ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 411 подписчиков, занимая 5 577 место в категории Религия и духовность и 2 191 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 411 подписчиков.

Согласно последним данным от 11 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 64, а за последние 24 часа — 24, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 24.26%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.47% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 737 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 458 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 23.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 12 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 411
Подписчики
+2424 часа
+237 дней
+6430 день
Архив постов
#የዐርብ_ፎቶ_ስብስብ_፬፤ ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ፤ ስቡሐ ዘተሰብሐ፡፡ /ጸሎተ ሙሴ ፩/ ይባርክዎ ኵሉ ግብረ እግዚእ ፤ ስቡሕኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም፡፡ /መዝ.ሠለ.ደቂቅ ፩/ ንኡስ አነ እምአኃውየ፤ /መዝ.፻፶(፻፶፩)፥፩-፰/ ግነዩ ለእግዚአብሔር እስመ ኄር፤ እስመ ለዓለም ምሕረቱ፡፡ /መዝ.፻፴፭፥፩/ እግዚኦ ኢትጸመመኒ ፤ ለይሁዳ ወልዱ ወለውሉደ ውሉዱ ይደምሰስ፡፡ /መዝ.፻፰፥፩/ ፍካሬ ዘጻድቃን ወዘኃጥአን ፤ ከአንባቢው ጋር ያስተዛዝሉ:: /መዝ.፩፥፩/ (2ቱ ፎቶዎች ከ2008ዓ.ም. ከመዛግብችት ክምትችት ክፍላችን የተወሰዱ ናቸው፡፡/

#የዐርብ_ፎቶ_ስብስብ_፪፤ ዐርብ፤ ኪራያላይሶን ኪራያላይሶን ኪራያላይሶን፡፡ (በቤተ ክርስቲያን ቅጽር ውስጥ)

#የዐርብ_ፎቶ_ስብስብ_፩፤ ኪራያላይሶን ኪራያላይሶን ኪራያላይሶን፡፡ (በቤተ ክርስቲያን ውስጥ) በሥራና በትምህርት ለራቃችሁ፤ የቀጨኔው ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ውል ውል ለሚልባችሁ ይኸው ውሎውን ዘግበንላችኋል፡፡

ሥርዐተ ጸሎት ወስግደት ዘዐርብ ሰሙነ ሕማማት፡፡ እየሰገድን የምንላቸው ቃላት፡፡ እግዘኦ ተሣሃለነ፣ ለከ ኀይል፣ ለአምላክ ይደሉ፣ ኪራያላይሶን ኪራያላይሶን፡፡ …….. ፠፩ኛ ስግደት፤ የወንጌል ምንባብ እንዳበቃ በማስከተል ተግሣጽ ተነቦ እንደተፈጸመ፤ ‹‹ጸልዩ በእንተ ጽንዐ ዛቲ መካን›› የሚለውን ካህኑ ሲመራና ዲያቆኑ በየምዕራፉ ቃጭል ሲደውል፤ ሕዝቡ እየተቀበሉ እግዚኦ ተሣሀለነ (አቤቱ ይቅር በለን) በማለት ፳፪ት ጊዜ በግእዝ፥ በዕዝልና በአራራይ ዜማ እያዜሙ ይሰግዳሉ፡፡ ፠፪ኛ ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት›› የሚለውን ምቅናይ በመሪና በአንሺ ወገን መቀባበል ፲፪ ጊዜ ይበሉ፤ በመጨረሻም በ፲፫ኛው ከ‹‹ለከ ኃይል›› እስከ ‹‹ዕብል በአኰቴት›› ድረስ አንድ ጊዜ በኅብረት ይበሉ፡፡ /ከሆሳዕና ሠርክ እስከ ሰኞ ሰርክ መሪ በቀኝ፤ ተመሪ በግራ ሲሆን፡፡ ከማክሰኞ ሠርክ ጀምሮ ግን መሪ የነበረው ተመሪ፤ ተመሪ የነበረው መሪ ይሆናል፡፡/ #ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤ አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፤ ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤ ኃይልየ ወፀወንየ ውእቱ እግዚእየ፤ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኰቴት፤ አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ፥ ትምጻእ መንግሥትከ፥ ወይኩን ፈቃድከ፥ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር፥ ሲሳየነ ዘለለዕለትነ፥ ሀበነ ዮም፥ ኅድግ ለነ፥ አበሳነ ወጌጋየነ፥ ከመ ንህነኒ ንኅድግ፥ ለዘአበሰ ለነ፥ ኢታብአነ፥ እግዚኦ ውስተ መንሱት፥ አላ አድኅነነ፥ ወባልሐነ፥ እምኵሉ እኩይ፥ እስመ ዚአከ፥ ይእቲ መንግሥት፥ ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም፡ ፠፫ኛ ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹ለአምላክ ይደሉ››ን መጀመሪያ በመሪ እየቀደሙ በአንሺ እየተከተሉ አንድ ጊዜ ይዝለቁ፤ በ፪ኛው ክፍል ደግሞ እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይበሉ፡፡ ለአምላክ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለሥሉስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለማሕየዊ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለዕበዩ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለዕዘዙ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለመንግሥቱ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለሥልጣኑ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለምኵናኑ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለኢየሱስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለክርስቶስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለሕማሙ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለመስቀሉ ይደሉ (ለዐርብ ብቻ)፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡  ቀጥሎ ያለውን የመዝጊያ ጸሎት እያዜሙና እየሰገዱ ፫ት ጊዜ መላልሰው ይዝለቁት፡፡ ለከ ይደሉ ኃይል፥ ወለከ ይደሉ ስብሐት፥ ወለከ ይደሉ አኰቴት፥ ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም፡፡ ፠፬ኛ ስግደት፤ ዜማው አሁንም በቀኝና በግራ በመቀባበል ነው የሚባለው፡፡ በመሪ ወገን እየቀደሙ፤በአንሺ ወገን ደግሞ እየተከተሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፤ ቀጥለውም በመሪና በተመሪ ወገን እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፡፡ መሪ፤ ክርስቶስ አምላክነ፥ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ፥ በሕማማቲሁ ቤዘወነ፤ ተመሪ፤ ንሰብሖ፥ ወናልዕል ስሞ ኅቡረ፥ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በብዝኀ (በዕበየ) ሣህሉ፡፡ /በዐርብ፤ ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ/ #ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ እብኖዲ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ ታኦስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ ማስያስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ ኢየሱስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ ክርስቶስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ አማኑኤል ናይናን/ናይን/፥ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ ትስቡጣ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፡፡  ኪርያላይሶን የሚለውን ብቻ በመሪ ፳፩ ጊዜ፥ በተመሪ ወገን ፳ ጊዜ ይበሉ፤ ድምሩ ፵፩ ኪርያላይሶን ይኾናል፡፡ የየሰዐቱን መልክአ ሕማማት ያድርሱ፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

‹‹ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፤ እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል፡፡›› መዝ. 40፥1 የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት በከተማችን ብሎም በሃገራችን በትንሣኤ በዓል ነዳያንን በማስፈሰክ አገልግሎት ቀዳሚው እንደኾነ ይታወቃል፤ ይህንንም አገልግሎት ለከዛሬ 50 ዓመታት በፊት በ1961ዓ.ም. በአንድ በግ ተጀምሯል፤ ሲጀመርም ነዳያንንና በአካባቢው ያሉ የአቅም ማነስ ያለባቸውን ምዕመናንን ታሳቢ አድርጎ ነው። በ1964ዓ.ም. ደግሞ ወደ 2 በግና አንድ እናት ባመጡት 1 ሌማት እንጀራና 1 ብረት ድስት ወጥ ከፍ አለ፨ እያደረ ወደ በሬ አደገ፨ በየዓመቱ እንደሚደረገው ዘንድሮም ነዳያንን፣ በጸበል ቦታ ያሉትን፣ በገዳም ውስጥ ያሉትን መነኰሳትና የአብነት ተማሪዎች ለማስፈሰክና ለመርዳት የሚያስፈልጉትን (ገንዘብ፣ ልብስ፥ ሳሙና፥ ንጽሕና መጠበቂያ፣ በሬ፥ በግ፥ ፍየል፣ የተማሪዎች የመማሪያ ቊሳቊሶችን) እንድትረዱ በመድኀኔዓለም ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

#ጸሎተ_ሐሙስ_ወሕጽበተ_እግር_ ሐዋርያቲሁ ከበበ፥ እግረ አርዳኢሁ ሐፀበ፤ ኮኖሙ አበ ወእመ፤ ወመሐሮሙ ጥበበ፡፡ (ሐዋርያቱን ሾመ፤ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጠበ፤ አባትና እናት ኾናቸው፤ ጥበብንም አስተማራቸው፡፡) /ሊቁ ቅዱስ ያሬድ፣ ድጓ/