ru
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Открыть в Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Больше
2 291
Подписчики
Нет данных24 часа
+27 дней
+3230 день
Архив постов
🙏🙏 የሰማዕቱ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ ቅድስት እየሉጣ ረድኤት በረከት ቃልኪዳን ይደርብን በእውነት። እንዲሁም በዚህ ቀን ወር በገባ በ15 የሚታሰበው ተወዳጁና ፈጥኖ ደራሹ ሰማዕት ማር ቅዱስ ሚናስ
+1
🙏🙏 የሰማዕቱ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ ቅድስት እየሉጣ ረድኤት በረከት ቃልኪዳን ይደርብን በእውነት። እንዲሁም በዚህ ቀን ወር በገባ በ15 የሚታሰበው ተወዳጁና ፈጥኖ ደራሹ ሰማዕት ማር ቅዱስ ሚናስ ወርሐዊ መታሰቢያ በዓሉ ነው። የቅዱሱ ረድኤት በረከት በሁላችን ላይ ይደር። መልካም ቀን ለሁላችን ይሁን! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

=> ምዕመናኑን ስለ ክፉ መናፍስት ውጊያ ያሳወቁ፣ ከ 40 ዓመታት በላይ በፈተና በታጀበ አገልግሎት የዘለቁ፣ ስድብን እንደምርቃት እየቆጠሩ፣ ትውልድን የአምልኮት ሕይወት ያስተማሩ፣ አገልግሎትን ካለመ
=> ምዕመናኑን ስለ ክፉ መናፍስት ውጊያ ያሳወቁ፣ ከ 40 ዓመታት በላይ በፈተና በታጀበ አገልግሎት የዘለቁ፣ ስድብን እንደምርቃት እየቆጠሩ፣ ትውልድን የአምልኮት ሕይወት ያስተማሩ፣ አገልግሎትን ካለመታከት፣ ተግባራዊ ክርስትናን ከጸሎት ጋር አስተባብረው የያዙት ክቡር አባታችን መላከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ! የማገለግላት ወለላይቱ እመቤት ዕድሜ ከጤና ጋር ትስጣቸው። በአንድ ወቅት ቀሲስ ሄኖክ አባታችን ያስተላለፉት መልዕክት ነው። አባቶቻችን ክበሩልን! ሕይወታችን ብዙ ነገር እንድናውቅ፣ እንድንማር፣ ጠላታችንን እንድንዋጋ፣ ከባዕድ አምልኮ እንድንርቅ ከሁሉም በላይ በተግባራዊ ክርስትና መኖርን ስላስተማራችሁን የምታገለግሉት አባት ቅዱስ እግዚአብሔር ረጅም ዕድሜ ይስጣችሁ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

photo content

"ንስሐ መግባት የመረረው መነኩሴ!" => ተወዳጆች ሆይ በመጽሐፈ ፊሊክስዮስ በገጽ 178 ላይ ያለውን ታሪክ እንይ፡፡ አንድ መነኩሴ አባ ቢሶይን ‹‹አባቴ በኃጢአት ተነሰካከያለሁና ምን ላድርግ›› አላቸው፡፡ አባ ሲሶይም ‹‹ንስሐ ግባ›› አለው፡፡ መነኩሴውም ‹‹ብዙ ግዜ እየተሰነካከልኩ በንስሐ ስመላለስ ኖርኩ እስከ መቼ ስወድቅ ስነሳ እኖራለሁ?›› አላቸው፡፡ አባ ቢሶይም ‹‹እስክትሞት ድረስ፡፡ አንድም ሞትህን በንስሐ፣ ኃጢአትህን በንስሐ፣ ወይም በሞት እስክትቀደም ድረስ›› አሉት፡፡ => ወዳጆቼ ደግ ሰው ከበጎ ሥረው በሚመለስበት፣ ኃጢአቱ በሚሰረየይበት ቀን ቢሞት የቀድሞ ኃጢአቱ አይታሰብበትም ኋላ በሠራው ኃጢአት ይሞታል እንጂ፡፡ ኃጥእ ከኃጢአቱ ተመልሶ በጎ ሥራ ቢሠራ የቀድሞ ኃጢአቱ አይታሰብበትም፡፡ ጻድቅም ኃጢአት ቢሠራ በቀደመው በጎ ሥራው አይድንም በመጨረሻ በሠራው ኃጢአት ይኮነናል፡፡ ምክንያቱም ሰው በጊዜው ግብሩ ነው የሚሄደውና፡፡ ስለዚህ በኃጢአት ስንወድቅ በቶሎ ንስሐ ልንገባ ይገባል፡፡ => አንዳንድ ሰነፎች ቀድሞ የጽድቅ ሥራ ሲሠሩ ይኖሩና በኋላ በኃጢአት ይወድቃሉ፡፡ ንስሐ ግቡ ሲባሉ ልባቸውን የሚያደነድኑት የቀድሞ በጎ ሥራቸውን በማሰብ በዛ ሥራ የሚድኑ፣ ከፈጣሪም ሰማያዊ ዋጋ የሚቀበሉ ይመስላቸዋል፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ በሕይወታችን መጨረሻ የምንሠራው ሥራ ለገነቱም ለሲዖሉም ሕይወት ይወስናሉ፡፡ ለዚህም ነው አባቶች ‹‹ፍጻሜዬን ያሳምርልኝ›› የሚሉት፡፡ => የመንፈሳዊ ሕይወታችን የጽድቅና የኃጢአት ፍጻሜ ነው ለሰማያዊ ሽልማት እና ቅጣት የሚዳርገን፡፡ ለዚህም ነው እግዚአብሔር ለነብዩ ሕዝቅኤል ለሰው ልጅ ንገርልኝ ብሎ ‹‹በበደለበት ቀን የጻድቅ ጽድቁ አያድነውም፣ ኃጢአተኛም ከኃጢአቱ በተመለሰበት ቀን በኃጢአቱ አይሰናከልም፤ ጻድቁም ኃጢአት በሠራበት ቀን በጽድቁ በሕይወት አይኖርም፡፡ => እኔ ጻድቁን በእርግጥ በሕይወት ትኖራለህ ባልሁ ጊዜ፣ እርሱ በጽድቁ ታምኖ ኃጢአት ቢሠራ በሠራው ኃጢአት ይሞታል እንጂ ጽድቁ አይታሰብለትም፡፡ እኔም ኃጢአተኛውን በእርግጥ ትሞታለህ ባልሁ ጊዜ፣ እርሱ ከኃጢአት ተመልሶ ፍርድንና ቅን ንገርን ቢያደርግ፣ ኃጢአተኛው መያዣን ቢመልስ የነጠቀውንም ቢመልስ በሕይወት ትእዛዝ ቢሄድ ኃጢአትም ባይሠራ፣ በሕይወት ይኖራል እንጂ አይሞትም፡፡ የሠራው ኃጢአት ሁሉ አይታሰብበትም፤ ፍርድንና ቅን ነገርን አድርጎአል፤ በእርግጥ በሕይወት ይኖራል›› በማለት ዘርዝሮ ቋጥሮ አስቀምጦልናል፡፡ /ት.ሕዝቅ 33÷12-16/ => የወለላይቱ እመቤት ልጆች ያለማነውና ያጠፋነው ነገር በእግዚአብሔር ዘንድ ይመዘናል፡፡ ሰው ከዚህ ዓለም በሚለይበት ጊዜ በፈጣሪው ፊት የሠራው ጽድቅ እና ኃጢአት ይመዘናል፡፡ ያለማነው ካጠፋነው ጋር ይመዘናል፡፡ ያለማነው በልጦ ቢገኝ ይፈረድልናል፡፡ ያጠፋነው በልጦ ቢገኝ ይፈረድብናል፡፡ ወዳጆቼ በፍቃደ ሥጋ ተስበን የሠራነውን ኃጢአት ንስሐ ልንገባበት ይገባል፡፡ በኋላ በሚያስፈራው ዙፋን ፊት የኃጢአታችን ሒሳብ ሲወራረድ፣ ለሲኦል እሳት እንዳንማገድ በንስሐ መንገድ እንጓዝ ጽድቁንም እንያዝ፡፡ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ከመምህር ተስፋዬ አበራ ለባለትዳሮች የተላለፈ መልዕክት || በደላችን በዝቶ ጸሎትና ስግደቱን ረሳነው || የችኮላ አምልኮና አገልግሎት መዘዙ || መምህር ግርማ => https://youtu.be/qHqHFzz95Dw

"ጻድቁ አባታን አቡነ አረጋዊ" => በቀደመ ስማቸው ዘሚካኤል ሲባሉ ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው። የንጉስ ልጅ ሆነው ሳለ የዓለምን ነገር ስለናቁ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ በመሄድ በአስራ አራቱ
"ጻድቁ አባታን አቡነ አረጋዊ" => በቀደመ ስማቸው ዘሚካኤል ሲባሉ ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው። የንጉስ ልጅ ሆነው ሳለ የዓለምን ነገር ስለናቁ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ በመሄድ በአስራ አራቱ ዓመታቸው ስርዓት ምንኩስናን ተቀብለዋል። እናታቸውም ንግስት እድና የምናኔው ሕይወት ስለሳባት ወደ ገዳሙ በመምጣት እንደ ልጇ መንኩሳለች። ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ በመጻሕፍት ስላነበቡ እንዲሁም ለእመቤታችን ድንግል ማርያም የአስራት ሀገር ሆና መሰጠቷን ከተረዱ በኋላ ይህችን ቅድስት ሀገር ለመጎብኘ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ጎብኝተው ወደ ሮም ተመለሰዋል። => ከዚያም ተመለሰው ለስምንት ባልንጀሮቻቸው ሃገርስ ባሳየኋችሁ ሐዋርያ ሳያስተምራት በህጉ በስርዓቱ ጸንታ የምትኖር ብለው ከስምንቱ ጋር ከኬልቄዶን ጉባኤ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል። አባታችን አቡነ አረጋዊ በዓት ፍለጋ ለብዙ ጊዜ ደክመዋል ኋላም በእግዚአብሔር ፍቃድ ደብረ ዳሞ በሚባለው ቦታ ደርሰዋል፤ በተራራውም ጫፍ ብርሃን ቢታያቸውም ተራራማ ስለነበር መውጫው ቢቸግራቸው የታዘዘላቸው ዘንዶ ተራራው ጫፍ አውጥቷቸዋል። => ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታችን በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾላቸው ምድራዊ መንግስትን ትተህ ስላገለገልኝ ህልፈት ሽረት የሌለባትን ሰማያዊ መንግስቴን አወርስሀለው ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል። በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሀለው አንተም ከሞት ኃይል ትሰወረላህ ብሏቸዋል። እነደ ተነገራቸውም አንደ ሄኖክና ኤልያስ ሞትን ሳያዩ ተሰውረዋል። 🙏 የጻድቁ አባታን አቡነ አረጋዊ ረድኤት በረከት አይለየን 🙏 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

መተት የሚባል ነገር የለም!! አጋንንትን ተቃወሙ ማለት ምንድነው ክፋቱ! አመጽና ኃጢአት ዲሞክራሲ ሆኗል! ቀልድና ፈዝ የበዛበት ቤት ውስጥ የአጋንንት ሴራ 😱😱 https://youtu.be/14BE_kOjRk4

=> ጌታዬ ሆይ የእኔ የልጅህን መከራ አርቅልኝ ታናሽነቴን አይተህ ያልናቅከኝ፣ በመስቀል ፍቅር የማረከኝ ሳይገባኝ ያከበርከኝ፣ በየዕለቱ በደሌን ይቅር እያልከኝ አዲስ ሰዉ የምታደርገኝ መዓትህ የራቀ
=> ጌታዬ ሆይ የእኔ የልጅህን መከራ አርቅልኝ ታናሽነቴን አይተህ ያልናቅከኝ፣ በመስቀል ፍቅር የማረከኝ ሳይገባኝ ያከበርከኝ፣ በየዕለቱ በደሌን ይቅር እያልከኝ አዲስ ሰዉ የምታደርገኝ መዓትህ የራቀ ምህረትህም የበዛ እዉነተኛ ጠባቂዬ የዘዉትር ፀሎቴን ልመናን ያልናቅህ የሚያስፈልገኝን በአንተ ፈቃድና በጊዜዉ ያደረክልኝ እጅ መንሳቴን በፍፁም ትህትና አቀርባለሁ። => የቸርነት አባት ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኔ ባሪያህ ስለሕይወቴ የሚያስፈልገኝን እንደምትሰጠኝ አምኜ ባመንኩበት እምነት እንደጐበኘኸኝ ሁሉ በዚህ ወቅት ክብርት ህግህንና ትዕዛዝህን አንተንም መፍራትን ጽድቅህን ማወጅን ሥርዓትህንም ማክበርን በልቦናዬ ሰሌዳ ጻፍ። የተማረኩትን የወንጌል ቃል ኃይሉን በሚገባ አዉቅ ዘንድ በአዲስ ተፈጥሮ ኃጢአትን ድል በመንሳት እንድኖር አድርገኝ። በመንፈሳዊ ደስታ ሁሌ አስጊጠኝ። የጣዖት ማምለክ ቅሬታን እርሱም ዝሙትን፣ ስካርን፣ ዘረኝነትንና፣ ገንዘብንም ወዳድነት ከልቦናዬ አርቅልኝ። ጌታዬ እየሱስ ክርስቶስ ሆይ ያለፍቃድህ በፍቃዴ የሠራሁትንም ኃጢአት ለዘለዓለሙ ደምስስልኝ። ሁልጊዜ በምስጋና መቅደስህ ተገኝቼ የመላዕክትን ዝማሬ አጥንትንም የሚያለመልመዉን የሕጻናትን ድምፅ እንድሰማና እንዳሰማ አድርገኝ። => ጌታ ሆይ በደምህ የተመሰረተችዉን ያንተ የምትሆነዉን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ደህንነት አስብ። ሃይማኖታቸዉ የቀና የቅዱሳን አባቶቻችንን ፈለግ ተከትለዉ በቤትህ ላሉት ሁሉ መባረክን ስጣቸዉ። አቤቱ የሀገራችንን ሁለንተናዋን ጠብቅ። የሰዉንና የእንስሳዉን ደህንነት አስብ ኃጥዕ የምሆን እኔንም ባርያህን ጠብቀኝ፣ አድነኝም ለዘለዓለሙ አሜን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የዝሙት መናፍስት ለእኛ የሚያዋርሷቸው ጠባያት || የትዳር አጋርን መሸሽና መጥላት || ሩካቤ ሥጋን የሚያስጠሉ መናፍስቶች #ethiopia #ebstv 🔥💥🚩😱 https://youtu.be/KaQrAZYtWeA

🙏 የቅዱስ ሩፋኤል ቃልኪዳኑ ረድኤት በረከቱ በእኛ በክርስትያን ልጆች ላይ ይደር። እንኳን ለሊቀ መልአኩ ለቅዱስ ሩፋኤል ወርሃዊ መታሰቢያ በሰለም አደረሰን አደረሳችሁ። 🙏🙏🙏
🙏 የቅዱስ ሩፋኤል ቃልኪዳኑ ረድኤት በረከቱ በእኛ በክርስትያን ልጆች ላይ ይደር። እንኳን ለሊቀ መልአኩ ለቅዱስ ሩፋኤል ወርሃዊ መታሰቢያ በሰለም አደረሰን አደረሳችሁ። 🙏🙏🙏

🙏 እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ። የቅዱስ ሚካኤል ረድኤት በረከት ይደርብን በእውነት። 🙏🙏🔥
🙏 እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ። የቅዱስ ሚካኤል ረድኤት በረከት ይደርብን በእውነት። 🙏🙏🔥

ዛር ካለባቸው ወላጆች የተወለዱ ልጆች ጠባያቸው የአፍዝ አደንግዝ መናፍስቶች ሴራ ብቸኝነትን የሚያለማሚዱ አጋንንቶች #ethiopia #ebstv 😱🔥 https://youtu.be/KNplyzGEocc?si=XPoNRaoK0Ptvh-ki

ታላቁ ጸሎት! ለሞት የቀረበ ሰው ጸሎት የመናኙ ጳጳስ ቅዱስ ኒፎን ጸሎት የቃልኪዳን ጸሎት #ethiopia #orthodox #ebstv 🔥🔥💥😱 https://youtu.be/j-MKG6gIV34

ከዲያብሎስ ጋር የተደረገ ክርክር በማለዳ ንቁ 2024 የአጋንንት ምስክርነት መናኙ ቅዱስ ኒፎን #ethiopia #ebstv #orthodox 🔥 https://youtu.be/t5tEY39iqRU?si=SuHTeFSt8-UKTTun

=> "ሰይጣን ክርስቶስ በልብህ መሆን አለመሆኑን ያውቃል። ስትቆጣ፣ ስትጮህ የማይረባ ነገር ስትናገር ሲያይህ፤ በአንተ ዘንድ እግዚአብሔር እንደሌለ ያውቃል። ያን ጊዜ ወደ ልብህ ገብቶ ውስጥህን ይቦረ
=> "ሰይጣን ክርስቶስ በልብህ መሆን አለመሆኑን ያውቃል። ስትቆጣ፣ ስትጮህ የማይረባ ነገር ስትናገር ሲያይህ፤ በአንተ ዘንድ እግዚአብሔር እንደሌለ ያውቃል። ያን ጊዜ ወደ ልብህ ገብቶ ውስጥህን ይቦረብረዋል። ስለዚህ እንጠንቀቅ!።" (ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

=> "ሁልጊዜ ሰይጣን ልብስ ለመግፈፍ ቆሟል፤ ሰንራቆት ሽፋን ሊያደርገን እግዚአብሔር ደግሞ ነጭ ሸማ ይዞ ቆሟል! አይቶ የማያሳይብን፣ ሰምቶ የማያሰማብን እንደዚህ ያለ ሸፋኝ አምላክ ነው ያለን። ስሙ
=> "ሁልጊዜ ሰይጣን ልብስ ለመግፈፍ ቆሟል፤ ሰንራቆት ሽፋን ሊያደርገን እግዚአብሔር ደግሞ ነጭ ሸማ ይዞ ቆሟል! አይቶ የማያሳይብን፣ ሰምቶ የማያሰማብን እንደዚህ ያለ ሸፋኝ አምላክ ነው ያለን። ስሙ የተመሰገነ ይሁን በእውነት።" #ሸር_ሸር ይደረግ! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ጸበል ስጠመቅ ያመኛል፣ ይጨንቀኛል፣ እረበሻለሁ!! መስገድ ስጀምር የሚሞት ይመስለኛል! ጉባኤያችን CEREMONY ሆኗል! || የልጆች አስተዳደግ 💥🔥😭 https://youtu.be/t46C1aK1OBw

"ዘግናኝ በሆንኩት በእኔ ላይ እንደምሕረትህ አንዲት ጸጋን አፍስብኝ፤ እንዲረዳና እንድለወጥ ቢያንስ ራሴን ለማስተካከል ጥቂት ጥረት እንዳደርግ ያንተ ጸጋ በነፍሴ ላይ ካላበራ፤ በስንፍናዬና በንዝኀላል
"ዘግናኝ በሆንኩት በእኔ ላይ እንደምሕረትህ አንዲት ጸጋን አፍስብኝ፤ እንዲረዳና እንድለወጥ ቢያንስ ራሴን ለማስተካከል ጥቂት ጥረት እንዳደርግ ያንተ ጸጋ በነፍሴ ላይ ካላበራ፤ በስንፍናዬና በንዝኀላልነቴ በክፉ ፍላጎቴ የበቀለብኝን ግድየለሽነቴንና ቸልተኝነቴን ማየት አልችልም።" (ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

የደብተራውን ጉድ ተመልከቱ! | የአረብ ሀገር መተትና ጥፋቱ || ትዳሯን በጠበጥን ዕድሏን ወሰድን || መንገድ ላይ መተት የቀበረው ሟርተኛ #ethiopia 😱😭 https://youtu.be/VBmZbuIWs68

=> የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች የቅዱሳን ወዳጆች የዚህ ዓመት ዘመነ ማቴዎስ 2017 የመጀመሪያ የፍኖተ ሕይወት ጉባኤ በ44ቱ ጸበል ቅድስት ሥላሴ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የሚጀምረው
=> የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች የቅዱሳን ወዳጆች የዚህ ዓመት ዘመነ ማቴዎስ 2017 የመጀመሪያ የፍኖተ ሕይወት ጉባኤ በ44ቱ ጸበል ቅድስት ሥላሴ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የሚጀምረው የፊታችን መስከረም 12 እሁድ መሆኑን እንገልጻለን። በቅዳሴ፣ በጸሎት፣ በጸበል፣ በቅብዐ ቅዱስ፣ በወንጌል አገልግሎታችን በሰፊው ይካሄዳል። ከሩቅ ቦታ ለሚመጡ ማረፊያ አዳራሽ ተዘጋጅቷል። => አድራሻ፦ከጎተራ ወደ ወሎ ሰፈር መሄጃ ወንጌላዊት ሕንጻ ጀርባ ወይንም ዘንባባ ሆስፒታል ጀርባ 44ቱ ጸበል ፈለገ ዮርዳኖስ ቅድስት ሥላሴ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን። የቤተክርስቲያኑ አድራሻ Google map https://maps.app.goo.gl/Bgfd3G8QiRErw8k86 የቴሌግራም ቻናል https://t.me/kesishenoktefera የዩቲዩብ ቻናል https://youtube.com/@kesishenoktefera835?feature=shared “እናንተም የሀገሩ ሕዝብ ሆይ በርቱና ሥሩ ይላል እግዚአብሔር እኔ ከእናንተ ጋር ነኝና ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።” ሐጌ 2፥4። መልእክቱን ለሌሎች ወገኖቻችሁ ሁሉ (share) በማድረግ ያስተላልፉ። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን። ©መልአከ ሕይወት ቀሲስ ሄኖክ ተፈራ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239