HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Открыть в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Больше2 269
Подписчики
+224 часа
+177 дней
+2930 день
Архив постов
በመተት አጋንንት ዕድላችን መወሰዱን በምንና እንዴት እናውቃለን? መፍትሔውስ ምንድነው? ዕድላችን በመተት ተወሰደ የሚባለው መቼ ነው?
https://youtu.be/Vma1Cu3VoB4?si=cWosvBce3jp6lqcC
ፓስፖርት አውጥቶ ውጭ ሀገር የገባው የመተትና የደብተራው ሴራ ስገለጥ!! መምህር ተስፋዬ ያስተላለፈው ጥብቅ መልዕክት! የአለባበስ መተት እንዳለ ስንቶቻችሁ ታውቃላችሁ?
https://youtu.be/y72Zp2Pt_UU?si=-E9wNuywPuTWdr3i
እኔ አባታችሁና መምህራችሁ ነኝ፥ ሁላችሁ ልጆቼ ትእዛዜን አዳምጡ፤ በቅድስት ሥላሴ ማመንን እንድትከተሉና እንድትጸኑ እነግራችኋለሁና፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ እርስ በእርሳችሁ በእውነተኛ ፍቅር ትዋደዱ ዘንድ እለምናችኋለሁ።
የተወደዳችሁ ልጆቼ በፍጹም ሰብአዊነት መልካምን አንድታደርጉ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ ዓለም እንድታታልላችሁ አትፍቀዱላት፤ በእግዚአብሔር አገልግሎት ዳተኞችና ቸልተኞች አትሁኑ ብዬ እለምናችኋለሁ።
የተወደዳችሁ ልጆቼ ያለማቋረጥ እና ያለ መታከት እንድትጸልዩ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ መለያየትን ከሚያመጣ ንግግር አንደበታችሁን እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።
የተወደዳችሁ ልጆቼ የተጠመቃችሁባትን ቅድስቲቱን ጥምቀት እንድትጠብቋት እለምናችኋለሁ፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ ሰውነታችሁን ለጌታ ንጹሕ አድርጋችሁ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።
ልጆቼ መብራታችሁ ፈጽሞ እንዲጠፋ አትፍቀዱ ይልቅስ ብርሃንን እንዲሰጥ እንድታደርጉት እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ እግዚአብሔር የሰጣችሁን ትእዛዝ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።
ልጆቼ እግዚአብሔርን መፍራት ከእናንተ ጋር እንዲሆን እለምናችኋለሁ፤ የነገርኳችሁን ሁሉ ከጠበቃችሁ የእባቡንና የዘንዶውን ራስ ትቀጠቅጣላችሁ፤ ያልኋችሁን ካደረጋችሁ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ ብርሃናዊያን ኪሩቤል ይጠብቋችኋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@iam_haile
እኔ አባታችሁና መምህራችሁ ነኝ፥ ሁላችሁ ልጆቼ ትእዛዜን አዳምጡ፤ በቅድስት ሥላሴ ማመንን እንድትከተሉና እንድትጸኑ እነግራችኋለሁና፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ እርስ በእርሳችሁ በእውነተኛ ፍቅር ትዋደዱ ዘንድ እለምናችኋለሁ።
የተወደዳችሁ ልጆቼ በፍጹም ሰብአዊነት መልካምን አንድታደርጉ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ ዓለም እንድታታልላችሁ አትፍቀዱላት፤ በእግዚአብሔር አገልግሎት ዳተኞችና ቸልተኞች አትሁኑ ብዬ እለምናችኋለሁ።
የተወደዳችሁ ልጆቼ ያለማቋረጥ እና ያለ መታከት እንድትጸልዩ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ መለያየትን ከሚያመጣ ንግግር አንደበታችሁን እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።
የተወደዳችሁ ልጆቼ የተጠመቃችሁባትን ቅድስቲቱን ጥምቀት እንድትጠብቋት እለምናችኋለሁ፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ ሰውነታችሁን ለጌታ ንጹሕ አድርጋችሁ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።
ልጆቼ መብራታችሁ ፈጽሞ እንዲጠፋ አትፍቀዱ ይልቅስ ብርሃንን እንዲሰጥ እንድታደርጉት እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ እግዚአብሔር የሰጣችሁን ትእዛዝ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።
ልጆቼ እግዚአብሔርን መፍራት ከእናንተ ጋር እንዲሆን እለምናችኋለሁ፤ የነገርኳችሁን ሁሉ ከጠበቃችሁ የእባቡንና የዘንዶውን ራስ ትቀጠቅጣላችሁ፤ ያልኋችሁን ካደረጋችሁ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ ብርሃናዊያን ኪሩቤል ይጠብቋችኋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
❗️መላሽ ያላገኘው ጥያቄ።
- በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በ44ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፋዊ ጉባዔ ላይ አንጋፋው አባት ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የሚከተሉትን መልስ የሌላቸው ጥያቄዎች እንዳቀረቡ ሰማን!
- የምንሰበሰበው ለምንድነው? ምክንያቱን አውቀን ነው የተሰበሰብነው? እስከ ዛሬስ የተወሰኑት ውሳኔዎች ይተገበራሉ? ልባችንን ሰጥተን ነው የምንመካከረው?
- ጉባዔው 44ኛ ነው። በ44 ዓመት ውስጥ ምን ሠራን? በፓትርያርክ መመራት ከጀመርን 66 ዓመታችን ነው። በግብጻውያን ሥር እያለን ምን ተሠራ? ከእነርሱ ነጻ ከወጣን በኋላስ ምን ሠራን? ከልባችን ብናስብ ኖሮ ዛሬ የሚታዩ ችግሮች ባልኖሩ።
- ክርስቶስን የምንከተለው ለምንድነው? ጌታችን በሚያስተምርበት ዘመን ለእንጀራና ልዩ ልዩ ምድራዊ ምክንያቶች የሚከተሉ ነበሩ። ዛሬስ?
- ይህ ጉባኤ ከተኛበት ይንቃ ይነሣ። ምንም አልሠራንም!!
- ብፁዕ አባታችን አቡነ ኤልያስ በዕድሜና በጤና ይጠብቅልን።
- እንደ እርስዎ የሚያስቡ ቢበዙ ኖሮ ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ባለ በታሪክ ባልታየ ምስቅልቅል ውስጥ አትገኝም ነበር።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@iam_haile
ከቤተሰቦቻችን የወረስናቸውን የዛርና የጬሌ መንፈስ በዚህ መንገድ አስወግዱ | መምህር ተስፋዬ አበራ | መምህር ግርማ ወንሙ | ዲያቆን ዘላለም ታዬ https://youtu.be/0ZBCjHg1lec
ቆንጆ ሴቶችና የቡዳ መንፈስን ምን ያገናኛቸዋል ይኼንን ልታዳምጡ ይገባል!! ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ስገባው እንዲህ ይሆናል!! ለሴቶች የጥንቃቄ መልዕክት!! https://youtu.be/l-0y4QSgyhw
«አንተ ኃጢአትን በምትሠራበት ጊዜ በገበያ መካከል ብዙ ሰዎች በዚያ ስላሉ በግልጽ በአደባባይ አትሠራም። ይህም ለክብርህና ኃጢአትን አብሮህ ለሚሠራው ሰው ክብር ፈርተህ ነው። ነገር ግን አንተ ሰዎችን የምትፈራና የምታፍር ከሆነ በሁሉ ቦታ ባለ ሁሉን በሚያይ ሁሉን በሚሰማ በልዑል እግዚአብሔር ፊት ይህን የመሰለውን ስድብና ድፍረት ስትሠራ እንዴት አታፍርም? አያይም እንዳትል ያያል፤ አይሰማም እንዳትልም ይሰማል።»
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@iam_haile
የንስሐ አባት የምንቀይርባቸው 10 መሠረታዊ ምክንያቶች!! በንስሐ አባትና ልጅ መካከል ያለው ግንኙነት!! የንስሐ አባት የሚያስቀይሩ ከባባድ ስህተቶች!! https://youtu.be/GEh1iwqwtoQ
በምትጸልይበት ጊዜ አትቸኩል፥
ምጽዋት መመጽወትንም አታቃልል።
የሚያሳዝን፥ ደስ የሚያሰኝም አለና፥
ባዘነ ሰው አትሳቅ።
.
ብዙ ናቸው ብለህ
ከኃጢአተኞች ጋር አንድ አትሁን።
[ሲራክ 7: 10-11 & 16]
———______———
1. ጥድፍ ጥድፍ ብለህ ብዙ ለመጸለይ ከመመኮር አጭርም ቢሆን ጸሎት ተረጋግተህ ከልብህ በማስተዋል ሆነህ መጸለይ
2. ስለ ምጽዋት ቅዱሳት መጽሐፍት የሚምሰክሩት ነገር በጣም ጠንካራ ነው.. “ለደሃ የሚሰጥ ለእግዚአብሔር ያበድራል” የሚልም ሳይቀር ነው ያለው[ምሳ 19:17].. ስለዚህም በፍቅር የሆነ ቸርነትን እናድርግ.. በማርያም ብሎ እየለመነን አልፈነው ቤት ስንገባ እኛም ጌታችንን “በማርያም” ብለን የምንለምን ነን..
3. በኃጢአት ውስጥ ያሉ ብዙዎች ቢሆኑ ለመመሳሰል ብለህ ኃጢአተኛ አትሁን.. ለነ ኖኅ እና ሎጥ የተነገረውን አስብ 2ጴጥ 5-8.. ራስህን ለእግዚአብሔር ለይ.. አብረህ መሞትና እግዚአብሔርን ማጣት የለብህም..
መልካም ውሎ..ይሁን ለሁላችን!
«ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ»
» በጥቅምቱ ጉባኤ መክፈቻ ከተናገሩት
» ያለምንም ደመወዝ በራሳቸው አቅም በግብርና እየተዳደሩ ቤተ ክርስቲያንን በጥሩ ስብዕና በንፅህና በቅድስና ጠብቀው ያስረከቡ እልፍ አእላፍ አበው እንዳልነበሯት ዛሬ የተሻለ ኑሮና ደመወዝ እያገኘን #እግዚአብሔርን እንደ ቀኖናው ማገልገል አቅቶናል። እግዚአብሔር ይማረን።
የብጹዕ አባታችን በረከት ይደርብን!
ጥቅምት ፭ /5/
አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ገብረ ሕይወት)
ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ::
አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ562 ዓመታት በዚህች ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ ልብስ ያልለበሱ ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ ነፍሳትን ያዳኑ አባት ናቸው።
የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ስለ ሀገራችን ፍቅር ሲሉ ለ100 ዓመታት በደብረ ዝቋላ መከራን ተቀብለዋል። ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው።
በ8ኛው ክ.ዘ አካባቢ የተወለዱት አባታችን ያረፉት በ14ኛው መቶ ክ.ዘ አካባቢ ነው። ፍጥረታትን ሁሉ አዘው መጋቢት 5 ቀን ሲያርፉ ግሩማን መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል።
ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍቱ መጋቢት 5 ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው ፍትሃ ነገስት አንቀጽ 15 ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ የመጋቢት 27 ስቅለት ጥቅምት 27 ቀን እንደሚከበረው ሁሉ ወደ ጥቅምት 5 ቀን ተዛውሮ እንዲከበር ተደረገ፡፡
የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን!አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር እና ፍትሃ ነገስት
ጸሎትን ጸሎት የሚያሰኙ 4ቱ መሠረታዊ ቅኝቶና ማወቅ ያሉብን ነገሮች!! የጸሎት ቅደም ተከተል ይኼንን እወቁ!! ከሦስት ዓይነት ሴቶች ተጠንቀቁ!!
https://youtu.be/WG1d_z9duck?si=YvjKYdZtVMgOJiAW
SPIRITUALISM ከአጋንንት ጋር የሚያቆራኝ ድብቁ የአዲሱ ዓለም ሃይማኖት!! መስገድ መጸለይ መንበርከክ ስትጀምሩ መንፈሳችሁ ይለያል! #spiritualism https://youtu.be/GQXhMmRG1DI
እግዚአብሔር ረስቶኛል ጸሎተን አይሰማኝም ለምትሉ ይኼንን አዳምጡና ወስኑ!! አስቀዳሹና መዝሙር ደጋሚው አጋንንት ጠቋርና ሴራዎቹ!! ጸጸት በንስሐ ወቅት! https://youtu.be/a-EdnBequS4
ውድ ቤተሰቦቼ፣ መወያየት የምትፈልጉት መንፈሳዊ ጥያቄ፣ ማጋራት የምትፈልጉት አስተማሪ ታሪክ፣ ወይም የሚያነቃ መልዕክት ካላችሁ፣ አብረን እንድንማማር በዚህ የቴሌግራም ቦት በኩል ያግኙን። 👉 https://t.me/Haile_Gebriel_Tube_bot 👉 ሰላም፣ ፍቅርና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን። በርቱ!
«ስለ ሌሎች መዳን ከማይጨነቅ ክርስቲያን በላይ ሰነፍ ሰው የለም፡፡ ወዳጄ “እኔ ድኻ ነኝና ይህን ማድረግ አልችልም” የምትል አትኹን፤ ባለ ኹለት ዲናሯ ሴት ትወቅስሃለችና፡፡ ዳግመኛም “ወርቅም ብርም የለኝም” ብሎ የተናገረ ጴጥሮስ ይወቅሰሃልና፡፡ ምናምንቴ ነኝ አትበል፤ እንዲህ ስትል ምናምንቴዎቹ ሐዋርያት እንዳይሰሙህ! "እኔ በሽተኛ ነኝ" አትበል፤ በሽተኛው ጢሞቴዎስ ይታዘብሃልና፡፡ ፈጽመህ “እኔ ሌሎች ሰዎችን ወደ ክርስቶስ ማምጣት አይሆንልኝም” አትበል፡፡ በእውነት ክርስቲያን ከኾንክ ይህን ከማድረግ ይልቅ አለማድረጉ ይከብዳልና፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ እንድትኾን አድርጎ ፈጥሮሃልና ተፈጥሮህን መካድ አይቻልህም፡፡ ክርስቲያን በጨለማ ውስጥ ለሚኖሩ ወንድሞቹ ብርሃኑን ከሚከለክል ይልቅ ፀሐይ ብርሃኗን ብትከለክል ይቀላልና ስለዚህ አልጠቅምም አትበል፡፡»
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@iam_haile
ጥቅምት ፫ /3/በዚሕችም ቀን ሊቀ ጳጳሳት አባ ስምዖን አረፈ። የዚሕ አባት ወላጆቹ ሃይማኖታቸው የቀና እርሱም ከታናሽነቱ የሃይማኖት ወተትን ጠጥቶ ያደገ የቤተክርስቲያንንም ትምሕርት ተምሮ ያደገ ነው። ወደ አስቄጥስ ገዳም በሊቀ ጳጳሳት በአባ ያዕቆብ ገዳም የምንኩስናን ልብስ ለብሶ መነኮሰ ተጋድሎውንም በየጊዜው ጨመረ ሥጋውንም አያደከመ በእርሱ ዘንድ ኖረ። ስለ በጎ ተጋድሎውና ስለ አገልግሎቱ ዳግማዊ ሊቀ ጳጳስ አባ ማርቆስ ወደ አባ ያዕቆብ ወስዶት እያገለገለው ከእርሱ ጋር ኖረ። አባ ያዕቆብ በአረፈ ጊዜም ካሕናትና ኤጲስቆጶሳት ትሩፋቱንና ያማረ ሥራውን ስለተመለከቱ አምላካዊ ፍቅር አነሳስቷቸዋልና በወንጌላዊ ማርቆስ መንበር ላይ ይዘው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት። በሹመቱ ጸንቶ መልካምን ጉዞ ተጓዘ እግዚአብሔርንም እያገለገለ የሃይማኖትንም ሕግ በማስጠበቅ የክርስቶስን መንጋዎች ጠበቀ። በሹመቱ ወራትም ቤተ ክርስቲያን በጸጥታና በሰላም ኖረች። ከዚሕም በኋላ እግሮቹን በጽኑዕ ደዌ ታመመ እግዚአብሔርንም ከዚሕ ደዌ ያሳርፈው ዘንድ ለመነው ክብር ይግባውና ጌታችንም ልመናውን ተቀብሎ በሰላም በፍቅር በአንድነት አሳረፈው የሹመቱም ወራት አምስት ወር ከዐሥራምስት ቀን ነው። የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን! አሜን ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@iam_haile
#ድንግል_ሆይ ፣ ቅድስት ሆይ፣ ንጽሕት ሆይ፣ 🌹 የተመሰገንሽ ቡርክት ሆይ የድግልናሽ ምስጋና በኹሉ መላ
ውዳሴሽም በዓለም ዙሪያ ሰፈፈ፤ የውቅያኖስ ባሕር በምልአቱ ውሱን ነው
የሐኖስም ባሕር በመጠኑ ልክ አለው፤
#ለአንቺ ምስጋና ግን ልክና መጠን ወሰንና መስፈርት፣ ማለቂያም የለውም አእምሮም አይወስነውም አንደበትም ተናግሮ ሊፈጽመው አይችልም“
#ኦ_ድንግል፣ ኦ ቅድስት፣ ኦ ንጽሕት ፣ኦ ቡሩክት፣ ኦ ኅሪት፣ ስብሐተ ድንግልናኪ መልአ በኵለሄ ወውዳሴ ዚአኪ ሰፈፈ ውስተ ኵሉ አጽናፈ ዓለም፤ ባሕረ ውቅያኖስ ውሱን በድንጋጊሁ ወባሕረ ሐኖስኒ ዐቅም ቦ በአምጣኒሁ ወለስብሐተ ዘኣኪሰ አልቦቱ ማኅለቅት ወኅሊናኒ ኢይክል አግምሮቶ ወልሳንኒ ኢይክል ፈጽሞቶ“
(አርጋኖን ዘሰኑይ ፰ ÷ ፲ - ፳፰)
እንኳን ለጥቅምት 3 በዓታ ማሪያም ወርሃዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ።
መምህር ግርማና ሊቁ ስምዓኮነ መልዓክ የነገሩን የማንቂያ መልዕክት!! መላዕክት ሲጸልዩ ካሳየኼኝ ኦርቶዶክስ እሆናለው!! https://youtu.be/L8D17Ker6Bk?si=hnNNO7nR98ogGldG
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
