fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 411 مشترک است و جایگاه 5 577 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 191 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 411 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 11 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 64 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 24 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 24.26% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.47% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 737 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 458 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 23 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 12 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 411
مشترکین
+2424 ساعت
+237 روز
+6430 روز
آرشیو پست ها
#የዐርብ_ፎቶ_ስብስብ_፬፤ ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ፤ ስቡሐ ዘተሰብሐ፡፡ /ጸሎተ ሙሴ ፩/ ይባርክዎ ኵሉ ግብረ እግዚእ ፤ ስቡሕኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም፡፡ /መዝ.ሠለ.ደቂቅ ፩/ ንኡስ አነ እምአኃውየ፤ /መዝ.፻፶(፻፶፩)፥፩-፰/ ግነዩ ለእግዚአብሔር እስመ ኄር፤ እስመ ለዓለም ምሕረቱ፡፡ /መዝ.፻፴፭፥፩/ እግዚኦ ኢትጸመመኒ ፤ ለይሁዳ ወልዱ ወለውሉደ ውሉዱ ይደምሰስ፡፡ /መዝ.፻፰፥፩/ ፍካሬ ዘጻድቃን ወዘኃጥአን ፤ ከአንባቢው ጋር ያስተዛዝሉ:: /መዝ.፩፥፩/ (2ቱ ፎቶዎች ከ2008ዓ.ም. ከመዛግብችት ክምትችት ክፍላችን የተወሰዱ ናቸው፡፡/

#የዐርብ_ፎቶ_ስብስብ_፪፤ ዐርብ፤ ኪራያላይሶን ኪራያላይሶን ኪራያላይሶን፡፡ (በቤተ ክርስቲያን ቅጽር ውስጥ)

#የዐርብ_ፎቶ_ስብስብ_፩፤ ኪራያላይሶን ኪራያላይሶን ኪራያላይሶን፡፡ (በቤተ ክርስቲያን ውስጥ) በሥራና በትምህርት ለራቃችሁ፤ የቀጨኔው ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ውል ውል ለሚልባችሁ ይኸው ውሎውን ዘግበንላችኋል፡፡

ሥርዐተ ጸሎት ወስግደት ዘዐርብ ሰሙነ ሕማማት፡፡ እየሰገድን የምንላቸው ቃላት፡፡ እግዘኦ ተሣሃለነ፣ ለከ ኀይል፣ ለአምላክ ይደሉ፣ ኪራያላይሶን ኪራያላይሶን፡፡ …….. ፠፩ኛ ስግደት፤ የወንጌል ምንባብ እንዳበቃ በማስከተል ተግሣጽ ተነቦ እንደተፈጸመ፤ ‹‹ጸልዩ በእንተ ጽንዐ ዛቲ መካን›› የሚለውን ካህኑ ሲመራና ዲያቆኑ በየምዕራፉ ቃጭል ሲደውል፤ ሕዝቡ እየተቀበሉ እግዚኦ ተሣሀለነ (አቤቱ ይቅር በለን) በማለት ፳፪ት ጊዜ በግእዝ፥ በዕዝልና በአራራይ ዜማ እያዜሙ ይሰግዳሉ፡፡ ፠፪ኛ ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት›› የሚለውን ምቅናይ በመሪና በአንሺ ወገን መቀባበል ፲፪ ጊዜ ይበሉ፤ በመጨረሻም በ፲፫ኛው ከ‹‹ለከ ኃይል›› እስከ ‹‹ዕብል በአኰቴት›› ድረስ አንድ ጊዜ በኅብረት ይበሉ፡፡ /ከሆሳዕና ሠርክ እስከ ሰኞ ሰርክ መሪ በቀኝ፤ ተመሪ በግራ ሲሆን፡፡ ከማክሰኞ ሠርክ ጀምሮ ግን መሪ የነበረው ተመሪ፤ ተመሪ የነበረው መሪ ይሆናል፡፡/ #ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤ አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፤ ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤ ኃይልየ ወፀወንየ ውእቱ እግዚእየ፤ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኰቴት፤ አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ፥ ትምጻእ መንግሥትከ፥ ወይኩን ፈቃድከ፥ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር፥ ሲሳየነ ዘለለዕለትነ፥ ሀበነ ዮም፥ ኅድግ ለነ፥ አበሳነ ወጌጋየነ፥ ከመ ንህነኒ ንኅድግ፥ ለዘአበሰ ለነ፥ ኢታብአነ፥ እግዚኦ ውስተ መንሱት፥ አላ አድኅነነ፥ ወባልሐነ፥ እምኵሉ እኩይ፥ እስመ ዚአከ፥ ይእቲ መንግሥት፥ ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም፡ ፠፫ኛ ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹ለአምላክ ይደሉ››ን መጀመሪያ በመሪ እየቀደሙ በአንሺ እየተከተሉ አንድ ጊዜ ይዝለቁ፤ በ፪ኛው ክፍል ደግሞ እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይበሉ፡፡ ለአምላክ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለሥሉስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለማሕየዊ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለዕበዩ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለዕዘዙ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለመንግሥቱ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለሥልጣኑ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለምኵናኑ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለኢየሱስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለክርስቶስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለሕማሙ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ለመስቀሉ ይደሉ (ለዐርብ ብቻ)፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡  ቀጥሎ ያለውን የመዝጊያ ጸሎት እያዜሙና እየሰገዱ ፫ት ጊዜ መላልሰው ይዝለቁት፡፡ ለከ ይደሉ ኃይል፥ ወለከ ይደሉ ስብሐት፥ ወለከ ይደሉ አኰቴት፥ ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም፡፡ ፠፬ኛ ስግደት፤ ዜማው አሁንም በቀኝና በግራ በመቀባበል ነው የሚባለው፡፡ በመሪ ወገን እየቀደሙ፤በአንሺ ወገን ደግሞ እየተከተሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፤ ቀጥለውም በመሪና በተመሪ ወገን እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፡፡ መሪ፤ ክርስቶስ አምላክነ፥ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ፥ በሕማማቲሁ ቤዘወነ፤ ተመሪ፤ ንሰብሖ፥ ወናልዕል ስሞ ኅቡረ፥ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በብዝኀ (በዕበየ) ሣህሉ፡፡ /በዐርብ፤ ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ/ #ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ እብኖዲ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ ታኦስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ ማስያስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ ኢየሱስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ ክርስቶስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ አማኑኤል ናይናን/ናይን/፥ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ ትስቡጣ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፡፡  ኪርያላይሶን የሚለውን ብቻ በመሪ ፳፩ ጊዜ፥ በተመሪ ወገን ፳ ጊዜ ይበሉ፤ ድምሩ ፵፩ ኪርያላይሶን ይኾናል፡፡ የየሰዐቱን መልክአ ሕማማት ያድርሱ፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

‹‹ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፤ እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል፡፡›› መዝ. 40፥1 የፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት በከተማችን ብሎም በሃገራችን በትንሣኤ በዓል ነዳያንን በማስፈሰክ አገልግሎት ቀዳሚው እንደኾነ ይታወቃል፤ ይህንንም አገልግሎት ለከዛሬ 50 ዓመታት በፊት በ1961ዓ.ም. በአንድ በግ ተጀምሯል፤ ሲጀመርም ነዳያንንና በአካባቢው ያሉ የአቅም ማነስ ያለባቸውን ምዕመናንን ታሳቢ አድርጎ ነው። በ1964ዓ.ም. ደግሞ ወደ 2 በግና አንድ እናት ባመጡት 1 ሌማት እንጀራና 1 ብረት ድስት ወጥ ከፍ አለ፨ እያደረ ወደ በሬ አደገ፨ በየዓመቱ እንደሚደረገው ዘንድሮም ነዳያንን፣ በጸበል ቦታ ያሉትን፣ በገዳም ውስጥ ያሉትን መነኰሳትና የአብነት ተማሪዎች ለማስፈሰክና ለመርዳት የሚያስፈልጉትን (ገንዘብ፣ ልብስ፥ ሳሙና፥ ንጽሕና መጠበቂያ፣ በሬ፥ በግ፥ ፍየል፣ የተማሪዎች የመማሪያ ቊሳቊሶችን) እንድትረዱ በመድኀኔዓለም ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

#ጸሎተ_ሐሙስ_ወሕጽበተ_እግር_ ሐዋርያቲሁ ከበበ፥ እግረ አርዳኢሁ ሐፀበ፤ ኮኖሙ አበ ወእመ፤ ወመሐሮሙ ጥበበ፡፡ (ሐዋርያቱን ሾመ፤ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጠበ፤ አባትና እናት ኾናቸው፤ ጥበብንም አስተማራቸው፡፡) /ሊቁ ቅዱስ ያሬድ፣ ድጓ/