ru
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Открыть в Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Больше
2 277
Подписчики
+224 часа
+97 дней
+3830 день
Архив постов
ሰይጣንን አስርቡት || አእምሮ የሰይጣን የጦር ሜዳ | ትልልቅ ህልሞች ትናንሽ ሰዎች | ተንኮለኛው ጠላታችን እባብን ላስተዋውቃችሁ | አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ 😱💥 https://youtu.be/3tmLWLp-U3M

ጸሎትና ስግደትን ስናቆም የሚከተለው ሆነብን በውሻና በእንስሳት የሚደግሙ ደብተራዎች የጳጉሜ ሦስት በረከቶች || መምህር ተስፋዬ አበራ 2024 🚩🔥😱💥 https://youtu.be/aytoF4XwFRU?si=Wsn0sQe45t-6lhib

=> ሰላም ለከ ሩፋኤል ዐቃቤ ኆኀቱ ለአምላክ፣ ሰላም ለከ መገሥፀ ዐንበሪ ድሩክ፣ ሰላም ለከ ምዑዝ ቅዳሴ ሰሊክ፣ ሰላም ለከ አምላከ አማልክት ዘትባርክ፣ ሰላም ለከ እምሁከተ ልሳን መሪር ወእመልዐክ
=> ሰላም ለከ ሩፋኤል ዐቃቤ ኆኀቱ ለአምላክ፣ ሰላም ለከ መገሥፀ ዐንበሪ ድሩክ፣ ሰላም ለከ ምዑዝ ቅዳሴ ሰሊክ፣ ሰላም ለከ አምላከ አማልክት ዘትባርክ፣ ሰላም ለከ እምሁከተ ልሳን መሪር ወእመልዐክ ሞት ድሩክ፤ ሰላም ለከ ሩፋኤል ዕቀበኒ ወአድኀነኒ በጽባሕ ወሠርክ ሊተ ለሀይለ ገብርኤል፣ ለሕሩተ ሥላሴ፣ ለሀብተ ማሪያም፣ ለወለተ ሥላሴ ...... እንኳን አደረሳችሁ። ሁላችሁም "ቅዱስ ሩፋኤል ወደ እኔ ና ና" እያላችሁ በኮሜን ላይ ጻፉ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

photo content

photo content
+1

=> ልናመሰግነው ይገባል!!! "በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ።" መዝ. ፷፭፥፲፩ /65፥11/ => እንደ ኃጢአታችን ብዛት ሳይሆን እንደ ቸርነቱ አንዱን ዓመት አሳልፎ ለሌላው ሊያበቃን በዋዜማው ላይ እንገኛለን፤ በደላችኝኝ እያየ ኑ ልጆቼ ወደ አባታችሁ ቤት ኑ እያለ ዘወትር ድምፁን ከፍ አድርጎ ይጠራናል። => እኛ ደካሞች፣ ምናምንቴዎች ሳለን በሞቱ በደላችንን ፍቆ ለዚህ ጊዜ አደረሰን፤ በማይመረመር ጥበብ፣ ዓለም ባልገባው ግን እፁብ ድንቅ በሆነ ተዓምር የኛን ስጋ ለበሰ፣ ከድንግል ማርያም ተወለደ፤ ይኽም በፍቅር እንጂ ከቶ በምን ይገለጣል። => "ጕልበቴ ዝማሬዬም እግዚአብሔር ነው፥ መድኃኒቴም ሆነልኝ፤ ይህ አምላኬ ነው አመሰግነውማለሁ፥ የአባቴ አምላክ ነው ከፍ ከፍም አደርገዋለሁ።" ዘጸ. ፲፭፥፪ /15፥2/ => ታዲያ እኛ ግን ከምስጋና ይልቅ ከንፈሮቻችን ለትችት ለነቀፋ በረቱ፤ ምላሳችን ለክፉ ንግግር ከትናጋችን ተጋጨ፤ እርሱ ግን ዛሬም ዓመታትን እየለገሰን ወደ እቅፉ እንገባ ዘንድ ይጠብቀናል፤ በሉቃስ ወንጌል ላይ እንዳነበበነው የጠፋው ልጅ ታሪክ እኛም ወደ አባታችን ቤት እንመለስ፣ እናመስግነውም፤ በድለነው ሳለን እርሱ ፊቱን አላዞረምና። => "...ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት፥ ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው..." ሉቃ. ፲፭፥፳ /15፥20/ => ምስጋና የራቀን ትውልዶች ነንና ችላ ብለን ጥበቃውን ጥሪው ረስተን በዓለም ውጣ ውረድ እንዳክራለን፤ ኑ እናመስግነው፤ ሊመሰገን ይገባልና፤ አምላካችን ልባችንን ቀልባችንን ይመልስ። በጠባቡ መንገድ እንመላለስ ዘንድ ይርዳን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

መንፈሳዊ ሕይወት አዝሎኛል ምን ላድርግ?? || መንፈሳዊ አገልግሎት ለምን ይከብደናል? | በምርጫዎቻችን የኃጢአት ባሪያ ሆነናል | መምህር ግርማ ወንድሙ 🔥😭🚩 https://youtu.be/E2G2Uen4utY

የመምህር ተስፋዬ የሕይወት ፈተናዎችና ገጠመኞቹ || ጊዜያችንን እንድናባክን የሚያደርጉ መናፍስቶች | ተግባራዊ ክርስትና ለምን ጎደለን? | ተስፋዬ አበራ 😱😭🔥 https://youtu.be/I45AwhX4we4?si=y6yhZdj4SY4b9YGh

እንድታመልከኝ፣ እንድትሰግድልኝ ነበር ፍላጎቴ || ከባህር የሚሳቡና የሚዋረሱ አጋንንቶች || ኦርቶዶክሳዊነት ራስን መግዛት ነው || መምህር ግርማ ወንድሙ 💥😱 https://youtu.be/nSlDj8QeqtU

photo content

«ሁሉንም ነገር ለእግዚአብሔር እንስጠው»           => ወርቅን የሚያነጥር ሰው አንዲትን የወርቅ ቅንጣት ወደ እሳት ውስጥ ጨምሮ እጅግ ንጹህ እስክትኾን ድረስ ይጠብቃታል፤ እግዚአብሔርም ልክ እንደዚሁ ሰዎች እስኪነጹ፣ እስኪለወጡና ባገኛቸው ነገር ጥቅም እስኪያገኙ ድረስ ፈተና ውስጥ እንዲቆዩ ይፈቅዳል፤ ይህ ደግሞ ከጥቅምም እጅግ ከፍ ያለ ጥቅም ነው፡፡ ስለዚህ ፈተና ሲገጥመን ውስጣችን ሊረበሽ ወይም ተስፋ ሊቈርጥ አይገባውም፤ ያ ወርቅን የሚያነጥር ሰው በእሳት ውስጥ የጨመራትን የወርቅ ቅንጣት እዚያ ውስጥ ምን ያኽል ጊዜ መቆየት እንዳለባት ያውቃል፤ መቼ ከእሳቱ ሊያወጣት እንደሚገባውም ያውቃል፤ እንዲሁ እስከ መጨረሻው በእሳቱ ውስጥ ተጥላ እንድትቀርና በዚያ እንድትቃጠል አይፈቅድም፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ከወርቅ አንጣሪው በላይ ያውቃል፤ መቼ ከርኵሰታችን እንደምንነጻ ያውቃል፤ በመኾኑም ራሳችንን በመጣልና ተስፋ በመቁረጥ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን እንዳንሔድ ሽቶ መቼ ከዚያ ፈተና እንደሚያወጣን ያውቃል፡፡ => ስለዚህ ድንገት ያላሰብነው ነገር ቢገጥመን በፍጹም የምናማርር፣ ወይም ተስፋ የምንቈርጥ ልንኾን አይገባንም፤ ከዚህ ይልቅ የእነዚህ ነገሮች ምንነትን የሚያውቅ እግዚአብሔርን መጠበቅ፣ እርሱ እስከ ፈቀደው ጊዜ ድረስም ልቡናችንን በእሳት እንዲፈተን ማድረግ ይገባናል፤ ምክንያቱም ይህ ነገር በእኛ ላይ እንዲኾን የፈቀደው ለእኛ ጥቅምና በዚያ ውስጥ ኾነን በምናሳየው ጥረት ይበልጥ ሊያከብረን ስለሚወድ ነው፡፡ ይህን በማስመልከትም ጠቢቡ ሰው እንደዚህ ሲል መክሮናል “ልጄ ሆይ! ለእግዚአብሔር ትገዛ ዘንድ ብትሔድ ሰውነትህን ለመከራ አዘጋጅ፤ ልብህን አቅና፤ ኹልጊዜ ታገሥ፤ አታወላውልም፤ በመከራ ብትጨነቅም አትጠራጠር።” (ሲራ.2፥1-2) => ኹሉንም ነገር ለእግዚአብሔር ስጠው ለምን? እግዚአብሔር ከዚያ መከራ መቼ እኛን ማውጣት እንዳለበት ያውቃልና፤ ስለዚህ ኹሉንም ለእርሱ ልንሰጥ፣ ዘወትር እርሱን ልናመሰግን፣ ኹሉንም ነገር ጥቅምም ይኹን ቅጣት በአኰቴት ልንቀበል ይገባናል፤ ይህም ቢኾን ለእኛ ረብሕ የሚኾን ነውና፡፡ አንድ ሐኪም፥ ሐኪም የሚባለው ታካሚውን ገላዉን ሲያጥበውና ሲመግበው እንዲሁም ደስ ወደሚያሰኝ ስፍራ ሲወስደው ብቻ አይደለም፤ በእርሱ (በታማሚው) ሰውነት ላይ የቀዶ ጥገና ምላጭና ቢላ ሲያሳርፍም ጭምር ሐኪም ነው፤ አባትም አባት የሚባለው ልጁን ሲንከባከብ ብቻ አይደለም፤ የገዛ ልጁን ከቤት ሲያስወጣው፣ ሲገሥጸው፣ ሲገርፈውም ያው አባት ነው፡፡ => ስለዚህ እኛም እግዚአብሔር ከሐኪሞችም በላይ ሰውን ወዳጅ እንደ ኾነ በማወቅ፥ ምን ዓይነት የሕክምና ዓይነት እንደሚሰጠን በጥልቀት አንጠይቅ፤ ወይም ደግሞ ለደረሰብን መከራ እርሱን ተጠያቂ አናድርግ፤ ከዚህ ይልቅ እርሱ የወደደውን ነገር ቅጣትም ይኹን ቅጣት የሌለው ነገር ብቻ ምንም ይኹን ምን በአኰቴት ልንቀበል ይገባናል፡፡ በየትኛውም መንገድም ቢኾን የእርሱ ፈቃድ እኛ እንድንድንና ከእርሱ ጋር አንድ እንድንኾን ነውና፤ የትኛው መንገድ ለእኛ እንደሚጠቅምም እርሱ ያውቋል፤ እያንዳንዱ ሰው የትኛው መንገድ ወደ እርሱ እንደሚመልሰው ያውቃል፤ ኹላችንም እንዴትና በምን ዓይነት መንገድ ልንድን እንደምንችል ያውቃል፤ በመኾኑም የሚመራን በዚህ እኛ በምንድንበት መንገድ ነው፡፡ => ስለዚህ ወደየትኛውም መንገድ ቢወስደንም ልክ እንደ መጻጉዑ እርሱ እንደሚያዘ’ን ተከትለን መሔድ እንጂ ትልቁ ጉዳያችን በለስላሳና በቀላል አልያም ደግሞ በከባድና በሸካራ ጎዳና እንድንሔድ የሚያዘ’ንን ትእዛዝ መኾን የለበትም (ልንሔድበት የሚገባው መንገድ እርሱ ስለሚያውቀው እንዲሁ መታዘዝ እንጂ የመንገዱን ከባድነት ወይም ቀላልነት የእኛ አጀንዳ ሊኾን አይገባውም፡፡) በርቱ! በሉ ወደ ጉዟችን! በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

photo content

«ወይ አባቶቻችን ይገርማል!» => ከመመስገን ይልቅ መነቀፍ የበለጠ ብፅዕና ነው፤ ሰዎች ሲያመሰግኑኝ ለእኔ መንፈሳዊነት አደገኛ እንደሆነና ሰዎች ሲነቅፉኝና በሐሰት ክፉ ሲናገሩብኝ ማመስገንን በአእምሮዬ ውስጥ ተክዬዋለሁ? የማይቻል ነገር ነው ልትሉ ትችላላችሁ ግን መሆን ያለበት ነው፡፡ እኛስ ወድ ቤተሰቦቼ?           => አቡነ ዮሐንስ የተባሉ አባት በየሳምንቱ ሐሙስ ሐሙስ በአቅራቢያቸው ወዳለ አንድ መንደር ለማስተማር ይሔዱ ነበር፤ በግብፅ እንደተለመደው ወደዚያች መንደር ለመሔድ ሲሳፈሩ ከእንድ ሌላ ሰው ጋር መዳበል ነበረባቸው፤ በዚህ ጊዜ አንድ አክራሪ ሙስሊም ሁል ጊዜ በተመሳሳይ ሰዓት አብሯቸው ይሳፈር ነበር፤ ሊሳፈሩ ሲገቡ ታዲያ ፊቱን ዞር ያደርግና [ጢቅ አድርጎ] ይተፋ ነበር! ይህን አስነዋሪ ድርጊት ለዓመታት ይፈጽም ነበር፤ አንድ ቀን ጳጳሱ ሊሳፈሩ ሲመጡ ያ ሰው አልነበረም፡፡ => አቡነ ዮሐንስ ከልባቸው አዝነው እግዚአብሔርን መጠየቅ ጀመሩ "ጌታዬ ይህንን በረከት ለምን አስቀረህብኝ? ይህንን በረከት ከዚህ በላይ እቀበል ዘንድ እንደማልገባ የወሰንከው በኃጢአቶቼ መብዛት ይሆን?" እኛስ የምጠይቀው ምን ይሆን ወገኖቼ? => ሌላው የተቀደሰ ትውስታ ባለቤት ደግሞ የማይታክቱት የእግዚአብሔር ሠራተኛ ጳጳሱ አቡነ ሳሙኤል ነበሩ፤ እኚህ አባት እንደተለመደው ብዙ ጠላቶች ነበሯቸው፤ እጅግ አስጸያፊ መልእክቶችን እየጻፉ በደብዳቤ መልክ ይልኩላቸው ነበር፤ እሳቸውም እነዚህን አስጸያፊ ስድቦች በመሳቢያቸው ውስጥ ያስቀምጡአቸው ነበር፡፡ => በሚከፋቸውና በሚተክዙ ጊዜ ማኅደራቸውን ከፍተው እነዚህን ደብዳቤዎች የነብቡ ነበር፤ ከዚህ በኋላ የመታደስ ስሜት ይሰማቸዋል ምክንያቱም ነቀፋዎቹን ሲያነብቡ በእያንዳንዱ ስድብ ውስጥ በረከት እንዳለ ስለሚያዩ ነበር፤ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የምናነብበውን በልባችን ውስጥ መትከል የምንለው እንግዲህ ይህንን ነው።" በረከታቸው ይደርብን በእውነት! (አቡነ አትናስዮስ እስክንድር) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ትዳሯን፣ ዕድሏን፣ ኑሮዋን ጉድጓድ ቆፍረን ቀበርንባት || አስገራሚው ቤተሰብና አጋንንቶቹ! || ግራ መጋባትን ለማራቅ ይሄን አናድርግ || መምህር ግርማ 🔥💥😭 https://youtu.be/fOq0bZaxQHc

«ወደ መንፈሳዊ ዓለም ከመጣን በኋላ ለእግዚአብሔር ስለሰጠነውና ስለ እግዚአብሔር ብለን ስለተውነው ነገር ብዙ እንቆጥራለን፣ እንቆጫለን። እኛን በመጥራቱና በማጽደቁ ክርስቶስ ሳይጸጸት የእኛ መቆጨት ይገርማል። ለጌታ ብለን ከተውነው ጌታ ለደሙ ብሎ የተወልን ይበዛል።» #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ደስታና ሰላምን የሚያሳጡ ሦስት የሰይጣን ወጥመዶች አሉ፦ => ስላለፈው መጸጸት => ስለሚመጣው መጨነቅ => ስለ ዛሬው አለማመስገን ናቸው! (ቅዱስ እንጦንስ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የልጇን ማህጸን በመተት የዘጋችው እናት | እንዴት እንዳን እንፈወስ? | አስገራሚው የቅዱስ ሚካኤል ተዓምር ||memihir tesfaye abera 2024 😱😭💥 https://youtu.be/yjWWicDrfJA

በመከራ በሃዘን ደስ ይለናል፤ በአንተ ፍቅር ማዕበሉን ቀዝፈናል፤ ስንጠራህ ስንልህ አምላካችን፤ ያ ተራራ ዘለለ ከፍታችን። ማአሯችንን ይዘን፤ በገለዓን ተራራ፤ በማያቆም ውዳሴ፤ አንተን ስንጠራ፤ ሐያል ክንድህ አርፎብን፤ ታርክ ተቀየር። (ዘማሪ እዝራ ኃ/ሚካኤል) ቃለ ሕይወትን ያሰማልን! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ጠንቋዩ ቄስና አስገራሚው ተዓምር || ሰይጣን እያሞኘን ይገኛል እንንቃ || በተለያዬ ምክንያት ሳይቆርቡ ለተጋቡ ባለትዳሮች || መምህር ግርማ ወንድሙ 💥🔥😱🚩 https://youtu.be/k9XlHLhBUcg

photo content