ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
رفتن به کانال در Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
نمایش بیشتر2 923
مشترکین
+3224 ساعت
+3727 روز
+36630 روز
آرشیو پست ها
+1
አህያ ሲሰለጥን እንዲህ ነው AI በደንብ ችላችሁበታል ወደዳችሁ ጠላችሁም አማራ ያሸንፋል። አለቀ አፋብን ድርጅታችን!!
የብልፅግና አገዛዝ 101ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ክፉኛ መመታቱ ተገለፀ!!
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ አፄ አምደጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር መርሐቤቴ ዓለም ከተማ መሽጎ የነበረው 101ኛ አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለ ጦር፣ ለኃይል ቅያሪ እንቅስቃሴ እያደረገ ባለበት ሰዓት በፋኖ የደፈጣ ጥቃት ከፉኛ መመታቱን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ኃላፊ አስታወቀ።
የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፣ ጠላት ከዓለም ከተማ ተነስቶ ወደ ኮላሽ ቀበሌ የኃይል ቅያሬ ለማድረግ ሲንቀሳቀስ፣ የወገን ኃይል ልዩ ቦታው ከማጋስ መሳለሚያ እስከ አበርጅት ድረስ ደፈጣ በመያዝ፣ ጠላት አቅዶት የነበረውን የኃይል ቅያሬ እቅድ እዳያሳካ ሲደረግ የሰውና የንብረት ኪሳራ ማስተናገዱን ታውቋል።
ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ የተከፈተው ጥቃት እስከ ቀኑ 07:00 ሰዓት ድረስ የዘለቀ ሲሆን፣ መጀመሪያ ከተደረገው የደፈጣ ጥቃት ወደ ተሟላ የግንባር ውጊያ በመቀየር፣ የጠላትን እቅድ ያከሸፈ፣ የንብረትና የኃይል ውድመት ያደረሰ ውጊያ መካሔዱን አክሎ ገልጿል።
በዚሕ ኦፕሬሽን በርካታ የጠላት ኃይል የተደመሰሰና የቆሰለ ሲሆን፣የተመታው ኃይል አሁንም ድረስ እዳልተነሳና ቁስለኛዎችን ብቻ ወደ ዓለም ከተማ እናት ሆስፒታል እያመላለሰ እንደሚገኝ ከስፍራው ባለን መረጃ አረጋግጫለሁ ብሏል። በደረሰበት ድንገተኛ ጥቃት የተደናገጠው የጠላት ኃይል፣ የዋርኝና የኮራ ተራሮችን በዶሽቃና በዙ-23 ከባድ መሣሪያዎች እየደበደበ እደሚገኝ ገልጿል።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 202ኛ ኮር ዞብል ጃኖ ክፍለ ጦር በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አደረሰ።
ነሐሴ 25/ 2018 ዓ.ም
ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ ጠላት ከአራት የተለያዩ አቅጣጫዎች፣ ማለትም ከቡሆና በጉንትር፣ ከጫንድባ በኳክ፣ ከጯሂት በሳንኪሳ እንዲሁም ከቆላድባ በባርካው በኩል የተቀናጀ ጥቃት ለመፈጸም እንቅስቃሴ አድርጎ ነበር። ሆኖም ግን የጠላትን እንቅስቃሴ አስቀድመው ሲከታተሉ የነበሩት የክፍለ ጦሩ የቃኝ ቡድኖችና ጀግኖች የሰጡት ፈጣን እና ብቁ ምላሽ የጠላትን እቅድ አክሽፎታል።
በተለይም በጫንድባ-ሽመልድባ ቀጠና ተንከል ምድር ላይ በተሰነዘረበት ድንገተኛና ከባድ ጥቃትና ምት ጠላት ከፍተኛ ስብራት አስተናግዶ፣ ሳይሳካለት ወደ መጣበት የመመለስ ግዴታ ውስጥ ወድቋል። ይህም የቃኝዎችን የላቀ የመረጃ የበላይነትና የክፍለ ጦሩን ዝግጁነት በግልጽ ያሳየ ውጊያ ነበር።
በተመሳሳይ በተንከል-ቀንወጣ ምድር የመሸገውን የጠላት ኃይል እስከ አይከል ጭልጋ ድረስ በማስጠጋት ከፍተኛ ምት ያረፈበት ሲሆን፣ በዚህ የተበሳጨው ዘረ ፈጅ ስርዓት በደንቢያና በጭልጋ የነበረው የጠላት ኃይል በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ ጥቃት ሲፈጽምና ንብረት ዘርፎ ወደ መጣበት አቅጣጫ ተመልሷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የጠላቶቻችንን የከፋፍለህ ግዛ ሴራ ያከሸፈ ታሪካዊ ህዝባዊ ውይይት በላይ አርማጭሆ ተካሄደ!
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም
በላይ አርማጭሆ ወረዳ ጃኒከው ንዑስ ወረዳ በአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር አዘጋጅነት የቅማንት ማህበረሰብ የሃይማኖት አባቶችና የአካባቢው አባላት በተገኙበት ሰፊና ታሪካዊ የሕዝብ ውይይት ተካሄደ።
በመድረኩ አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 305ኛ ኮር የቀጣና 1 ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ መምህር አበባው ወርቁ እና የ52ኛ ክፍለ ጦር ባብየው የሻለቃ ዋና አዛዥ አርበኛ ማሩ ኪዴ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፤ የፋኖነትን ታሪካዊ ዳራ እና የትግል መነሻ ምክንያቶች ፣ የትግሉን ዋና ዋና አላማዎችና ግቦች፣የአማራና የቅማንት ህዝብ ማህበራዊ መስተጋብርን በተመለከተ ለተወያዬቹ በዝርዝር አስረድተዋል። የአማራ ፋኖ ትግል ዘር፣ ቀለም፣ ሃይማኖትና ጎጥ ሳይለይ ሁሉንም አቃፊ የሆነ፣ የሕዝቦችን እኩልነት የሚያረጋግጥና አገራዊ አንድነትን የሚያስከብር የነጻነት መንገድ እንጂ ሕዝብን ከሕዝብ የሚለይ እንዳልሆነ በአጽንኦት አስገንዝበዋል።
በተደጋጋሚ በጠላቶችና በፖለቲካ ቁማርተኞች ሲሰራበት የነበረው የማንነት ውጥረት፣ የከፋፍለህ ግዛ ሴራና በሁለቱ ማህበረሰቦች መካከል መጠራጣርን የመፍጠር እኩይ አጀንዳ እና ስሁት አካሄድ መሆኑን መረዳት አስፈላጊ ነው ተብሏል።
በመድረኩ ላይ የተሳተፉት አስተያየት ሰጭዎች የአማራና የቅማንት ሕዝብ በደም፣ በጋብቻና በሃይማኖት የተጋመደ አንድ ሕዝብ በመሆኑ ለፖለቲካ ትርፍ ሲሉ ክፍተት እና ስንጥቅ ለመፍጠር የሞከሩ አካላት ጥረት እንዳልተሳካ ገልጸዋል። ቀደም ሲል በሁለቱ ሕዝቦች መካከል እገታ፣ የከብት ዝርፊያ፣ የህዝብ መፈናቀልና የብጥብጥ ድራማ በመስራት ሕዝባዊ ዕረፍት ለመንሳት ሲሰሩ የነበሩ ሌቦችና የብልጽግና ስርዓት ተላላኪዎች፤ ፋኖ ወደ ቀጠናው መንቀሳቀስ ከጀመረበት ጀምሮ ይፈጠሩ የነበሩ የሰላም እጦት መመለሱን የመድኩ ተሳታፊዎች አረጋግጠዋል።
በመጨረሻም፣ ሁለቱ ወንድማማች ሕዝቦች የጋራ ጠላት እንዳላቸውና አጠቃላይ የከፋፍለህ ግዛው አጀንዳ የውጭና የውስጥ ጠላቶች ስልት መሆኑን በመገንዘብ፣ ለሴረኛው ስርዓት በር ሳይከፍቱ አጋጣሚዎችን ሁሉ በጋራ ለመመከት ሙሉ መግባባት ላይ ደርሰዋል።
የጃኒከው ንዑስ ወረዳ ሕዝብ እናትና አባትን፣ ወንድምና እህትን የሚለይ ምንም ዓይነት ተፈጥሯዊ ኡደት በሌለበት እና ማህበራዊ ውቅር ውስጥ የገቡ አካላትን አሳፍሮ መመለሱን በመግለጽ፤ ፋኖ ለቆመለት ፍትሃዊ ትግል ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጥ፣ በማንኛውም ጊዜና ሰዓት ከጎን እንደሚሆኑና ሰላማቸውን በጋራ ለመጠበቅ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ነው።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በወለጋ አማራዎች ላይ መጠነ ሰፊ ጭፍጨፋ እያካሔደ ያለው የሸመልስ አብዲሳ ሸኔና የኦሮሚያ ገዳ ልዩ ኮማንዶ ጥምረት "በአንድ መድረክ ላይ ተቀምጠው" የሚያሳይ ተጨባጭ ፍቶግራፍ የአማራው ቄራ ከሆነችው ከወለጋ ሰማይ ስር!
25/12/2018 ዓ.ም
የአገዛዙ ጄኔራሎችና ኮሎኔሎች በዲማ ጊዮረጊስ ገዳም፣ በዲማና ደብረፅሞና ኗሪዎች ላይ ከፍተኛ ውድመትና ዝርፊያ ፈፅሞል!!
64ኛ ክ/ጦር ነሀሴ 24/018 ዓ.ም
አገዛዙ በም/ጎጃም ዞን እነማይ ወረዳ ዲማ ጊዮረጊስ ገዳም፣ በዲማ ከተማ እና ደብረፅሞና ቀበሌ ኗሪዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ እንግልት፣ ድብደባ፣ዛቻ፣ ፆታዊ ጥቃት፣ ውድመት፣ ዝርፊያና ንፁሃንን በመረሸን በአለም ላይ ተፈፅመው የማይታወቁ አሰቃቂ ወንጀሎችን በዲማ ከተማ በመፈፀም ወደ መጣበት ቦታ ተመልሶ ሄዶል።
ለሰው ልጆች ዕርህራሄ የሌላቸው የብልፅግና አገዛዝ አስፈፃሚ አካላት ጄኔራል ሶፊያ በክሪንና ጄኔራል ብረሃኑ ጥላሁን እና ኮሎኔል ፀጋየ በም/ጎጃም እነማይ ወረዳ ታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ ሜካናይዝድ፣ መድፍ፣ BM፣ ዙ23፣ ሞርተር፣ ዲሽቃና በረካታ የእግረኛ ሰራዊት በመያዝ ከጥዋቱ 1:30 እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት በቅዱሳን ምድር እና በአርበኞች መፍለቂያ የሆነችው ዲማ ከተማ የሚገኙት የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ ልጆች ጋር ባካሄደው ውጊያ ከፍተኛ ኪሳራ በማስተናገዳቸው ምክንያት ይዘውት የገቡትን ወራሪ ሀይል ትዛዝ በመስጠት በታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ ገዳም፣ በዲማና ደብረፅሞና ቀበሌ ኗሪዎች ላይ እንግልት፣ ውድመትና ዝሪፊያ እንዲፈፀም ትዛዝ በመስጠት የባንዳነት ስራቸውን ለህዝባቸው እንዲህ አሳይተዋል።
በዲማ ከተማ የገባው አገዛዙ ጥምር ጦር በታላቁ ዲማ ጊዮረጊስ ገዳም የሚገኙ አባቶችን በማሰር፣ በማንገላታት፣ ዛቻ በመፈፀም፣ በገዳማ የሚኖሩ መነኩሳት ውስጥ 6 የገዳሙ አባቶችና እናቶች ከፍተኛ ቁስለኛ አድርጓል። አገዛዙ በተኮሳቸው ከባድ መሳሪያዎች የገዳሙ መጠለያ ቤቶችና ዲማ ጊዮርጊስ ሙዚየም ከፍተኛ ጉዳት አስተናግዶል። በዲማ ከተማ እና ደብረፅሞና ቀበሌ የሚገኙ ኗሪዎች መኗሪያ ቤት ወድሞል፣ ቤት ውስጥ ይጠቀሙበት የነበረው የቤት ዕቃ ወድሟል። ቤት ውስጥ ይጠቀሙበት የነበረው እህል፣ ዱቄት፣ ሽሮ በረበሬና ሙሉ የቤት ዕቃ በማውደም እና በመዝርፍ በዲማ ከተማና ደብረፅሞ ቀበሌዎች የሚገኙ ኗሪዎች ላይ ከፍተኛ ወንጀሎችን ፈፅሞል።
በመጨረሻም በዲማ ከተማ ሰፍሮ የነበረው ከጎጃም የተለያዩ ቦታዎች የተሰባሰበው የሶስት ክ/ጦሮች ጥምር ጦር በአይበገሬዎቹ የ64ኛ ክ/ጦር ሰራዊት ቀለበት ውስጥ መግባታቸውን ሲያረጋግጡ ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 7:00 ሰዓት ጨለማን ተገን አድርገው ወደ መጣበት ቦታ ተመልሶ ወጥቷል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ነሀሴ 24/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
እንዲገባህ ነው የፃፍኩልህ እዛው በጎጥህ ዝምታ የነፃነት መንገዴ እንጅ እንደ አንተ በእየቤቱ እየሔድኩኝ ማውራት እችል ነበር ስለዚህ አርፈህ ተቀመጥ የመጨረሻ ነው የምነግርህ አንተ እና እኔ እንለያያለን!! #dave #Amhara
አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ''እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር ''በጠላት ላይ የማያዳግም እርምጃ ወሰደ!!
ነሐሴ 24/12/2018 ዓ.ም
ፀረ-ህዝብ የሆነው ስርዓት ብልፅግና፣ ያደራጀው አድማ ብተና ኃይል በቀን 24/12/2018 ከቀኑ 6፡00 ሰዓት አካባቢ መነሻውን ከአንኮበር ከተማ በማድረግ በፓትሮል ተጭኖ ወደ ቁንዲ በመጓዝ ላይ እያለ፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር 3ኛ ሻለቃና የኮሩ ቃኝዎች በቅንጅት ድንገተኛ እርምጃ ወስደውበታል። ይህ እርምጃ የተወሰደው ልዩ ቦታው ቁንዲ ጊዮርጊስ ላይ ሲሆን ወጤታማ ምት በመሆኑ የጠላት ኃይል መከላከል ሳይችል በርካታ አድማ ብተና ተጎድቷል ሲል የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ገልጿል።
የወገን ኃይል በወሰደው የደፈጣ ጥቃት፣ መቋቋም ያቀተው የጠላት ስብስብ፣ ወደ አንኮበር ከተማ ለመፈርጠጥ ጥረት ቢያደርግም፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለጦር የ2ኛ ሻለቃ እና የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ቃኝዎች ልዩ ቦታው አሸዋ መድፊያ አካባቢ መንገዱን ዘግተው በመፈርጠጥ ላይ የነበረውን ጠላት በጨበጣ ውጊያ በርካታ ኃይሉ ላይ መጠነ ሰፊ ርምጃ ተወስዷል።
በዚሕም የጠላት መመላለሻ የነበረው ፓትሮል መኪና በወገን ጥይት ተመትቶ ከጥቅም ውጪ ሲሆን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ሙትና በርካታ ቁስለኞች በሌላ መኪና ተጭኖ ወደ መጣበት ከተማ ለመመለስ ተገዷል ሲል አክሎ ገልጿል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር 23ኛ ነበልባሉ ክፍለ ጦር አይበገሬዋ 3ኛ መብረቅ ሻለቃ በዘረ ፈጁ ስርዓት ጦር ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አደረሰ።
ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም
መነሻውን ከወረታ ከተማና እና ከዓለም በር ከተማ ያደረገው የጠላት ኃይል ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት በአሲቃ ከተማ ላይ ሙሉ ከበባ በማድረግ ከንጋቱ 11:30 ላይ ተኩስ የከፈተ ቢሆንም፣ 3ኛ መብረቅ ሻለቃ በተለመደው ጀግንነቷና በላቀ ወታደራዊ ጥበብ በጠላት ላይ መብረቃዊ ምት እንዲያርፍበት ሆኗል። ከፍተኛ ኪሳራ የደረሰበት የጠላት ኃይልም እየተዝረከረከ ወደመጣበት እንዲመለስ ተገዷል።
በሌላ በኩል 23ኛ ነበልባሉ ክፍለ ጦር 1ኛ ተከዜ ሻለቃ እና ተወርዋሪ ሻለቃ ከሀገረ ሰላምና ከመነጉዘር በመነሳት ወጂ አርባ አምባን እና ወጂ ጊዮርጊስን በማካለል ሌሊቱን ወጂ ከተማ ላይ ምሽግ ይዞ የነበረውን የጠላት ኃይል ከበባ ውስጥ በማስገባት ቀኑን ሙሉ ሲቀጠቅጡት ውለዋል።
ይህ የድል ውሎ የጀግኖች ሰማዕታት የሻለቃ ሙሉዬ ፈጠነ 3ኛ ዓመት፣ የኮማንዶ በለጠ ሙጨ 2ኛ ዓመት እንዲሁም የሻለቃ ሰለሞን 3ኛ ወር መታሰቢያ ቀን በመሆኑ ዕለቱን ልዩ ያደረገ የአውደ ውጊያ ውሎ ነበር።
በተመሳሳይ በሌላኛው አውደ ውጊያ በታች ፎገራ ቀጠና ሻጋ ቀበሌ ሶስት ፓትሮል ጦርና የወረዳ አመራሮችን ይዞ በመንቀሳቀስ ሻጋ ማርያም ቤተክርስቲያን ማህበረሰብ ሰብስቦ የፕሮፓጋንዳ ስራ ለመስራት ቢያስብም በ2ኛ ሻለቃ አባላት ውጊያ ተከፍቶበት ከፍተኛ ኃይሉ ሙትና ቁስለኛ ሆኖ ተመልሷል ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ነው።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
#ሴት_ፋኖ፦ #የትግሉ_ሞተር #የነፃነቱ_ማገር አርበኛ ፍቅርተ የታሪክ ማህደር ሲገለጥ፣ የድል አውድማው ሲቃኝ፣ በጀግንነት ስም ዝርዝር ውስጥ የሴት ፋኖ አሻራ የጎላ ነው። እርሷ ለትግሉ ድምቀት ብቻ ሳትሆን፣ መላውን እንቅስቃሴ ወደፊት የምታስፈነጥር "ሞተር" ናት።
በአንድ እጇ ቤቷን፣ በአንድ እጇ ነጻነቷን የጨበጠችው ሴት ፋኖ፤ በቁጭት ስትነሳ ተራራ የምታንቀጠቅጥ፣ ስትራመድም ምድርን የምታናውጥ የጽናት ተምሳሌት ናት። ሰንቀው ለሚዘምቱት ወንድሞቿ ስንቅ ብቻ ሳትሆን፣ ለውጊያው ወኔ፣ ለድሉም ተስፋ የምትዘራ የብርታት ምንጭ ናት።
የእርሷ የትግል ሞተርነት በሁለት መልክ ይገለጣል፦ #በግንባር፦ እንደ ጥይት ተኳሽነቷና እንደ ስትራቴጂ ነዳፊነቷ፣ ጠላትን የምታስበረግግ ቆራጥ ተዋጊ ናት።
#በጀርባ፦ እንደ እናትነቷና እንደ እህትነቷ፣ የትግሉን ማገዶ አቀጣጥላ፣ ተስፋው እንዳይከስም የምታደርግ የህልውና ዋስትና ናት።
#ሴት_ፋኖ ስትታጠቅ፣ ትጥቁ የብረት ብቻ ሳይሆን የሞራልና የማንነት ጭምር ይሆናል። እርሷ በሌለችበት ትግል ውስጥ ትንፋሽ የለም፤ እርሷ ባልቆመችበት አውድማ ላይም ፅናት አይታሰብም። በእውነትም፣ የነፃነት ጉዞው ጋሪው ህዝብ ከሆነ፣ ያንን ጋሪ አድካሚውን ዳገት አስወጥታ ለድል የምታበቃው ብቸኛዋ ሞተር "ሴት ፋኖ" ናት!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አሳምነው 5ኛ ዕዝ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር የሴት ጅግና ታጋይ የሻለቃ ቃኘ አርበኛ ፍቅርተ
ቆሎ መሸጫ እና ገመሱ ላይ የሎቬድ ሹፌሩ ሲሰናበት ተሽከርካሪው እና የአብይ ጀበና ሰባሪወች አስክሬን መንገዱን ዘግተውታል።
=== =====================
.......ነሐሴ24/2018 ዓ.ም
አስደናቂ ጥምረት እና መናበብ የታየበት ድንቅ ኦፕሬሽን በዛሬው እለት ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ ከሞጣ14 መኪና 4ኮንቲነሮች የጫኑ በዙ=23 ታጅቦ የመጣውን ጠላት እና ከአዴት እና ከገረገራ 4 መኪና የአብይ ጀበና ሰባሪ ሀይል በማምጣት ሽፋን በመስጠት አጅቦ ወደ ባህርዳር ለመጎዝ የተነሳውን ሀይል ድንቅ ጥምረት በመፍጠር በተጠና በተናበበ መልኩ አይበገሬወች 54ኛ ክፍለ ጦር ሻለቃ ሁለት (መብረቅ ሻለቃ) እና 33ኛ ክፍለ ጦር ዮሀንስ አለማየሁሻለቃ እና አበረ አዳሙ ሻለቃ በግራ እና በቀኝ በዲሽቃ እና በብሬንአጣድፈው አንድ የሎቬድ ሹፌሩ በአልሞ ተኳሾች የተሰናበተ ሲሆን ተሽከርካሪው ላይም ጉዳት በማድረስ ልዩ ስሙ ገመሶ ከርቩ ላይ ጥቃት በመፈፀም እጀባ ላይ የነበረው ጀበና ሰባሪ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን የፋኖ ሐይሎች የሞት ሽረት ትግል በማድረግ ቆሎ መሸጫ ላይ በሁለት አቅጣጫ ገዥ መሬቶችን ቀድመው በመያዝ መሀል መስመሩ በአስክሬን የተዘረከረከ ሲሆን አስክሬኑን እና ከሞት የተረፈውን ቁስለኛውን ለማንሳት ለ7ሰዓት ያህል ተሽከርካሪወችን በማገድ ወደ አዴት ሆስፒታል ቁስለኞችን ሲያመላልስ ውሏል።
የአፋብን 2ኛ ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
#ጥቆማ_ለንጉስ_ተክለኃይማኖት_ሺ_አለቃ‼️
ይድረስ ለጀግኖቻችን ለንጉስ ተ/ሀይማኖት ሺ - አለቃ!
ይህ አረመኔ ጨቃኝ ሌባ በደ/ማርቆስ ከተማ ምኒሻ በመሆን የደ/ማርቆስን ማህበረሰብ በመደብደብ በመዝረፍ የፋኖ ደጋፊ በማለት በመረሽን ድፍን ሁለት አመት ለደ/ማርቆስ ህዝብ ስቆቃ ሁኖብን የቆየ ሲሆን ታህሳስ 19 /2017 ዓ.ም ብሬን በመያዝ ፋኖን ሲቀላቀለ ለእኛ ለደ/ማርቆስ ህዝብ እንደ አይን ብሌን ለምናያቸው የንጉስ ተ/ሀይማኖት ሺ - አለቃ ይበትንብናል በማለት ስጋት ኖሮብን ተጠንቀቁ ከማለት ውጪ ምንም ማምጣት አልቻልንም ነበረ። ብዙም ሳይቆይ ንጉስ /ተሀይማኖት ለሁለት ተከፈለች ይህም የሱ ስራ ነው ከከፈለ በኃላ ሺ - አለቃ ብኔን በሱ መረጃ በደ/ማርቆስ አስገደለ፣ በስንት ስቃይ ንጉስ አንድ ሆነች እሱም አመራር ሁኖ ተመረጠ ፣ በሚሊሻ ስም ሲያሰቃየን የነበረ ሌባ ማልያ ቀይሮ በፋኖ ስም ደግሞ ዘረፈን፣ አንገራገርን ፣አስቃያን ፣አድማ እየላከ ፋኖ ነኝ እያለ አዘረፈን የምንነግረው ሰው አጣን እየዘርፈን በተስፋ ቆየን በስተመጨረሻ ንጉሶን ደ/ዘይት የሚባል ቀበሌ አስከባባት የፈጣሪ ስራ ሆኑ ንጉሷ ወጣች በስተመጨረሻ የፀድ የምትባል ቀባሌ በተኙበት አስከበባቸው ስራውን ሲጨርስ ተምልሶ ወደ ብልፅግና መጣ።
ነግሩ እንዲህ ነው ደ/ማርቆስ በመግባት እያሰቃየን ነው ድጋሚ የፋኖ ደጋፊ ነበራቸው በማለት እያንገራገረ እየዘርፉን ነው እባካቸው ንጉሶች እናተ ጀግኖች ብዙ ባንዳዎችን ያጠፋችሁ ኩራታችን ናችሁና ይህን ሰውየ አስወግዱልን እኛም በምንችለው እየለፋን ነው ይህን የምታነብ አማራ በየ ሚዲያው አሰራጭ፣ ንጉሶች ይህንን ሌባ እርምጃ ውሰዱልን ሲሉ ከንስር አማራ ጋር ቆይታ ያደረጉ በደል እየደረሰባቸው ያሉ የደብረማርቆስ ኗሪዎች ለንጉስ ተክለኃይማኖት ሺ አለቃ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል::
#Dave #Amhara
24/12/2018 ዓ.ም
