cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Show more
Advertising posts
35 704
Subscribers
No data24 hours
+387 days
+87330 days
Posts Archive
📸⚪️🔥 ሰላም እደሩ 🙏 #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
🥰 10👍 3 3👎 2🤯 1
Photo unavailableShow in Telegram
ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች በራሳቸውን ገንዘብ ለመገበያየት ተስማምተዋል ተባለ! ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ለግብይት የራሳቸውን ገንዘብ ለመጠቀም ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ስምምነቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ብሔራዊ ባንክ ገዢ ካሊድ ሞሃመድ ባላማ መፈረማቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ በዚህም በሁለቱ ሀገራት ለሚደረግ ግብይት የራሳቸውን ገንዘብ ማለትም ድርሃምና ብር ለመጠቀም ከስምምነት የደረሱ ሲሆን ሁለቱ አካላት ለተግባራዊነቱ ምቹ መደላድል ለመፍጠር ጥረት እንደሚያደርጉ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች የኢትዮጵያ አንዷ የንግድ አጋርና የውጪ ኢንቨስትመንት ምንጭ መሆኗን ገልጸው ስምምነቱ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ እንዲጠናከር ያደርገዋል ብለዋል። በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረት ቀጣይነት ያለው ልማትና ብልጽግናን የሚያረጋግጥ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ብሔራዊ ባንክ ገዥ ካሊድ ሞሃመድ ባላማ በበኩላቸው ስምምነቱ ሁለቱ ሀገራት የኢኮኖሚ ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ መምጣታቸውን እንደሚያሳይ አመላክተዋል። #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 35😁 3🔥 1
በቻይና 25 ኪሎ ግራም የምትመዝነው ወጣት አሁንም ክብደቷን ለመቀነስ እየሞከረች መሆኑን አስታወቀች 25 ኪሎ ግራም ብቻ የምትመዝነው ቻይናዊት ወጣት እንስት አስደንጋጭ ገላዋን ኦንላይን ካሳየች እና የበለጠ ከሲታ መሆን እንደምትፈልግ መግልጻን ተከትሎ ከፍተኛ ትኩረትን ስባለች። ቤቢ ቲንዚ በሚል መጠርያ የምትታወቀው ወጣቷ 160 ሴ.ሜ ቁመት ቢኖራትም ወደ 25 ኪሎ ግራም ብቻ ነው ክበደቷ ይመዝናል። አስገራሚው ነገር ግን እንስቷ አሁንም ቢሆን ክብደቷን መቀነስ መፈለጓ ነው። በቻይናው የቲክቶክ ተመሳሳይ ገፅ ዱዪን ላይ ከ42,000 በላይ አድናቂ ተከታዮች ያሏት እንስቷ ተከታዮቻ ስለጤንነቷ ያለማቋረጥ እንደሚጠይቋት ነው መረጃዎች ያሳያሉ። ቤቢ ቲንዚ ሁል ጊዜ እንደዚህ ያሉ ስጋቶችን እንደማያሳስቧት የምትናገር ሲሆን አፅም ብቻ የሚታይበት ምስሏ በህይወቷ ላይ ምንም አይነት አሉታዊ ተፅእኖ እንደሌለው ታክላለች። ከጊዜ ወደ ጊዜ እየመጣ ያለው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪኘት ከቻይና ጓንግዶንግ ግዛት የጓንግዙ ነዋሪዋ እንስት ቀጫጫን ሰውነትዋን ለማሳየት የሚረዱ ልብሶችን ለብሳ የራሷን ቪድዮዎች ያለማቋረጥ ትለጥፋለች። የሰውነት ቅርፅና ቀጫጫነቷን ተከትሎ ለሚሰጧት ትችቶች ግን ግድ የላትም። በአብዛኛዎቹ ቪዲዮዎቿ ላይ ቤቢ ቲንዚ በካሜራ ፊት ትጨፍራለች እንዲሁም ሰውነቷን አጋልጠው የሚያሳዩ ልብሶችን ታዘወትራለች። በዚህም ቀጭን እግሮቿን እና እጆቿን ታሳያለች።ቤቢ ቲንዚ በቻይና ማህበራዊ ሚዲያ እጅግ ብዙ ከታየች በኋላ ብዙዎች አኖሬክሲያ በተባለ ህመም እንደተጠቃችና አስቸኳይ የህክምና እርዳታ እንደሚያስፈልጋት ሲጠቁሟት አንዳንዶች ደግሞ የአፅም ዳንሰኛ በማለት ሲያሾፉባትና ቅፅል ስም ሲሰጧት ተስተውለዋል። ለእንስቷ ከተሰጡ አስተያየቶች መካከል ደግሞ 25 ኪሎ ግራም የሚመዘን ሰው ይኖራል ብሎ መገመት ይከብዳል ግን እውነታ ይህ ነው። እንዲሁም እኔ አንቺ ብሆን አጥንቶቼ እንዳይሰበሩ አይደለም መደነሰ ከመደበኛ እንቅስቃሴም እቆጠብ ነበር ሲሏት ተደምጠዋል። በሚሊዮን ሙሴ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
😁 35👍 11👎 4🤬 3 1
😁 6👍 3🤬 2
በእኔ እና በእናትህ ጸብ ለምን ገባህ በማለት የገዛ ልጁን የገደለው አባት በእስራት ተቀጣ በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ  ካሊድ ሃሰን የተባለው ግለሰብ ትዳር መስርቶ ልጆች  አፍርቶ የሚኖር ሲሆን  ከልጆቹ መሃል  የመጀመሪያ ልጁ የሆነውን መገርሳ  በመግደል ወንጀል በእስራት መቀጣቱ  ፖሊስ  ገልጿል  ። መገርሳ የተባለው ልጅ  ቤተሰቦቹ መካካል  በተደጋጋሚ ግጭት  ይፈጠር የነበረ ሲሆን  የተፈጠረው ግጭት  በሽማግሌዎች እንዲፈታ ያደረጋል  ። ነገር ግን የባል እና ሚስት ግጭት መቆም አልቻለም በመሆኑም እናቱ ግጭት በተፈጠረ ቁጥር ወደ ልጇ ቤት በተደጋጋሚ ትሄድ እንደነበር  እና በዛም ባለቤቷ ቅሬታ እንዳደረባቸው ብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ሰምቷል። አባት ፊት እየሰጠሃት ነው በትንሽ ትልቁ እያኮረፈች ወደ አንተ ቤት የምትመጣው  በሚል ከልጃቸው ጋር ይጋጫሉ ። ሚስት አባት እና ልጅ መጣላታቸውን ሲያውቁ ወደ ህግ በመሄድ ክስ  ይመሰርታሉ ። አቶ ካሊድ ባለቤታቸው እና ልጃቸው እንደከሰሷቸው ሲያውቁ  በንዴት ከሌሊቱ 6 ሰዓት ላይ  ስለታም መጥረቢያ በመያዝ  ወደ ልጃቸው ቤት ሄደው  ልጃቸው በር እንደከፈተላቸው  በመጥረቢያ ጉዳት እንዳደረሱበት የምስራቅ ሀረርጌ ዞን  ከፍተኛ  ፍርድ ቤት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች  ሃላፊ አቶ ሱሌማን ቱጅሃን በተለይ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል ። ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ ወደ ቤታቸው ያመራሉ:: የአካባቢው ነዋሪዎች እና የተጎጂውን ባለቤት ጩኸት በመስማት ወደ ቦታው በማምራት ተጎጂውን የህክምና አገልግሎት እንዲያገኝ  ያደርጋሉ፡፡ ነገር ግን ጭንቅላቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት  ደርሶበት ህይወቱ ሊያልፍ መቻሉ ተረጋግጧል።ፖሊስ ጉዳዩን በማጣራት ተከሳሽ ካሊድ በቁጥጥር  ስር በማዋል ድርጊቱን መፈጸሙን የሚያሳዩ መረጃዎቹን በማሰባሰብ መዝገቡን ለዓቃቢ ህግ ይልካል ።  ዓቃቢ ህግ ጥር 16 ቀን 2016 ዓ.ም ተከሳሽ ካሊድ የገዛ ልጁን በመግደል ከባድ የሰው መግደል ወንጀል ክስ ይመስርታል።የምሰራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት  ጉዳዩን በመመልከት  ሃምሌ 2 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት  ተከሳሽ ካሊድ ሀሰን በ14  ዓመት እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን የምስራቅ ሀረርጌ ዞን  ከፍተኛ  ፍርድ ቤት የኮሙኒኬሽን  ጉዳዮች  ኃላፊ አቶ ሱሌማን ቱጅሃን ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በኤደን ሽመልስ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 25👎 12😢 7 1😁 1
ትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ 14 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደረሰ በሶማሌ ክልል ቀብሪበያህ ወረዳ ጉዮው በተባለ ቦታ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሥድስት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ በተጨማሪም በ14 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱ ተገልጿል፡፡ አደጋው የተከሰተው በሁለት ተሸከርካሪዎች ግጭት መሆኑ ተመላክቷል፡፡ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 5🤔 3😱 1💔 1
Photo unavailableShow in Telegram
እስራኤል በጋዛ የሚገኘዉን ብቸኛ የካንሰር ታማሚዎች ሆስፒታልን የጦር ካምፕ አድርጋዋለች ተባለ እስራኤል በጋዛ ብቸኛዉ የካንሰር ታማሚዎች ሆስፒታል ነዉ የተባለለትን ተቋም የጦር ካምፕ አድርጋዋለች መባሉ ተሰምቷል። ይህ የእስራኤል ድርጊትን ተከትሎም ቱርኪዬ ሆስፒታሉን እስራኤል ለወራት እንደ ወታደራዊ ጣቢያ ተጠቅማበታለች ያለች ሲሆን ፤ ይህም  የጋዛ ብቸኛ ልዩ የካንሰር ሆስፒታል ላይ ጉዳት በማድረሱ የእስራኤልን ጦር በማውገዝ ጥፋተኛ እና ተጠያቂዎቹ "በአለም አቀፍ ፍርድ ቤቶች ለፍርድ እንደሚቀርቡ" ዝታለች ። በተጨማሪነትም እስራኤል በማዕከላዊ ጋዛ ኑሴራት የስደተኞች ካምፕ ላይ ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ 11 ፍልስጤማውያን አምስት ህፃናትን ጨምሮ መሞታቸው ተዘግቧል። ከጥቅምት 7 ጀምሮ በእስራኤል በጋዛ ጦርነት በፍልስጤም በኩል ቢያንስ 38 ሺህ 664 ሰዎች ተገድለዋል የተባለ ሲሆን 89 ሺህ 97 ያህሉ ደግሞ ቆስለዋል ይባላል ። በጥቅምት 7 በሀማስ መሪነት በእስራኤል የሞቱት ሰዎች ቁጥር 1 ሺህ 139 ሆኖ የሚገመት ሲሆን በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም በጋዛ ታግተዉ ይገኛሉ። ሀይ ባይ ያጣዉ የእስራኤል ጦር በዉጊያዉ በጋዛ ላይ ባደረገው ጦርነት ምክንያት የታንክ እና ጥይቶች እጥረት መኖሩን ለእስራኤል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረበው ሪፖርት አመልክቷል። በበረከት ሞገስ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
😢 37👍 9 1🔥 1👏 1💔 1
አዲስ አበባ ከተማ በ2016 በጀት ዓመት ከህዝብ መፀዳጃ ቤቶች አገልግሎት ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘች አዲስ አበባ ከተማ ባለፉት አስራ ሁለት ወራት ከህዝብ መፀዳጃ ቤቶች አገልግሎት ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቷን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አስታውቋል።በቢሮው የተቀናጀ ዘላቂ ማረፊያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አጃይብ ኩምሳ ለብስራት ሬድዬና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት የአዲስ አበባን ፅዳትና ውበት ለማስጠበቅ ባለፉት ጊዜያት የመፀዳጃ ቤቶችን ቁጥር ለመጨመር  በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ ያለው የመፀዳጃ ቤት አገልግሎት እየተሻሻለ በመምጣቱ ባለፉትአስራ ሁለት ወራት ውስጥ የተገልጋዮች ቁጥር ጨምሯል።በዚህም በዘንድሮ በጀት አመት ይህን ያህል ገቢ ማግኘት ተችሏል ሲሉ አቶ አጃይብ ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል ።በ2016 በጀት አመት የተገኘው ገቢ ጥሩ አፈጻጸም የታየበት ነው ሲሉ የተናገሩት አቶ አጃይብ የመፀዳጃ ቤት አገልግሎት በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች ላይ ተደራሽ እንዲሆን በመደረጉ የተገልጋዮች ቁጥር እንዲጨምር አስተዋጾኦ አድርጓል ብለዋል። ይህን ተከትሎ ባለፉት አስራ ሁለት ወራት የተገኘው ገቢ የተሻለ ውጤት የታየበት ነው ሲሉ ዳይሬክተሩ  ተናግረዋል።በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ  ከተማ 3መቶ 58 የሚሆኑ የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች መኖራቸው የተገለፀ ሲሆን የመፀዳጃ ቤት አገልግሎትን የተሻለ ለማድረግ  በ2017 በጀት አመት ተጨማሪ አዳዲስና ዘመናዊ የሆኑ መፀዳጃ ቤቶች እንደሚገነቡ ተጠቅሷል። በቅድስት ደጀኔ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
😁 20👍 13🤔 2
በርናቤዪ የአለማችን የወቅቱ ምርጡ ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ በደመቀ መልኩ በሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎቿ ታጅባ አቀባበል አድርጋለች 🔥 #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 21 4🔥 1
በ2016 ዓመት በመልካም ወጣት መርሀ ግብር ከ30 ሺ በላይ ወጣቶች ይሳተፋሉ ተባለ ለሰባተኛ ጊዜ የሚሰጠው የመልካም ወጣት ስልጠና በ2016 ዓ.ም ከ30 ሺ በላይ ወጣቶች ተመዝግበው ስልጠናው በሀዋሳ ከተማ ሊሰጥ መሆኑን የአዲስ ኪዳን ቤተክርስቲያን የመልካም ወጣት መስራች አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። እንደ አገልጋይ ዮናታን ገለፃ የምንፈልጋትን ኢትዮጵያ ለማግኘት ያላትን ሀይል በመጠቀም ከሀሳብ ወደ ትግበራ መግባት የሚቻለው በወጣቶች በመሆኑ ከተለያዩ ወጣቶች ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ መሆኑን ተናግረዋል።የ2016 ዓ.ም  የመልካም ወጣት ስልጠና መርሃ ግብር የሚካሄደው ከሀምሌ 21እስከ ጳጉሜ 2 ድረስ ነው። እስካሁን በመልካም ወጣት መርሀ ግብር ከ180 ሺህ በላይ ወጣቶች የተሳተፉበት ሲሆን በዘንድሮው የመልካም ወጣት መርሃ ግብር ላይ  ከ30 ሺህ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጪ የሚመጡ ሰልጣኞች ስልጠናውን እንደሚወስዱም ተነግሯል። የመልካም ወጣት ዋንኛ ራዕይ በሁለንተናዊ አቅጣጫ ወጣቶችን የበለጸጉ እንዲሆን ማስቻል፣ማንቃት፣መንገድን በማሳየት ብቁ ማድረግ እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡ በኢትዮጲያ ካለዉ ህዝብ ዉስጥ 70 በመቶ የሚሆነዉ ወጣት እንደመሆኑ በመርሃ ግብሩ በስራ ፈጠራ፣ ከሱስና ሱሰኝነትን መላቀቅ እንዲሁም ወንጀልን ለመከላከል በሚሉ ሀሳቦች ላይ ስልጠና ይሰጣል። ስነልቦናዊ ጫናዎች ማከም ትልቅ ትኩረት የሚያስፈልገው ጉዳይ በመሆኑ በቤተክርስትያን በመንግስት  ይህ አይነቱ መርሃ ግብር መደገፍ እና መበረታት   እንደሚገባው ተጠቁሟል ። በመልካም ወጣት ፕሮጀክቶች በሀዋሳ እና በወላይታ የሚገነቡ የህክምና ተቋማት አሉ ።ወላይታ ላይ ከ500 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ 500 አልጋዎች የሚኖሩት የስነአዕምሮ ማዕከል እየተገነባ ነው። እንዲሁም በሀዋሳ ከተማ በ1ቢሊየን 200ሚሊየን ብር እየተገነባ ያለ የህክምና ተቋም መኖሩን እና በአንድ አመት ውስጥ እነዚህ ፕሮጀክቶች እንደሚጠናቀቁ ተናግረዋል። መልካም ወጣት ስልጠና ላይ ለመካፈል ማንኛውም ፍላጎት ያለው ወጣት መሳተፍ እንደሚችል አገልጋይ ዮናታን ጨምረው ለ ብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል በምህረት ታደሰ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👎 83👍 46😁 24 9🔥 3
👍 5👎 2 1
2 ዴስክቶፕ ኮምፒዩተሮችን ሰርቆ የተገኘው ግለሰብ በ8ዓመት ከ5 ወር እስራት ተቀጣ!! ተከሳሽ ቃቁሽ ከበደ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸመው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ጋዜቦ አደባባይ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ከሚገኝ አንድ ህንፃ ውስጥ ነው። የደምበል አካባቢ ፖሊስ ወንጀል መርማሪ ዋና ሳጅን አበበ ደሳለኝ እንደተናገሩት ተከሳሹ የህንጻው የጥበቃ ሰራተኛ ሲሆን የተሰጠውን ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው ከሚጠብቀው ድርጅት ውስጥ ሁለት ኮምፒውተሮችን ሰርቆ ሲንቀሳቀስ በአካባቢው ስራ ላይ በነበሩ ፖሊሶች እጅ ከፍንጅ ተይዞ ምርመራ ከተጣራበት በኋላ ክስ ተመስርቶበታል። ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት በሰው እና በሰነድ ማስረጃ  የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመ መሆኑን በማረጋገጥ ተከሳሹን ያርማል ሌሎችን የስጠነቅቃል  በማለት በ8 ዓመት ከ5 ወር  እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል። ተቋማት የጥበቃ ሠራተኞችን ሲቀጥሩ ዋስትና ማቅረብ የሚችሉ እና ትክክለኛ አድራሻቸው የሚታወቅ ሊሆን እንደሚገባና ከቀጠሩ በኋላ አስፈላጊውን ቁጥጥርና ክትትል ሊያደርጉ ይገባል ሲሉ  መርማሪው አሳስበዋል። ምንጭ:- አ.አ ፖሊስ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 15👎 5👏 2
ከድሬዳዋ ወደ ሀረር ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አፈጋ የ11 ሰዎች ህይወት አለፈ 👉🏼በሌሎች 10 ሰዎች ላይም ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል በትናንትናው እለት ከሌሊቱ 6 ሰዓት ከ 30 ላይ ሲሆን ከድሬዳዋ ወደ ሀረር 21 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ዶልፊን ተሽከርካሪ 75601 ኢቲ ከሆነ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭቶ የ 11 ሰዎች ህይወት ወዲያዉኑ ማለፉን የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታዉቋል። በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ደሊና ገበሬ ማህበር ቢርካ በተሰኘዉ አካባቢ ነዉ አደጋዉ ሌሊቱን የደረሰዉ። በአደጋዉ ሌሎች 10 ሰዎች ላይም ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የትራፊክ አደጋ ምርመራ ዲቪዥን ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ሰዓዳ መሀመድ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት የአደጋዉ መንስዔ በከባድ ፍጥነት ሲጓዝ የነበረዉ የህዝብ ማመላለሻ ዶልፊን ተሽከርካሪ ከከባድ መኪናዉ ጋር በመጋጨታቸው ነዉ ብለዋል። አደጋዉ በተከሰተበት ወቅትም ከፍተኛ ዝናብ እየጣለ እንደነበርም የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የትራፊክ አደጋ ምርመራ ዲቪዥን ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ሰዓዳ መሀመድ ጨምረዉ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በበረከት ሞገስ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
😱 12👍 10😢 7 1🤔 1
Photo unavailableShow in Telegram
ዶናልድ ትራምፕ መትረፌ ተዓምር እንደሆነ ያከመኝ ዶክተር ነግሮኛል ሲሉ አሳወቁ ከግድያ ሙከራ ያመለጡት የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሙከራው ለሞት የመጣ ቢሆንም “በእርግጥ በህይወት የተገኘ ልምድ” ሲሉ ተናግረዋል።ትራምፕ ለሪፐብሊካን ብሄራዊ ስብሰባ ወደ ሚልዋውኪ ሲያቀኑ ለኒውዮርክ ፖስት እንደተናገሩት “እዚህ መሆን አልነበረብኝም ፣ ሞቼ ነበር” ብለዋል ። ትራምፕ ቀኝ ጆሮአቸዉን የሚሸፍን ነጭ ማሰሪያ አድረገዉ የነበረ ሲሆን ነገርግን ረዳቶቻቸዉ ምንም አይነት ፎቶግራፍ እንዲነሱ ፍቃድ አልሰጡም ሲል ኒዉዮርክ ፖስት ዘግቧል።ትራምፕ አክለው በሆስፒታሉ ውስጥ ያለው ዶክተር እንደዚህ አይነት ነገር አላየሁም ተአምር ነዉ ብሎኛል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ የቀድሞ የኤፍቢአይ ልዩ ወኪል ኬን ግሬይ እንደተናገሩት ጥቃት አድራሹ ይህን ያህል በመቅረብ ጥቃት ማድረስ መቻሉ "በደህንነት ላይ ውድቀት" መኖሩን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል፡ ኤፍቢአይ ለዚህ አይነት ሰልፍ በቂ ነው ወይስ አይደለም በሚለው ላይ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል፡፡ ከዝግጅቱ በፊት የደህንነት ጥበቃ የሚጀምረው ከየት ሊመጡ እንደሚችሉ እና አንድን ሰው ከህዝቡ መካከል እንዴት ነጥሎ ማውጣት እንደሚችሉ የሚያስገነዝብ የዳሰሳ ጥናት እየተደረገ ይገኛል፡፡ጡረተኛው የቀድሞ የኤፍቢአይ ወኪሉ ትራምፕን ከቦታው ለማራቅ ለደህንነት መሥሪያ ቤቱ የፈጀውን “አስፈሪ ረጅም ጊዜ” በመተቸት ሁለተኛ ተኳሽ ቢኖር በድጋሚ በጥይት ሊመቱ ይችል እንደነበር ይጠቁማል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 30😁 7 1
Photo unavailableShow in Telegram
"ሃያ ሄክታሩን አጥረውታል፣ መጋዘኖችንም እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ”--- ቤተክርስቲያኗ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን 40 በመቶ የሚሆን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ‘በጉልበት ሊወስደው ነው' ስትል ከሰሞኑን በተደጋጋሚ መግለጫ መስጠቷ ይታወቃል። ጉዳዩ ከምን ደረሰ ? ቤተ ክርስቲያኗ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠችው ቃል “20 ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችን እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን” ብላለች። “ዛሬ (ሰኞ ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ/ም) ግቢ ውስጥ ገብተው በጉልበት አጥረውታል። መሳሪያ በያዙ ሰዎች እያስጠበቁት ነው ያሉት” ስትል ገልጻለች። ይህንን ያሉት አንድ የቤተ ክርስቲያኗ አካል “እኛም ዛሬ ለጠቅላይ ሚኒስቴሩም፣ ለኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮችም ደብዳቤ እየላክን ነው” ብለዋል። “ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጠዋት ነው የላከነው፣ ለአቶ ሽመልስ አብዲሳም ልከናል። ገና ምንም የሰጡት ምላሽ የለም” ሲሉ አክለዋል። “40 በመቶ ገደማ ይዞታችን ነው ይወሰዳል የተባለው ” ያሉት እኝሁ አካል፣ “አሁን ግማሹን አጥረዋል። ለሁለት ግለሰቦች ነው ይሰጣል የተባለው ” ነው ያሉት። በተጨማሪ ፣ በፍርድ ቤትም እግድ እንዲያወርድላቸው እንደጠየቁ፣ የሚጠብቁት ያስገቡትን ደብዳቤ ምላሽ እየጠበቁ እንደሆነ ገልጸዋል። “አስቸኳይ ምላሽ የማይሰጠን ከሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ወደ መጥራት የምናመራ ይሆናል። በሰላማዊ መንገድ ድምፃችንን እናሰማለን። ሁል ጊዜ ቤተ ክርስቲያን የምትቆመው ከሰላም ጎን ነው። የመረበሽ የማስረበሽ ዓላማ የላትም ” ብለዋል። ቅሬታ የቀረበበት የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም። Via Tikvah #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 41😁 11😢 4💔 3 2🤔 2🔥 1👏 1🤬 1
ከ 12 አመታት በፊት በነበሩ ተማሪዎች ላይ በተሰራ ጥናት 90 በመቶ ያህሉ ኮራጆች ነበሩ ተባለ በኢትዮጵያ የኩረጃ ደረጃ ምን ያህል ነው? ሀገርንስ ምን ያህል ይጎዳል? በሚል በ2004 ጥናት መደረጉን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአካቶ ትምህርት ክፍል ተመራማሪ የሆኑት አለማየሁ ተ/ማሪያም (ዶ/ር) ለኢቢሲ ዘግቧል። ተመራማሪው ፤ በተደረገው ጥናት 90 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ኮራጅ መሆናቸው መረጋገጡን ነው የተናገሩት፡፡ በቀደመው የትምህርት ሥርዓት የመመዘኛ ፈተናዎች የሚሰጡበት ሂደት ለኩረጃ ምቹ እንደነበሩም አስታዉሰዋል፡፡ ተማሪዎች በፈተና ወቅት የማያውቁትን ጥያቄ መልስ ከሌሎች ለመቅዳት ድሮም ይሞክሩ እንደነበር ገልጸው ፤ አሁን ላይ ሥር ሰዶ በዘመቻ መልክ የሚካሄድ ሆኗል ማለታቸዉን ዳጉ ጆርናል ከዘገባው ተመልክቷል። ተማሪዎች ከትምህርቱ በበለጠ የኩረጃ መንገዶችን ያጠናሉ የሚሉት ተመራማሪው ፤ በጥናቱ 27 የሚሆኑ የኩረጃ ዘዴዎች እንዳሉ ደርሰንበታል ብለዋል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ወላጆች ልጆቻቸው እንዲያልፉ ከመፈለግ አንፃር እንዲሁም መምህራን፣ ርዕሰ መምህራን፣ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ጭምር ለኩረጃው እገዛ እንደሚያደርጉ ከሰዋል፡፡ ይህም ፈተናውን አልፈው ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎች የሥብዕና ጉድለት እንደሚታይባቸው እዲሁም መሰረታዊ የሆነው መፃፍ እና ማንበብ ሲቸግራቸው እንመለከታለን ይላሉ፡፡ ተመራማሪው፤ ከፈተና አሰጣጥ በተጨማሪ ለግምት አጋላጭ የሆኑ የፈተና ዓይነቶችን ለማስተካከል መስራት እንደሚገባ አዲሱ የፈተና ሥርዓት ያመላከተ መሆኑንም ይናገራሉ፡፡ በተለይም የተጀመረው የበይነ በረብ (ኦን ላይን) ፈተና አሰጣጥ ሲጠናከር የተንሰራፋውን የኩረጃ መጠን በመቀነስ እና ተማሪዎችን በማብቃት ረገድ ላቅ ያለ ሚና ይኖረዋል ነው ያሉት፡፡ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
😁 62👍 30🔥 4 1
Photo unavailableShow in Telegram
😁 19👍 2👏 1
በአዲስ አበባ ከተማ ከደረጃ በታች ሲያመርቱ የነበሩ ስምንት የፌስታል ምርት አምራቾች ታሸጉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከደረጃ በታች በሚያመርቱ የፕላስቲክ ፋብሪካዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን ገልጿል።በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ  የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሙክታር ሰይድ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ከዚህ በፊት አምራች ድርጅቶቹ በተደረገባቸዉ ክትትል እንዲያስተካክሉ በተለያየ ጊዜ ቢነገራቸዉም ማስተካከል ባለመቻላቸዉ ድርጅቶቹን የማሸግ እርምጃ ተወስዶባቸዋል። በተደረገባቸዉ ክትትልም ከደረጃ በታች የፌስታል ምርቶችን ሲያመርቱ ከተገኙ ስምንት ድርጅቶች  መካከል ኤል.ኤች ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ ኤ.ኤች ስማርት ፕላስቲክ ማምረቻ፣ ኢለኒ ፕላስቲክ ፋብሪካ፣ ሪም ፕላስቲክ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ ኤስ. ኤስ ፕላስቲክ ፋብሪካ፣ ወይንሸት፣ ሳራና ጓደኞቻቸዉ ፕላስቲክ መልሶ መጠቀም ሽርክና ማህበር፣ አግማስ ማኑፋክቸሪንግ እና ዘቢባ ፕላስቲክ ማምረቻ ይገኙበታል። በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ በወጣዉ አዋጅ ቁጥር 513/1999 መሰረት 0.03mm እና ከ0.03 mm በታች የሆኑ ከአፈር ጋር መዋሃድ የማይችሉ የፕላስቲክ ምርቶችን ማምረትም ሆነ ወደ ሀገር ዉስጥ ማስገባት የተከለከለ መሆኑን ያስቀምጣል ሲሉ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተሩ ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል። በዛሬው እለት የተወሰደዉ እርምጃም ይህንኑን መነሻ ያደረገ መሆኑን አያይዘው ገልፀዋል። በቀጣይ ከተቀመጠዉ ደረጃ በታች የሚያመርቱ የፕላስቲክ ማምረቻ ድርጅቶች ላይም እርምጃዉ የሚቀጥል መሆኑን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ገልጿል። በቅድስት ደጀኔ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 32 2
በትራምፕ ላይ ጥቃት የፈፀመው የ20 ዓመቱ ወጣት ሰው አክባሪ እና ጨዋ እንደነበር መምህራኑ ተናገሩ በቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ላይ ተኩሱ ከፍቶ ጥቃት ስላደረሰው የ20 ዓመቱ ቶማስ ማቲው ክሩክስ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን የተለያዩ መረጃዎችን በማውጣት ላይ ይገኛሉ። በቦታው ላይ በጥይት የተገደለው ክሩክስ በትውልድ ከተማው በፔንስልቬንያ አቅራቢያ በሚገኝ የአረጋውያን መንከባከቢያ ማዕከል ውስጥ በኩሽና ረዳትነት የሚሰራ ወጣት ነበር። በ2022 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን አጠናቋል። የእድሜ እኩዮቹ እና አስተማሪዎቹ ሰው አክባሪ፣ ብሩህ አእምሮ ያለው እና ጸጥተኛ ልጅ ነበር ሲሉ ገልፀውታል። የትምህርት ቤቱ አማካሪ ለሮይተርስ እንደተናገሩት ክሩክስ ስለ ፖለቲካ የሚያስብ ሰው ስለመሆኑ በጭራሽ አላውቅም ሲሉ ተደምጠዋል። የዩናይትድ ስቴትስ መገናኛ ብዙሃን ግን በሪፐብሊካን የተመዘገበ የሪፐብሊካን ደጋፊ እንደነበር ዘግበዋል። ለዚህም ማስረጃ ያደረጉት የመራጮች መዝገቦችን በማጣቀስ ነው። ነገር ግን እ.ኤ.አ. በ2021 ለሊበራል ፓርቲ የምርጫ ዘመቻ ቡድን 15 ዶላር መለገሱ ከፋይናንስ ዝውውሩ ላይ መመልከት ተችሏል። ኤፍቢአይ እሁድ እለት እንዳስታወቀው በክሩክስ ማህበራዊ ሚዲያ ገፅ ላይ ምንም አይነት የዛቻ እና የማስፈራሪያ መልዕክት እንዳላገኘ እንዲሁም ምንም አይነት የአእምሮ ጤና ችግር እንዳለበት የሚያሳይ የኋላ ታሪክ አለመኖሩን በምርመራው የደረሰበትን ግኝት አሳውቋል።ትራምፕን ለማጥቃት ጥቅም ላይ የዋለው ሽጉጥ የኤአር ዓይነት 556 ሽጉጥ ነው። በህጋዊ መንገድ በወሌጅ አባቱ የተገዛ መሳሪያ እንደሆነ መርማሪዎች ተናግረዋል። ነገር ግን ይህንን ጥቃት ክሩክስ ብቻውን የፈፀመው ነው። የክሩክስ ወሌጅ አባት ማቲው ክሩክስ ስለ ልጃቸው ከመናገራቸው በፊት "ምን እየተፈጠረ እንደሆነ" ለማወቅ እሞክራለሁ "ከህግ አስከባሪዎች ጋር እስካወራ ድረስ ዝምታን እመርጣለሁ" ብለዋል። በስፍራው ከተገደለ በኋላ ክሩክስ በሰውነቱ ላይ ምንም አይነት መታወቂያ ስላልነበረው የደህንነት ወኪሎች “የዲኤንኤው ምርመ እና የባዮሜትሪክ ማረጋገጫ ማግኘት ነበረባቸው” ሲል የኤፍቢአይ ፒትስበርግ የመስክ ጽህፈት ቤት ልዩ ወኪል ኬቨን ሮጄክ አስቀድሞ ተናግረው ነበር።ዶናልድ ትራምፕ ከቅዳሜው የግድያ ሙከራ ከተረፉ በኃላ በዚህ ሳምንት እየተካሄደ በሚገኘው የሪፐብሊካኑ ስብሰባ ላይ አገሪቷን "አንድ እንደሚያደርጓት" ተናግረዋል። ዶናልድ ትራምፕ ለሪፐብሊካን ብሄራዊ ጉባኤ ዊስኮንሲን ገብተዋል። ቅዳሜ ምሽት በፔንስልቬንያ በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ላይ የተኩስ ልውውጥ ቢኖርም የሚልዋውኪ የፓርቲው ኮንፈረንስ አስቀድሞ በታቀደው መሰረት እየተካሄደ ይገኛል። ትራምፕ ጉዟቸውን ለሁለት ቀናት ለማዘግየት አስበው እንደነበር በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ገልፀው ነበር፣ “ነገር ግን የነፍሰ ገዳዩ ጥቃት የመርሐግብር ለውጥ ሊያስከትል እንደማይችል ለማሳየት ወስኛለሁ ብለዋል። በትራምፕ ላይ የተፈጸመው ጥቃት ሰኞ በጀመረው የዝግጅቱ ደህንነት ላይ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶታል። በህዳር ወር ከሚካሄደው አጠቃላይ ምርጫ በፊት ፓርቲው እጩዎቹን ለመራጮች በይፋ ሲያቀርብ 50,000 ያህል ሰዎች በአራት ቀናቱ ጉባኤ ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በዶናልድ ትራምፕ ላይ ከተካሄደው የግድያ ሙከራ በኋላ “የፖለቲካው ግለቱ” እንዲቀንስ ጥሪ አቅርበዋል ። ፖለቲካ በፍፁም የውጊያ አውድማ መሆን የለበትም፣ ፈጣሪ የግድያ ሜዳ ይከለክላል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። በቅዳሜው የድጋፍ ሰልፍ ላይ ትራምፕ በጆሮዋቸው ላይ በጥይት ከተመቱ በኃላ ጥቃቱን ተከትሎ አሜሪካውያን “በአንድነት እንዲቆሙ” ጠይቀዋል።ባይደን ሀገሪቱ ወዴት እያመራች እንደሆነ እና ማን ይመራታል በሚለው ላይ አለመግባባት ቢኖርም ፖለቲካ "የሰላማዊ የውይይት መድረክ" መሆን እንዳለበት ደጋግመው አሳስበዋል።የእኛ እምነት የቱንም ያህል ጠንካራ ቢሆን ወደ ሁከት መግባት የለብንም ሲሉ አክለዋል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 44😁 18👎 2 2🤔 1
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.