ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 411 подписчиков, занимая 5 577 место в категории Религия и духовность и 2 191 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 411 подписчиков.

Согласно последним данным от 11 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 64, а за последние 24 часа — 24, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 24.26%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.47% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 737 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 458 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 23.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 12 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 411
Подписчики
+2424 часа
+237 дней
+6430 день
Архив постов
#መልክአ_ሕማማት፤ *መልክአ ሕማማት ማለት ስለ ጌታችን መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሕማም፥ መከራ፥ ስቃይ፥ የሚናገር መጽሐፍ ሲሆን፤ ደራሲው ታላቁ ሊቅና የደብረ ባሕርይ ጋሥጫ መምህር #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ_ ነው፡፡ *መልክአ ሕማማት በባለ 3ት መስመር አርኬ የተደረሰ ግጥማዊ ድርሰት ሲሆን፤ የተደረሰውም በ7ቱ የጸሎት ጊዜያት አንጻር በመሆኑ ‹‹#ጸሎት_ዘሰባዐቱ_ጊዜያት›› በሚል መጠሪያም ይጠራል፡፡ የእያንዳንዱ ጊዜ ድርሰትም በዋነኛነት 3ት ክፍሎችን የያዘ ነው፤ እነርሱም፤ 1ኛ) ስብሐተ እግዝእትነ ማርያም /የእመቤታችን ምስጋና/ 2ኛ) ስበሐተ ኢየሱስ ክርስቶስ /የኢየሱስ ክርስቶስ ምስጋና/ 3ኛ) ስብሐተ ሥሉስ ቅዱስ /የሥሉስ ቅዱስ ምስጋና/ **በ7ቱ ጊዜያት ጸሎት ማድረስ እንደሚገባን ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 118 ላይ ‹‹ሰባት ጊዜ በቀን አመሰግንሃለሁ ይላል››፤ አባቶቻችን ሐዋርያትም ይህንኑ ደንግገዋል፡፡ /ዲድስቅልያ 37፣ ቀሌምንጦስ 1ና 7፣ አቡሊዲስ 25ኛና 27ኛ፣ ባስልዮስ 28ኛ አንቀጽ፣ ፍትሐ ነገሥት ገጽ 21/፡፡ ፠ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ መልክአ ሕማማትን ሲደርስም በ7ቱ የጸሎት ጊዜያት የተፈጸሙትን ድጊቶች ከ3ቱ የየጊዜያቱ የድርሰቱ ክፍሎች ምስጋና (የማርያም፣ የጌታ፣ የሥሉስ ቅዱስ ምስጋና) ጋር እያመሠጠረና እያራቀቀ፥ እያስዋበና ምሥጢር እያመጣ፤ እንደ ወርቅ እያንከባለለ፥ እንደ ሸማ እየጠቀለለ፥ በግጥም እያስጌጠ፥ በቃላት እየሰደረ፥ በዜማ እያሸበረቀ፥ መንፈስን እየመሰጠ፤ ነው የደረሰው፡፡ #የ7ቱ_የጸሎት_ጊዜያት_የሚባሉትም፤ ፠1ኛ) መንፈቀ ሌሊት(ሌሊት 6 ሰዐት)፤ ጌታችን የተወለደበት፥ የተጠመቀበት፥ የተነሣበትና ዳግመኛ የሚመጣበት ፥ … ሰዐት ነው፡፡ ፠2ኛ) ነግህ (ማለዳ፥ ጧት)፤ ጨለማን አርቆ ብርሃንን የሚያመጣበት፥ አባታችን ቅዱስ አዳም የተፈጠረበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በጲላጦስ አደባባይ ፊት ቁሞ የተመረመረበት፥ …. ሰዐት ነው፡፡ ፠3ኛ) ሠለስት (ጠዋት ሦስት ሰዐት)፤ እናታችን ሔዋን የተፈጠረችበት፥ ነቢዩ ዳንኤል ጸሎት ያደረሰበት፥ እመቤታችን ከቅዱስ ገብርኤል ብሥራትን ሰምታ የጸነሰችበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ለኛ ሲል በጲላጦስ አደባባይ የተገረፈበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡ ፠4ኛ) ቀትር (6 ሰዐት)፤ አጋንንት የሚሰለጥኑበት ሰዐት ስለሆነ እንዳይሰለጥኑብን፥ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ የሳተበት ስለሆነ እንዳንስት እንጸልያለን፡፡ በተጨማሪም ነቢዩ ሄኖክ ቤተ መቅደስን ያጠነበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ለኛ ሲል በመስቀል ላይ የተሰቀለበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡ ፠5ኛ) ተስዓት (ዘጠኝ ሰዐት)፤ ቅዱስ ጴጥሮስና ዮሐንስ ለጸሎት ወደ ቤተ መቅደስ የወጡበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው የለየበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡ ፠6ኛ) ሠርክ (ዐሥራ አንድ ሰዐት)፤ ነቢዩ ኤልያስ መሥዋዕት የሰዋበት፥ ዕዝራ ጸሎትን ያቀረበበት፥ ሕዝቅያስ ጸልዮ ፀሐይን ወደ ዐሥር ደረጃዎች የመለሰበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ወደ በፈቃዱ ወደ አዲስ መቃብር የወረደበት፥ …… ሰዐት ነው፡፡ ፠7ኛ) ንዋም (የመኝታ ሰዐት)፤ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በጌቴሴማኒ የጸሎትን ሥርዐት ያስተማረበት ፥ እንዲሁም ሌሊቱን በመላእክት ጥበቃ ከርኵሳን አጋንንት እንዲጠብቀን የምንጸለይበት …… ሰዐት ነው፡፡ #ለቡ(ልዩ ማስታወሻ)!! ይህ ታላቅ ጸሎት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስር ባሉ በሁሉም ገዳማትና አድባራት በሰሙነ ሕማማት የሚደርስ ሲሆን፤ በአንዳንድ ትላልቅ ገዳማት (እንደ ዋልድባ፣ ማኅበረ ሥላሴ፣ ደብረ ባሕርይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ወደብረ ጎል አቡነ በጸሎተ ሚካኤል) ያሉ መነኰሳትና መናንያን ግን ከዓመት እስከ ዓመት ጸሎቱን በዜማ /በንባብ/ ያደርሱታል፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

#ሥርዐተ_ጸሎት_ወስግደት_ዘሰሙነ_ሕማማት፡፡ በሰሙነ ሕማማት የሚባሉትን በአጭሩ ስንቃኛቸው፡፡ (ለዐርቡ ጸሎት እንደ ዘማች ስለሚያገለግል) ነገ ከምንለቀው የዐርቡ ጸሎት ጋራ አብራችሁ ተጠቀሙበት፡፡ /ይህን ጽሑድ በአድካሚ ሁኔታ እንደ ንብ ቀስመንና ሰብስበን አዘጋጅተንላችኋል፤ ላልደሰረሰው አዳርሱ፤ ማተሚያ ቤት ያላችሁ አትማችሁ ስጡ፡፡/ ፠የሰሙነ ሕማማት ጸሎት የሚደረገው በ7ቱ የጸሎት ጊዜያት መሠረትነት 7ት ጊዜ ነው፡፡ ለዚሁ አገልግሎት ታላቁ ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በ7ቱ ጊዜያት ከፋፍሎ የደረሰው መልክአ ሕማማትም አብሮ በዜማ ይደርሳል፡፡ ፠ደወልና ቃጭል ይመታል፤ ፠ጸሎታት(ሙሉ ውዳሴ ማርያምና ዳዊት)ና (የኦሪትና የነቢያት) ምንባባት ይደርሳል፤ ፠የተአምር መቅድምና ምንባብ ይነበባል፤ የተአምራት መርገፍ በዜማ ይባላል፡፡ ፠የወንጌል አቡን በቅብብሎሽ ይደርሳል፤ ፠ምስባክ ይሰበካል ፥ ወንጌል ይነበባል፡፡ #1ኛ_ስግደት፤ ‹‹ጸልዩ በእንተ ጽንዐ ዛቲ›› እያለ ቃጭል ሲያሰማ 22ት ጊዜ ‹‹እግዚኦ ተሣሃለነ›› እየተባለ ይሰገዳል፡፡ #2ኛ_ስግደት፤ ‹‹ለከ ኀይል ክብር ወስብሐት›› የሚለውን በቅብብሎሽ 6ት ፥ 6ት ጊዜ (በድምሩ 12)፤ 7ኛውን በኅብረት እየተሰገደ ይባላል፡፡ #3ኛ_ስግደት፤ ‹‹ለአምላክ ይደሉ›› የሚለውን 1ኛውን ዙር በቅብሎሽ፤ 2ኛውን ዙር እያስተዛዘሉ፤ ከስግደት ጋራ ይባላል፡፡ #4ኛ_ስግደት፤ ‹‹ክርስቶስ አምላክነ…›› የሚለውን በመሪና ‹‹ንሰብሖ ..›› ወናልዕል ስሞ የሚለውን በቅብብሎሽ ብለው በዚያው ቀጥለው፤ ‹‹ኪራያላይሶን፥ ኪራያላይሶን፥ ኪራያላይሶን›› የሚለውን በመሪ 21 ጊዜ፤ በተመሪ 20 ጊዜ (በድምሩ 41 ጊዜ) እየተሰገደ ይደርሳል፡፡ ፠የየሰዓቱን (የሌሊት፣ የነግህ፣ የጠዋት 3 ሰዐት፣ የቀትር/6 ሰዐት/፣ የተሰዐት/9ኝ ሰዐት/፣ የሰርክ /11 ሰዐት/፣ የንዋም) መልክአ ሕማማት በዜማ ይደርሳል፡፡ ፠ካህኑ ቡራኬ ሰጥቶ፤ ዲያቆኑ ደግሞ ‹‹ሑር በሰላም›› ብሎ ሕዝቡን ያሰናብታል፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

ይግባኝ ለክርስቶስ ፬ወ ፭፡፡ #በስሪላንካ ያለች ጽዮን ቤተ ክርስቲያንን ባሰብናት፥ ድምጿን በሰማናትና ገጿን ባየናት ጊዜ አለቀስን፤ ቤተ ክርስቲያን ሆይ! ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ፤ ባላስብሽ አንደበቴ ከጕሮሮዬ ጋር ይጣበቅ፡፡ ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/ #ኢሀሎኑ በዝ ስሪላንካ ሰማይ፥ አምላከ አዶናይ፡፡ #በጠራሁህ ቀን ፈጥነህ ስማኝ፤ ምንም በመከራ መካከል ብሄድ አንተ ታድነኛለህ፤ በአሕዛብ ቊጣ ላይ እጆቼን ዘረጋህ፤ ቀኝህም አዳነኝ፤ እግዚአብሔር ይበቀልልኛል፤ አቤቱ ይቅርታህ ለዘለዓለም ነው፡፡ /መዝ. 137/ በስሪላንካ መዲና ኮሎንቦ እሑድ ሚያዝያ 13 የEastern Sunday (የትንሣኤ እሑድን) በዓል በሦስት አብያተ ክርስትያናት በማክበር ላይ በነበሩ የክርስቲያን እምነት ተከታዮች ላይና በሦስት ሆቴሎች በድምሩ ስድስት በደረሰ የቦንብ ጥቃት 137 ሰዎች ማረፋቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገለጸ፡፡ የሟቾች ቊጥር ወደ 300 እነደሚጠጋም እየተነገረ ነው፡፡ ዘጠኝ የሚሆኑት የውጭ ዜጎች ናቸው፡፡ አብዛኞቹም ሕሊናቸው ንጹሕና ብሩሕ የሆነው ሕፃናጽ ናቸው፡፡ ስለ ክርስቶስ መሞት ሕይወት ነው፣ ሰውን መግደል ኀጢአት፤ የኃጢአትም ኀጢአትም ነው፤ ሰውንም በመግደል ጽድቅ የለም፤ አይኖርምም፤ ልብ ያለው ልብ ይበል፤ እንደእርሱ በአምላክ አርአያ የተፈጠረን ሰው ገድሎ እጸድቃለሁ ማለት አላዋቂነትና ስንፍና ነው፤ የሚያጸድቅማ ቢሆን የገደሉ ለምን ሕሊናቸው ይታወካል!!!!!!!?????፡፡ ‹‹ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ!፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ:: ማቴ. 10፥28::

በሰሙነ ሕማማት የሚባሉ የአምላክ ስሞችና ትርጕማቸው፡፡ /ምንጭ፤ ቅዱስ ያሬድ፣ ድጓ/

#የሰሙነ_ሕማማት_ዕለታት_ስያሜዎች †ሰኞ፤ መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ፤ አንጽሖተ ቤተ መቅዳስ የተፈጸመበት ሰኞ:: †ማግሰኞ፤ የጥያቄና የትምህርት ቀን:: †ረቡዕ፤ ምክረ አይሁድ፥ የዕንባ ቀን፥ የመልካም መዓዛ ቀን:: †ሐሙስ፤ ጸሎተ ሐሙስ፥ ሕጽበተ ሐሙስ፥ የምሥጢር ሐሙስ፥ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ፥ የነጻነት ሐሙስ:: †ዐርብ፤ የስቅለት ዐርብ:: †ቅዳሜ፤ ቀዳም ሥዑር (ሹር ቅዳሜ)፤ ለምለሚቱ ቅዳሜ፥ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፥ ሰንበት ዐባይ፥ ቅዱስ ቅዳሜ፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

የ2011 የተፂዕኖ (ሆሳዕና) በዓል በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን፡፡ *ተፂዕኖ ዲበ ዕዋል ኢየሩሳሌም ቦአ ሃገረ /በአህያ ውርንጫ ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ/

የሆሳዕና አከባበር፤ ፎቶ ላይ የምትመለከቱት፤ *በሃገራችን በግንባር ቀደምትነትና በፊታውራሪነት የሆሳዕና በዓል እጅግ በጣም በተለየ ሁኔታ፤ ከዋይዜማው ጀምሮ የሚከበርባት ርዕሰ ገዳማት ወአድባራር አኵሱም ደብረ ጽዮን ማርያም፡፡ *ከአፄ ምኒልክ ዘመን ጀምሮ በአኵሱም ደብረ ጽዮን የሚካሄደውን ሥርዐት ቀድታ በማምጣት ለአዲስ አበባ ዛሬ ለምናየው የሆሳዕና ሥርዐት አብነት የሆነችውና በአዲስ አበባ በደማቅ ሁኔታ የሚከበርባት ርዕሰ አድባራት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ማርያም፡፡ *በአዲስ አበባ ጥንታውያን ከኾኑ አድባራት መካከል የኾነውና የሆሳዕና ሥርዐት በደመቀ ሁኔታ የሚከበርበት ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን፡፡

ሆሣዕና የሰሞነ ሕማማት የመጀመሪያው ቀን ሆሣዕና ይባላል፤ ትርጉሙም ‹‹እባክህ አሁን አድን አንድም መድኃኒት›› ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት ጌታችን የማዳን ሥራውን ወደሚፈጽምባት ወደ ኢየሩሳሌም ገባ፡፡ ቤተ ፋጌ ሲደርስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ልኮ ‹‹ያስፈልጉኛልና የታሠሩትን አህያና ውርንጫ ይዛችሁልኝ ኑ፡፡›› ብሎ ላካቸው፡፡ በምስጢሩም የአዳምን ልጆች ከዲያብሎስ ቁራኝነት ሊፈታ እንደ መጣ ለማጠየቅ ነው፡፡ እነርሱም እንደታዘዙት መጡ፤ ከኢየሩሳሌም እስከ ቤተ መቅደስ 16 ምዕራፍ ሲሆን 14ቱን በእግሩ፣ 2ቱን በአህያ ሄዶ፣ ቤተ መቅደሱን 3 ጊዜ በውርንጫላዋ ከዞረ በኋላ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ፡፡ ቀድሞ በነቢያት ዘመን ጸብዕ (ጥል) በሆነ ጊዜ በፈረስ ተቀምጠው የጦር ዕቃ ይዘው ይታዩ ነበር፤ ዘመነ ሰላም በሆነ ጊዜ ደግሞ በአህያ ተቀምጠው መነሳንስ ይዘው ይታያሉ፤ እርሱም ‹‹ዘመነ ሰላም ይዤላችሁ›› መጣሁ ሲል በአህያ ተቀምጦ መጣ፡፡ (ስለ ሰላምሽ የሚሆነውን አንቺስ ብታውቂ … /ሉቃ. 19፥24/) ፡፡ ነቢዩ ዘካርያስም በትንቢቱ በአህያ እንደሚመጣ ተናግሮ ነበር /ዘካ. 9፥9/፡፡ በግራና በቀኝ የነበሩትም ‹‹እንኳን አንተ የተቀመጥክባትም አህያ መሬት መርገጥ አይገባትም›› እያሉ ግማሹ ልብሱን ግማሹ የዘንባባ ዝንጣፊ አነጠፉለት፡፡ አብርሃም ይስሐቅን፣ ይስሐቅ ደግሞ ያዕቆብን በወለዱ ጊዜ፣ እስራኤል ከግብጽ በወጡ ጊዜ፣ ዮዲት ሆሎፎርኒስን በገደለች ጊዜ ዘንባባ ይዘው አመስግነው ነበር፤ በዚያ ልማድ ጌታችንንም ዘንባባ ይዘው ‹‹ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ሆሣዕና በአርያም›› እያሉ አመሰገኑት፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ በዚያ ይሸጡ ይለውጡ የነበሩትን ‹‹ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፤ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት›› ብሎ በመቆጣት የለዋጮችን ገበታ እየገለበጠ አስወጣቸው፡፡ አይሁድም ሕፃናት ሲያመሰግኑ ሰምተው በቅንአት በታወረ ልቦናቸው ‹‹ዝም አስብላቸው እንጂ›› አሉት፡፡ ጌታችንም ‹‹ከሕፃናትና ከሚጠቡ አፍ ምስጋና ለራስህ አዘጋጀህ›› /መዝ. 8፥2/ የሚለውን የመጽሐፍ ቃል ጠቅሶ አሳፍሯቸዋል፡፡ በሌላም አንቀጽ እነሱ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ሲያመሰግኑ አይተው አፍረዋል፡፡ይህ በዓል ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ዓበይት በዓላት መካከል አንዱ ነው፡፡ ልዩ ማስታወሻ፤ የማኅሌቱን ሥርዐት በበዓታ(በታች ቤት)ና በዐቢየ እግዚእ(በላይ ቤት) አብነት የምትቆሙ አድባራት እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትቆሙበት ዘንድ፤ የሚለያዩባቸውን ዘበዐታና ዘዐቢየ እግዚእ በሚል አስቀምጠንላችኋል፡፡

+*" ሰማዕታተ ኢትዮጵያ "*+ (በዛሬዋ በሚያዝያ 11 ቀን የኢትዮጵያ ሰማዕታት በሊብያ አረፉ፤ ይህም የሆነው በሚያዝያ 11 2007 ዓ.ም. ሲሆን፤ አይሲስ በተባሉ ተንባላት ኢትዮጵያውያኖቹ ክርስትናቸውን እንዲክዱ፤ ማዕተባቸውን እንዲበጥሱ ቢጠይቋቸውም እምቢ በማለታቸው፤ ሓሳባቸውን ለማስቀየር በግፍና በመከራ፤ በውኃ ጥምና በረሃብ ቢቀጧቸውም ልባቸውን ለአምላካቸው ያጸኑ መኾናቸውን ሲረዱ አንገታቸውን በሰይፍ መቷቸው፡፡) አመ ዐሡሩ ወአሚሩ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለት አዕረፉ ሰማዕታተ ኢትዮጵያ:: በረከቶሙ የሃሉ ምስሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡ ከመዝ ኮነ በውስተ ሀገረ ሊብያ በዕሥራ ምዕት ወሰብዐቱ ዐመተ ምሕረት፡፡ በአሜሃ ዘመን ተንሥኡ ተንባላት እለ ስሞሙ አይሲስ በውስተ ሀገረ ኢራቅ ወሶርያ ወሊብያ ወየመን፡፡ አሐዙ ይቅትሉ ሰብአ ዘረከቡ ወፈድፋደሰ እለ ኮኑ ክርስቲያነ በእምነቶሙ፡፡ ብዙሓን ክርስቲያን ተመትሩ አርእስቲሆሙ በአይሲስ ወተወክፉ አክሊለ ስምዕ እምእላ ሀገራት፡፡ በዝ ዘመን ውእቱ ዘረከቦሙ አይሲስ ለሰብአ ኢትዮጵያ በውስተ ሀገረ ሊብያ እንዘ የሐውሩ ኀበ ሀገረ ኢጣልያ በእንተ መፍቅደ ልቦሙ፡፡ እሉ ከሀድያን ውሉደ ሰይጣን ወአራዊተ ገዳም አሐዝዎሙ ወአዘዝዎሙ ወአፍርሕዎሙ ከመ ይክሀዱ ስሞ ለኢሱስ ክርስቶስ፡፡ ወእምዝ ዘበጥዎሙ በዘዚአሁ ዝብጠታተ በእንተ ዘኮኑ ክርስቲያነ ርእዮሙ ማዕተበ ክሣዶሙ፡፡ ውእቶሙሰ አበዩ ይእዜኒ ክሂደ ሃይማኖቶሙ እመኒ አመከርዎሙ በረሐብ ወጽምዕ ወበካልኣን ኵነኔያት፡፡ ሶበ አበዩ ክሂደ ወሰድዎሙ ኀበ ምድረ በድው ኀበ አልቦ እክል ወማይ ከመ ይእመኑ እምጽንዐ ረሐብ ወጽምዕ፡፡ ወእምዝ ጠየቅዎሙ ከመ ይብትኩ ማዕተበ ክሣዶሙ ወይክሀዱ ስሞ ለእግዚአብሔር አምላኮሙ፡፡ እሉሰ ሰማዕታት ይእዜኒ አበዩ ክሂደ ስሞ ለፈጣሪሆሙ፡፡ አዲ ይቤልዎ ለአይሲስ "ኦ አይሲስ ለእመ ክህልከ ቀቲሎታ ለሥጋነ ኢትክል ቀቲሎታ ለነፍስነ፡፡ ኢንፈርሕሂ ወኢንደነግጽ እምብልሐ ሰይፍከ እስመ አቅዲሙ ነገረነ አምላክነ እንዘ ይብል ኢትፍርሕዎሙ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ ወለነፍስክሙሰ ኢይክሉ ቀቲሎታ፡፡" አዲ ይቤለነ በውስተ ወንጌሉ ቅዱስ እስመ ኵሉ ዘከቀተለክሙ ይመስሎ ከመ ዘመሥዋዕተ ያበውእ፡፡ ይእዜኒ አንተ ላእኩ ለዲያብሎስ ፈጽም በላዕሌነ መልእክተከ ሰይጣናዌ ወአብእ መሥዋዕተከ ርኩሰ ለእምላክከ ሰይጣናዊ፡፡ ንህነኒ ናበውእ ክሣደነ ንጹሐ ለእምላክነ ዘፈጠረነ እስመ ነአምር ዘከመ ያነሥአነ በትንሣኤሁ ቅድስት አመ ዳግም ምጽአቱ፡፡ አሲስኒ አላዊ መተሮሙ አርእስቲሆሙ በሰይፍ ወኮኑ ሰማዕተ በከመ ዛቲ ዕለት፡፡ ወእምዝ ተሀውከት ኵላ ኢትዮጵያ ወኵላ ዐለም እስመ ትርእየ ትእይንተ ጥብሐቶሙ ለሰማዕታት በመስኮተ ትእይንት፡፡ ኵሎሙ ሰብአ ኢትዮጵያ አስቆቀዉ ወበከዩ ብካየ መሪረ እንዘ ይገብሩ ሰላማዌ ትእይንተ በበአዕዋዲሁ ወበበፍኖቱ፡፡ ወይብሉ በበቃሎሙ "አይሲስ አይሲስ እንተ ትቀትሎሙ ለሰማዕታት: ወታውሕዝ ደመ ንጹሓን በበፍናዊሁ ከመ ደመ አክልብት: ይደልወከ ትቁም ውስተ ዐውደ ፍትሕ ሰማያዊ፡፡" በዝንቱ ዘመን ቈስለ ልቡ ለህዝብ በሐዘነ ሥጋ እስከነ ይብል "ፍትሐ ጽድቅ ዘዐርገት ውስተ ሰማይ ከመ ትንበር ምስለ ዘፈጠራ እግዚአብሔር እስመ ኢረከበት ውስተ ዛቲ ምድር ኀበ ትነብር ወኀበሂ ታጸልል፡፡ ናሁ ይጸርሕ ደሞሙ ለሰማዕታት ቅድመ ገጹ ለኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይረድ ፍትሐ ርትዕ ዲበ ምድር ወይሠረው አሲስ እምውስተ ገጻ ለምድር፡፡" በረከቶሙ: ወጽንዐ ገድሎሙ ለእሉ ሰማዕታት ይሕድር ላዕሌነ ለዐለመ ዐለም አሜን፡፡ **ሰላም ለክሙ በቃለ ማሕሌት ወእንዚራ፡፡ ምስለ ሰማዕታት ዘግብጽ መከራቲክሙ ዘሐብራ፡፡ ቅዱሳን ሰማዕታት ዘኦርቶዶሳዊት ሐራ፡፡ እፎ ክህልክሙ ተዐግሦ ጽኑዕ መከራ፡፡ እስከ ክሳውዲክሙ በአሲስ ተመትራ፡፡ (በአንድ ስሙን ባልጠቀሰ /ባልታወቀ/ ጸሓፊ የተጻፈ) <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>> ሰማዕታት ከኾኑት መካከል የቂርቆስ ልጆች አብዛኛው ስላሉበት የሚከተለው ግጥም ተገጥሞላቸዋል፡፡ #የቂርቆስ ልጆች የቂርቆስ ልጆች መች ልብ አላቸው፤ ሁሌም ሁከት ነው የለት ሥራቸው፤ ይኸው ዛሬ ደግሞ እንደለመዱት፤ የኢትዮጵያን አንጀት በኀዘን ጎመዱት፡፡ የቂርቆስ ልጆች ያውቃሉ አድማ፤ ሌላው አይሸሽም አንዱ ሲደማ፤ ይኸው ባደባባይ ጎን ለጎን ቆመው፤ ሀገር አሳመሙ እነሱ ታመው፡፡ ድሮም አልወደው እኔ ያንን ሰፈር፤ ሰው እንዴት ይሠራል የሕፃን ነገር፡፡ ሕፃኑን ቂርቆስ እያዩ አድገው፤ አይቅርብን አሉ እሱ ያደረገው፡፡ ይኸው እንደ ቂርቆስ እንደ ኢየሉጣ፤ እነሱም አሉ የመጣው ይምጣ፡፡ አይ የቂርቆስ ልጆች፤ ሕፃኑን ሰምታችሁ እናንተም ትሔዱ? እሱ እንደሆነ ይህ ነው ልማዱ፡፡ እናቱን እንኳን እየጎተተ፤ እንሙት ያለ የወተወተ፤ የሱን ምክር ቃል ስትሰሙ አድጋችሁ፤ ይኼው ይህ ሆነ መጨረሻችሁ፡፡ ሌላ ምን እላለሁ፤!? እግዜር ይይላችሁ፡፡ የፊጥኝ ታስራችሁ መነዳታችሁን፤ ስለ ክርስቶስ ስም መመስከራችሁን፤ በባሕር ዳርቻ መንበርከካችሁን፤ እንደ በግ በስለት መቈረጣችሁን፤ በጥይት እሩምታ መደብደባችሁን፤ እግዜር ይይላችሁ!፡፡ የሕፃኑ መንገድ ያዋጣል ካላችሁ፤ ወደ እኛ እንዳትመጡ ቤት አለን ብላችሁ፤ ሕፃኑ ካለበት ማረፊያ ይስጣችሁ!፡፡ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ፤ ሚያዝያ 13 2007 ዓ.ም.፡፡ እንዲሁም፤ የቂርቆስ ልጆች እነ ሞት አይፈሬ፤ እርግፍ እርግፍ ያሉት እንደ ሾላ ፍሬ፡፡

ስንናፍቀው የነበረው የአንድነት ጕባኤ፤ እንደ መድኀኔ ዓለም ፈቃድ #በዕለተ_ሆሣዕና_ሚያዝያ_13/2011 ዓ.ም.፤ #ከቀኑ 8-11 ሰዐት፤ #በመናገሻ_ገነተ_ጽጌ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሰንበት_ትምህርት_ቤት_አዳራሽ ይካሄዳል፡፡ #የመርሐ ግብሩ አዘጋጆች፤ (የ5ቱ የሰ/ት/ቤቶች የጋራ ጕባኤ) ፠የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤ/ክ ኆኅተ ሰማያት ሰ/ት/ቤት፤ ፠የምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት፤ ፠የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት፤ ፠የደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ፍቊረ እግዚእ ሰ/ት/ቤት፤ ፠የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት፡፡ #የመርሐ ግብሩ አስተባባሪዎች፤ የአራዳና የጉለሌ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት፡፡ /በ5ቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀድሞ አገልጋይ የነበራችሁና የተማራችሁ፤ እንዲሁም አሁን በመማርና በማገልገል ላይ የምትገኙ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡/ #ላልሰሙት_ያሰሙ፡፡#ላልሰሙት_ያሰሙ፡፡ *ወንድሞች በጋራ ቢቀመጡ እነሆ ያማረ ነው፤ እነሆ መልካም ነው፡፡