en
Feedback
ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

Open in Telegram

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

Channel ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal (@zena24now) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 42 067 subscribers, ranking 6 127 in the News & Media category and 775 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 42 067 subscribers.

According to the latest data from 08 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -337 over the last 30 days and by -31 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 15.18%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 12.43% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 6 385 views. Within the first day, a publication typically gains 5 228 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 37.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

42 067
Subscribers
-3124 hours
-777 days
-33730 days
Posts Archive
ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ የ2018 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ሻምፒዮን ሆነ ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ፍፃሜ ባገኘው የ2018 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ፍፃሜ ጨዋታ ወልዋሎ ኢዲግራት ዩንቨርስቲ የፕሪሚየ
ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ የ2018 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ሻምፒዮን ሆነ ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ፍፃሜ ባገኘው የ2018 የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ፍፃሜ ጨዋታ ወልዋሎ ኢዲግራት ዩንቨርስቲ የፕሪሚየር ሊጉን ሻምፒዮን ሲዳማ ቡናን 2 ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የጥሎ ማለፉ ሻምፒዮን መሆን ችሏል። ወልዋሎ የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫን ሲያነሳ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የመጀመሪያው የትግራይ ክለብም ሆኗል። #ዳጉ_ጆርናል

በሮቤ ከተማ የጤና ባለሙያዉን በደቦ በመደብደብ የአካል ጉዳት ያደረሱ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ በሮቤ ከተማ አስተዳደር አዶሼ ክፍለ ከተማ ሮቤ የተሽከርካሪ መናሕርያ ውስጥ አንድን የጤና ባለሞያ በደቦ
በሮቤ ከተማ የጤና ባለሙያዉን በደቦ በመደብደብ የአካል ጉዳት ያደረሱ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ   በሮቤ ከተማ አስተዳደር አዶሼ ክፍለ ከተማ ሮቤ የተሽከርካሪ መናሕርያ ውስጥ አንድን የጤና ባለሞያ በደቦ የደበደቡ ወጣቶች በእስራት ተቀጡ።እንደ ሮቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምርያ የኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ሐላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ጌታቸው ታምሩ ገለፃ 1ኛ ሱልጣን ሑሴን ፣ 2ኛ ኢብራሔም ሑሴን እና 3ኛ ቦንሣ አወሉ የተባሉ ተከሳሾች የአንደኛ ተከሣሽ የእጅ ስልክ ጠፋ በሚል ሠበብ በአንድ የጤና ባለሞያ ላይ በደቦ ከፍተኛ ድብደባ በማድረስ የአካል ጉዳት አድርሰዋል።   ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓም ከጥዋቱ አንድ ሠዓት ተኩል ላይ አሮጌው መናሕርያ ውስጥ የጊኒር ከተማ ጤና ፅህፈት ቤት የጤና ባለሞያ የሆኑትን ዋቆ ከድር የተባሉትን የአንደኛ ተከሣሽ ሞባይል በመጥፋቱ ወስደኃል በሚል ያልተረጋገጠ ማስረጃ በቡድን ተደራጅተው የድብደባ ወንጀል ፈፅመውባቸዋል።ባልተጣራና ባልተረጋገጠ ጉዳይ በመቀናጀት የፈፀሙት የድብደባ ወንጀል በማሕበራዊ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ ቁጣ ማስከተሉ ይታወሳል፡፡   ፖሊስም በወቅቱ ሁኔታውን ተከታትሎ የድርጊቱ ፈፃሚ ወጣቶችን በቁጥጥር ስር በማዋል የምርመራ መዝገቡን በተለያዩ ማስረጃዎች በማጣራት መዝገቡን ለአቃቢ ሕግ ልኳል፡፡ አቃቢ ሕግም ከፖሊስ የቀረበውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በውንብድና ወንጀል ክስ መስርቷል፡፡ ክሱን የተመለከተው የሮቤ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓም በዋለው ችሎት እያንዳንዳቸዉን በሁለት ዓመት ከሶስት ወራት  እስራት እንዲቀጡ የወሠነባቸው መሆኑ ምክትል ኢንስፔክተር ታምሩ ጌታቸው ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡   በመባ ወርቅነህ #ዳጉ_ጆርናል

በካፋ ዞን ያረስኩትን አተር ለምን ነቀልክ በማለት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ድዲፋ ቀበሌ በከባድ የሰው መግደል ወንጀል የ
በካፋ ዞን ያረስኩትን አተር  ለምን ነቀልክ በማለት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ   በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በካፋ ዞን ጌሻ ወረዳ ድዲፋ ቀበሌ በከባድ የሰው መግደል ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱ ተገልጿል።የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ  አብርሃም አበቶ ይባላል።   ተከሳሹ "በራሴ ይዞታ ላይ ያረስኩትን አተር ለምን አልፈህ ነቀልክ" በሚል በተፈጠረ ፀብ ተበዳይን  አንገቱን  በስለት ይቆርጠዋል፡፡ተበዳይ  መሬት ላይ በወደቀበት ወቅትም በቀኝ በኩል ጭንቅላቱን፣ አውራ ጣቱን፣ መዳፋን እና የተለያዩ የሰውነት ክፍሉን ደጋግሞ በስለት በመቆራረጥ ከባድ ጉዳት ያደረሰበት ሲሆን ወደ ደካ ከተማ አስተዳደር ጤና ጣቢያ በመሄድ ላይ እንዳለ ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል፡፡   የወረዳው ፖሊስ ወንጀሉን በአጭር ጊዜ አጣርቶ ለካፋ ዞን ዓቃቤ ሕግ ያስተላለፈ ሲሆን፣ የዞኑ ዓቃቤ ሕግ መዝገቡን መርምሮ ተከሳሹ በፈጸመው ድርጊት ክስ መስርቶ ለዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቧል።ፍርድ ቤቱም የቀረበለትን የክስ መዝገብ ከተመለከተ በኋላ ተከሳሽን በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ ማስተላለፉን ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ ጨምረው ተናግረዋል፡፡   በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል

የሆርሙዝ የትራፊክ እንቅስቃሴ ከኢራን እና አሜሪካ ጥቃት በኋላ ተቋረጠ ዩናይትድ ስቴትስ ለሁለተኛ ተከታታይ ቀን ኢራንን ካጠቃች በኋላ በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በኩል የሚደረገው የመርከብ ጭነት እንቅ
የሆርሙዝ የትራፊክ እንቅስቃሴ ከኢራን እና አሜሪካ ጥቃት በኋላ ተቋረጠ   ዩናይትድ ስቴትስ ለሁለተኛ ተከታታይ ቀን ኢራንን ካጠቃች በኋላ በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በኩል የሚደረገው የመርከብ ጭነት እንቅስቃሴ ቆሟል በሚባል ደረጃ ቀነሰ።በወሳኙ የውሃ መስመር ላይ የሚደረገው እንቅስቃሴ አሁን በአብዛኛው በኢራን በተፈቀደው ሰሜናዊ መንገድ ላይ ብቻ የተወሰነ ሲሆን በኦማን እና በአሜሪካ የሚደገፍ ኮሪደር ደግሞ ብዙም እንቅስቃሴ አላሳየም።   ከባህር ወሽመጥ የሚወጣ አንድ የአሜሪካ ፈቃድ ያለው ሱፐርታንከር መርከብ እና የኢራን ባንዲራ የተሸከመ የኮንቴይነር መርከብ ብቻ የባህር ወሽመጥን ሲያቋርጡ ታይተዋል ሲል ብሉምበርግ ኒውስ ዘግቧል፡፡ ይህ ከቅርብ ጊዜ የእንቅስቃሴ ደረጃዎች በእጅጉ ቀንሷል።   ሆርሙዝን ለመክፈት የአሜሪካ-ኢራን ጊዜያዊ ስምምነት ከተደረገ በኋላ ባሉት ሶስት ሳምንታት ውስጥ፣ አማካይ የዕለት ተዕለት የሸቀጥ መርከቦች መተላለፊያዎች 34 የነበሩ ሲሆን ሰኔ 24 ላይ 59 ደርሷል ሲል የክፕለር መረጃ ያሳያል።በአብዛኛዎቹ ቀናት በጦርነት ጊዜ የሚደረጉ የዕለታዊ የሚሻገሩ መርከቦች ቁጥር ከ20 በታች መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል

በኢትዮጵያ የሚገኙ በርካታ ሆስፒታሎች የኢንሱሊን ማስቀመጫ ፍሪጅ እጥረት እንዳለባቸው ተነገረ ​የኢትዮጵያ ስኳር ህመም ማህበር በኢትዮጵያ የሚገኙ ሆስፒታሎችን የኢንሱሊን መድኃኒት ማከማቻ እጥረት ለመቅረፍ እና መድኃኒቱን በቀዝቃዛ ሙቀት ለማስቀመጥ የሚያስችሉ ዘመናዊ የፋርማሲዩቲካል ፍሪጆችን እያሰራጨ መሆኑን አስታውቋል ።የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ኤርሚያስ ገብረማርያም ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ማህበሩ ከስድስት ወራት በፊት 15 ተመሳሳይ ፍሪጆችን ለሆስፒታሎች አሰራጭቷል።በአሁኑ ወቅት ላይ ተጨማሪ 65 ፍሪጆችን በማስመጣት በአጠቃላይ ለ80 ሆስፒታሎች የሚደርስ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።   የኢንሱሊን መድኃኒት ውጤታማነትን ለመጠበቅ ከ2 እስከ 8 ዲግሪ ሴልሺየስ ባለ የሙቀት መጠን መቀመጥ እንዳለበት የተገለፀ ሲሆን አዲሶቹ ፍሪጆች ይህንን ችግር ሙሉ ለሙሉ ይቀርፋሉ ተብሏል። አዲስ ከገቡት 65 ፍሪጆች መካከል 35ቱ ፍሪጆች 1 ሺህ 30 ሊትር መያዝ የሚችሉ ባለ ሁለት በር ሲሆኑ ከፍተኛ የታካሚ ቁጥር ለሚያስተናግዱ ትላልቅ ሆስፒታሎች ይሰራጫሉ። 30ዎቹ ፍሪጆች ደግሞ 490 ሊትር መያዝ የሚችሉ ባለ አንድ በር ፍሪጆች ናቸው።ሁሉም ፍሪጆች ከኃይል መቆራረጥና መዛባት ለመጠበቅ ከዩፒኤስ እና ከኤሌክትሪክ መከላከያ ብሬከር ጋር ተሟልተው የሚቀርቡ መሆናቸው ተገልጿል። ማህበሩ እነዚህን የህክምና ቁሳቁሶች ያለምንም እንግልት ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ላደረጉት ለመድኃኒት ምግብ ቁጥጥር ባለስልጣን፣ ለገንዘብ ሚኒስቴር ፣ ለጤና ሚኒስቴር ፣ ለጉምሩክ ኮሚሽን እና ለኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ምስጋናውን አቅርቧል። ማህበሩ ዕድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ለሆኑ ሕፃናትና ወጣቶች የስኳር ህመም ታካሚዎች ልዩ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም ብስራት ሬዲዮ ከዚህ ቀደም መዘገቡ ይታወሳል። በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል

በኢትዮጵያ 42 በመቶ የሚሆነው የእናቶች ሞት የሚከሰተው በወሊድ ወቅት በሚከሰት የደም መፍሰስ ነው ተባለ   በዓለም አቀፍ ደረጃ  ለእናቶች ሞት ቀዳሚ ምክንያት የሆነው በወሊድ ወቅት የሚከሰት የደም መፍሰስ  ሲሆን የደም ግፊት በሽታም ሌላኛው መንስኤ ነዉ፡፡ የደም ግፊት  በሽታ ህፃናት ያለ እድሜያቸው እንዲወለዱ የሚያደርግ  ሲሆን  ይህንን ለመቆጣጠር  የእርግዝና ክትትልን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የእናቶች ጤና ፕሮግራም አስተባባሪ ሲስተር ዘምዘም መሃመድ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።   ሲስተር ዘምዘም አክለውም በኢትዮጵያ  42 በመቶ የሚሆነው የእናቶች ህይወት የሚያልፈው በወሊድ ወቅት በሚከሰት የደም መፍሰስ ነው  ሲሉ ጠቅሰዋል። እንዲሁም ለእናቶች ሞት 18 በመቶ የሚሆነውን ድርሻ የሚይዘው  የደም ግፊት ነዉ። የቅድመ እርግዝና ጤና እንደ ሀገር ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑ ተመላክቷል።አንዲት እናት ከፍተኛ ራስ ምታት ፣ ድብልቅልቅ ያለ የቀለም  እይታ ፣ ከፍተኛ የሆነ የእጅ እና የፊት እብጠት ፣ የመተንፈስ ችግር  የሚያጋጥማት ከሆነ ራስን  መሳት ሊያስከትል ይችላል።   በመሆኑም የቀጠሮ ቀኗ ባይደርስም በፍጥነት የህክምና ክትትል ማድረግ እንዳለባት  ሲስተር ዘምዘም መሃመድ  አስገንዝበዋል።በአሁኑ ወቅት በርካታ እናቶች ለደም ግፊት ተጋላጭ እንደሚሆኑ የተጠቆመ ሲሆን ከጊዜያት በኋላ  ደም ግፊትን ጨምሮ  እንደ ስኳር ያሉ በሽታዎች የተበራከቱት በበርካታ ምክኒያቶች ነዉ። ጤናማ የአመጋገብ ስርአትን አለመከተልና የታሸጉ ምግቦችን ማዘውተር እንዲሁም በቂ እንቅስቃሴ አለማድረግ ከእነዚህ መካከል ይገኙበታል። በተጨማሪም አንዲት እናት በእርግዝና  ክትትል ወቅት ከባለቤቷ ወይም ከቅርብ ሰዎች ጋር አብራ ብትሄድ የተሻለ  ምልክቶችን ለማወቅ እንደሚረዳት መክረዋል።   በኤደን ሽመልስ #ዳጉ_ጆርናል

በትግራይ ክልል ለአንድ ሳምንት ብቻ አብረዉ የኖረችዉን የትዳር አጋሩን ገድሎ የተሰወረው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ በትግራይ ክልል ፅራእ ወንበርታ ወረዳ ሓይቂ መስሓል ከተማ ሰኔ 25 ቀን 2018
+2
በትግራይ ክልል ለአንድ ሳምንት ብቻ አብረዉ የኖረችዉን የትዳር አጋሩን ገድሎ የተሰወረው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ   በትግራይ ክልል ፅራእ ወንበርታ ወረዳ ሓይቂ መስሓል ከተማ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም  የባለቤቱን የወይዘሮ ሸዊት አረጋዊን ህይወት በማጥፋት ወንጀል ተጠርጥሮ የነበረው ግለሰብ ለአምስት ቀናት በተደረገ ጥብቅ ክትትል ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ በትግራይ ፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።   የክልሉ ፖሊስ እንዳስታወቀው ተጠርጣሪው ግለሰብ ወንጀሉን ከፈጸመ በኋላ ያስመልጠኛል ወዳለው አካባቢ ሄዶ ተደብቆ የነበረ ቢሆንም የፖሊስ አባላቱ ባደረጉት ረቂቅ ክትትልና ህብረተሰቡ ባሳየው ያልተቆጠበ ትብብርና ርብርብ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።   ፖሊስ ከተጠርጣሪው ባገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ቃል እንደተረጋገጠው  ጥንዶቹ ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የጋብቻ ስርዓት የፈጸሙ ሲሆን  እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በተለያዩ ቤቶች ቆይተው ወንጀሉ ከመፈጸሙ ከአንድ ሳምንት በፊት ነበር በአንድ ላይ መኖር የጀመሩት፤ይሁን እንጂ ሰኔ 25 ቀን  ከምሽቱ 12:00 ሰዓት አካባቢ በመካከላቸው በተፈጠረ አለመግባባት የተነሳ ተጠርጣሪው የባለቤቱን ህይወት ሊያጠፋ እንደቻለ ራሱ ለፖሊስ በሰጠው ቃል አምኗል።   በአሁኑ ወቅት በተጠርጣሪው ላይ የተጀመረውን ሙሉ የምርመራ ሂደት በማጠናቀቅ  አስፈላጊውን መረጃ በቀጣይ ለህብረተሰቡ ይፋ እንደሚያደርግም ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል።   በሰብል አበበ #ዳጉ_ጆርናል

ይፋዊ : ቼልሲ የስፖርቲንግ ሊዝበኑን ፣ ጂኦቫኒ ቁዌንዳ በ8ዓመት ውል አስፈርሟል until June 2034 ✍️🔵 💰£44.5m #ዳጉ_ጆርናል
ይፋዊ : ቼልሲ የስፖርቲንግ ሊዝበኑን ፣ ጂኦቫኒ ቁዌንዳ በ8ዓመት ውል አስፈርሟል until June 2034 ✍️🔵 💰£44.5m #ዳጉ_ጆርናል

ኢትዮጵያዊ አማካኝ ጋቶች ፓኖም ለኩዌት ክለብ ፈረመ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ጋቶች ፓኖም ወደ ኩዌት ሊግ ማምራቱ ለማወቅ ተችሏል። በሳውዲው ክለብ አል አረቢ ጥሩ ጊዜን በግሉ ያ
ኢትዮጵያዊ አማካኝ ጋቶች ፓኖም ለኩዌት ክለብ ፈረመ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ጋቶች ፓኖም ወደ ኩዌት ሊግ ማምራቱ ለማወቅ ተችሏል። በሳውዲው ክለብ አል አረቢ ጥሩ ጊዜን በግሉ ያሳለፈው ጋቶች ፓኖም ለኩዌቱ አል ፋሂሊ ክለብ ፊርማውን ማኖር ችሏል። ጋቶች ፓኖም በክለቡ ለአንድ አመት ለመቆየት ለአል ፋሂሊ ስፖርት ክለብ ፊርማውን አኑሯል። ጋቶች ፓኖም ከሳምንታት በኃላ ወደ ግብፅ በማቅናት በቅድመ ውድድት ዝግጅት ቡድን እንደሚቀላቀል ይጠበቃል። ጋቶች ፓኖም ከሀገራችን ሊግ አልፎ :- በሩሲያ ኢራቅ ግብፅ እና ሳውዲ አረቢያ ሊጎች ላይ ባለፉት አመታት ተጫውቶ አሳልፏል። “ ጭልፊቶቹ “ የሚል መጠርያ ያለው ክለቡ አስር ክለቦች በሚሳተፉበት የሀገሪቱ ሊግ በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን 6ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። #ዳጉ_ጆርናል

ትራምፕ ከስፔን ጋር ያለውን ንግድ ሙሉ በሙሉ እንዲያቋረጥ ትዕዛዝ ሰጡ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የገንዘብ ሚኒስትሩ ስኮት ቤሴንት ከስፔን ጋር ያለውን ንግድ ሙሉ በሙሉ እንዲያቋርጡ ትዕዛ
ትራምፕ ከስፔን ጋር ያለውን ንግድ ሙሉ በሙሉ እንዲያቋረጥ ትዕዛዝ ሰጡ   የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የገንዘብ ሚኒስትሩ ስኮት ቤሴንት ከስፔን ጋር ያለውን ንግድ ሙሉ በሙሉ እንዲያቋርጡ ትዕዛዝ የሰጡ ሲሆን ማድሪድ በሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ኔቶ ውስጥ “አስፈሪ አጋር” ሲሉ ጠርተዋታል።በመጋቢት ወር ስፔን አሜሪካ በኢራን ላይ ለምታደርገዉ ወታደራዊ ዘመቻ በግዛቷ ላይ የጋራ ወታደራዊ ሰፈሮችን እንደማትጠቀም እና የአየር ክልሏን በጦርነቱ ውስጥ ለሚሳተፉ የአሜሪካ አውሮፕላኖች እንደምትዘጋ መናገሯ ይታወሳል፡፡   ከስፔን ጋር ንግግራ በራሱ አስፈላጊ አይደለም ተስፋ ቢስ፣ መጥፎ ሰዎች ናቸው ሲሉ ፕሬዝዳንት ትራም ተናግረዋል።ትራምፕ ከስፔን ጋር በመከላከያ ወጪዋ ምክንያት የተፈጠረ የቅርብ ጊዜ ውዝግብ መኖሩ ይታወሳል። በ2035 ዓመት 5 በመቶ የሚሆነውን የሀገር ውስጥ ምርት እድገት ጂዲፒ ለመከላከያ ወጪ ለማድረግ ዉሳኔ ያላሳለፈች ብቸኛው የወታደራዊ ጥምረት ኔቶ አባል ሀገር ስፔን ናት፡፡   "ከእኛ በጣም ብዙ ገንዘብ ያገኛሉ፣ ነገር ግን ተባባሪዎች አይደሉም ስለዚህ ከእነርሱ ጋር ምንም አይነት ንግድ አልፈልግም።" ሲሉ ትራምፕ ተደምጠዋል፡፡ዩናይትድ ስቴትስ በስፔን ውስጥ ሁለት አስፈላጊ የጦር ሰፈሮች ያሏት ሲሆን የባህር ኃይል ጣቢያ ሮታ እና ሞሮን አየር ማረፊያ ናቸዉ፡፡ በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል

🌍አጫጭር መረጃዎች   🇺🇸🇮🇷 የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቴህራን ጋር የተኩስ ልዉዉጥ ካደረጉ በኋላ የአሜሪካ እና የኢራን የተኩስ አቁም ስምምነት "አብቅቷል" ብለዋል።"ከእንግዲህ ወዲህ ከእነሱ ጋር መነጋገር አልፈልግም፣ እነሱ ቆሻሻ ናቸው"፤ " የታመሙ ሰዎች ናቸው፣ በታመሙ ሰዎች ይመራሉ። ጨካኞች እና ዓመፀኞች ናቸው። የኑክሌር ጦር መሳሪያ ቢኖራቸው ኖሮ ይጠቀሙበት ነበር።" ሲሉ ተደምጠዋል፡፡   🇮🇷🇺🇸 ኢራን የተፈጸመባትን የአየር ጥቃት በማዉገዝ ጎረቤቶች አሜሪካን ከመርዳት እንዲቆጠቡ አስጠነቀቀች፡፡የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በደቡብ ኢራን የተፈጸመዉን ወታደራዊ ጥቃቶችን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ የፈጸመችውን “ጥቃትየመግባቢያ ሰነዱን ከባድ ጥሰት” ሲል አጥብቆ አውግዟል።   🇦🇪ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በኳታር እና በሳዑዲ የንግድ ታንከሮች ላይ የፈጸመችው ጥቃት እንዲሁም በባህሬን እና ኩዌት ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት መፈጸሟ ቴህራን ፍጥጫውን ለማብረድ የሚያስፈልጉትን መስፈርቶች ለማሟላት ፈቃደኛ አለመሆኗን ያሳያል ሲሉ የኤምሬትስ ዲፕሎማት የሆኑት አንዋር ጋርጋሽ ተናግረዋል።   🇺🇸🇮🇷 በሆርሙዝ ወሽመጥ ሲጓዙ የነበሩ ሦስት የነዳጅ ጫኝ መርከቦች ከተመቱ በኋላ አሜሪካ ኢራን ላይ “ጠንካራ” ጥቃት ከፈተች።የአሜሪካ ጦር ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም)፤ በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚገኙ ከ60 በላይ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ አነስተኛ ጀልባዎችን ጨምሮ ከ80 በላይ ዒላማዎችን መምታቱን አስታውቋል   🇶🇦 የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በባህሬን እና ኩዌት ላይ የተፈፀመውን የኢራን ጥቃት ያወገዘ ሲሆን የሀገራት ሉዓላዊነት እና ዓለም አቀፍ ህግን በግልጽ የሚጥስ ነው ሲል ገልጾታል። 🛢 ትራምፕ የተኩስ አቁም ገደቡ 'አብቅቷል' ብለዉ ካወጁ በኋላ የነዳጅ ዋጋ በድጋሚ ጨመረ፡፡ጨምሯልየነዳጅ ነጋዴዎች የተኩስ አቁም ገደቡን 'አብቅቷል' ብለው ትራምፕ ላወጡት መግለጫ በፍጥነት ምላሽ ሰጥተዋል። ትራምፕ ይህንን አስተያየት ከመስጠታቸዉ በፊት፣ ነዳጅ በበርሜል ከ76 ዶላር በታች ነበር። አሁን ከ78 ዶላር በላይ እየጨመረ ይገኛል፡፡   🇮🇷የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ኔቶ ዋና ፀሐፊ ማርክ ሩት አሜሪካ በኢራን ላይ የፈፀመችውን ጥቃት ፣ ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነቱን በመጣሷ ምክንያት “እጅግ አስፈላጊ” ሲሉ ጠርተውታል።በአንካራ በተካሄደው የኔቶ መሪዎች ጉባኤ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ሩት የዋሽንግተን ጠንካራ ምላሽ ከሁኔታው አንጻር ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል።"የተኩስ አቁም ስምምነት ባለበት ሁኔታ ኢራን በመሠረቱ ስምምነቱን እየጣሰች ከሆነ፣ አሜሪካ በጽኑ ምላሽ መስጠቷ እጅግ ወሳኝ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።   🇮🇶🇮🇷 የኢራቁ 'ፖፑላር ሞቢላይዜሽን ፎርስ' ወይም 'ሀሽድ አል-ሻዕቢ'፣ ከ2.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በኢራቅ ቅድስት ከተማ ናጃፍ በተካሄደው የጎረቤት ሀገር መሪ የነበሩት የኢራኑ አያቶላህ አሊ ካሜኔይ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ መሳተፋቸውን አስታወቀ።    🇮🇷🇺🇸 የአሜሪካ ጦር በደቡባዊ ኢራን ላይ ጥቃት ከሰነዘረ በኋላ የኢራን ጦር በባህሬን በሚገኘው የሼክ ኢሳ የአየር ማረፊያ በአሜሪካ ወታደሮች ላይ የአጸፋ የድሮን ጥቃት እንደፈፀመ አስታወቀ።“ከአሜሪካ ጋር የተደረገውን የተኩስ አቁም ስምምነት በግልጽ እና ተደጋጋሚ ጥሰት የሚያስከትለው መዘዝ ወንጀል ነው፣ እናም በክልሉ ውስጥ ያሉት ሁሉም የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች ትክክለኛ የጦር ድሮኖች ኢላማ ይሆናሉ” ሲል አስታውቋል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል

የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ምናንጋግዋ የስልጣን ዘመናቸዉን ለተጨማሪ ሁለት ዓመታት ለማራዘም የሚያስችል ህግ ፈረሙ የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ ማክሰኞ ዕለት የሕገ መንግሥት ማሻሻያዎችን መፈ
የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ምናንጋግዋ የስልጣን ዘመናቸዉን ለተጨማሪ ሁለት ዓመታት ለማራዘም የሚያስችል ህግ ፈረሙ   የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ ማክሰኞ ዕለት የሕገ መንግሥት ማሻሻያዎችን መፈረማቸዉን የመንግሥት ቃል አቀባይ ኒክ ማንግዋና ተናግረዋል፡፡ማሻሻያዎቹ የፕሬዚዳንታዊ እና የፓርላማ ዘመንን ከአምስት ወደ ሰባት ዓመታት ያራዝማሉ እንዲሁም በህዝብ ቀጥታ የፕሬዚዳንታዊ ምርጫዎችን በማስቀረት ፕሬዚዳንቱ በፓርላማ አባላቱ እንዲመረጡ አዲሱ ህግ ያስችላቸዋል።   የዚምባብዌ ፓርላማ ባለፈው ወር የገዢው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ህብረት-አርበኞች ግንባር በሁለቱም ምክር ቤቶች የሚያስፈልገውን ሁለት ሶስተኛ አብላጫ ድምጽ ካገኘ በኋላ ማሻሻያዎችን አጽድቋል።"ፈርመዋል፣ ታትመዋል እና ተላልፈዋል ፤አሁን ሕግ ነው" ሲሉ ማንግዋና በኤክስ  የሕጉን ቅጂ በማያያዝ ያጋሩት መልዕክት ያሳያል።   የ83 ዓመቱ ምናንጋግዋ በ2028 ከሥልጣን ለመልቀቅ አቅደዉ ነበር፤ ነገር ግን አሁን እስከ 2030 ድረስ በሥልጣን ላይ ለመቆየት የሚያስችላቸዉን ህግ አሻሽለዋል፡፡"አዞ" በሚል ቅጽል ስያሜ የሚታወቁት ምናንጋግዋ በማሻሻያዎቹ መሠረት ለ12 ዓመታት ፕሬዝዳንት ሆነው ያገለግላሉ። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል

ሂጅራ ባንክ 1.9 ቢሊዮን ብር ትርፍ አስመዘገበ 👉 ሂጅራ ባንክ ለሰራተኞቹ የሁለት ወር ቦነስ እና የ40በመቶ የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን አስታወቀ ሂጅራ ባንክ በ2025/2026 በጀት ዓመት 3.55
ሂጅራ ባንክ 1.9 ቢሊዮን ብር ትርፍ አስመዘገበ 👉 ሂጅራ ባንክ ለሰራተኞቹ የሁለት ወር ቦነስ እና የ40በመቶ የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን አስታወቀ ሂጅራ ባንክ በ2025/2026 በጀት ዓመት 3.55 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ገቢ ያስመዘገበ ሲሆን  ይህም ካለፈው ዓመት ጋር  ሲነፃፀር 97 በመቶ እድገት ማሳየቱን አስታውቋል። በተጨማሪም 1.9 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ትርፍ ማግኘቱን የሂጂራ ባንኩ የሂጅራ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ዳዊት ቀኖ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።የባንኩ ጠቅላላ ሀብት በአንድ ዓመት ውስጥ ከ14.61 ቢሊዮን ብር ወደ 31.45 ቢሊዮን ብር ያደገ ሲሆን፣ ተቀማጭ ገንዘቡም ከ11.94 ቢሊዮን ብር ወደ 24 ቢሊዮን ብር ደርሷል። ሂጅራ ባንክ በበጀት ዓመቱ ከ16.78 ቢሊዮን ብር በላይ የፋይናንስ አገልግሎት ለደንበኞች ማቅረቡን ጠቅሶ፣ ለአነስተኛና መካከለኛ ሥራዎች፣ ለሴቶችና ወጣቶች ያለ ማስያዣ 1.5 ቢሊዮን ብር የኢሙራበሃ ፋይናንሲንግ መስጠቱን ገልጿል። በዲጂታል ባንኪንግ ዘርፍም የደንበኞቹን ቁጥር 2.24 ሚሊዮን ማድረሱን እና የዲጂታል ግብይት መጠኑ 41.72 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል። በቅርንጫፍ ማስፋፊያ በኩል 41 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት አጠቃላይ ቅርንጫፎቹን 170 ማድረሱን አስታውቋል።ባንኩ በማህበራዊ ኃላፊነት ዘርፍ ከትርፉ 8 ሚሊዮን ብር ለዘካ እና 2 ሚሊዮን ብር ለወቅፍ መመደቡን እንዲሁም ለሐጅ ጉዞ ለሚያደርጉ 35 ሰዎች  ያለ ትርፍ የፋይናንስ ድጋፍ ማድረጉን አቶ ዳዊት ቀኖ አክለው ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል። ባንኩ በዓመቱ ከፍተኛ ትርፍ በማስመዝገቡ ለሰራተኞቹ የሁለት ወር ቦነስ እና የ40በመቶ የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን አስታውቋል። በትግስት ላቀው #ዳጉ_ጆርናል

ጤና ሚኒስቴር የሕክምና ትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራው ነው አለ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ላለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው 2ኛው አህጉራዊ ኮሜሳ እና ሜድኤድ - አፍሪካ 2026
+1
ጤና ሚኒስቴር የሕክምና ትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራው ነው አለ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ላለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው 2ኛው አህጉራዊ ኮሜሳ እና ሜድኤድ - አፍሪካ 2026 ኮንፈረንስ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ተጠናቋል። በኮንፈረንሱ ከ800 በላይ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የጤና ባለሙያዎችና ምሁራን የተሳተፉ ሲሆን የጉባኤው ማጠቃለያ መርሃግብር ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ የመዝጊያ ንግግር አድርገዋል። ሚኒስትር ዴኤታዋ በንግግራቸው፤ የጤና አገልግሎት ጥራትንና ደህንነትን ለማሻሻል የሕክምና ትምህርትን ማስፋፋትና የባለሙያዎችን አቅም መገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል ። ኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎችን ቁጥርና ተደራሽነት በማሳደግ የሥልጠና ጥራትን ለመጨመር የተለያዩ ፕሮግራሞችን በመቅረፅ የጤና ስርዓቱን ለማጠናከር ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በጉባኤው ላይ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ከ800 በላይ የጤናው ዘርፍ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን፣ በዘርፉ ላይ የሚያጋጥሟቸውን ችግሮችና መፍትሔዎቻቸውን በተመለከተ የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸው ተገልጿል። ይህ አህጉራዊ ጉባኤም በአፍሪካ ደረጃ ብቃት ያለው የሰው ሃይል ለማፍራትና የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ትልቅ መሠረት የጣለ መሆኑን ጠቁመዋል። በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ የጤና አገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ የጤና ስርዓቱን በጋራ ለማጠናከር የሚያስችል ስምምነት ላይ መግባባት ተደርሷል። በሰመሀር አለባቸው #ዳጉ_ጆርናል

ገዳ ባንክ አንድ ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ አቀረበ 👉 የአንዱ አክሲዮን ዋጋ 1 ሺህ 50 ብር ነዉ ገዳ ባንክ ለገበያ ያቀረበዉ የአክሲዮን ሽያጭ ከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 17
ገዳ ባንክ አንድ ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ አቀረበ     👉  የአንዱ አክሲዮን ዋጋ 1 ሺህ 50 ብር ነዉ ገዳ ባንክ ለገበያ ያቀረበዉ የአክሲዮን ሽያጭ ከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 17 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ገበያ ላይ እንደሚቆይ የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ ወልዴ ቡልቶ መናገራቸውን ብስራት ሬዲዮ ሠምቷል ። የአክሲዮን ሽያጩ የሚከናወነው ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን የአክሲዮን ሽያጭ ፈቃድ ባገኙ ተቋማት በኩል መሆኑን ባንኩ አስታውቋል ። በገዳ ሴኩሪቲ ዲለር ፣በሲቢኢ ካፒታል ኢንቨስትመንት ፣በአዋሽ ካፒታል ኢንቨስትመንት ፣በወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አክሲዮን ማህበር እና ከባለስልጣኑ ፈቃድ ባላቸዉ ሌሎች ተቋማት አማካኝነት ብቻ ነዉ ተብሏል ። ባንኩ በ2025/26 በጀት ዓመት ከታክስ በፊት 1 ቢሊዮን ብር ትርፍ በማግኘት አጠቃላይ ሀብቱን 16.5  ቢሊዮን ብር ማድረሱንና የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን 12.6 ቢሊዮን ብር ማድረሱን ማስታወቁ የሚታወስ ነዉ ። በመባ ወርቅነህ #ዳጉ_ጆርናል

በጋሞ ዞን ቤተሰቦቿን ለመፈለግ በመጣችው የ19 ዓመት ታዳጊ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ከፈጸሙ ተከሳሾች መካከል ሁለቱ በፅኑ እስራት ተቀጡ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ ቤተሰቦቿ
+1
በጋሞ ዞን ቤተሰቦቿን ለመፈለግ በመጣችው የ19 ዓመት ታዳጊ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ከፈጸሙ ተከሳሾች መካከል ሁለቱ በፅኑ እስራት ተቀጡ   በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ ቤተሰቦቿን ለማፈላለግ የመጣችውን የ19 ዓመት ታዳጊ በማታለልና በማስፈራራት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸሙ ሁለት ተከሳሾች በፅኑ እስራት ተቀጥተዋል።የቦረዳ ወረዳ ታክቲክ ምርመራ ክፍል ማስተባበሪያ ኃላፊ ኢንስፔክተር ታደለች አሸንጎ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ተበዳይዋ ቤተሰቦቿን ለመፈለግ ወደ አካባቢው በመጣችበት ወቅት  በክስ ዝርዝሩ ላይ ስሙ ያልተጠቀሰ ተጠርጣሪ ከዘመዶችሽ ጋር አገናኝሻለሁ በማለት ወደ ጎቾ ከተማ አታሎ ይወስዳታል።   በመቀጠልም ከሌሎች ግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን በማስፈራራት ለሦስት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈፀማቸው ተገልጿል።በድርጊቱ የተሳተፉ ሌሎች ግለሰቦች ለጊዜው እንዳልተያዙ የክስ መዝገቡ ያመለክታል።በችሎቱ ሂደት አንደኛው ተከሳሽ ክሱን በመካድ የተከራከረ ሲሆን ሁለተኛው ተከሳሽ ድርጊቱን ማመኑ ተገልጿል።   ፍርድ ቤቱም የቀረቡትን የሰነድና የምስክር ማስረጃዎች ከመረመረ በኋላ ተከሳሾቹን ጥፋተኛ በማለት ውሳኔ ሰጥቷል።በዚሁ መሠረት አንደኛው ተከሳሽ በ7 ዓመት ፅኑ እስራት፣ ሁለተኛው ተከሳሽ ደግሞ በ7 ዓመት ከ8 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ መወሰኑን ኢንስፔክተር ታደለች አሸንጎ ለብስራት ሬዲዮ ገልጸዋል።   በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል

አንዲት የአርጀንቲና ደጋፊ "ወደ መካነ አራዊት ሂድና አልቅስ" ስትል በአይሾውስፒድ ​​ላይ የሰነዘረችዉን የዘረኝነት ጥቃት ፊፋ አወገዘ ፊፋ በዩናይትድ ስቴትስ በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ላይ በ
አንዲት የአርጀንቲና ደጋፊ "ወደ መካነ አራዊት ሂድና አልቅስ" ስትል በአይሾውስፒድ ​​ላይ የሰነዘረችዉን የዘረኝነት ጥቃት ፊፋ አወገዘ   ፊፋ በዩናይትድ ስቴትስ በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ላይ በቀጥታ ስርጭት ላይ በማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪው አይሾውስፒድ ​​ላይ የተሰነዘረውን የዘረኝነት ጥቃት አውግዟል።የእግር ኳስ ዓለም አቀፍ የአስተዳደር አካል ባወጣው መግለጫ "ፊፋ ዘረኝነትን፣ ጥላቻን እና አድልዎን በሁሉም መልኩ አጥብቆ ያወግዛል" ሲል አስታዉቋል፡፡   የአሜሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪ አርጀንቲና ባለፈው ሳምንት ከካቦ ቨርዴ ጋር ባደረገችው የመጨረሻ 32 ጨዋታ ላይ በአንድ ደጋፊ የዘረኝነት ጥቃት ደርሶበታል፡፡አይሾው ስፒድ ጨዋታውን በቀጥታ እያሰራጨ ነበር፣ የአርጀንቲና ማልያ የለበሰች ደጋፊ ምን በስፓኒሽ ቋንቋ ጥቁር ለሆነው አይሾው ስፒድ "ወደ መካነ አራዊት ሂድና አልቅስ" የሚል የዘረኛነት ጥቃት እንደተፈጸመችበት ተነግሯል፡፡   “ፊፋ ጁላይ 3 ቀን 2026 በአርጀንቲና እና በካቦ ቨርዴ ጨዋታ ወቅት በማያሚ ስታዲየም ደጋፊ አይሾውስፒድ ላይ ያገጠመዉን የዘረኝነት ጥቃት ወዲያውኑ ምርመራ መጀመሩን” አስታውቋል።ስፒድ፣ የመዝገቡ ስሙ ዳረን ዋትኪንስ ጁኒየር የሚባል ሲሆን፣ ፊፋ ከአሜሪካው አስተናጋጅ ፎክስ ስፖርትስ እና ዩቲዩብ ጋር በተደረገው ስምምነት መሰረት በርካታ የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ተገኝቶ በቀጥታ ስርጭት በማስተላለፍ ላይ ይገኛል፡፡ በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል