HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Kanalga Telegram’da o‘tish
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Ko'proq ko'rsatish2 280
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+77 kunlar
+3930 kunlar
Postlar arxiv
«ይኼው አሁንም ሌላ ሐዘን!! ጌታ ሆይ ይቅር በለን!»
በአርሲ ሀገረ ስብከት በኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።
ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]
በአርሲ ሀገረ ስብከት ጉና ወረዳ በሚገኘ ኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን መገዳላቸውን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያሳያል።
በደረሰን መረጃ መሠረት በቀበሌው የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን ከለሊቱ 6:00 ሰዓት አካባቢ በዕለተ ረቡዕ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ለ14 አጥቢያ ከተኙበት ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ሲሆን ስድስቱ ከመገደላቸው ከአንድ ቀን በፈት ቀድመው ታፍነው ተወስደው ነበር ተብሏል።
የተገደሉት ምእመናን የዕድሜ ክልላቸው ከ2 ዓመት ጀምሮ እስከ 76 ዓመት አዛውንት እንደሚገኙበት መረጃው ይገልጻል።
በተጨማሪም ሁለት ሰዎች በጥቃቱ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ለተሻለ ሕክምና ወደ አቦምሳ ከተማ ሪፈር መሄዳቸውን በመረጃው ተያይዞ ተነግሯል፡፡
ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ በቀበሌው ውስጥ የሚኖሩ 8 ኦርቶዶክሳውያን ሌሊት ላይ ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ መግደላቸውን በደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል።
ከተገደሉት ምእመናን ውስጥ 6ቱ በገገሌ በዓለወልድ ቤተ ክርስቲያን፣አንድ ደግሞ በሞዬ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን እና ቀሪ ሟቾች ባሉበት አካባቢያቸው ሥርዓተ ቀብራቸው መፈጸሙ ተገልጿል።
በመረጃው እንደተመላከተው በቀበሌው ባለ ከፍተኛ ስጋት በቀጣይ የባሰ ችግር እንዳይፈጠር በሀገረ ስብከት ደረጃ ከመንግሥት ጋር በጋራ መሥራት ይገባል ተብሏል።
በአሁኑ ሰዓት በአካባቢው ሁኔታዎችን ለማረረጋት የሀገር መከላከያ በስፍራው እንደሚገኝ በመረጃው ተጠቅሷል።
👉 ©ማኅበረ ቅዱሳን
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@iam_haile
«ውድ ቤተሰቦቼ ህልምን በተመለከተ ስትልኩልኝ እባካችሁ በተቻላችሁ መጠን "በጹሁፍ አድርጉልኝ" ብዙ ሰው በድምጽ ይልካል አይሰማም ወይም ድምጹ ይቆራረጣል ወይም ደግሞ ድምጹ ያነሰ ይሆናል ወይም ደግሞ መልዕክቱን በግልጽ አይናገርም። ስለዚህ በተቻላችሁ መጠን እንድንረዳዳ "በጽሁፍ" አጠር አድርጋችሁ ላኩልኝ። እኔም እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ በገባኝና ባወኩት መጠን ለመፍታት እሞክራለሁ ካልመለስኩ ደግሞ ታገሱ አደራ!» በዚህ በኩል ላኩ https://t.me/haile_gebriel_tube_bot
👉ስትጮሁ ለነበራችሁ መናፍቃን ይኼው ከሊቃንት አባታችን መልስ! ገድለ ዮሐንስ ተወገዘ ብላችሁ ለጮሃችሁ በሙሉ ይደረስ! ቤተክርስቲያን ለሁሉም መልስ አላት የምንለው በምክንያት ነው። ይኼንን ሸር በማድረግ ላልሰሙት አሰሙ።
https://youtu.be/GVSRt1kexZA
🔴የዚህ ዘመን የዲያብሎስ ወጥመዶችና ማወቅ ያሉብን ነገሮች!! ይኼንን መጠቀም ክልክል ነው ብላችሁ ጻፉ!! ከሰይጣን ይልቅ ልማድህን ፍራ!! #አጋንንት #ጸሎት https://youtu.be/fUUU0W-K1WU
ጥቅምት ፲፰ /18/ + በዚህች ቀን ክርስቲያኖችን በአሳደደ በመኰንን አስቅልጵያኖስ ዘመን የከበረ መነኰስ ሮማኖስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ የክርስቲያን ወገኖችን መኰንኑ እንዳሳደዳቸው በሰማ ጊዜ ከቀሳውስትና ከዲያቆናት ጋር የክርስቲያን ወገኖችን ሁሉ በአንድነት ሰበሰባቸው ስለ ክርስቶስ ሃይማኖትም መክሮ አጸናቸው። + አስቅልጵያኖስም ይህን ሰምቶ እንዲአመጡት አዘዘ በፊቱም በቆመ ጊዜ አስቅልጵያኖስ በወገን የከበርክ ሮማኖስ አንተ ነህን አለው ቅዱሱም የወገን ክብር ምን ይጠቅመኛል ክብሬ ግን ክርስቶስ ነው ብሎ መለሰለት። መኰንኑም ሰምቶ እንዲሰቅሉትና ጉንጮቹን ይሰነጣጥቁ ዘንድ አዘዘ ጉንጮቹንም ሲሰነጣጥቁት ምንም አልተናገረምና መኰንኑ ትዕግሥቱን አደነቀ። + በዚያንም ጊዜ ሮማኖስ መኰንኑን እንዲህ አለው እነሆ ስንፍናህን እዘልፍ ዘንድ ፈጣሪዬ አፌን ከፈተ በዚያንም ጊዜ የሕፃኑን ራስ በሰይፍ እንዲቆርጡ የቅዱስ ሮማኖስንም ምላሱን ከግንዱ እንዲቆርጡ መኰንኑ አዘዘ። ያን ጊዜ መኰንኑን ይዘልፍ ዘንድ ለአባ ሮማኖስ ረቂቅ አንደበት ተሰጠው ሲዘልፈውም መኰንኑ ሰምቶ ምላሱ እንዳልተቆረጠ ተጠራጠረ። + ወታደሩንም ጠርቶ ምላሱን ያልቆረጥክ ለምንድን ነው አለው ወታደሩም የምላሱን ቁራጭ ያመጡ ዘንድ እዘዝ አለው አምጥተውለትም አይቶ መኰንኑም ወደ ወህኒ ቤት አስገብተው በዚያ አንቀው እንዲገድሉት አዘዘ። እንዲህም ምስክርነቱን ፈጽሞ የምስክርነት አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን አሜን ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@iam_haile
ይኼንን ምክርና ተግሳጽ ሰምታችሁ እባካችሁ እራሳችሁን ፈትሹ!! በአርተፍሻል ብልት ድንግልናዋን ያጣችው ልጅ! ሰርጸ ፍረስብሃት ሙዝቃ ኃጢአት አይደልም እያለን ነው!
https://youtu.be/imz5SRUmTKw?si=A0IB7ffUx-L6P23z
🛑 ሰይጣን ኃጢአት ስንሰራ የሚሰጠን ድፍረትና ንስሐ እንዳንገባ ያለው ፈተና!! አርትስቷ ከ11 ዓመት በኋላ ልጅ ወለደች!! የትዕብት እግር አይምጣብኝ! #ጸሎት https://youtu.be/Cc97zxHZlLg
- ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ጥቅምት 17 ማዕረገ ዲቁናን በሐዋርያት እጅ በአንብሮተ እድ እንደተሾመ አሥራ ሁለቱም ደቀ መዛሙርት ሁሉን ጠርተው እንዲህ አሉአቸው፦ የእግዚአብሔር ቃል ትተን ማዕድን እናገለግል ዘንድ የሚገባ ነገር አይደለም። ወንድሞች ሆይ፥ በመልካም የተመሰከረላቸውን መንፈስ ቅዱስና ጥበብም የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ ምረጡ፥ ለዚህም ጉዳይ እንሾማቸዋለን፤ እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን። ይህም ቃል ሕዝብን ሁሉ ደስ አሰኛቸው፤ እምነትና መንፈስ ቅዱስም የሞላበትን ሰው እስጢፋኖስን ፊልጶስንም ጵሮኮሮስንም ኒቃሮናንም ጢሞናንም ጳርሜናንም ወደ ይሁዲነት ገብቶ የነበረውን የአንጾኪያውን ኒቆላዎስንም መረጡ።
- በሐዋርያትም ፊት አቆሙአቸው፥ ከጸለዩም በኋላ እጃቸውን ጫኑባቸው። የእግዚአብሔርም ቃል እየሰፋ ሄደ፥ በኢየሩሳሌምም የደቀ መዛሙርት ቍጥር እጅግ እየበዛ ሄደ፤ ከካህናትም ብዙ ሰዎች ለሃይማኖት የታዘዙ ሆኑ። እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር።
(የሐዋርያት ሥራ 5፥2-8)
🙏የቅዱስ እስጢፋኖስ
ረድኤት በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን🙏
ተሳክቶልሃል! ቤተሰቦቼን አጣሁ ኑሯችንና ሥራችን ምስቅልቅሉ ወጣ! መተት የሚባል ነገር የለም ያላችሁ ይኼንን አዳምጡ!
https://youtu.be/OpRzXwExUCo?si=vnQByiWPUtQnw7mi
«ትሕትና»
".. ልቡ አብዝቶ የጸለየውን ያህል በዚህ መጠን ልብ ትሑት ይሆናል፡፡ ትሑት ቢሆን እንጂ ትሑት ካልሆነ የሚለምን፣ የሚማልድ የለም፡፡ ፈጣሪ ጽኑ፣ ክቡር፣ ትሑት፣ ኅዙን፣ ልቡና የጸለየውን ጸሎት አልቀበልም አይልምና፡፡ ልቡናም በመከራ ትሑት ካልሆነ ትዕቢትን መተው አይቻለውም፡፡ ትሕትና መከራን ያርቃልና፤ ሰው ትሑት በሆነ ጊዜ ይቅርታን ያገኛል፡፡ ረድኤተ እግዚአብሔር እንደተሰጠችው ያውቃል፡፡ ያድነኛል ብሎ በማመን ዕውቀት ገንዘብ ያደርጋል፡፡ ሰው ረድኤተ እግዚአብሔር ጸጋ እንደተሰጠችው ያወቀ እንደሆነ ያድነኛል ብሎ ያምናል፡፡ የድኅነት መገኛ እንደሆነች፣ የሃይማኖት መገኛ እንደሆነች፣ ከመከራ ማዕበል ሞገድ ከውስጧ የሚያድን ወደብ እንደሆነች፣ በመከራ ድንቁርና ላሉ ዕውቀታቸው እንደሆነች፣ የድኩማን መጠጊያ በመከራ ጊዜ የሚያርፉባት ክንፍ እንደሆነች፣ በጽኑ ደዌ ጊዜ የሚድኑባት ረድኤት እንደሆነች፣ በጭንቅ ጊዜ የሚያርፉባት የሕይወት ተክል እንደሆነች፣ በጠላት ፊት የተቃጣ ፍላጻ እንደሆነች ያውቃል፡፡"
(ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ-ገጽ 31)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@iam_haile
🛑የመናፍስት በቀልና ተንኮል በህይወታችን ስኖር ይኼንን ምልክት ታያላችሁ!! ከመቁረባችን በፍት መጸለይ የሚገባ ጸሎት!! 3ቱ ክፉ ልማዶች አሁኑኑ ይወገዱ! https://youtu.be/fvjFLYBc-_c
🛑አጋንንትና ሰይጣን እኔን በጭራሽ አይነካኝ! ካመንክ ይሆናል! አጋንንት ዕድለን አይደለም ዝንበን አያባርርም! #አጋንንት #ዕድል #መተት #ሰይጣን #ክርስቶስ https://youtu.be/C_u-UcEmsaA
መዝሙረ ዳዊትን የሚጸልይ ሰው የሚያገኛቸው መንፈሳዊ በረከቶች! አባታችን መምህር ግርማ ያስጠነቀቁንና የነገሩን 4ቱ የሕይወት መመሪያዎች!! ስለ ንስሐ ማወቅ ያለባችሁ ወሳኝ ነገር!! https://www.youtube.com/watch?v=iJX2jqOgcR0
ጥቅምት ፲፫/13/ በዚችም ቀን ደግሞ የመነኰስ ዘካርያስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ። የዚህም መስተጋድል የአባቱ ስም አቃርዮስ ነው። ይህም አቃርዮስ ምንኩስናን ሽቶ ሚስቱን አስፈቅዶ ሁለት ልጆቹን ትቶ በገዳመ አስቄጥስ መነኰሰ። ከጊዜ በኋላ ረኃብ ሆነ ሚስቱም ልጆቿን ይዛ ወደባሏ አቃርዮስ መጣች በዚህም ምክንያት እኔ ወንዱን ልጄን እወስዳለሁ አንቺም ሴት ልጅሽን ውሰጂ አላት ይህንንም ብሎ ዘካርያስን ልጁን ወሰደ። ዘካርያስም በበጎ ሥራ በገዳም ውስጥ አደገ። መነኰሳትም ከመልኩ ማማር የተነሳ በመነኰሳት መካከል እንዴት ይኖራል ተባባሉ። ዘካርያስም መነኰሳት ስለእርሱ እንዳንጐራጐሩ በሰማ ጊዜ ናጥራን ወደሚባል ተራራ ስር ወደአለች ዐዘቅት ሔደ ልብሱንም አውልቆ በረግረግ ውስጥ ተኛ ሥጋውም ተነፋፍቶ ጠቆረ ተመላልጦም ቈሰለ ብዙ ዘመንም በደዌ እንደኖረ ሆነ ከዚህም በኋላ ልብሱን ለብሶ ወደ ገዳም መጣ ያወቀውም የለም። ከብዙ ቀኖችም በኋላ አባቱ አስተውሎ ልጁ ዘካርያስ እንደ ሆነ አወቀውና መልክህን የለወጠው ምንድን ነው ብሎ ጠየቀው እርሱም ያደረገውን ሁሉ ነገረው። አንድ ቀንም እግዚአብሔር ሥራውን ለአባ ኤስድሮስ ገለጸለት እርሱም ለመነኰሳት ነገራቸው። እነርሱም አስቀድሞ እንደ ሰው ሁነህ መጣህ ዛሬ ግን እንደ እግዚአብሔር መልአክ ሁነህ መጣህ አሉት። አባቱም ስለእርሱ እኔ በገድል ብዙ ደክሜአለሁ ነገር ግን ከልጄ ሥርዓተ ገድል አልደረስኩም ብሎ ተናገረ። በዚህ ተጋድሎውም 45 ዓመት እግዚአብሔርን አገልግሎ በ52 ዓመቱ በክብር አረፈ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር
🛑ብጹዕ አባታችን አቡነ ማቲያስ ዝምታቸውን ሰበሩ!! የዛር መንፈስና አጋንንት ወገቡን የሚመታው በቅዳሴ ነው!! ጅሃድ ከሌለ እስልምና ውቤት የለውም!! https://youtu.be/83EEKWpULkU
"የባዕዳን ስም የማጥፋት ዘመቻ፣ የቤተ ክርስቲያኗን እምነት ከመንቀፍና ከማብጠልጠል በላይ አልፎ የቅዱሳንን ቅዱስ ሥዕል በአደባባይ እስከ መቅደድ ተደርሶአል።" (ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ)
አባታችን በረከቶ ይደርብን!
አባ በርገር ማንነቱ ሲጋለጥና እፎይ ወንድማችን በድጋሚ ጉድ አወጣ!! ዳቤ ቀምሳ ከሞት የተነሳችው የሙስሊሟ እህታችን ታርክ!! #አጋንንት #ሰይጣን #ጸሎት https://youtu.be/AmPZ0P5I0WU
#ጸጉራችሁን ቀለም የምትቀቡ ከሆነ ይኼንን ቪዲዮ ሳታዩ በጭራሽ እንዳታልፉ!! ፓስተር ዮናታን ማደናገሩን ቀጥሏል!! መምህር ምህረተዓብ ያስተላለፈው መልዕክት!! https://youtu.be/4fESAMJ2GkQ
