en
Feedback
ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

Open in Telegram

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

Channel ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal (@zena24now) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 42 066 subscribers, ranking 6 115 in the News & Media category and 775 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 42 066 subscribers.

According to the latest data from 09 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -325 over the last 30 days and by -6 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 15.21%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 12.42% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 6 399 views. Within the first day, a publication typically gains 5 225 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 37.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

42 066
Subscribers
-624 hours
-797 days
-32530 days
Posts Archive
ፈረንሳይ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች። በቦስተን ጁሌት ስታዲየም በተደረገው የሁለቱ
ፈረንሳይ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች። በቦስተን ጁሌት ስታዲየም በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የፈረንሳይን ግቦች ኪሊያን ምባፔ እና ኦስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል። ፈረንሳይ በሦስት ተከታታይ የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ላይ የፍጻሜ ተፋላሚ ለመሆን በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትገናኛለች፡፡

ነፍሰ-ጡር ሴትን ጨምራ ሿሿ ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 9ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 1:40 በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ
+4
ነፍሰ-ጡር ሴትን ጨምራ ሿሿ ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 9ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 1:40 በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ሪቼ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው። የግል ተበዳይ ከአጎና ወደ እስታዲየም ለመሄድ በማሰብ ኮድ 3-83620 ኦሮ ነጭ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በማስቆም ትገባለች። ተጠርጣሪዎችም የግለሰቧን ወደ ተሽከርካሪው መግባት ተከትለው በማዋከብ እና ትኩረቷን በማሳጣት ይዛው ከነበረው ቦርሳ ውስጥ 32 ሺ ብር ግምት ያለው ሳምሰንግ ስልክ ሰርቀው ጥለዋት ይሄዳሉ። ይህን የተመለከቱ የትራፊክ ፖሊሶች ተሽከርካሪውን በማስቆም እና ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋል ስራ ሰርተዋል። ተጠርጣሪዎቹ ከተያዙ በኋላ በተሽከርካሪው ውስጥ በተደረገ ፍተሻ 7 ስልኮች መገኘታቸውን የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አስታውቋል። ከተጠርጣሪዎቹ መካከል ነፍሰ ጡር መኖሯ የተገለጸ ሲሆን የቀን ውሎ አበል በመክፈል እና ተሽከርካሪ በመከራየት ወንጀሉን የሚፈፅሙ ግለሰቦች እንዳሉ ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ትራንስፖርት ሲጠቀም ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። ምንጭ:- አአ ፖሊስ #ዳጉ_ጆርናል

ቦኖ የምባፔን ፍፁም ቅጣት ምት ሲያድን 🚫
ቦኖ የምባፔን ፍፁም ቅጣት ምት ሲያድን 🚫

በአማራ ክልል ሶስት አዳሪ ትምህርት ቤቶች በቀጣዩ ዓመት ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር ይጀምራሉ በአማራ ክልል የትምህርት ጥራትን በከፍተኛ ደረጃ ሊያሳድጉ የሚችሉ የአዳሪ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እየ
በአማራ ክልል  ሶስት አዳሪ ትምህርት ቤቶች በቀጣዩ ዓመት ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር ይጀምራሉ   በአማራ ክልል የትምህርት ጥራትን በከፍተኛ ደረጃ ሊያሳድጉ የሚችሉ የአዳሪ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ እንደሚገኝ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።በፍኖተ ሰላም፣ ደብረ ታቦርና ሰቆጣ ከተሞች እየተገነቡ ያሉ የአዳሪ ትምህርት ቤቶች በ2019 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር እንደሚጀምሩ ቢሮው ገልጿል፡፡   የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ  እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ፈታኝ ችግሮች የነበሩ ቢሆንም የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማሳደግ አበረታች ስኬቶች ተመዝግበዋል። የአዳሪ ትምህርት ቤቶችን ግንባታ ለማጠናከር ከፍተኛ የድጋፍና የክትትል ስራዎች መከናወናቸውን የገለጹት ኃላፊው የሰቆጣ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ 78 በመቶ፣ የደብረ ታቦር 88 ነጥብ 75 በመቶ፣ የፍኖተ ሰላም አዳሪ ትምህርት ቤት የግንባታ ስራ ደግሞ 62 በመቶ መድረሱን ጠቁመዋል።   ትምህርት ቤቶቹ በ2019 ዓ.ም ተማሪዎችን ተቀብለው ለማስተማር በሚያስችል ደረጃ ላይ ይገኛሉ ያሉት ኃላፊው በቀጣይ ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ የተቀናጀ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል። #ዳጉ_ጆርናል

በሀረሪ ክልል በተደረገ ፍተሻ ግምታዊ ዋጋቸው 2 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የፕላስቲክ ከረጢት በቁጥጥር ስር ዋሉ በክልሉ የፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ እና የኘላስቲክ ክልከላ አዋጅ አተገባበር ዘመቻ እና የቁ
በሀረሪ ክልል በተደረገ ፍተሻ ግምታዊ ዋጋቸው 2 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የፕላስቲክ ከረጢት በቁጥጥር ስር ዋሉ   በክልሉ የፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ እና የኘላስቲክ ክልከላ አዋጅ አተገባበር ዘመቻ እና የቁጥጥር ስራ መከናወኑን የሀረሪ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።ሌሊት ላይ የባለስልጣኑ ሰራተኞች ባደረጉት ድንገተኛ የክትትልና የቁጥጥር ስራ በሸዋበር የገበያ አካባቢ አዋጁን በመተላለፍ ለንግድ ቤቶች ሊከፋፈል የነበረ 64 ኩንታል ወይም  2 ሚሊዮን ብር የሚገመት የፕላስቲክ  ከረጢቶች  ለህብረተሰቡ ከመድረሳቸው በፊት መያዛቸውን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ነቢላ መህዲ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።   በክልሉ የፕላስቲክ ክልከላ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 ን በመጣስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን መጠቀም ባላቆሙ የንግድ ቤቶች እንዲሁም አከፉፉዮች ላይ ባለስልጣኑ የሚያደርገው ቁጥጥር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።ህጉን ተላልፈው በሚገኙ አካላት ላይም አስተዳደራዊ እርምጃ ይወስዳል ሲሉ ዳይሬክተራ ነቢላ ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል::   ህብረተሰቡ የፕላስቲክ ፌስታሎችን ብክለት ተረድቶ ከመጠቀም እና ከመሸጥ እንዲቆጠብ ኃላፊዋ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።   በትግስት ላቀው #ዳጉ_ጆርናል

በማህበራዊ ሚዲያ በህክምና ባለሙያዎች የሚለቀቁ ማስታወቂያዎች አሳስቦኛል ሲል የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አስታወቀ   ያለፈቃድ የሕክምና መሣሪያዎችንም ሆነ መድኃኒቶችን በሚያስተዋውቁ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ባለሥልጣኑ አስታውቋል።የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበራ ደመቀ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት በጤና ባለሙያዎች የሚደረግ የማስተዋወቅ ተግባር ሊከናወን የሚችለው በባለሥልጣኑ ዕውቅና በተሰጠው አካል ብቻ ነው።   ይህም በባለስልጣኑ መድኃኒት እና መሳሪዎችን ለማስተዳደር በወጣ መመሪያ ይደነግጋል።ሆኖም አሁን ላይ የጤና ባለሙያዎችም ይሁኑ በዘርፉ ባልተሰማሩ ሰዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ላይ የህክምና መሳሪያዎችን እና መድኃኒቶችን እያስተዋወቁ መሆናቸው ስጋት እንደሆነበት ተቋሙ ገልጿል።ለጉዳዮ መፍትሄ ለማምጣት  ከመገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ጋር እየተነጋገረ ይገኛል።   የህክምና መሳሪያን እንዲያስተዋውቁ ለጤና ባለሙያዎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የገንዘብ፣ የዓይነት ወይም ሌላ ተመሳሳይ ጥቅማጥቅም መስጠት በሕግ እንደሚያስቀጣ አቶ አበራ ተናግረዋል።በርካታ አካላት የማስተዋወቂያ ቁሳቁሶቻቸውን አስገምግመው ፈቃድ ሳያገኙ በማኅበራዊ ሚዲያዎች  ላይ የሕክምና መሣሪያዎችን እያስተዋወቁ መሆናቸውን ባለሥልጣኑ ደርሼበታለሁ ብሏል።በተጨማሪም በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ እየተላለፉ ያሉ የተወሰኑ የሕክምና መሣሪያዎች በሕግ ጨርሶ ሊተዋወቁ እንደማይገባቸው  ተናግሯል።   እንደ አቶ አበራ ማብራሪያ  ለተወሰኑ አድራሻቸው ለታወቁት የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ መፃፉን ነግረውናል።ማንኛውንም ያለፈቃድ የተለቀቀ የሕክምና መሣሪያ ማስታወቂያ ከማኅበራዊ ሚዲያዎችም ሆነ ከመደበኛ ብዙኃን መገናኛዎች በአስቸኳይ እንዲያነሱ አሳስበዋል።በመሆኑም ማንኛውም የማስተዋወቅ ስራ ሊከናወን የሚችለው ከባለሥልጣኑ ይፋዊ የፈቃድ ደብዳቤ ሲገኝና መመሪያዎቹን በጥብቅ በመከተል ብቻ ነው ተብሏል።ይህንን መመሪያ በማይከተሉ ግለሰቦችም ሆነ ድርጅቶች ላይ ባለሥልጣኑ ጥብቅ ሕጋዊ እርምጃ ይወስዳል ሲሉ አክለዋል፡፡   በትግስት ላቀው #ዳጉ_ጆርናል

photo content
+1

በአሜሪካ በተፈፀሙ የሁለት ምሽት ጥቃቶች 14 ሰዎች መገደላቸዉን ኢራን አስታወቀች የኢራን የጤና ሚኒስቴር በዚህ የቅርብ ጊዜ የጦርነት ዙር 14 ሰዎች መሞታቸውን አስታውቋል።እሮብ እና ሀሙስ በኢራን
በአሜሪካ በተፈፀሙ የሁለት ምሽት ጥቃቶች 14 ሰዎች መገደላቸዉን ኢራን አስታወቀች   የኢራን የጤና ሚኒስቴር በዚህ የቅርብ ጊዜ የጦርነት ዙር 14 ሰዎች መሞታቸውን አስታውቋል።እሮብ እና ሀሙስ በኢራን ውስጥ በአምስት ግዛቶች ላይ ያነጣጠሩ የአሜሪካ ጥቃቶች 78 ሰዎች መቁሰላቸውን የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሆሴይን ኬርማንፑር ተናግረዋል።   ከቆሰሉት መካከል 47 ሰዎች በሆስፒታል ውስጥ እንዳሉ አክለዋል።ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በኢራን ደቡባዊ ክፍል የሚገኘው የኢራንሻህር ግዛት ገዥ ለመንግስት ሚዲያዎች እንደተናገሩት አንድ ሰው በአውሮፕላን ማረፊያ ህንጻ ላይ በተፈጸመ ጥቃት መሞቱን ተናግረዋል።   ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ "በድጋሚ በኃይልን እንመታቸዋለን" በማለት ከተናገሩ በኋላ፤ የአሜሪካ ጦር ኢራን ላይ አዲስ ዙር ጥቃት ከፈተ።የሆርሙዝ ወሽመጥ የወደብ ከተሞች የሆኑትን ሲሪክን እና ባንደር አባስን ጨምሮ በአገሪቱ ደቡባዊ ክፍሎች ፍንዳታ መከሰቱን የኢራን መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።   ትራምፕ ከአዲሱ ጥቃት በኋላ በትሩዝ ሶሻል ማኅበራዊ ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፤ “ይህ በኢራን ለተፈጸመው የመርከቦች ድብደባ የተወሰደ የአጸፋ እርምጃ ነው። በድጋሚ ከተፈጠረ፤ ከዚህም የባሰ ይሆናል” ብለዋል።ከአሜሪካ እርምጃ በኋላ የባህረ ሰላጤው አገራት በኢራን ጥቃት እንደተፈጸመባቸው አስታውቀዋል። በባህሬን ዋና ከተማ መናማ ፍንዳታዎች መከሰታቸው የተገለጸ ሲሆን ኩዌት ሚሳዔሎችን እና ድሮኖችን ማክሸፏን አስታውቃለች። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል

ያንጎ ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ አዲሱን የ”ትራንስፖርት” አገልግሎቱን ይፋ አደረገ በያንጎ መተግበሪያ የተካተተው አዲሱ ”ትራንስፖርት” የተሰኘ አገልግሎት፣ የአውቶቡስ መስመሮችን እና የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር መረጃዎችን በአንድ ቦታ በማቅረብ በአዲስ አበባ ውስጥ ያለውን የትራንስፖርት አገልግሎት የበለጠ ቀላልና ምቹ ያደርጋል ተብሏል። በያንጎ ጉዞ መተግበሪያ ውስጥ የተካተተው ይህ አዲስ አገልግሎት፣ ተገልጋዮች የሕዝብ መጓጓዣ መስመሮችን እና የጉዞ መርሐ ግብሮችን በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ያስችላቸዋል። አገልግሎቱ የአውቶቡስ መስመሮችን እና የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር መረጃዎችን በማካተት፣ የከተማዋ ነዋሪዎችም ሆኑ ጎብኚዎች በአዲስ አበባ ውስጥ ጉዟቸውን በቀላሉ፣ በፍጥነት እና በምቾት እንዲያቅዱና እንዲያከናውኑ ያግዛል። በ”ትራንስፖርት” አገልግሎት፣ ተገልጋዮች የሕዝብ መጓጓዣን በመጠቀም የሚያደርጓቸውን ጉዞዎች በቀጥታ በያንጎ መተግበሪያ ማቀድ ይችላሉ፤ እንዲሁም በመስመሩ ዝርዝር፣ በተገመተው የጉዞ ጊዜ፣ በማቆሚያዎች እና በመቀየሪያ ነጥቦች መሰረት ያላቸውን የጉዞ አማራጭ ማነጻጸር ይችላሉ። አገልግሎቱን ለመጠቀም፣ ተገልጋዮች በያንጎ መተግበሪያ ዋና ገጽ ላይ ትራንስፖርት (Transport) የሚለውን በመምረጥ መዳረሻቸውን ማስገባት ይኖርባቸዋል። ከዚያም መተግበሪያው ተዛማጅ የሕዝብ መጓጓዣ አማራጮችን በአንድ ማሳያ ላይ በማቅረብ፣ ተገልጋዮች በከተማው ውስጥ የሚጓዙበትን መንገድ በተሻለ ሁኔታ እንዲረዱና ለጉዟቸው ተስማሚ የሆነውን መስመር እንዲመርጡ ያግዛል። ያንጎም የመስመርና የጉዞ መርሐ ግብር መረጃዎችን በአንድ ቦታ በማቅረብ፣ የሕዝብ መጓጓዣን ለዕለት ተዕለት ተጓዦችም ሆነ ብዙም ወደማያውቋቸው የከተማዋ ክፍሎች ለሚጓዙ ሰዎች ተደራሽ ለማድረግ እና ለአጠቃቀም ቀላል ለማድረግ በማለም ስራውን መጀመሩን ብስራት ሰምቷል። የያንጎ የኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ የሆኑት ዶ/ር ይቅናዓለም አበበ በመግለጫው ላይ ያንጎ፣ ቴክኖሎጂ በከተሞች ውስጥ የሰዎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የበለጠ ቀላልና ምቹ ማድረግ እንዳለበት ያምናል። የአውቶቡስ መስመሮችንና የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር መረጃዎችን በያንጎ መተግበሪያ ውስጥ በአንድ ቦታ በማሰባሰብ፣ ተገልጋዮቻችን በየዕለቱ በከተማዋ ውስጥ ለሚያደርጓቸው ጉዞዎች የሚያግዛቸውን ተግባራዊ መሳሪያ አቅርበናል። ዓላማችንም ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሰዎች በከተማዋ ውስጥ በቀላሉ እንዲንቀሳቀሱ፣ ጊዜ እንዲቆጥቡ እና የሚያስፈልጓቸውን አገልግሎቶች በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ማስቻል ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ሰላማዊ ነጋሲ #ዳጉ_ጆርናል

photo content
+1

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቦላ ቫይረስ ስርጭት የቀጠለ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 600 መድረሱ ተዘገበ በሀገሪቱ የጤና ባለሥልጣናት በኩል በወጣው መረጃ መሠረት፣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የተከሰተ
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቦላ ቫይረስ ስርጭት የቀጠለ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 600 መድረሱ ተዘገበ   በሀገሪቱ የጤና ባለሥልጣናት በኩል በወጣው መረጃ መሠረት፣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የተከሰተው የኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ የሟቾች ቁጥር 600 ደርሷል።የጤና ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያሳየው የቫይረሱ ስርጭት ሲቀጥል የተረጋገጡ የተጠቂዎች ቁጥር 1,759 ደርሷል።የቡንዲቡግዮ ቫይረስ ዝርያ ወረርሽኙ በኢቱሪ፣ በሰሜን ኪቩ እና በደቡብ ኪቩ በሚገኙ 37 የጤና ዞኖች ውስጥ ተሰታጭቷል፡፡   ወደ 750 የሚጠጉ ሰዎች ከቫይረሱ አገግመዋል፣ 285 ታካሚዎች ደግሞ በጽኑ የህክምና እንክብካቤ ስር ይገኛሉ፡፡የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የአፍሪካ ክልላዊ ጽሕፈት ቤት እንዳስታወቀው ወረርሽኙ እየጨመረ የመጣው የማህበረሰብ ሞት እና ቀደም ሲል ባልተጎዱ የጤና ዞኖች ውስጥ ኢንፌክሽኖች በመስፋፋታቸው ነው።   ኢቱሪ ወረርሽኙ ከግንቦት 15 ጀምሮ ከታወጀበት ጊዜ አንስቶ ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑ የቫይረሱ ተጠቂዎች እና ከ84 በመቶ በላይ ሞት ተመዝግቧል፡፡ከሐምሌ 5 ጀምሮ ከተመረመሩት 430 የተረጋገጠ ሞት መካከል 400 የሚሆኑት ታካሚዎች ወደ ህክምና ተቋም ከመሄዳቸው በፊት በበሽታዉ ተይዘዉ ነበር፣ ይህም በቫይረሱ ምርመራ፣ በሪፈራል፣ በለይቶ ህክምና እና በክሊኒካዊ እንክብካቤ ተደራሽነት ላይ መዘግየት መኖሩን አጉልቶ ያሳያል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል

በካፋ ዞን ያረስኩትን አተር ለምን ነቀልክ በማለት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ድዲፋ ቀበሌ በከባድ የሰው መግደል ወንጀል የ
በካፋ ዞን ያረስኩትን አተር  ለምን ነቀልክ በማለት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ   በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ድዲፋ ቀበሌ በከባድ የሰው መግደል ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱ ተገልጿል።የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ  አብርሃም አበቶ ይባላል።   ተከሳሹ "በራሴ ይዞታ ላይ ያረስኩትን አተር ለምን አልፈህ ነቀልክ" በሚል በተፈጠረ ፀብ ተበዳይን  አንገቱን  በስለት ይቆርጠዋል፡፡ተበዳይ  መሬት ላይ በወደቀበት ወቅትም በቀኝ በኩል ጭንቅላቱን፣ አውራ ጣቱን፣ መዳፋን እና የተለያዩ የሰውነት ክፍሉን ደጋግሞ በስለት በመቆራረጥ ከባድ ጉዳት ያደረሰበት ሲሆን ወደ ደካ ከተማ አስተዳደር ጤና ጣቢያ በመሄድ ላይ እንዳለ ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል፡፡   የወረዳው ፖሊስ ወንጀሉን በአጭር ጊዜ አጣርቶ ለካፋ ዞን ዓቃቤ ሕግ ያስተላለፈ ሲሆን፣ የዞኑ ዓቃቤ ሕግ መዝገቡን መርምሮ ተከሳሹ በፈጸመው ድርጊት ክስ መስርቶ ለዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቧል።ፍርድ ቤቱም የቀረበለትን የክስ መዝገብ ከተመለከተ በኋላ ተከሳሽን በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ ማስተላለፉን ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ ጨምረው ተናግረዋል፡፡   በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል

በደቡብ ቻይና ኃይለኛ አውሎ ንፋስ ባስከተለዉ የጎርፍ አደጋ የ39 ሰዎች ህይወት አለፈ በደቡባዊ ቻይና የተከሰተው ኃይለኛ አውሎ ንፋስ ሜይሳክ 39 ሰዎችን ህይወት ነጥቋል፡፡ የጎርፍ አደጋዉ ያጋጠመዉ
በደቡብ ቻይና ኃይለኛ አውሎ ንፋስ ባስከተለዉ የጎርፍ አደጋ የ39 ሰዎች ህይወት አለፈ   በደቡባዊ ቻይና የተከሰተው ኃይለኛ አውሎ ንፋስ ሜይሳክ 39 ሰዎችን ህይወት ነጥቋል፡፡ የጎርፍ አደጋዉ ያጋጠመዉ የዉሃ ግድቡ በናኒንግ ከተማ መዉደሙን ተከተሎ በጎርፍ ከተጥለቀለቀ በኋላ ነው።የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ዲንግ ዌይ ሐሙስ ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የሟቾችን ቁጥር ይፋ አድርገዋል፤ ይህም ቀደም ሲል ከተገለጸዉ ስድስት ሰዎች ቁጥር በእጅጉ ጨምሯል፡፡   ከፍተኛ የሆነ ዝናብ በጓንግክሲ ክልል በሚገኙ ከተሞች ከፍተኛ የውሃ ማዕበል አስከትሏል።በናኒንግ የሚገኘው የግድብ ጥፋት 26 ሰዎችን ገድሏል ሲሉ ዲንግ ተናግረዋል።ከክልሉ ወደ 130,000 የሚጠጉ ሰዎች ተፈናቅለዋል፣በውሃ ውስጥ ለተያዙ ሰዎች ለመድረስ ድሮኖች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ጀልባዎች የነፍስ አድን ስራዉ ቀጥሏል፡፡   በደቡብ ጓንግዢ ለቀናት ከባድ ዝናብ ተከስቶ ነበር፣ በአንዳንድ አካባቢዎች ከ10 እስከ 40 ሴ.ሜ እና ከባድ ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች ከ90 ሴ.ሜ በላይ ዝናብ እንደጣለ ብሔራዊ የሜትሮሎጂ ማዕከል አስታውቋል። በነፍስ አድን ስራው ከ8,000 በላይ ሰዎች እና ወደ 5,700 የሚጠጉ ጀልባዎች ተሰማርተዋል፣ ዲንግ የጎርፍ ውሃው እየቀነሰ መሆኑን ተናግረዋል፣ ነገር ግን በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ በተወሰኑ አካባቢዎች ተጨማሪ ዝናብ እንደሚኖር ይጠበቃል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል

ለራሱ ምርቃት የተገዛው በሬ ወግቶት ህይወቱ ያለፈው ተመራቂ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈጸመ በቅርቡ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ኢንጅነሪንግ ዘርፍ በታላቅ ስኬት ተመርቆ፣ ለነገው ህይወቱ ትልቅ ተ
ለራሱ ምርቃት የተገዛው በሬ ወግቶት ህይወቱ ያለፈው ተመራቂ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈጸመ በቅርቡ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ኢንጅነሪንግ ዘርፍ በታላቅ ስኬት ተመርቆ፣ ለነገው ህይወቱ ትልቅ ተስፋ ሰንቆ የነበረው ፍሰሐ አስማማው እጅግ ልብ በሚሰብር አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ይህ ተስፋ የተጣለበት ወጣት ከሳምንት በፊት ነበር የምርቃት ካባውን የደረበው። ወላጆችና ዘመድ አዝማድም የምርቃቱን ደስታ አብረውት ለማሳለፍ ከጎንደር ጋይንት (ጎብጎብ) ከተማ ወደ ተወለደበት አካባቢ ይዘውት አምርተው ነበር። ነገር ግን በትላንትናው ዕለት ለምርቃቱ ድግስ ተብሎ የተገዛው በሬ በድንገት ወግቶት ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል። የዚህ ወጣት ስኬትና ህልም በአጭር የተቀጨበት አሳዛኝ የቀብር ስነ-ስርዓት ዛሬ በጋይንት ጎብጎብ ቀራኒዮ መድሃኒዓለም ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ፣ የክፍል ጓደኞቹና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት ተፈፅሟል። ለወላጆቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለጓደኞቹ በሙሉ ፈጣሪ ፍጹም መፅናናትን ይስጥልን። Via ጉርሻ Page #ዳጉ_ጆርናል

ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ የ2018 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ሻምፒዮን ሆነ ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ፍፃሜ ባገኘው የ2018 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ፍፃሜ ጨዋታ ወልዋሎ ኢዲግራት ዩንቨርስቲ የፕሪሚየ
ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ የ2018 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ሻምፒዮን ሆነ ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ፍፃሜ ባገኘው የ2018 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ፍፃሜ ጨዋታ ወልዋሎ ኢዲግራት ዩንቨርስቲ የፕሪሚየር ሊጉን ሻምፒዮን ሲዳማ ቡናን 2 ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የጥሎ ማለፉ ሻምፒዮን መሆን ችሏል። ወልዋሎ የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫን ሲያነሳ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የመጀመሪያው የትግራይ ክለብም ሆኗል። #ዳጉ_ጆርናል

በሮቤ ከተማ የጤና ባለሙያዉን በደቦ በመደብደብ የአካል ጉዳት ያደረሱ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ በሮቤ ከተማ አስተዳደር አዶሼ ክፍለ ከተማ ሮቤ የተሽከርካሪ መናሕርያ ውስጥ አንድን የጤና ባለሞያ በደቦ
በሮቤ ከተማ የጤና ባለሙያዉን በደቦ በመደብደብ የአካል ጉዳት ያደረሱ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ   በሮቤ ከተማ አስተዳደር አዶሼ ክፍለ ከተማ ሮቤ የተሽከርካሪ መናሕርያ ውስጥ አንድን የጤና ባለሞያ በደቦ የደበደቡ ወጣቶች በእስራት ተቀጡ።እንደ ሮቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምርያ የኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ሐላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ጌታቸው ታምሩ ገለፃ 1ኛ ሱልጣን ሑሴን ፣ 2ኛ ኢብራሔም ሑሴን እና 3ኛ ቦንሣ አወሉ የተባሉ ተከሳሾች የአንደኛ ተከሣሽ የእጅ ስልክ ጠፋ በሚል ሠበብ በአንድ የጤና ባለሞያ ላይ በደቦ ከፍተኛ ድብደባ በማድረስ የአካል ጉዳት አድርሰዋል።   ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓም ከጥዋቱ አንድ ሠዓት ተኩል ላይ አሮጌው መናሕርያ ውስጥ የጊኒር ከተማ ጤና ፅህፈት ቤት የጤና ባለሞያ የሆኑትን ዋቆ ከድር የተባሉትን የአንደኛ ተከሣሽ ሞባይል በመጥፋቱ ወስደኃል በሚል ያልተረጋገጠ ማስረጃ በቡድን ተደራጅተው የድብደባ ወንጀል ፈፅመውባቸዋል።ባልተጣራና ባልተረጋገጠ ጉዳይ በመቀናጀት የፈፀሙት የድብደባ ወንጀል በማሕበራዊ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ ቁጣ ማስከተሉ ይታወሳል፡፡   ፖሊስም በወቅቱ ሁኔታውን ተከታትሎ የድርጊቱ ፈፃሚ ወጣቶችን በቁጥጥር ስር በማዋል የምርመራ መዝገቡን በተለያዩ ማስረጃዎች በማጣራት መዝገቡን ለአቃቢ ሕግ ልኳል፡፡ አቃቢ ሕግም ከፖሊስ የቀረበውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በውንብድና ወንጀል ክስ መስርቷል፡፡ ክሱን የተመለከተው የሮቤ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓም በዋለው ችሎት እያንዳንዳቸዉን በሁለት ዓመት ከሶስት ወራት  እስራት እንዲቀጡ የወሠነባቸው መሆኑ ምክትል ኢንስፔክተር ታምሩ ጌታቸው ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡   በመባ ወርቅነህ #ዳጉ_ጆርናል

በካፋ ዞን ያረስኩትን አተር ለምን ነቀልክ በማለት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ድዲፋ ቀበሌ በከባድ የሰው መግደል ወንጀል የ
በካፋ ዞን ያረስኩትን አተር  ለምን ነቀልክ በማለት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ   በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ድዲፋ ቀበሌ በከባድ የሰው መግደል ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱ ተገልጿል።የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ  አብርሃም አበቶ ይባላል።   ተከሳሹ "በራሴ ይዞታ ላይ ያረስኩትን አተር ለምን አልፈህ ነቀልክ" በሚል በተፈጠረ ፀብ ተበዳይን  አንገቱን  በስለት ይቆርጠዋል፡፡ተበዳይ  መሬት ላይ በወደቀበት ወቅትም በቀኝ በኩል ጭንቅላቱን፣ አውራ ጣቱን፣ መዳፋን እና የተለያዩ የሰውነት ክፍሉን ደጋግሞ በስለት በመቆራረጥ ከባድ ጉዳት ያደረሰበት ሲሆን ወደ ደካ ከተማ አስተዳደር ጤና ጣቢያ በመሄድ ላይ እንዳለ ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል፡፡   የወረዳው ፖሊስ ወንጀሉን በአጭር ጊዜ አጣርቶ ለካፋ ዞን ዓቃቤ ሕግ ያስተላለፈ ሲሆን፣ የዞኑ ዓቃቤ ሕግ መዝገቡን መርምሮ ተከሳሹ በፈጸመው ድርጊት ክስ መስርቶ ለዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቧል።ፍርድ ቤቱም የቀረበለትን የክስ መዝገብ ከተመለከተ በኋላ ተከሳሽን በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ ማስተላለፉን ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ ጨምረው ተናግረዋል፡፡   በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል

የሆርሙዝ የትራፊክ እንቅስቃሴ ከኢራን እና አሜሪካ ጥቃት በኋላ ተቋረጠ ዩናይትድ ስቴትስ ለሁለተኛ ተከታታይ ቀን ኢራንን ካጠቃች በኋላ በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በኩል የሚደረገው የመርከብ ጭነት እንቅ
የሆርሙዝ የትራፊክ እንቅስቃሴ ከኢራን እና አሜሪካ ጥቃት በኋላ ተቋረጠ   ዩናይትድ ስቴትስ ለሁለተኛ ተከታታይ ቀን ኢራንን ካጠቃች በኋላ በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በኩል የሚደረገው የመርከብ ጭነት እንቅስቃሴ ቆሟል በሚባል ደረጃ ቀነሰ።በወሳኙ የውሃ መስመር ላይ የሚደረገው እንቅስቃሴ አሁን በአብዛኛው በኢራን በተፈቀደው ሰሜናዊ መንገድ ላይ ብቻ የተወሰነ ሲሆን በኦማን እና በአሜሪካ የሚደገፍ ኮሪደር ደግሞ ብዙም እንቅስቃሴ አላሳየም።   ከባህር ወሽመጥ የሚወጣ አንድ የአሜሪካ ፈቃድ ያለው ሱፐርታንከር መርከብ እና የኢራን ባንዲራ የተሸከመ የኮንቴይነር መርከብ ብቻ የባህር ወሽመጥን ሲያቋርጡ ታይተዋል ሲል ብሉምበርግ ኒውስ ዘግቧል፡፡ ይህ ከቅርብ ጊዜ የእንቅስቃሴ ደረጃዎች በእጅጉ ቀንሷል።   ሆርሙዝን ለመክፈት የአሜሪካ-ኢራን ጊዜያዊ ስምምነት ከተደረገ በኋላ ባሉት ሶስት ሳምንታት ውስጥ፣ አማካይ የዕለት ተዕለት የሸቀጥ መርከቦች መተላለፊያዎች 34 የነበሩ ሲሆን ሰኔ 24 ላይ 59 ደርሷል ሲል የክፕለር መረጃ ያሳያል።በአብዛኛዎቹ ቀናት በጦርነት ጊዜ የሚደረጉ የዕለታዊ የሚሻገሩ መርከቦች ቁጥር ከ20 በታች መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል

በኢትዮጵያ የሚገኙ በርካታ ሆስፒታሎች የኢንሱሊን ማስቀመጫ ፍሪጅ እጥረት እንዳለባቸው ተነገረ ​የኢትዮጵያ ስኳር ህመም ማህበር በኢትዮጵያ የሚገኙ ሆስፒታሎችን የኢንሱሊን መድኃኒት ማከማቻ እጥረት ለመቅረፍ እና መድኃኒቱን በቀዝቃዛ ሙቀት ለማስቀመጥ የሚያስችሉ ዘመናዊ የፋርማሲዩቲካል ፍሪጆችን እያሰራጨ መሆኑን አስታውቋል ።የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ኤርሚያስ ገብረማርያም ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ማህበሩ ከስድስት ወራት በፊት 15 ተመሳሳይ ፍሪጆችን ለሆስፒታሎች አሰራጭቷል።በአሁኑ ወቅት ላይ ተጨማሪ 65 ፍሪጆችን በማስመጣት በአጠቃላይ ለ80 ሆስፒታሎች የሚደርስ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።   የኢንሱሊን መድኃኒት ውጤታማነትን ለመጠበቅ ከ2 እስከ 8 ዲግሪ ሴልሺየስ ባለ የሙቀት መጠን መቀመጥ እንዳለበት የተገለፀ ሲሆን አዲሶቹ ፍሪጆች ይህንን ችግር ሙሉ ለሙሉ ይቀርፋሉ ተብሏል። አዲስ ከገቡት 65 ፍሪጆች መካከል 35ቱ ፍሪጆች 1 ሺህ 30 ሊትር መያዝ የሚችሉ ባለ ሁለት በር ሲሆኑ ከፍተኛ የታካሚ ቁጥር ለሚያስተናግዱ ትላልቅ ሆስፒታሎች ይሰራጫሉ። 30ዎቹ ፍሪጆች ደግሞ 490 ሊትር መያዝ የሚችሉ ባለ አንድ በር ፍሪጆች ናቸው።ሁሉም ፍሪጆች ከኃይል መቆራረጥና መዛባት ለመጠበቅ ከዩፒኤስ እና ከኤሌክትሪክ መከላከያ ብሬከር ጋር ተሟልተው የሚቀርቡ መሆናቸው ተገልጿል። ማህበሩ እነዚህን የህክምና ቁሳቁሶች ያለምንም እንግልት ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ላደረጉት ለመድኃኒት ምግብ ቁጥጥር ባለስልጣን፣ ለገንዘብ ሚኒስቴር ፣ ለጤና ሚኒስቴር ፣ ለጉምሩክ ኮሚሽን እና ለኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ምስጋናውን አቅርቧል። ማህበሩ ዕድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ለሆኑ ሕፃናትና ወጣቶች የስኳር ህመም ታካሚዎች ልዩ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም ብስራት ሬዲዮ ከዚህ ቀደም መዘገቡ ይታወሳል። በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል