አል በያን Al_beyan 📚
Открыть в Telegram
6 497
Подписчики
-224 часа
-567 дней
-8630 день
Архив постов
6 497
~
﴿ قُلْ عَسَى أَن يَكُونَ قَرِيبًا ﴾
"ምናልባትም ቅርብ ሊሆን ይችላል በላቸው።" [ አል-ኢስራእ ፡ 51]
ጌታዬ ሆይ!.. 🤲🏼
ለስብራታችን መጠገንን፣ ሰላምን/እርጋታን እና የዘገየው ሐጃችን ሁሉ እንዲሳካ እለምንሃለሁ።
6 497
Repost from فوائد أبي معاذ🕋🕋 ፈዋኢዱ አቢ ሙዓዝ
📖 ይህንን ኪታብ በኦን ላይን መቅራት ለምትፈልጉ ፣
🌍ጊዜው አብቅቷል ከመጀመሩ በፊት ቶሎ ወደ ቻናሉ በመቀላቀል ደርሱን ተካፈሉ፣
ለመቀላቀል👇
👇👇👇👇
📚ኪታብ አተውሂድ የኢማም ሙሀመድ ኢብን አብድልወሃብ
📙كتاب التوحيد للشيخ محمد بن عبدالوهاب
6 497
🌸 "ውድ ወንድሜና እህቴ... ቤታችሁ ውስጥ ማን ነው የሚኖረው?"ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦
ቁርአን የማይቀራበት ቤት፣ ልክ እንደ ፈረሰ (ባዶ) ቤት ነው።" (ቲርሚዚ)ቤትሽን በቆንጆ እቃዎች ብታስውቢው፣ ቤትህን በትላልቅ ቁሳቁሶች ብትሞላውም... ቁርአን የማይቀራበት ከሆነ ግን በውስጡ ላለው ሰው ጨለማና የጭንቀት ማከማቻ ነው የሚሆነው። ቤታችሁ በብርሃንና በሰላም እንዲሞላ፣ ሸይጧንም እንዲሸሽ ከፈለጋችሁ ዛሬውኑ ቁርአንን በቤታችሁ አድምቁት። ወንድሜ ሆይ፣ እህቴ ሆይ... ዛሬ ቢያንስ አንድ ገጽ እንኳ ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ቅሩና የቤታችሁን ድባብ ቀይሩት! 📖✨
6 497
🔥 ለቅሶ ቤት ⁉️
🔥 ... تعزية الكافر للمسلم والاجتماع في بيت الميت
الجواب:
يجوز أن يُعَزَّى المصاب سواء كان المعزي مسلماً أو كافراً.
ولكن الاجتماع في البيت لتَلَقِّي المعزين بدعة لم يكن في عهد الرسول صلى الله عليه وسلم ولا أصحابِه، وإنما تُغْلَق الأبواب -أي: أبواب الذين مات ميتهم-، ومن وجدهم في السوق، أو في المسجد ورآهم مصابين عزاهم؛ لأن المقصود بالتعزية ليست التهنئة، المقصود بالتعزية تقوية الإنسان على الصبر، ولهذا رد النبي صلى الله عليه وسلم رسول ابنته الذي أرسلته لتخبره عن ابنٍ لها كان في سياق الموت، فرد النبي صلى الله عليه وسلم الرسول وقال له: «مرها فلتصبر ولتحتسب، فإن لله ما أخذ وله ما أعطى وكل شيء عنده بأجل مسمى». ولم يذهب ليعزيها، حتى ألحَّت على أبيها أن يحضر، ليس من أجل العزاء؛ ولكن من أجل حضور هذا الغلام أو الطفل المحتضر.
👉 "ሙስሊም"ም ይሁን "ካፊር" "ሙሲባ" የገጠመውን ሰው ማስተዛዘን ይቻላል።
🔥 ነገር ግን በሟች ቤት ከለቅሰኞች ጋር ለመገናኘት ለቅሶ በሚል መሰባሰብ (በእስልምን ውስጥ የተፈጠረ) የሆነ "ቢድዓ" ነው‼️
👉 (ይህ ነገር) በረሱል (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)ም ይሁን በሰሓባዎች ዘመን አልነበረም !!!
👉 የእነዚያ ሟች የሞተባቸው የሆኑት ሰዎች (ቤተሰቦች) የቤታቸው በር መዘጋት አለበት !!!
👉👉👉 በሱቅ (በስራ ቦታ) ወይም በመስጂድ ውስጥ ያገኛቸው የሆነ ሰው አዘንተኛ ሆነው ካገኛቸው ያፅናናቸዋል።
"ታዕዚያ" ማፅናናት በሚለው ነገር የተፈለገበት ነገር አዘንተኛውን ማስተዛዘን ሳይሆን የሰውን ልጅ በገጠመው (አዘን) ላይ ትዕግሥተኛ እንዲሆን ማበረታታት ነው።
ለዚህም ሲባል ነው ረሱል (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ልጃቸው "ልጄ በመሞት ላይ ነው" በሚል ልትነግራቸው እርሳቸው እንዲመጡላት የላከችውን መልዕክተኛ ( እንዲህ በላት) የሚሉ ሲሆን የመለሱት « ወደእርሷ ሂድ ያ የያዘውም ይሁን የሰጠውም የሆነው እሱ አላህ ነው። ሁሉ ነገር እርሱ ዘንድ በዕለተ ቀጠሮ ነው። ትዕግሥት ታድርግ ከአላህም ትተሳሰብ ! » (ንገራት) በማለት አሉት። ሊያስተዛዝኗት አልሄዱም።
(እርሷም) መልዕክተኛውን በአባቷ ላይ ፈጥኖ እንዲሄድና (እየሞተ ባለው ልጇ ላይ) እንዲገኝ እስከምታደርግ ድረስ (ደረሰች።)
👉👉👉 ይህም የሆነው እንዲያስተዛዝኗት በሚል አይደለም ! ነገር ግን በዚህ በመሞት ላይ ባለው ዕፃን ልጅ ላይ እንዲገኙ በሚል ነው።
ولم يكن معروفاً في عهد الصحابة أن يجتمع أهل الميت ليتلقوا العزاء من الناس، بل كانوا يعُدُّون صُنْعَ الطعام في بيت أهل الميت والاجتماع على ذلك من النياحة، والنياحة من كبائر الذنوب، فإن النبي صلى الله عليه وسلم لَعَنَ النائحة والمستمعة، وقال: «النائحة إذا لم تتب تقام يوم القيامة وعليها سربال من قطران، ودرع من جرب». نعوذ بالله.
فلهذا نحن ننصح إخواننا المسلمين عن فعل مثل هذه التجمعات التي هي ليست خيراً، بل هي شر لهم.
المصدر: سلسلة لقاءات الباب المفتوح > لقاء الباب المفتوح [1]
🌿 በሰሓባዎች ዘመን (የሟች ቤተሰቦች) ከሰዎች ውስጥ የሚያስተዛዝናቸው የሆነ ለቅሶኛ እንዲገናኛቸው በሚል ተሰባስበው መቀማመጣቸው የሚታወቅ ነገር አልነበረም !!!
🔥 እንደሁም በሟች ቤት ውስጥ ምግብን ማዘጋጀት መጠቀምንና ለእሱ በሚል መሰባሰብን እነደ " ኒያሓ"
(የጃሂሊያ ዘመን) ለቅሶ የሚቆጥሩት ነበር❗️
🔥 " ኒያሓ" (የጃሂሊያ ዘመን)
ለቅሶ ከትላልቅ ወንጀል ነው❗️
🔥 ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) አስለቃሽና ለቅሶ አዳማጭ ዕንስቶችን ረግመዋል !!!
👉 ነብዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) " አስለቃሽ "ናኢሓ" ከመሞቷ በፊት "ተውበት" ካላደረገች የቂያማ ቀን "ከካትራም" የሆነ ልብስና የሚያሳክክ "ጡሩሩ" ለብሳ ትቀሰቀሳለች !!! " ብለዋል።
👉 በአላህ እንጠበቃለን !!!
🌱 ከዚህም በመነሳት እኛም ሙስሊም ወንድሞቻችንን እነዚህን የመሳሰሉ ጥሩ ያልሆኑ መሰባሰቦችን ከመተግበር (እንዲርቁ) እንመክራለን !!! እንደሁም ይህ ነገር ለነርሱ "ሸር" ነው❗️
(ታላቁ ኢማም መሐመድ ሷሊሕ ኢብን ዑሰይሚን)
6 497
‼️ የ 𝗢𝗻𝗹𝗶𝗻𝗲 ኢስላማዊ አካዳሚ 📖
📖"በተደጋጋሚ የኦን ላይን ትምህርት ስትጠይቁኝ ለነበራቹህ ወንድሞችና እህቶች እንኳን ደስ አላቹህ፣
📖 ትምህርታችን ጥራቱን የጠበቀ የኢስላማዊ ትምህርቶችን በኦንላይን ባሉበት/ማለትም መገኘት ለማትችሉ ባሉበት ሆነው እንድትማሩ እድሉን አመቻቸንላቹህ።
✅ የምንሰጣቸው ትምህርቶች፦
💫የአቂዳና የተውሂድ ኪታቦች
💫የፊቅህ ኪታቦች
💫 ተጅዊድ ቁርአን ነዘር
ለጨረሳቹህ/ማንበብ
ለምትችሉ፣
🆕 ማስተማሪያ መንገዶች፦
⏩በቴሌግራም፣
♻️👉 የክፍለ ጊዜ ሰዓት፦
• ጊዜው እናንተንም እኔንም በሚመቸን ሰዓት ተስማምተንበት የምንወስነው ይሆናል ባይሆን (በሳምንት 3 ቀን)ነው የምንሰጠው
💰 የክፍያ ሁኔታ፦
• በወር፦ 0 ብር ብቻ!
• በፍላጎቱ ላደረገ አንቃወምም።
⏬ ለመመዝገብና አሁኑኑ ቦታ ለመያዝ፦
🛃 ➡️ @lemamezgeb
🛃 ➡️ @lemamezgeb
👉👇
https://t.me/abu_muaz_ibrahim/8179
6 497
✍️ራስን በራስ ማርካት!–ክፍል 1―
~
በርግጥም የምንኖርበት ዘመን ከባድ ነው። ቴክኖሎጂው የመጣው ህይወትን ሊያቀል ነበር፤ ነገር ግን ሰይጣን ለክፉ ተጠቅሞበት በጣትህ ጫፍ በሚነካ ስክሪን አማካኝነት ወደ መኝታህ ገብቷል። ዛሬ ላይ ብዙ ወጣቶች በድብቅ የሚያለቅሱበት፣ ከሰው ተደብቀው አንገት የሚደፉበት፣ የህሊና እረፍት ያጡበት ትልቁ በሽታ «ኢስቲምናእ» (ራስን በራስ ማርካት) አንዱና ትልቁ የወጣቱ ችግር ነው።
ይህ ተግባር ዝም ብሎ መጥፎ ልማድ ብቻ አይደለም፤ የወጣትነትን ወዝ የሚጠጣ፣ ከአላህ የሚያጣላ፣ የነገን ተስፋ የሚያጨልም «የድብቅ ካንሰር» ነው። እስቲ ቆም ብለህ ተመልከት! ጌታችን አላህ የሰው ልጅን ሲፈጥር ክብር ሰጥቶታል። ስሜትንም የሰጠህ ለተፈቀደ ትዳርና ለዘር መተካት እንጂ በእጅህ ልትጫወትበት አይደለም። በቁርኣን ውስጥ አማኞችን ሲገልፅ እንዲህ ይላል፡-
«እነዚያም እነሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ናቸው፡፡ በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙት (ባሮች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡ ከዚያም ወዲያ (ሌላን) የፈለጉ ሰዎች እነዚያ እነሱ ወሰን አላፊዎቹ ናቸው፡፡» (ሱረቱ አል-ሙእሚኑን 5-7)
ከዚህ አያ መረዳት እንደምንችለው ከትዳር ውጪ ስሜትን ማውጣት «ወሰን አላፊነት» ነው። ነብያችን(ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ወጣቶችን አግብተው ራሳቸውን እንዲጠብቁ፣ ካልቻሉ ደግሞ እንዲጾሙ አዘዋል እንጂ ራስን በራስ ማርካትን አልፈቀዱም።
ውድ ወንድሜ! ስሜትህን በተከለከለ መንገድ ባወጣህ ቁጥር፣ ከአላህ እዝነት ትርቃለህ። ዱዓህ እንዳይሰምር፣ ዒባዳህ እንዳይጣፍጥህ የሚያደርገው ይሄው የረከሰ ተግባር ነው።አላህ የሰጠህን የተከበረ አካል ማርከስ በእስልምና የተጠላ ተግባር ነው።
ከ አላህ ጋር ከማጣላቱ ባሻገር ይህ ሱስ ከአደንዛዥ ዕፅ ባልተናነሰ በአእምሮ ላይ ከባድ ተጽእኖ አለው። ዶክተሮች ይህን ተግባር በሚፈፅሙ ሰዎች ላይ የሚከተሉትን አደጋዎች ያስቀምጣሉ፡-
📎1ኛ―የአእምሮ ባርነት (Addiction): ልክ እንደ ኮኬይን አእምሮህ ላይ የደስታ ሆርሞን (Dopamine) በውሸት እንዲረጭ ስለሚያደርግ፣ አእምሮህ ይደነዝዛል። ነገ ከትዳር አጋርህ ጋር የምታገኘው ተፈጥሯዊ ደስታ አይጣፍጥህም።
🕹2ኛ―የማስታወስ ችሎታ መቀነስ እና የመርሳት ችግር፡ አእምሮ ሁሌም በወሲባዊ ቅዠት ስለሚጠመድ፣ ለትምህርትና ለቂርኣት እንድሁም ለቁምነገር የሚሆን ቦታ ያጣል። ብዙ ተማሪዎችም ሆኑ ብዙ ዒልም ፈላጊዎች ትምህርታቸውን እና ዒልም መማራቸውን የጠሉት በዚህ ምክንያት ነው።
😞3ኛ―የጭንቀት እና የደብርት በሽታ (Depression): ድርጊቱን ከፈጸምክ በኋላ የሚሰማህ የጥፋተኝነት ስሜት ራስን መጥላትና ባዶነት ወደ ድብርት ይወስዳል። "እኔ ርካሽ ነኝ" ብለህ እንድታስብ ያደርግሃል።
👨👦4ኛ―የትዳር ህይወትን ማበላሸት፡ ራስን በራስ በማርካት የለመደ ሰው፣ በትዳር ውስጥ ያለውን ትክክለኛ ግንኙነት መፈጸም ይከብደዋል (Sexual Dysfunction)። ለወንዶች የቶሎ መጨረስ ችግር (Premature Ejaculation) ዋነኛ መንስኤው ይህ መጥፎ ልማድ ነው።
🎯5ኛ―የሰውነት መዛል እና የጀርባ ህመም፡ የወጣትነት ጉልበትህን በከንቱ እያፈሰስክ ስለሆነ፣ ለእድገት የሚሆን ጉልበት ታጣለህ። አይንህ ይቦዝዛል፣ ጉልበትህ ይንቀጠቀጣል፣ኑርህም ይጠፋል…ከሁሉም በላይ የሚያስፈራው ግን የአኼራ ጉዳይ ነው።
ውድ ወንድሜ! እስኪ ለአፍታ ቆም ብለህ አስብ!ያ በጨለማ የቆለፍከው በር ሰዎች እንዳያዩህ ነው አይደል? ግን የዓለማቱ ጌታ አላህ እየተመለከተህ እንደሆነስ ዘነጋህን? እጅህ፣ እግርህና ብልትህ ነገ በአላህ ፊት «እንዲህ አደረገብን»ብለው ሲመሰክሩብህ ምን ልትመልስ ነው? ያንተ እኩዮች ቁርኣን ሲያነቡ፣ ኢልም ሲቀስሙ፣ በትዳር ሲረጋጉ፤ አንተ ግን መጸዳጃ ቤት ውስጥ ወይም አልጋህ ላይ ከራስህ ጋር ትታገላለህ። ይህ ላንተ ክብር አይመጥንም!
የወደፊት ሚስትህ ንጹህ ሆና እየጠበቀችህ፣ አንተ ግን አላህ በሐላል ላይ እንድታውለው የሰጠህን ውድ ስጦታ በቆሻሻ ቦታ እያፈሰስከው ነው። ነገ ትዳር ስትይዝ የምትሰጠው ፍቅር፣ የምትሰጠው ጉልበት ከየት ይመጣል? ጨርሰህው እኮ ነው!
ሞት በዚያ ሁኔታ ውስጥ ቢመጣስ?
አላህ ይጠብቀንና፣ ያንን ቆሻሻ ቪዲዮ እያየህ ወይም ያንን ሐራም እየፈጸምክ ነፍስህ ብትወጣ፣ ከአላህ ጋር እንዴት ትገናኛለህ? ወንድሜ... እህቴ... ይሄ ጉዳይ ቀልድ አይደለም። የእሳትና የጀነት ጉዳይ ነው።
🔍መፍትሄው ምንድን ነው?
☑ተስፋ አትቁረጥ! አላህ መሐሪ ነው። ዛሬውኑ ቆርጠህ ከተነሳህ መመለስ ትችላለህ።ወሏሂ ከዚህ ሱስ መውጣት ከባድ እንደሆነ ብታስቡም በ አላህ ከታገዛችሁና ከወሰናችሁ እጁግ በጣም ቀላል ነው።
☑በንፁህ ልብ አልቅሰህ አላህን ምህረት ጠይቅ። «ጌታዬ ሆይ! ተሸነፍኩ፣ አቅም አነሰኝና እርዳኝ» በለው።
☑ብቸኝነትን አጥፋ። ይህ ሱስ የሚመጣው ለብቻ ስትሆን ነው። ከሰዎች ጋር ተቀላቀል። ስልክህን መኝታ ቤት አታስገባ።
☑የአይን ዚናን ተጠንቀቅ።እይታህን ስበር። በቲክቶክና በፌስቡክ የሚመጡ ስሜት ቀስቃሽ ምስሎችን አግድ (Block)። አይን የልብ መስኮት ናት።
☑ጾም እና ስፖርት ስራ። ነብያችን እንዳሉት ጾም ጋሻ ነው። ስፖርት ደግሞ ትርፍ ጉልበትህን በጥሩ ነገር እንድታወጣው ይረዳሃል።
☑ትዳርን አስብ። አቅሙ ካለህ አግብ። ካልቻልክ እራስህን ለትዳር አዘጋጅ እንጂ በሐራም አትጨርስ።
🫀ያ አላህ! በዚህ የሱስ ሰንሰለት ተጠፍረው የሚሰቃዩ ወንድም እህቶቼን አንተ ድረሰላቸው። በወንጀል የጠቆረውን ልባቸውን በምህረትህ ብርሃን አፅዳው። የዚህን ሱስ አስከፊነትና አስጠያፊነት አሳይተህ፤ ከልባቸው ጠልተው እንዲርቁትና በምትኩ የአንተን ፍቅርና የኢማንን ጣፋጭነት አላህ ይለግሳቸው። አላህ ሆይ! ወዳንተ መመለስን ለከበዳቸው ሁሉ እጃቸውን ይዘህ ወደ ብርሃን ማውጫው መንገድ ምራቸው።
6 497
✅እዉነተኛ ታሪክ
አንድት ሴት እንዲህ ትላለች
ከእለታት አንድ ቀን በትዳሬ ተስፋ ቆርጨ ባሌን ለመግደል አስባለሁ , ማታውን ሳሰላስል አድርና ጧት ላይ እንዴት ማንም ሰው በማይጠራጠርና እኛንም ወንጀለኛ በማያስደርገን መልኩ መግደል እንደምችል ለመመካከር ወደ #ኡሚ ጋር ሄድኩኝ።
#ኡሚም "ማንም በማይጠረጥረው መንገድ እንድትገይው እረዳሻለሁ። ግን አንቺም ማድረግ ያለብሽ ነገሮች አሉ።
✅1ኛ መጀመሪያ ከባልሽ ጋር መታረቅ አለብሽ። ምክንያቱም ከሞተ በኋላ በፊት ፀብ ካልነበረሽ ማንም አይጠረጥርሽም
✅2ኛ ራሰሽን መጠበቅና ለባልሽ ቆንጆ ሆነሽ መታየት አለብሽ፡፡
✅3ኛ ጥሩ እንክብካቤና አድናቆት ስጪው። ያሰብሽውን እንዳይጠረጥር ያደርገዋል።
✅4ኛ #ሶብረኛ ሁኚ ፍቅር ሰጪው ቅናት ቀንሺ የሚናገረውን ጆሮ ሰጥተሽ አዳምጪው።
እነዚህን ነገሮች ማድረግ ትችያለሽ?"ብላ ጠየቀችኝ።
እኔም "ምንም ችግር የለውም። #ኡሚ ብቻ እርሱን የምገድልበትን መንገድ ንገሪኝ።" አልኳት፡፡
"እንደዚያ ከሆነ ምን ማድረግ እንዳለብሽ እነግርሻለሁ። በደንብ
አድምጪኝ።"አለችኝ። እኔም በአትኩሮት መስማት ጀመርኩ።
"ይህንን መርዝ በሚበላው ምግብ ውስጥ በየቀኑ ትንሽ ትንሽ ጨምሪ ቀስ በቀስ እያዳከመው ይገድለዋል።" አለችኝ። ከዛ መርዙን ይዠ በደስታ ወደ ቤቴ ሄድኩ። በተነገረኝ መሰረትም ለባሌ መስጠት ጀመርኩ።
ከወር በኋላ እንደገና እያለቀስኩ ወደ ኡሚ ሄድኩ።
"#ኡሚ አሁን ባለቤቴን መግደል አልፈልግም።በጣም ተለውጧል። እንደያውም ለርሱ ያለኝ ፍቅር ከቀን ቀን እየጨመረ ነው።እባክሽ #ኡሚ መርዙ
እንዳይገድለው ምን ላድርግ?ያለ እርሱ መኖር አልችልም አልኳት ስቅስቅ ብየ እያለቀስኩ።
#ኡሚም "አይዞሽ ልጄ አታልቅሺ የሰጠሁሽ መርዝ አልነበረም።የደቀቀ ስኳር ነበር። በርግጥ መርዝ የነበርሽው አንቺ ነበርሽ። ያ ነበር ባለቤትሽን ቀስ በቀስ እየገደለው የነበረው አየሽ አይደል ፍቅርና እንክብካቤ ስትሰጪው እንዴት አይነት መልካም ባል እንደሆነ።ስለዚህ ከዚህ ተምረሽ ለባልሽ መልካም ሚስት ሁኚለት።"ብላ ነገረችኝ።
✅የኔ እህት ወንድ ልጅ የፈለገ አረመኔ ቢመስል ልቡ ገራገር ነው
በፍቅር ልታሸንፊው ትችያለሽ። መልካም ሚስት ሁኚለት መልካም ባል ይሆንልሻል።
ከታሪኩ ምን ተረዳችሁ❓
م.ق
6 497
የጁምአ ቀን ነብዩን ﷺ በብዛት የምናስታውስበት ቀን ነው
✍ ወንጀልን ከሚያሥምሩ እና ሀሳብ እና ጭንቀት ከሚያስወግዱ ነገሮች መካከል በአላህ ነብይ ﷺ ላይ ሰለዋት ማውረድ ትልቁ ነው።
🪐ጁሙዐ ቀን ሲሆን ደግሞ ሰለዋት ማብዛት ይወደዳል
6 497
Repost from N/a
⭕️ይህ መልዕክት ለሱና ቻናል ባለቤቶች ⭕️
➲ ቻናላችሁን ባጭር ግዜ ዉስጥ በነፃ ማሳደግ የሚያስችል ዌቭ በአዲስ መልክ ጀምረናል
🛑በነፃ ነዉ ፈጥነው ያስመዝግቡ 📥
➦ ከ #300 በላይ ተከታዮች
ከ #500 እና #1000 በላይ ተከታዮች
ላላቸው
⚡️ የሱና ቻናል ለማስመዝገብ አናግሩኝ
👉 @Quran_mylife1
6 497
በሽታው ምን እንደሆነ ላልገባቹህ፣
ቋቁቻ ይባላል፣ ብዙ ጊዜ የሚወጣው አንገት አካባቢ ነው።
ለበለጠ መረጃ 09 72 72 60 01 ይደውሉ
6 497
Repost from N/a
ትክክለኛውን መልስ ያገኝ ሰው ብዙ
የሱና ቻናሎችን add የሚለውን በመጫን
ያገኛል ።
ጥያቄ 1
💎ተዉሂድ በስንት ይከፈላል?
6 497
ብዙ ሙስሊም ወንድምና እህቶች
የሚገኙበት
🪞ልብ የሚነኩ ዲናዊ ምክሮች🥹
◌ ልዩ የሆኑ ዳዓዋዎችን
◍ ቁርዓን እና ሀዲስ የምታገኙበት
◌ ምርጥና ተወዳጅ ቻናል ተጋበዙልኝ🎉
🎈ሙስሊም አይዋሽም ተቀላቀሉ🎈
