል:: ††† እግዚአብሔር በቸር ጥሪው ሁላችንም ወደ ቀናው የጽድቅ ጐዳና ይጥራን:: ከሰማዕታቱም ረድኤት በረከት ይክፈለን:: ††† ሐምሌ 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅድስት መሪና እናታችን (ታላቋ ሰማዕት) 2.ቅዱስ ለንጊኖስ ሐራ (ሐዋርያና ሰማዕት) 3.ቅዱስ አብጥልማዎስ ††† ወርኀዊ በዓላት 1.ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት 2.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት 3.ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ሰሎሞን (ንጉሠ እሥራኤል) 4.አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ 5.ቅዱስ ዳንኤል ነቢይ 6.አባ ሳሙኤል 7.አባ ስምዖን 8.አባ ገብርኤል ††† "ወደ ጌታ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን እርሱ ፈጽሞ እንደ ሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም:: ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጐኑን በጦር ወጋው:: ወዲያውም ደምና ውሃ ወጣ:: ያየውም መስክሯል : ምስክሩም እውነት ነው:: እናንተም ደግሞ ታምኑ ዘንድ : እርሱ እውነት እንዲናገር ያውቃል:: ይህ የሆነ:- "ከእርሱ አጥንት አይሰበርም" የሚል የመጽሐፍ ቃል እንዲፈጸም ነው:: ደግሞም ሌላው መጽሐፍ:- "የወጉትን ያዩታል" ይላል::" ††† (ዮሐ. 19:33) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† ❖•°ೋ•❖ °   ❖•°ೋ•❖ ° 👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇 https://t.me/Sinksar https://t.me/Sinksar
121
3
没有文字...
156
4
没有文字...
151
5
✝ ስንክሳር ሐምሌ 22 ✝ † እንኳን ለሰማዕታት አበው አቡነ ጴጥሮስ ኢትዮጵያዊ : ቅዱስ መቃርስ እና ቅዱስ ለውንትዮስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። † † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † 🙏† ታላቁ ኢትዮጵያዊ ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ † ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ምንም እንኳ ለሃገራቸውና ሃይማኖታቸው ያን ያህል ዋጋ ቢከፍሉም ትውልዱም : መንግስቱም : ራሷ ቤተ ክርስቲያናችንም ተገቢውን ክብር ሰጥተው እያሰቧቸው አይደለም:: እስኪ እንዲያው ቢያንስ እንደ ክርስቲያን : አንድም እንደ ኢትዮጵያዊ እነዚህ ነገሮቻቸውን እናስብ:: ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ከልጅነታቸው ጀምረው ትምሕርት : ትሕርምትና ደግነት ወዳጅ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ወቅቱ ኢትዮጵያ የራሷን ጳጳሳት የምትሻበት ጊዜ ነበርና በፈቃደ እግዚአብሔር ለመጀመሪያ ጊዜ የሃገራችን አራት አባቶች ጵጵስናን ተሾሙ:: እነርሱም ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ እና አበው አባ ሚካኤል: አባ አብርሃም እና አባ ይስሐቅ ናቸው:: የተሾሙትም ግንቦት 18 ቀን 1921 ዓ/ም ነው:: አቡነ ጴጥሮስ ከተሾሙ በኋላ በሐዋርያዊ አገልግሎትና በጸሎት ተግተው ኑረዋል:: በ1928 ዓ/ም ፋሺስት ጣልያን ሃገራችንን በወረረች ጊዜ ቆራጡ ጳጳስ በዱር በገደል ለመሔድ ተነሱ:: በየበርሃው እየሔዱ አርበኞችን ሲያጽናኑ : ሲናዝዙ : ሲባርኩም ቆይተዋል:: ለሃገራቸውና ለሃይማኖታቸው ረሃብ : ጥም : እንግልትን ታግሰዋል:: በተያዙባት በዚያች ሌሊትም በጣልያኖች ለሮም እምነትና ለአገዛዙ እንዲያጐበድዱ ተጠየቁ:: ቆራጡ ሰው ግን እንቢ ቢሉ የሚደርስባቸውን እያወቁ "አይደረግም" አሉ:: በማግስቱ በአደባባይ መትረየስ ተደግኖባቸው አሁንም ጥያቄ ቀረበላቸው:: አቡነ ጴጥሮስ አፋቸውን ከፍተው ሊናገሩ ጀመሩ:- "የሃገሬ ሕዝብ ሆይ! ለሃገርህ : ለሃይማኖትህ ባትጋደል ትውልድ ይፋረድህ:: ለጣልያን ግን እንኳን ሰው ዛፍ ቅጠሉ መሬቱ እንዳይገዛለት አውግዣለሁ" አሉ:: በደቂቃዎች ልዩነት በግራዚያኒ ትዕዛዝ የመትረየስ ጥይት ዘነበባቸው:: አካላቸው ተበሳስቶ በሰንሰለት እንደ ታሠሩ መሬት ላይ ወደቁ:: አንዱ ወታደር ቀርቦ ቢመለከት ትንሽ ትንፋሽ ነበረቻቸው:: "ይሔ ቄስ አልሞተም" ብሎ ጭንቅላታቸው ላይ ተኮሰባቸው:: አቡነ ጴጥሮስ ለሃገራቸውና ሃይማኖታቸው ተሠው:: ነገሩ በአርበኞች ዘንድ ሲሰማ ትግሉ ተቀጣጠለ:: ይሄ የተደረገው ሐምሌ 22 ቀን በ1928 ዓ/ም ነው:: አቡነ ጴጥሮስም በተ/መ/ድ (UN) የሺህ ዓመቱ ምርጥ ሰማዕት (MARTYR OF THE MILLENIUM) በመባል ይታወቃሉ:: ††† ቅዱስ መቃርስ ሰማዕት ††† ††† ሰማዕቱ ተወልዶ ያደገው በአንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን የታላቁ ቅዱስ ፋሲለደስ እና የቅድስት ሶፍያ ልጅ ነው:: ምንም በቤተ መንግስት ውስጥ ቢያድግም ከወላጆቹ ፍቅረ ክርስቶስን : ንጽሕናንና ደግነትን ወርሷል:: በተለይ ነዳያንን ሰብስቦ ዕለት ዕለት ያበላ ነበር:: (መቃርስ ማለት በልሳነ ዮናኒ ብጹዕ : ንዑድ : ክቡር ማለት ነው::) ቅዱሱ ያ የመከራ ዘመን ሲመጣ ሁሉም ቤተሰብ ስለ ክርስቶስ መሞትን በመምረጡ እርሱም ደስ እያለው የመከራው ተካፋይ ሆኗል:: ያን የመሰለ የቤተ መንግስት ክብር ስለ ክርስትና ናቀው:: ተገረፈ:: ተሰቃየ:: በእሳትም ተቃጠለ:: አንድ ጊዜም በአደባባይ የሞተ ሰው በጸሎቱ አስነስቶ "መስክር" አለው:: ከሞት የተነሳውም የክርስቶስን አምላክነት በመመስከሩ በአደባባይ የነበሩ ብዙ አሕዛብ በክርስትና አምነው ተሰይፈዋል:: ቅዱስ መቃርስን ግን ብዙ አሰቃይተው በዚህች ቀን አንገቱን ቆርጠውታል:: ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ አጽሙን አፍልሶ በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በስሙ ቤተ ክርስቲያን አንጾለታል:: ††† ቅዱስ ለውንትዮስ ሰማዕት ††† ††† ቅዱሱ የተወለደው በተመሳሳይ ዘመን (በቅዱስ መቃርስ) ሲሆን ሃገሩ ጠራብሎስ ትባላለች:: በወቅቱ በወታደርነት ነገሥታቱን ያገለግል ነበር:: ድንግል : ደም ግባት የሞላለት ወጣት ስለ ነበር በሰዎች ፊት ሞገስ ነበረው:: እርሱ ግን ምንም ወታደር ቢሆን ጾምና ጸሎትን ያዘወትር ነበር:: በተለይ ደግሞ የዳዊትን መዝሙር እየመላለሰ ይጸልየው : ይወደው ነበር:: ንግግሩ ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ጨውነት የታሸ ነውና ብዙ ጓደኞቹን ከክህደት ወደ ሃይማኖት : ከክፋት ወደ ደግነት መልሷል:: የመከራ ዘመን በደረሰ ጊዜም በገሃድ ስመ ክርስቶስን ይሰብክ ነበር:: ክፉ ሰዎች ከሰውት በመኮንኑ ፊት በቀረበ ጊዜም አልፈራም:: ወታደሮቹ መሬት ላይ ጥለው እየደበደቡት : ደሙ እንደ ጐርፍ እየተቀዳ እርሱ ግን ይዘምር ነበር:: በመጨረሻም ስለ ክርስቶስ ፍቅር በዚህች ቀን አንገቱን ተሰይፏል:: ቅዱስ ለውንትዮስ እጅግ ተአምረኛ ሰማዕት ነውና በእምነት እንጥራው:: ††† እግዚአብሔር ዐጽመ ሰማዕታትን ይጠብቅልን:: ከሰማዕታቱ ጽናትን : ጸጋ በረከትን ይክፈለን:: ††† ሐምሌ 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕት (ኢትዮጵያዊ) 2.ቅዱስ መቃርስ ሰማዕት (የፋሲለደስ ልጅ) 3.ቅዱስ ለውንትዮስ (ክቡር ሰማዕት) 4.አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት (ቅዳሴ ቤታቸው) 5.ቅዱስ መርካሎስ ††† ወርኀዊ በዓላት 1.ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት 2.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ 3.ቅዱስ ደቅስዮስ (የእመቤታችን ወዳጅ) 4.አባ ጳውሊ የዋህ ††† "እንግዲህ አትፍሯቸው:: የማይገለጥ የተከደነ: የማይታወቅም የተሠወረ ምንም የለምና:: በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ:: በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ:: ሥጋንም የሚገድሉትን: ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ:: ይልቅስ ነፍስንም: ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ::" ††† (ማቴ. ፲፥፳፮) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† ❖•°ೋ•❖ °   ❖•°ೋ•❖ ° 👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇 https://t.me/Sinksar https://t.me/Sinksar https://t.me/S
181
6
✝ ስንክሳር ሐምሌ 21 ✝ ††† እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም : ቅዱስ ዑራኤል እና ለቅዱሳኑ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† ድንግል እመቤታችን እና ቅዱስ ዑራኤል። ††† በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት በዚህች ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዑራኤል:- 1.ድንግል ማርያም በአካለ ሥጋ እያለች ወደ ሰማይ አሳርጓታል:: በሠረገላ ብርሃን ጭኖ: በክንፎቹም ተሸክሞ: አስቀድሞ ገነትን ቀጥሎም ሲዖልን አስጐብኝቷታል:: በዚህም ምክንያት እመ ብርሃን ስለ ኃጥአን የምታለቅስ: የምትለምንና የምትማልድ ሆናለች:: ለምናም አልቀረች የምሕረት ቃል ኪዳን ተቀብላለች:: 2.ቅዱሱ መልአክ እመ ብርሃንን በስደቷ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መርቶ አምጥቷታል:: በክንፉ ተሸክሞ: በአራቱም አቅጣጫ አዙሮ አሳይቶ አሥራት እንድትቀበል አድርጓል:: 3.ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ ደሙን በጽዋዕ አድርጐ በኢትዮጵያ ወንዞች ላይ አፍስሷል:: 4.ለብዙ ቅዱሳን (አባ ጊዮርጊስን ጨምሮ) ጽዋዐ ልቡናን አጠጥቷል:: ††† አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ኢትዮጵያዊ ††† ††† ወላጆቻቸው ማርቆስ እና እግዚእ ክብራ ይባላሉ:: ተአምራትን ገና ከእናታቸው ማኅጸን ጀምሮ ይሠሩ የነበሩት ጻድቁ በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው መንነዋል:: በስብከተ ወንጌልም ትግራይና አካባቢውን አድርሰዋል:: በነዚህም ጊዜያት ብዙ አርድእትን አፍርተዋል:: በጋስጫ ገዳም መስርተው የወንድና የሴት ብለውም ለይተዋል:: ሲጸልዩም ሆነ ሲያስተምሩ ተደሞ ይመጣባቸው የነበረ ሲሆን አንድ ቀን እባቡን ዓሣ አድርገው ደቀ መዛሙርትን አስደንቀዋል:: ከጾም: ከጸሎትና ከስግደት ባሻገር ከወቅቱ ንጉሥ ዓምደ ጽዮን መከራ በመቀበላቸው እንደ ሰማዕትም ይቆጠራሉ:: ከብዙ የገድል ዓመታት በኋላም በ1330 ዓ/ም በዚህች ቀን ትግራይ ውስጥ ዐርፈዋል:: በቆይታ ግን ወደ ጋስጫ ዐጽማቸው ፈልሷል:: ††† ቅዱስ ላዕከ ማርያም ኢትዮጵያዊ ††† ††† ቅዱሱ የአፄ ናዖድ የልጅ ልጅ : የቅድስት ሮማነ ወርቅ ልጅ : የልብነ ድንግል የእህት ልጅና የገላውዴዎስ አጐት ነው:: በግራኝ አህመድ ዘመን ተማርኮ ወደ የመን : ከዛም ቱርክ ተወስዷል:: ሃይማኖቴን አልክድም ስላለ ብዙ አሰቃይተው : አባለ ዘሩን ቆርጠው ጃንደረባ አደረጉት:: በድንቅ ተአምር ግን ወደ ሃገሩ ተመለሰ:: እስከ ዕለተ ሞቱም ነዳያንን ሲያበላ ኑሮ ዛሬ ዐርፏል:: ††† ቅዱስ ሱስንዮስ ††† በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረ የኤፌሶን ሰው ሲሆን ጃንደረባም ነበር:: በ431 ዓ/ም ሁለት መቶውን የጉባዔ ኤፌሶን ሊቃውንት አገልግሎ በዛው ዓመት አርፏል:: ቅዱስ ቄርሎስ ገንዞ ቀብሮታል:: ††† ብጹዕ አወ ክርስቶስ ††† ከተባረከች ሚስቱ ጋር በአንድ ቤት ውስጥ : ግን ደግሞ በድንግልና ኑረዋል:: ቀን ቀን እንግዳ ሲቀበሉ: ነዳያንን ሲያበሉ ውለው ሌሊት ሲገሰግዱና ሲጸልዩ ያድሩ ነበር:: ጌታችን ከሰማይ መስክሮላቸው ዛሬ ዐርፈዋል:: ††† ቅዱስ ዮራኖስ ††† በሉቃስ ወንጌል ላይ (ሉቃ. 23:47) የምናገኘው የመቶ አለቃው ሲሆን በጌታችን ትንሣኤ ቀን የጠፋች ዓይኑ በርታለት በክርስቶስ አምኖ ለሰማዕትነት በቅቷል:: ††† ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟን ፍቅሯን : ከቅዱሳኑ ሁሉ ጸጋ በረከትን እግዚአብሔር ያድለን:: ††† ሐምሌ 21 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም ወላዲተ አምላክ 2.ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት 3.አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ጻድቅ (ኢትዮጵያዊ) 4.ቅዱስ ላዕከ ማርያም ሔር (ኢትዮጵያዊ) 5.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ (ኢትዮጵያዊ) ልደታቸው 6.ብጹዕ አወ ክርስቶስና ሚስቱ (ጻድቃን) 7.ቅዱስ ሱስንዮስ ጻድቅ 8.ቅዱስ ዮራኖስ መኮንን (የመቶ አለቃው) ††† ወርኀዊ በዓላት 1.አበው ጎርጎርዮሳት 2.አቡነ ምዕመነ ድንግል 3.አቡነ አምደ ሥላሴ 4.አባ አሮን ሶርያዊ 5.አባ መርትያኖስ ጻድቅ ††† "እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ: ስለ ሶምሶንም: ስለ ዮፍታሔም: ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም: ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና:: እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ:: ጽድቅንም አደረጉ:: . . ." ††† (ዕብ. ፲፩፥፴፪) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† ❖•°ೋ•❖ °   ❖•°ೋ•❖ ° 👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇 https://t.me/Sinksar https://t.me/Sinksar https://t.me/Sinksar
163
7
ትርክትና መዘዙ! ለተሳሳተ ትርክት በራችንን ከፍተን የሰጠን እኛው ነን። እነአህመዲን ጀበል በተከፈተው በር እየገቡ የክርስትናችንን ታሪክ ይበልጥ ለማዛባት ዕድል አግኝተዋል። የኢትዮጵያ ክርስትና በስደት የመጡትን የመጀመሪያዎቹን እስላሞች በማስተናገድ እስልምናን ከመጥፋት ታድጓል። ይህን በመጽሐፋቸው ሳይቀር በደማቅ የተጻፈ የማይካድ ታሪክ ኢስታንቡካውያን ለማጠየምና ለማረሳሳት የሚያደርጉት ጥረት ይታወቃል። አሁን ደግሞ ራሳቸውን የእንግዳ ተቀባይነቱ ቦታ ላይ የማስቀመጥና የታሪክ ነጠቃ ዘመቻ ላይ ተሠማርተዋል።አዲስ ትርክት ለመፍጠር ደፋ ቀና እያሉ ነው። በተደጋጋሚ ጊዜ እንዳነሣሁት የኢትዮጵያን ታሪክ ከራሳቸው ፍላጎት አንፃር የጻፉት የአውሮፓ ጻሕፍት ብዙ ነገር አዛብተዋል። አንዱ ማሳያ የኢትዮጵያን የክርስትና ታሪክ ሦስት መቶ ክፍለ ዘመን አዘግይተውና ወደ አራተኛው መ/ክ/ዘ አሻግረው መተረካቸው ነው። ይህን ያደረጉበት ዋናው ምክንያታቸው ከአውሮፓዊ ትምክህት ወይም ከErocentric ጠባያቸው ጋር የተያያዘ ነው። ብዙዎቹ አውሮፓውያን በባርባሪክ አኗኗር እያሉ በክርስትና ትኖር የነበረች አፍሪካዊ ሀገር እንደነበረች ማሳየት አይፈልጉም። ስለዚህ ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ የገባበትን ዘመን ታላቁ የሮማ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ለክርስትና የነጻነት ዐዋጅ(Edict of Milan) በሮም ግዛት ካወጀበት ዘመን በኋላ ወስደው ከንጉሥ ኢዛና ጋር ያያይዙታል። የሚያሳዝነው የራሳችን የታሪክ ምሁራን ታሪካችንን ሲያጠኑ የጥንት የክርስትና ታሪክ ተጠያቂ ሊቃውንት አነሩፊኖስ እና አውሳብዮስን በዘመንም የቀደመ ምስክርነት በምንጭነት አልተጠቀሙም። የሀገራችንን የቃል ትውፊት፣ ድርሳናትና ገድላትን በአግባቡ አልተጠቀሙም። በአውሮፓውያን ተንኮል አዘል ስሑት ትረካ ላይ ተንጠልጥለው እነርሱም ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ የገባበትን ዘመን ወደ 4ኛው መ/ክ/ዘ ይወስዱታል። ከቅዱስ መጽሐፍም ሆነ የቀደምት የታሪክ ጻሕፍት መዛግብት የሚያስረግጡልን እውነት ክርስትና በመጀመሪያው ምእተ ዓመት፣ በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ቅዱስ ባኮስ አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን፣ ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ በኢትዮጵያ መስበኩን፣ በቅዱስ ፍሬምናጦስ ተጋድሎ፣ በተሣእቱ ቅዱሳን የተጠናከረ ሥምሪትና በቅዱስ ያሬድ አገልግሎት መስፋፋቱን ነው። ፬ኛው መክዘ ክርስትና በንጉሥ ኢዛና በኩል ብሔራዊ ሃይማኖት ተደርጎ የታወጀበት ነው። ከአርመንያ ቀጥሎ ክርስትናን ብሔራዊ ሃይማኖት በማድረግ ኢትዮጵያ በታሪክ ስሟ ይነሣል። ሰሞኑን አህመዲን ጀበል ለተከታዮቹ የክርስትናን አገባብ በማዛባት እርሱ ለሚያራምደው የጽንፈኝነት ዘውግ አይዶሎጂ እየገነባ ይበጃል ያለውን ትርክት እያስታጠቀ ነው። #መፍትሔ ፩ኛ ቤተ ክርስቲያን ስለ ኢትዮጵያ ክርስትና የሚነገረውን የተንሸዋረረ ታሪክ እንዲታረምና በማስተማሪያ መጻሕፍትም ሆነ በኦፊሴላዊ መንገዶች በትክክል እንዲገለጽ ደጋግማ መጠየቅ። ፪ኛ ቤተ ክርስቲያን ዓርማዋ የአጀማመር ታሪኳን እንዲያካትት አድርጋ ማዘጋጀትና ለይፋዊ አገልግሎት እንዲውል ማድረግ አለባት። የሕንድ ማላንካራ ቤተ ክርስቲያን ዓርማዋ ላይ «ጌታዬ አምላኬ!» የሚል ቃል አለ። መሥራች አባቷ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ መሆኑን ፍንትው አድርጎ ያሳያል። የእኛም ቤተ ክርስቲያን «እነሆ ውኃ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድን ነው?» (ሐዋ ፰፥፴፮) ወይም «ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ አምናለሁ!» (ሐዋ ፰፥፴፯) የሚለውን ዓርማዋ ላይ በማስገባት ቋሚ ምስክር እንዲሆን ማድረግ ትችላለች። ለምን ይህ ቃል የዓርማዋ አካል እንደሆነ የሚጠይቅ ሰው በቀላሉ የቤተ ክርስቲያኗን ጥንትና የእምነት ዓምዷን ይረዳል ማለት ነው። ፫ኛ ሁላችም ኦርቶዶክሳዊ በማንኛውም መድረክ የኢትዮጵያን የክርስትና ታሪክ ወደ አራተኛ መክዘ የሚወስድ አነጋገር ወይም ሰነድ ስንሰማ እንዲታረም መጠየቅ፣ በአሳማኝ የታሪክ ምንጮች የተደገፈውን እውነት መግለጥ ይኖርብናል። Wondwosen Wubie
260
8
የዛሬውን የአህመዲን ጀበልን መናደፍ የተወ የሚመስል ልጥፍ ሳይ እርሱና መሰሎቹ የሚከተሉት Door-in-the-Face (DITF) ስልት ታወሰኝ። አህመዲን ጀበልና መሰሎቹ ሲበርድ በእጅ ሲፋጅ በማንኪያ ስልትን ይጠቀማሉ። ይህ የውሃብያዎች ስልት በአንድ ሀገር ውስጥ የተፅእኖ አድማሳቸው አስተማማኝ ደረጃ ደርሷል ብለው እስኪያምኑ ድረስ ብዙ ቦታ የተገብሩት የተለመደ ስልታቸው ነው። የሌላውን ሃይማኖት ተከታይ ግብረ መልስ ለመለካት የሚጠቀሙት፣ ካልታየሁ እሰርቃለሁ ከታየሁ እስቃለሁ ዓይነት ስልት ነው፤ Door-in-the-Face (DITF) technique ይባላል። ስልቱ የተጋነነ የተበዳይነት ጩኸት በማሳማት ሚገባው በላይ ድርሻን ለመውሰድ የሚደረግ አንድ የድርድር ጥበብ ስልት ነው። አክራሪው ኃይል ግን የድርድር መንገድ ደጋፊ አይደለም። ለድርድር የሚቀመጠው ለመጨፍለቅ ዕድል እስኪያገኝ ድረስ ብቻ ነው። ጭፍለቃው ክርስትናን ወይም ከእስልምና ውጭ ያለውን ዒላማ በማድረግ የሚቆም አይደለም። ከእስልምናም የእነርሱን ፖለቲካዊ እስላም (Poletical Islam) ያልተከተለን ወይም አሁን ያለውን የውሃብያ መንገድ ለዘረጋው፣ ለመሀመድ አብዱል ዋሐብ አስተምህሮ ያላጎነበሰን ሙስሊምም አይምርም። በDoor-in-the-Face (DITF) ስልት መሠረት አህመዲን ጀበልና የውሃብያው ክንፍ እጅግ የተጋነነ ጥያቄ እያነሡ ነው። ለዚህ ግባቸው ማስፈጸሚያ ከመካከለኛው ዘመን እስካሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ሙስሊሙ በጭቆና የቆየና ያለ አስመስሎ ማቅረብን ተያይዘውታል። ጆሮ ለሰጣቸው ሁሉ ያልነበረ ጭቆናን ወይም እነርሱ በአህመድ ግራኝ በኩል ዕድል ሲያገኙ ሕዝበ ክርስቲያኑን ቅቤ ሲቀቡ የቆዩ የሚያስመስል በመካከለኛው ዘመን ኢትዮጵያ ውስጥ ዲሞክራሲ ባለመኖሩ( ያው የhistoricism ችግር ነው፤ ትናንትን በዛሬ መነጽር የማየት ችግር) የእኩልነት ዕድል አጥተው ሲጨቆኑ የቆዩ፣ አሁንም ያ ትከሻቸው በጭቆና መዛሉን ደጋግመው ያስተጋባሉ። የነገሥታቱን ዘመን እንተወውና ሃምሳ ዓመት የሞላውን የመንግሥትና የሃይማኖት መለያየት መርሕ ረስተን አሁንም የእኩልነት መብታቸውን እንደተነፈጉ እንድናስብ ይጎተጉታሉ። ለብዙ ዘመናት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እኩልነቱ ተጠብቆለት የኖረው፣ ከሃምሳ ዓመት በላይ ደግሞ ፖለቲካዊ እኩልነቱን በዓዋጅ የሚያረጋግጥ ዕድል ተሰጥቶት(የዐፄውን ዘመን ሃይማኖት የግል ሀገር የጋራ መርሕ ለጊዜው አቆይተነው) የኖረው ብዙኃኑ ሙስሊም በዚህ የእነአህመዲን ጀበል ጩኸት ስሑት አረዳድ እንዲኖረው እየተደረገ ነው። ይህም ለሀገራዊ አንድነት ሰላምና አጠቃላይ አብሮነት አደጋ አለው። ውሃቢያው ክንፍ (ኢስታንቡላውያን) ሌላው ቢቀር ባለፉት ሃምሳ ዓመታት የፖለቲካ እኩልነቱን ከማረጋገጥ አልፎ የክርስቲያኖች ቁጥር አናሳ በሆነበት የሀገራችን ክፍል እንዳሻው የሚገድልና የሚያሳድድ ኃይል ሁኖ እያለ ወንጀሉን «እኩልነት አጣሁ» በሚል የአደባባይ ጩኸት መደበቅን ተያይዞታል። ይህን የሚያደርገው በፖለቲካው ዓለም ከቁመቱ በላይ የሆነ ያልተገባ ውክልና ፍለጋ ላይ ስለሆነ ነው። በDoor-in-the-Face (DITF) ስልት መሠረት አስቀድሞ የተጋነነ ድርሻ በመጠየቅ ነው የሚጀመረው። በጣም ከልክ ያለፈው ፍላጎቱ እንደማይሳካ ሲያውቀው አሁንም ሌላ ከልክ ያለፈ ግን ከመጀመሪያው ቀነስ ያለ ጥያቄ እንዲመለስለት ያቀርባል። ተጠያቂው ወይም ሌላኛው ተደራዳሪ አካል በጫና ውስጥ ይገባና የራሱን መብት ለማመቻመች የሚገደድበት ሁኔታ ይፈጠራል። ውሃቢያው ኃይል በዚህ ቀዳዳ ሾልኮ በመግባት ከእኔ ውጭ ወደ ውጭ በሚል መርሕ የማይጠረቃ ፍላጎቱን ለማስፈጸም ዘመቻውንም ሥራውንም ይቀጥላል። ማንም ሰው አህመዲን ይህን ስልት እየተገበረ መሆኑን በልጥፎቹ መታዘብ ይችላል። የዛሬው ጽሑፉ ረገብ ያለ ሐሳብ ያነሳበት፣ ምናልባት የተለጠጠ ጥያቄው እንደማይሠራ ሲረዳ ሁለተኛውን ጥያቄ ለማንሣት ኪሱን የዳበሰበት ይመስላል። በጽሑፎቹ ይህን ስልቱን እንዴት እንደሚጠቀምበት አንድ በአንድ ማሳየት ይቻላል። አንድም ማንም ሊረዳው በሚችል ሁኔታ በግልጽ ስለሚያቀርበው፣ አንድም ጽሑፌ እንዳይረዝም በመሥጋት ለዛሬ ትቼዋለሁ። ይህ ስልት ሲሳካላቸው እንደ ማሳለጫ ካልተሳካ ደግሞ እንደ አማራጭ የሚጠቀሙባቸው ሌሎች ስልቶችም አሏቸው። ሲያስፈልግ እንመለስባቸዋለን። እስከዚያው በቀይ ያከበብኩትን ተመልከቱልኝ። «እስልምና ወደ ኢትዮጵያ የገባው በወረራ አይደለም፤» ይላል። ይህ ወሳኝ ነጥብ ከአህመዲን መውጣቱን ያዙልኝ። Wondwosen Wubie
214
9
መዝግባችሁ ያዙ በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ ጽንፈኛ ፕሮቴስታንቶችን አሰማርተው የቡታራ ኢስጢናፋኖስ ቤተ ክርስቲያንን ያስፈረሱና ኦርቶዶክሳውያንን ያስጨፈጨፉ የብልጽግና ወንጌል(የፕሮቴስታንት ) ባለሥልጣ+2
መዝግባችሁ ያዙ በሀዲያ  ዞን አመካ ወረዳ  ጽንፈኛ ፕሮቴስታንቶችን  አሰማርተው የቡታራ ኢስጢናፋኖስ ቤተ ክርስቲያንን ያስፈረሱና ኦርቶዶክሳውያንን ያስጨፈጨፉ የብልጽግና ወንጌል(የፕሮቴስታንት ) ባለሥልጣናት፦ ፩  አቶ ደገፈ ሞላንጎ (የአመካ ወረዳ አስተዳዳሪ) 2)ኢ/ር እሸቱ አዳነ አሼቦ( የአመካ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ) 3)፶ አለቃ ጡምሲዶ ሞላጎ(የወረዳው ሰላምና ጸጥታ ሀላፊ) የጊዜ ጉዳይ ነው ሁሉም የዘራውን ነው የሚያጭደው
257
10
没有文字...
267
11
ትርጓሜ ስትማሩ ይህ ያስጨንቃችኋልን? 99% የዓለም ሕዝብ ከድኅነት(ከመዳን) መስመር ውጭ ነው ( የኔታ መዝገበ ቃል በፈለገ አእምሮ ጉባኤ ቤት ካስተላለፉት) ከዓለም 8 ቢሊየን ገደማ ሕዝብ በእውነተኛዋ የመዳን ተስፋ ባላት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለው ስንት % ይመስላችኋል? 👉 በዓለም ከ 6ቱ አኃት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያን(ያውም ሐዋርያት ራሳቸው የሰበኳቸው ሀገራት ናቸው) ያላቸውን አማኝ ብናይ 👉 ኢትዮጵያ(40-45ሚሊየን) : 👉ግብጽ(10 ሚሊየን አካባቢ 11%): 👉 አርመን(6 ሚሊየን): 👉ኤርትራ(2.5-3 ሚሊየን) : 👉ሕንድ (2.4 ሚሊየን ኦርቶዶክስ- ከሶርያ የተገነጠለችው ቤ/ክን ነች): 👉 ሶሪያ ( 1.4 ሚሊየን ኦርቶዶክስ) በድምሩ 70-80 ሚሊየን ኦርቶዶክስ አለ ተብሎ ይገመታል። ይሄ ማለት ከ 8 ቢሊየን የዓለም ህዝብ 1% የማይሞላው ነው ማለት ነው የመዳን ተስፋ ባላት ቤተ ክርስቲያን ሥር ያለው። የሚያሳዝነው ይሄም በአማኝ ስም የተመዘገበ እንጂ የገነት የመንግሥተ ሰማያት መግቢያ ካርድ (ንስሐን) ያልያዘ ደግሞ በውስጡ አለበት ማለት ነው። ይሄ የእግዚአብሔር ቸርነትና የእኛ የድኅነት ተልዕኮ ውጤት ነው የሚሆነው። ሥለዚህ ይሄንን ስናስብ 99 % ያላነሰ ከእግዚአብሔር ያፈነገጠች ዓለምን ነው የያዝነው ማለት ነው። ይሄ እጅግ አያስጨንቅም? እናንተ የምትማሩት ታዲያ ይሄንን እያሰባችሁ ነውን? የዓለሙ መዳን ያሳስባችኋልን? ይሄ ይጨንቃችኋል ወይስ ነገ ተምራችሁ የምትቀጠሩበት ደብር ነው የሚያስጨንቃችሁ? ትልቅ ዕዳ ውስጥ እንዳለን ታስባላችሁን? .....ክፍል 2 ይቀጥላል። ለየኔታ ቃለ ሕይወት ያሰማልን::
274
12
✝† ስንክሳር ሐምሌ 20 †✝ እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ለታላቁ ሰማዕት ማር ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† 🌹† በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም †🌹 † ለስም አጠራሯ ክብር ይሁንና እመ ብርሃን ድንግል ማርያም በዚህች ቀን ወደ ቤተ መቅደስ ገብታለች:: በዓሉ ከሰላሳ ሦስቱ የእመቤታችን በዓላት እንደ አንዱ አይቆጠርም:: ምክንያቱም ቅዱሳን ሊቃውንት በዓታ ከበዓታ ጋር ይስማማል ብለው የታኅሣሥ ሦስትን በዓል ከሰላሳ ሦስቱ ደምረውታል:: እመቤታችን ወደ ቤተ መቅደስ የገባችው ሁለት ጊዜ ሲሆን:- 1.ዛሬ የምናከብረውና በተወለደች በሰማንያ ቀኗ የገባችበት ነው:: (ከግንቦት 1 ጀምረን እናስላው: 80 ቀን ይመጣል::) ኦሪት እንዳዘዘው ቅዱሳን ኢያቄምና ሐና ንጽሕት ሕፃን ድንግል ማርያምን ታቅፈው: የርግብ ልጆች (ግልገሎች): ዋኖስም ይዘው ወደ ቤተ መቅደስ ሒደዋል:: ካህናቱ ዘካርያስና ስምዖን ወጥተው በደስታ ተቀብለዋቸዋል:: እመቤታችን ለወላጆቿ ማኅጸን የከፈተች በኩር ናትና በእግዚአብሔር ፊት አቅርበዋታል:: 2.ከሦስት ዓመታት በኋላ እንደ ስዕለታቸው ወደ ቤተ መቅደስ ወስደው ለእግዚአብሔር ሰጥተዋት ተመልሰዋል:: እግዚአብሔር ዛሬ ያልቃል: ነገ ይደቃል የማይባለውን የድንግል እናቱን ፍቅር አብዝቶ ያድለን:: በረከቷም በእኛ ላይ ጸንቶ ይኑር:: 🌹† ቅዱስ ቴዎድሮስ ሰማዕት †🌹 † በቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት አለቅነት ከተሰጣቸው ሰማዕታት አንዱ የሆነው ማር ቴዎድሮስ የተወለደው በምድረ አንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: አባቱ ዮሐንስ በትውልድ ግብጻዊ የሆነ ክርስቲያን ነው:: እናቱ ግን አስቸጋሪና ጣዖት አምላኪ ሶርያዊት ነበረች:: ባልና ሚስት አብረው ሲኖሩ ሚስት ባሏ ክርስቲያን መሆኑን አታውቅም ነበር:: ቴዎድሮስ (የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው) በተወለደ ጊዜ ግን ጠብ ተነሳ:: እሱ ክርስትና ለማስነሳት: ሚስት ደግሞ ወደ ጣዖት ቤት ለመውሰድ ተጋጩ:: ሚስት ወገኖቿ ባለስልጣኖች ናቸውና ልጁን ቀምታ ባሏን ዮሐንስን ወደ ግብጽ አሳደደችው:: ዮሐንስ በስደት ባለበት ሃገር ስለ ልጁ ፈጽሞ ይጸልይ: ያለቅስም ገባ:: እግዚአብሔር ደግሞ ልመናውን ሰማ:: ማር ቴዎድሮስ ወጣት በሆነ ጊዜ ማንም ሳይጠራው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔዶ ተማረ: ተጠመቀ:: ዕለት ዕለትም ጾምና ጸሎትን ከምጽዋት ጋር ያበዛ: ድንግልናውን ለመጠበቅ ይተጋ ነበር:: በዛው ልክ ደግሞ ገና በሃያ ዓመቱ በጉልበቱ ኃያል: በውበቱም ደመ ግቡ: በጠባዩም ገራገር ነበርና ተወዳጅ ነበር:: ነገሥታቱም የአንጾኪያ የጦር ሠራዊት አለቃ አድርገው ሾሙት:: እነሆ እስከ ዛሬ "የሠራዊት አለቃ" ተብሎ ይጠራል:: ማር ቴዎድሮስ በተሳተፈባቸው ጦርነቶች ሁሉ ተሸንፎ አያውቅም:: ይልቁኑ የነገሥታቱን (የጠላት) ልጆች በመማረክ ነው የሚታወቀው:: እንዲያውም አንድ ጊዜ ከአሕዛብ ጋር በተደረገ ጦርነት ብቻውን አሸንፏቸዋል:: የፋርስ ሰዎች ሊዋጉ ሲመጡ መልአክ ከሰማይ ወርዶ ሰይፍ ሰጠው:: ፋርሶችን "በከንቱ ከምትጠፉ ወደ ሃገራችሁ ተመለሱ" አላቸው:: እነርሱ ግን ተሳለቁበት:: ከፈረሱ ወርዶ ወደ ምስራቅ ዙሮ ጸልዮ በመስቀል አማተበ:: በመካከላቸው ገብቶም በመልአኩ ሰይፍ ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር አጠፋቸው:: አንድ ቀን ወደ አንድ ከተማ ቢገባ ዘንዶ ሲመለክ አገኘ:: ይባስ ብሎ የአንዲት ክርስቲያን ልጆችን ለመስዋዕትነት ሲያቀርቧቸው ተመለከተ:: በስመ ሥላሴ አማትቦ: በፈረሱ ላይም ተቀምጦ ዘንዶውን በጦር ገደለው:: የዘንዶውም ርዝመት ሃያ አራት ክንድ ነበር:: ከነገር ሁሉ በኋላ ቅዱስ ቴዎድሮስ ስለ አባቱ ወሬ ሰምቶ: ካለበት ሥፍራ አፈላልጎ አግኝቶ ደስ አሰኘው:: እስኪያርፍ አብሮት ቆይቶ: ቀብሮት ወደ አንጾኪያ ሲመለስ ግን የሚያሳዝን ነገር ጠበቀው:: ክርስቶስ ተክዶ: ጣዖት ቁሞ: አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለው: የክርስቲያኖች ደም ፈሶ: ከተማዋ በግፍ ተሞልታ ተመለከተ:: እርሱም በዚያች ሰዓት መወሰን ነበረበትና አደረገው:: የሁሉ ሠራዊት አለቃ ቢሆንም የክብር ልብሱን አውልቆ: ባጭር ታጥቆ በንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ፊት ቆመ:: ††† ማር ቴዎድሮስ በአደባባይ እንዲህ ተናገረ:- "አንሰ አመልኮ ለክርስቶስ ንጉሠ ስብሐት በኩሉ ልብየ: ወእሠውዕ ሎቱ - እኔስ የክብር ባለቤት ክርስቶስን በፍጹም ልቤ አመልከዋለሁ: ለእርሱም ብቻ እሠዋለሁ::" ንጉሡ በቁጣ መሬት ላይ ጥለው እንዲደበድቡት አዘዘ:: ወታደሮቹ ደሙ እስኪንጠፈጠፍ ገረፉት:: በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃይተው በእሳት አቃጠሉት:: እርሱ ግን በጸሎቱ እሳቱን ውኃ አደረገው:: ወታደሮቹ እርሱን በብዙ አሰቃዩ:: እርሱ ግን በእግዚአብሔር ኃይል ጸና: ታገሠ:: በመጨረሻም ጌታችን በግርማ ወርዶ "ወዳጄ ቴዎድሮስ ስምህን የጠራ: መታሠቢያህን ያደረገ: ገድልህን (ዜናህን) የጻፈ: ያጻፈ: ያነበበ: ገዝቶ በቤቱ ውስጥ ያኖረውን ሁሉ እምርልሃለሁ" አለው:: በስሙም ረድኤት እንደሚደረግ ነግሮት ዐረገ:: ወታደሮቹም በዚህ ቀን አንገቱን ሰይፈው የክብር አክሊልን ተቀብሏል:: እጅግ ብዙ ሺህ ሰዎችም አብረውት ተሰይፈዋል:: => ቸሩ ፈጣሪ ከሰማዕቱ በረከት ይክፈለን:: † ሐምሌ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም (በሰማንያ ዕለት) 2.ቅዱስ ወክቡር ማር ቴዎድሮስ ሰማዕት (የሠራዊት አለቃ) 3.ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘእስክንድርያ 4.አራት መቶ አራት ሰማዕታት (የቅዱስ ቂርቆስ ማኅበር) 5.ቅድስት አውስያ (የማር ቴዎድሮስ እናት - በልጇ ምክንያት ያመነች እናት ናት) ††† ወርኀዊ በዓላት 1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር 2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ 3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮጵያ) 4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና 5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት ††† "እግዚአብሔር ለኛ የሰማዕትነትን ሥራ ይሰጠን ዘንድ ቅዱሳን ስለሚሆኑ ሰማዕታት እንማልዳለን::" ††† (ሥርዓተ ቅዳሴ ቁ. ፸፫) ††† "በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ ብጹዓን ናችሁ:: ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ:: አትናወጡም:: ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት:: በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ:: ነገር ግን በየውሃነትና በፍርሃት ይሁን::" ††† (፩ጴጥ. ፫፥፲፫-፲፮) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† ❖•°ೋ•❖ °   ❖•°ೋ•❖ ° 👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇 https://t.me/Sinksar https://t.me/Sinksar https://t.me/Sinksar
205
13
ለምን በድህነቴ ላይ ብሶት ትጨምርብኛለህ ወዳጄ? አሁን እንደውም የግብር ወቅት ነው። ከየት አምጥቼ ነው የምከፍለው፣ የቀጣይ ወር የቤት ኪራይ ከየት ነው የማመጣው? ብዬ እየተከዝኩ ገብርኤልን ላማክር ስመጣ በር ላይ የ 1.5 ሚሊየን ብር አበባ ሲገባ ምን እንደሚሰማኝ አታቅም? ድሃ ሆኜ አውደምኅረት ላይ ሰላም ለኪ እንዳልደግም የ 1.5 ሚሊየን ብር አበባ ከጎኔ አስቀምጠህ ለምን ታሳቅቀኛለህ? ቢያንስ አዳፋ ልብሴን እንደለበስኩ አምላኬን አመስግኜ እንዳልወጣ ድህነቴን remind እንዳደርገው ለምን ታደርጋለህ? እሱንማ ከቤተክርስቲያን ስወጣ አየው የለ? ቢያንስ እዚህ እንኳን እኩል እንደሆንን እንዲሰማኝ አታደርግም? ሁለት ዲናር አውጥታ ስትሰጥ ያየ፣ አይቶም "ይቺ መበለት ያላትን ሁሉ ሰጠች" ብሎ ያከበራት ምስካየ ኅዙናን፣ መልካም እረኛ የሆነው የገብርኤል አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ የሚደሰት ይመስልሃል? "ይሄ ነገር ተገቢ አይደለም ድሃ ይቅደም" ስትል ይሁዳ ነህ እንዴ? ይሉሃል። (ያው ይሁዳ መቅደላዊት ማርያም ያመጣችው ሽቶ ውድ ስለነበር "ተሽጦ ለምን ድሃ አይረዳበትም?") ስላለ ማለት ነው። ለዚህ ጥያቄ ግን ራሱ ዮሐንስ አፈወርቅ ይመልስልን። የሚገርመው ዮሐንስ አፈወርቅ በነበረበት ጊዜ ቤተክርስቲያን ላይ በተመሳሳይ እንደዚህ አይነት ችግር ተፈጥሮ ነበር። አንዳንዱ ባለጠጋ ዛሬ የ1.5 ሚሊየን ብር አበባ እንዳመጡት ቤተክርስቲያኒቱን በሐርና በውድ ልብስ ከልክ በላይ ያስጌጡ ነበር። ከንጹህ ወርቅ የተሰራ ጽዋና እርፈ መስቀል ያመጡ ነበር። ዮሐንስ አፈወርቅ ግን "ለቤተክርስቲያኒቷ ከወርቅም በላይ ይገባታል።" አላለም። እንደውም በተቃራኒው ከዚህ በኋላ እንዲህ እንዳያደርጉ ገስጿቸዋል። ምን አለ? "ክርስቶስ በረሃብ እየሞተ የቅዱስ ቁርባን ማዕድ በወርቅ ጽዋዎች የተሞላ ከሆነ ምን ጥቅም አለው? መጀመሪያ ረሃቡን አብልታችሁ አጥግቡት፣ ከዚያም በቀረው መሠዊያውን አስጊጡ።" አየህ መጀመሪያ የተራበውን አብላ። ድሃው የደረቀ አንጀቱን ይዞ መጥቶ አይመለስ። 19/11/2018 ✍️ አቤል አማረ
218
14
አሁን አሁን በተለይም እንጦጦ ኪዳነምኅረት መግቢያው ላይ ያለችው የእመብርሃን ስዕል ላይ እቅፍ አበባ ማስቀመጥ የተለመደ ሆኗል። ዛሬ ደግሞ ብስራተ ገብርኤል አበባ በመኪና ጭነው ሲያስገቡ አየሁ። በካ
አሁን አሁን በተለይም እንጦጦ ኪዳነምኅረት መግቢያው ላይ ያለችው የእመብርሃን ስዕል ላይ እቅፍ አበባ ማስቀመጥ የተለመደ ሆኗል። ዛሬ ደግሞ ብስራተ ገብርኤል አበባ በመኪና ጭነው ሲያስገቡ አየሁ። በካፌና በሬስቶራንቱ፣ በሚነዳው መኪና፣ በሚያዘው ስልክ፣ even በሚፖሰተው ፖስት የተፈጠረው የclass ልዩነት አልበቃ ብሎ ጭራሽ ቤተክርስቲያን ይዘኸው መጣህ? ሳይታወቅህ ቤተክርስቲያን ውስጥ ድሃና ሃብታም የሚል class እየፈጠርክ ነው።
198
15
https://youtu.be/F2T4Pll3hl4?si=qG3zq3woQkER7awe
206
16
🟢† ስንክሳር ሐምሌ 19 † እንኳን ለቅዱሳኑ ገብርኤል ሊቀ መላእክት: ቂርቆስ ወኢየሉጣ: በጥላን ጠቢብ እና ሰማዕታተ እስና ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † †††✝ ቅዱሳን ቂርቆስ ወኢየሉጣ: ወቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት †††✝ † ቅድስት ኢየሉጣ እናታችን በዘመነ ሰማዕታት ከነበሩና በዚህ ስም ከሚጠሩ ቅዱሳት አንዷ ናት:: በወቅቱ ቅዱስ ቂርቆስ የሚባል ደግ ልጅ ወልዳ ባሏ ባለመኖሩ በመበለትነት ትኖር ነበር:: የዚያ ዘመን ክርስቲያኖች ለክርስቶስ የነበራቸው ፍቅር ከመነገር በላይ ነው:: በዛው ልክ ደግሞ መከራው በጸጉራቸው ቁጥር ልክ ነበር:: ከሮም ግዛት በአንዱ ከቅዱስ ልጇ ጋር የምትኖረው ቅድስት ኢየሉጣ የስደቱ ዘመን ሲመጣ እርሷም እንደ ሌሎቹ ክርስቲያኖች ተሰደደች:: እስክንድሮስ የተባለው ከሃዲ ንጉሥ ግን ያለችበት ድረስ ተከትሎ እንድትያዝና እንድትቀርብ አደረገ:: ወዲያውም "ስምሽ ማን ይባላል?" ቢላት "ክርስቲያን እባላለሁ" አለችው:: ንጉሡ ተቆጣ:: "መዋቲ ስሜን ከፈለክ ኢየሉጣ ይባላል" አለችው:: ንጉሡ መልሶ "አሁን ለጣዖት ካልሠዋሽ ሲጀመር ስቃይ: ቀጥሎም ሞት ይጠብቅሻል" ቢላት ቅድስቲቱ መልሳ "በከተማ ውስጥ የሦስት ዓመት ሕፃን አለና እርሱን አምጣው:: ማንን ማምለክ እንዳለብን ይነግረናል" አለችው:: አስፈልጐ ቅዱስ ቂርቆስን አስመጣው:: "ስምህ ማን ይባላል?" አለ ንጉሡ:: "ከማይደፈርስ ከንጹሕ ምንጭ የተቀዳ ጥሩ ምንጭ ስሜ ክርስቲያን ይባላል:: መዋቲ ስሜን ከፈለግህ ግን ቂርቆስ ይባላል" አለው:: ንጉሡ ሊያታልለው "ደስ የተሰኘህ ሕፃን" ቢለው ቅዱሱ ሕፃን "ትክክል ተናገርክ: ለእኔ በሰማያት ደስታ ይጠብቀኛል:: አንተ ግን እውነተኛው አምላክ ይፈርድብሃል" አለው:: በሦስት ዓመት ሕፃን አንደበት ዘለፋ የገጠመው ከሃዲ ተቆጣ:: እናትና ልጅን በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃያቸው:: ሰውነታቸውን ቸነከረ: አካላቸውን ቆራረጠ: ዓይናቸውን አወጣ:: ሌላም ሊናገሩት የሚጨንቅ ስቃይን አሰቃያቸው:: በዚህች ቀን ግን ትልቅ ድስት አሰርቶ ባሩድ: አረር: ስብና የመሳሰሉትን ጨምረውበት በእሳት አፈሉት:: የእሳቱ ወላፈን አካባቢውን በላው:: በድስቱ ውስጥ ያለው ነገር እየፈላ ሲገላበጥ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ይጮህ ነበር:: የስድስት ሰዓት የእግር መንገድ ድረስም ተሰምቷል:: ቅድስት ኢየሉጣ ይሔኔ ነበር ልቧ ድንግጥ ያለው:: ሕፃኑ ቂርቆስ የእናቱን ፍርሃት ሲመለከት ጸለየ:: "ፈጣሪዬ! ፍሬው ያለ ግንዱ አይቆምምና እኔን እንዳጸናሕ እናቴንም አጽናት" ሲል ለመነ:: "እግዚኦ ትፈቅድኑ ለፍሬሁ ተአልዶ: እንዘ በእሳት ታውኢ ጉንዶ" እንዲል:: በዚያች ሰዓት ቅድስት ኢየሉጣ ዓይኖቿ ተከፍተው ሰማያዊ ክብርን ተመለከቱና ልቧ ወደ ድፍረቱ ተመለሰ:: ልጇንም "አንተ አባቴ ነህ: አንተን የተሸከመች ማኅጸኔ የተባረከች ናት" አለችው:: ከዚያም ሁለቱንም ወደ ፈላው ድስት ውስጥ ቢጨምሯቸው ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደላቸው:: በበትረ መስቀሉ ባርኮ የፈላውን አቀዘቀዘው:: የነደደውን ውኃ አደረገው:: ቅዱሳኑ ቂርቆስና ኢየሉጣ ከብዙ መከራ በኋላ በሰማዕትነት አልፈዋል:: ††† ቅዱስ በጥላን ጠቢብ ††† ††† ቅዱሱ ከአሕዛብ ወላጆቹ ተወልዶ: ያደገውም በጣዖት አምልኮ ነው:: በሙያው እጅግ የተመሠከረለት ሐኪም ነበር:: የሃገሩ ሰዎች "ጠቢብ" እያሉም ይጠሩታል:: በጥላን ምንም ጣዖት አምላኪ ቢሆን በተፈጥሮው ተመራማሪና ቅን ነበር:: አንድ ካህንም በጐረቤቱ ነበርና ዘወትር ስለ ሃይማኖት ይከራከሩ ነበር:: ካህኑ ሌሊት ሌሊት ስለ በጥላን ተግቶ ይጸልይ ነበርና ተሳክቶለት አሳመነው:: አንድ ቀን በጥላን መንገድ ሲሔድ እባብ ሰው ነድፎ ለሞት ደርሶ አየውና ጸሎት አድርሶ ስመ ክርስቶስን ቢጠራ የተነደፈው ድኖ እባቡ ሞተ:: በዚህ ተዓምር ደስ ብሎት ወደ ካህኑ ሒዶ ተጠመቀ:: ከዚያም ጾም ጸሎትን ጀመረ:: በየቦታው እየዞረ ሕሙማንን እንደ ቀድሞው በመድኃኒት ሳይሆን በጸሎት ያድናቸው ነበር:: ስላዳናቸውም በርካቶቹ ወደ ክርስትና መጡ:: የአካባቢው ሰው: ወላጆቹን ጨምሮ ክርስቲያኖች ሆኑ:: በመጨረሻም ቅዱስ በጥላን: ቤተሰቦቹ: ካህኑና ከደዌ የዳኑት ወገኖቹ በአካባቢው ጣዖት አምላኪ ንጉሥ ፊት ቀርበው ክርስቶስን ሰብከው በሰማዕትነት ዐርፈዋል:: ††† ቅዱሳን ሰማዕታተ እስና ††† ††† እስና ማለት ግብጽ ውስጥ የምትገኝ የቀድሞ አውራጃ ናት:: በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በከተማዋ በርካታ ክርስቲያኖች ይኖሩ ነበር:: የእንዴናው መኮንን መጥቶ "ክርስቶስን ካዱ: ለጣዖት ስገዱ" አላቸው:: ሕዝቡ በአንድ ድምጽ መለሱ:- "ይሕማ ፈጽሞ ሊደረግ አይችልም::" መኮንኑ ተቆጥቶ "ሁሉንም ግደሉ" አለ:: ወታደሮቹ ሰው አልመረጡም:: ከታዘለ ሕፃን አልጋ ላይ እስካለ ሽማግሌ: ከጤነኛ እስከ ሕመምተኛ: ሁሉንም ጨፈጨፏቸው:: ከተማዋ በደም ተነከረች:: ከከተማዋ ክርስቲያኖች ወሬ ለመንገር አንድ ሰው እንኳ አልተረፈም:: ሁሉም ስለ ክርስትና ደማቸውን አፈሰሱ:: ††† ጌታችን ስለ ሰማዕታቱ ብሎ: ደማቸውንም አስቦ በሃይማኖታችን ያጽናን:: ከመከራም ይሰውረን:: በረከታቸውንም ያድለን:: ††† ሐምሌ 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት 2.ቅዱስ ቂርቆስ ወእሙ ኢየሉጣ 3.ቅዱስ በጥላን ጠቢብ ሰማዕት እና ማኅበሩ 4.ቅዱሳን ሰማዕታተ እስና ††† ወርኀዊ በዓላት 1.ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት 2.አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ 3.አቡነ ስነ ኢየሱስ 4.አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም ††† "ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ: ወይስ ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ መራቆት: ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን? 'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች ተቆጠርን::' ተብሎ እንደተጻፈው ነው:: በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::" ††† (ሮሜ. ፰፥፴፭-፴፯) † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † ❖•°ೋ•❖ °   ❖•°ೋ•❖ ° 👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇 https://t.me/Sinksar https://t.me/Sinksar https://t.me/Sinksar
288
17
没有文字...
250
18
没有文字...
217
19
没有文字...
184
20
没有文字...
191