💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
Открыть в Telegram
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Больше9 027
Подписчики
-724 часа
-367 дней
-14030 день
Архив постов
ዝምተኛ ልቦች…
የተመረኮዙት እምነት ታጥፎባቸው፣
ድንገት የወደቁ ፍቅር ያዳጣቸው፤
ሚስጥር የሚያጋሩት ሰው የበረዳቸው፣
ብቸኝነት ሰርቆ ብቻ ያስቀራቸው፤
ዝምተኛ ልቦች—ምን ይሆን ቋንቋቸው?!
✅ t.me/Sle_qelbachn1
👉 ለአንቺ ለውዷ ሙስሊም እህቴ፦ ከልብ የመነጨ ምክር!
እህቴ ሆይ! ከልብ የመነጨ ከልብ ይደርሳልና ከልቤ የመነጨ ምክር ላንች ለጀግናዋ ሙስሊም እህቴ ትንሽ ምክር ቢጤ ናት ተጠቀሚባት ።
ጀግናዋ እህቴ ሆይ! በሕይወትሽ ውስጥ ትልቁ ትኩረትሽ ዲንሽን ማወቅ፣ ሸሪዓዊ እውቀትን መገብየት፣ ተውሒድሽንና ትክክለኛውን ዐቂዳ ማስተካከል እንዲሁም የነቢዩን (ﷺ) ሱና መከተል ይሁን። በአኺራ ዘላቂ ጥቅምን የሚሰጥሽ ይህ ብቻ ነው።
ያለፈው ታሪክሽ ውስጥ "እንዴት በደሉኝ?"፣ "እንዴት አሳነሱኝ?" ወይም "መብቴን ሙሉ በሙሉ አልወሰድኩም" እያልሽ ስለ ካለፈው ነገር አትጨነቂ፤ በዛም ውስጥ አትኑሪ።
የሌሎችን የግል ሕይወት ለመሰለል ወይም
ስለ ሰዎች ግላዊ ጉዳይ ጥያቄዎችን ለማብዛት አትሞክሪ። እነዚህ መሰል ተራ ነገሮች ለጭንቀት፣ ለስነ-ልቦና መታወክ፣ ለቅናት፣ ለምቀኝነትና ባለሽ ነገር እንዳትረኪ ከማድረግ ውጭ ምንም አይፈይዱሽም። እውነተኛዋ ሙስሊም ሴት ትርጉም በሌላቸውና በማይጠቅሙ ጥያቄዎች ውስጥ ራሷን ከማድከም የላቀችና የረቀቀች ናት።
ራስሽን ከፍ አድርጊ! "እገሊት ስለ እኔ እንዲህ አለች"፣ "በሌለኝ ነገር ከሰሰችኝ"፣ "እገሊት መልእክቴን (Message) አይታ ዝም አለችኝ"፣ "እገሊት ተጓዘች ግን አልነገረችኝም"፣ "እገሊት ይሄን ገዛች"፣ "እገሊት አረገዘች ግን አልሰማሁም"፣ "እገሊት ተፋታች... ለምን ይሆን?" የሚሉ መሰል ወሬዎች ውስጥ አትግቢ።
ትኩረትሽ ራስሽን ወደ ተሻለ ደረጃ ማሳደግ፣ ለዲንሽ የሚጠቅምሽን ነገር መማርና ለሌሎችም መልካም መምከር ብቻ ይሁን። አላህ ያፈሰሰልሽ ጸጋዎች እኮ ተቆጥረው አያልቁም፤ ስለዚህ የሌለሽን ነገር ብቻ በማየት ራስሽን አታሳዝኚ። ሕይወትሽን ከማንም ጋር አታወዳድሪ፤ ዲናችን ከዚህ ሁሉ የላቀና ሰፊ ነው።
ነርቭሽንና አእምሮሽን በሚያደክሙ፣ ጉልበትሽን በሚያባክኑና ስነ-ልቦናሽን በሚያሻክሩ ነገሮች ውስጥ ራስሽን አትዘፍቂ። ይልቁንም አላህን በመታዘዝ ተጠመጂ፤ ትልቁ ጭንቀትሽና ስራሽ ለአኺራ የሚሆን ስንቅ ማዘጋጀት ይሁን።
منقولالسلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ውድና የተከበራችሁ ወንድምና እህቶች. እንደዚሁም የቻናል ባለቤቶች በሙሉ
ይህ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ወንድማችን አሊ አህመድ ይባላል
የትውልድ ሀገሩ ደቡብ ወሎ ወግድ ወረዳ ሲሆን ልዩ ቦታው ሰኮሩ ቀበሌ 022
እና እደማንኛውም ሰው ሰርቶ
ለመለወጥ ወዴ ሳኡድ አረብያ
መንገድን ጀምሮ ነበር ድበር
እስኪድርስ ይደውልልኝ ነበር ከዚያ ብኳላ ግን ድበር ሲቆርጥ እንደተያዘና ወደ ጂዛን እስር ቤት እንደወሰዱት ደላሉች ነገሩኝ ከሱ ከራሱ ተያዝኩኝ የሚል ድምፅን አልሰማሁም ደላሎችም አይታወቁምና
ደውሎልኝም አያውቅም እባካችሁ ቤተሰብ ከዛሬ ነገ ይደውላል በማለት እጪንቅ ላይ ናቸው በስደት የምትኖሩ ወንድም እህቶች ይህን ወንድሜን ያያችሁ እንድሁም ጂዛን እስር ቤት የተያዘባችሁ ሰው ከሏችሁ እነሱጋ እንድደርስልኝ በተቻላችሁ መጠን ከአሏህ በታች ስበብ ትሆኑኝ ስል እጠይቃለሁ ሼር ሽር አድርጉልኝ ለተላላቅ ሚደያ እንድደርስልኝ አድርጉልኝ ይህን ወድሜን ያያችሁ ከታች በማስቀምጥላችሁ ስልክ ቁጥር በመደወል እንድትተባበሩኝ ስል በአሏህ ስም እጠይቃለሁ
የወንድሙን ጭንቀት ያቀለለ አላህ የቂያማ ቀን የእሱን ጭንቀት ያቀልለታል። ،
رسول الله صلى الله عليه وسلم
አሏህ ከንደዚህ አይነት ነገር ይጠብቃችሁ.
05. 32. 74. 30 54
05 51 54 92 97
Repost from የኮምቦልቻ አህለሱና አንሷር መስጅድ official የሰለፍዬች channel
🌍 እውቀት ፈላጊዎች ሆይ! - بشرى سارة للجميع
📢 ለዲን እውቀት ናፋቂዎች
ርቀት ለእውቀት እንቅፋት አይሆንም! በወሎ ኮንቦልቻ በአንሷር መስጂድ የሚሰጡ ተከታታይ የደርስ ፕሮግራሞች፣ በታላቁ ዓሊም በሸይኽ ሰዪድ ሙሐመድ ያሲን (ሐፊዘሁላህ) አማካኝነት ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ በይፋ ይጀምራሉ።
📚 ለምን ይህን እድል ያመልጠዎታል መጠቀም አለብዎት?
የዒልም ምንጭ በሆነችው ወሎ ውስጥ የሚሰጡ ትልልቅ የሐዲስ እና የኡሱል ኪታቦችን በታላቅ ዓሊም ለመከታተል ወርቃማ እድል ነው።
🕒 የትምህርት መርሃ ግብር (የጧት)
🗓 ቀናት: ዘውትር ከሰኞ - እሁድ
⏰ ሰዓት: 3:00 - 6:30 (የኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር)
የሚቀሩ ታላላቅ ኪታቦች፡
✅ صحيح البخاري (ሶሒሑል ቡኻሪ)
✅ صحيح مسلم (ሶሒሑል ሙስሊም)
✅ سنن أبي داود (ሱነን አቢ ዳውድ)
✅ علم المصطلح (ዒልሙል ሙስጦላህ)
✅ علم الأصول (ዒልሙል ኡሱል)
🌙 ተጨማሪ የማታ ፕሮግራም (ከመግሪብ - ኢሻዕ)
🔹 ከሰኞ - ሐሙስ: 📚 بلوغ المرام (ቡሉጉል መራም)
🔹 ቅዳሜና እሁድ: 📚 كتاب المقصود في علم التصريف
ቤተሰቦቻችሁን ያሳትፉ: በሀገር ቤት ያሉ ወንድም እህቶቻችሁንና ጓደኞቻችሁን ወደ አንሷር መስጂድ በመላክ የእውቀት ተካፋይ እንዲሆኑ አድርጉ።
ለሌሎች አጋሩ: ይህን መልእክት ሼር በማድረግ የዲን እውቀት ለሚፈልጉ ወገኖች መንገድ ይሁኑ።
🔗 የዲን እውቀትን ለመገብየት ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡
👉 t.me/Ye_kombolcha_Ansuar_Mesjid_Jemea
https://t.me/kombolcha_Ansuarmesjid_channel
📍 አድራሻ: ወሎ ኮንቦልቻ፣ ደወይ በርበሬ ወንዝ፣ አንሷር መስጂድ።
"እውቀትን መፈለግ በሁሉም ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።"
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ፋጢማ ቢንት ሙሐመድ፣ አባቷን መሳይ፣ የሴት አይነታ
~
1. አባቷ የፍጡር ቆንጮ የሆኑት ነብያችን ﷺ ናቸው።
2. እናቷ የነብያችን የመጀመሪያ ሚስት፣ በፈተናቸው ጊዜ ከጎናቸው የቆመች፣ ወደ ኢስላም በመግባት ቀዳሚ የሆነችዋ ኸዲጃ ቢንት ኹወይሊድ ናት።
3. ባሏ አራተኛው ኸሊፋ አንበሳው ዐሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ ናቸው።
4. ልጆቿ የጀነት ወጣቶች አይነታዎች የሆኑት ሐሰንና ሑሰይን ናቸው።
5. እሷ ራሷ ደረጃዋ ከፍ ያለ ታላቅ የታላቅ ልጅ ናት።
ፋጢማ
* ከነብያችን ﷺ ልጆች መጨረሻ የሞተች ናት።
* በ24 አመቷ ከነብዩ ﷺ ሞት ከሰባት ወር በኋላ ዱንያን ተሰናብታለች።
* የነብያችን ﷺ ዘር የቀጠለው በሷ በኩል ነው፣ በሐሰን እና በሑሰይን በኩል።
እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ብላለች፦
أقبَلَت فاطِمةُ تمشي كأنَّ مِشْيَتَها مَشْيُ النَّبِيِّ ﷺ، فقال النَّبِيُّ ﷺ: ((مَرْحبًا يا ابنتي))، ثُمَّ أجلَسَها عن يمينِه -أو عن شِمالِه- ثُمَّ أسَرَّ إليها حديثًا، فبَكَت، فقُلتُ لها: لمَ تَبكِينَ؟ ثُمَّ أسَرَّ إليها حديثًا فضَحِكَت، فقُلتُ: ما رأيتُ كاليومِ فَرَحًا أقرَبَ مِن حُزنٍ! فسألْتُها عمَّا قال، فقالت: ما كُنتُ لأُفشيَ سِرَّ رَسولِ اللهِ ﷺ، حتى قُبِضَ النَّبِيُّ ﷺ فسألتها، فقالت: أسرَّ إليَّ ((أنَّ جِبريلَ كان يعارِضُني القرآنَ كُلَّ سَنَةٍ مَرَّةً، وإنَّه عارَضَني العَام مرَّتينِ، ولا أراه إلَّا حَضَر أَجَلي، وإنَّكِ أوَّلُ أهلِ بَيتي لَحاقًا بي))، فبَكَيتُ، فقال: ((أمَا تَرضَينَ أن تكوني سَيِّدةَ نِساءِ أهلِ الجنَّةِ -أو نِساءِ المُؤمِنين- فضَحِكْتُ لذلك ))
"ፋጢማ እየተራመደች መጣች፤ አረማመዷ ልክ እንደ ነቢዩ (ﷺ) አረማመድ ነበር። ነቢዩም (ﷺ) 'እንኳን ደህና መጣሽ ልጄ' አሏት። ከዚያም በቀኛቸው ወይም በግራቸው በኩል አስቀመጧት። ከዚያም በጆሮዋ ምስጢር ነገሯት፣ አለቀሰች። እኔም 'ለምንድነው የምታለቅሽው?' አልኳት። ከዚያም ደግመው ሌላ ምስጢር ነገሯት፣ ሳቀች። እኔም 'እንደ ዛሬው ለሀዘን ቅርብ የሆነ ደስታ አይቼ አላውቅም!' አልኩ። ምን እንዳሉ ጠየቅኳት። 'የአላህ መልክተኛን (ﷺ) ምስጢር አላወጣም' አለች።
ነቢዩ (ﷺ) ከዚህ ዓለም እስካለፉ ድረስ ምስጢሩን አልተናገረችም ነበር። ከዛ በኋላ ጠየቅኳትና እንዲህ አለች፦
'መጀመሪያ የነገሩኝ ምስጢር፦ 'ጅብሪል በየዓመቱ ቁርአንን አንድ ጊዜ ያቀርብልኝ ነበር፤ ዘንድሮ ግን ሁለት ጊዜ ነው ያቀርብልኝ። ይህ የሚያሳየው መሞቻዬ መቃረቡን ነው። አንቺም ከቤተሰቦቼ ውስጥ ቀድመሽ እኔን የምትከተይ ነሽ' የሚል ነበር፤ በዚህም ምክንያት አለቀስኩ።
ከዚያም ደግመው፦ 'የጀነት ሴቶች አለቃ (ወይም የምእመናን ሴቶች ዋና) በመሆንሽ ደስ አይልሽም?' አሉኝ፤ በዚህ ጊዜ ደግሞ ሳቅኩ።'" [ቡኻሪይ፡ 3623፣ 3624] [ሙስሊም፡ 2450]
እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዳላቸው ፋጢመህ አቋቋሟም፣ አቀማመጧም፣ ሁሉ ነገሯ አባቷን መሳይ ነበረች። ትቀጥላለች ዓኢሻህ
وكانت إذا دخَلَت على النبيِّ ﷺ قام إليها فقَبَّلَها وأجلَسَها في مجلِسِه، وكان النبيُّ ﷺ إذا دخل عليها قامت من مجلِسِها فقَبَّلَتْه وأجلَسَتْه في مجلِسِها
"እሷ (ፋጢማ) ወደ ነቢዩ (ﷺ) ዘንድ በገባች ጊዜ እሳቸው ተነስተው ይቀበሏታል፤ ይስሟትም ነበር፤ ከዚያም እሳቸው በተቀመጡበት ቦታ ያስቀምጧታል። እንዲሁም ነቢዩ (ﷺ) ወደ እሷ (ቤት) በገቡ ጊዜ እሷ ከመቀመጫዋ ተነስታ ትቀበላቸዋለች፤ ትስማቸውም ነበር፤ ከዚያም እሷ በተቀመጠችበት ቦታ ታስቀምጣቸዋለች።" [አቡ ዳውድ፡ 5217] [ቲርሚዚይ፡ 3872]
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሸዋል 9/1447)
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
🔖ዳዒያው ሆይ! ለተውሒድ ቦታውን ስጥ!!
~
ጥረትህ ፍሬ ያፈራ ዘንድ ቅድሚያ ለሚሰጠው ቅድሚያ ስጥ። "የደዕዋ አላማው ባሪያዎችን ወደ ተፈጠሩበት ጉዳይ ማድረስ ነው ጌታቸውን ተጋሪ ሳያደርጉለት በብቸኝነት ማምለክ። ወንድሜ ሆይ!
የአላህ ነብይ ኑህ ዐለይሂሰላም ዘጠኝ መቶ ሃምሳ አመት ተውሒድ ሲያስተምሩ አልሰለቹም። አንተ ስንት አመት አስተምረህ ነው የሰለቸህ? ለመሆኑ ምን ብታይ ነው ውስጥህ ለተውሒድ የደፈረሰው? ከማንም በፊት ለራስህ እዘን። "ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ። ያለበለዚያ ድንጋይ ነህ ተብለህ ትወረወራለህ" ይላል ባህሉ። አደራህን ካልተወጣህ አላህ የራሱን ሰው ይተካል። ይልቅ ነገ የውመል ቂያማህ በእሳት ልጓም እንዳትለጎም ፍራ። በዙሪያህ ላሉት እውነቱን ካላወጣህ ነገ አላህ ፊት ሞጋቾችህ ይሆናሉ። መርማሪው፡ ውስጥ አዋቂው፡ ሁሉን መዝጋቢው ጠቢቡና ሃያሉ ጌታ መሆኑን አትዘንጋ።
~እንዲሁ ድፍን አድርገህ "ተውሒድ ጥሩ ነው" "ሺርክ መጥፎ ነው" ብቻ አትበል። ሺርክ የሚበላ ነው የሚጠጣ!? እውነቱን አውጣ። ከትምህርታችን ህዝባችን ሐቁን ካልየ፣ ከአካባቢው እውነታ ጋር እንዲያገናዝብ ካላገዝነው ስለምን እንለፋለን? ማስተማር እንዲህ ቢሆን ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከማን ጋር ይጋጩ ነበር? በአካባቢያችን ያለው ሺርክ ሌላ እኛ የምናወራው ሌላ ከሆነ የማስተማራችን ፋይዳ ምንድነው? ህዝባችን በተለያዩ የሺርክ አይነቶች ላይ ወድቆ ሳለ እኛ የድንጋይና የእንጨት አምልኮት ላይ ብቻ ከተገደብን ማንን ልናነቃ ነው? ስራችንስ ከሽወዳ በምን ተነጥሎ ይታያል? ቁርአኑ እኮ ዘመናት ተሻግሮ የሚያቀና፣ ጥቁር ነጭ ሳይል የሚመራ፣ አፅናፍ አቋርጦ የሚያበራ ድንቅ መለኮታዊ ስጦታ እንጂ ያረጀ ያፈጀ የታሪክ ድርሳን አይደለም።
👉ተዉሂድ የሁለት ሀገር የስኬት ቁልፍ ከሚለው ከኢብኑ ሙነወር መፅሐፍ የተወሰደ
[ገፅ፡ 285] የተወደ
=
t.me/https_AsselfyaRepost from ስለ ስልካችን
💡 አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ
📚 በዚህ ቻናል ላይ አንድን አነስ ያለ ኪታብ እንጀምራለን ኢንሻ አላህ እሱም የሸይኽ አኒስ ኪታብ ነው ።
انتبه أنت مراقب
" ንቃ በአንተ ላይ ተጠባባቂ አለብህ "
📱 ኪታቡ ከስሙ እንደምትረዱት በዚህ ዘመን የተለያዩ ፈተናዎች በበዙበት ስአት በተለይ ከስልካችን ጋ ተያይዞ ያሉ ፈተናዎች ለመቋቋም ወሳኝ መልእክት ይዟል ።
🔖 በሳምንት ሁለት ቀን፣
ሐሙስ እና ቅዳሜ ከምሽቱ⏰ 3:00 ይጀምራል ።
✒ ደርሱ ነገ ይጀምራል ኢንሻ አላህ ።
መልእክቱን ሽር አድርጉ !
https://t.me/SleSlkachin
https://t.me/SleSlkachin
✺ አዲስ ወሳኝ ትምህርት
➖〰➖〰➖〰➖〰
☞ርእስ ፦ በመንሃጅ ላይ ለመፅናት ከሚያግዙን ሰበቦች
« በሸዋል 09/ 1447 ھ በመርከዝ ኢብኑ ከሲር የተደረገ »
🎙 አብዱረሕማን አቡ ዑሠይሚን
⬍⬍⬍⬍⬍⬍⬍⬍⬍⬍⬍
t.me/abuUseyminabdurehman
አላህን በምን አወቅሽ?" አሏት። እኔ ካሰብኩበት ቀርቶ እርሱ ያሰበበት ስውል!" - አለች።
=
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
