ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
رفتن به کانال در Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
نمایش بیشتر2 924
مشترکین
+10524 ساعت
+3357 روز
+33630 روز
آرشیو پست ها
#ሰበር አንድ ኮሎኔልና ሁለት የሻለቃ አዛዦችን ጨምሮ 213 ዩአገዛዙ ወታደሮች ተደመሰሱ‼️
በአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር ፊታውራሪ ገበየሁ ክ/ጦር አርበኞች አውላላ ከተማ በመሸገው የጠላት ኃይል ላይ መብረቃዊ እርምጃ በመውሰድ ከፍተኛ ድል አስመዘገቡ።
በዚህ አውደ ውጊያ የተደመሰሰ #ኮሎኔል_አለሙ የተባለ አንድ ከፍተኛ አዛዥ #ሻለቃ_አስምሮ አዲሱ እና #ሻለቃ_ኮስትር የተባለ የሬጅመንት አዛዦችን ጨምሮ 213 የአገዛዙ ወታደሮች ተደምስሰዋል።
#ባለክሻፋ_ዲሽቃን ጨምሮ ሁለት ዲሽቃ፤ ሁለት ብሬን፤ ሁለት አርባጎራሽ እና በቁጥር 173 የነፍስ ወከፍ ክላሽ በፋኖ ቁጥጥር ስር ውሏል።
በተጨማሪም ስድስት ሳጥን የዲሽቃ ተተኳሽ፤ ዘጠኝ ሳጥን የብሬን ተተኳሽ፤ 25 አስቃጥላ የክላሽ ተተኳሽ፣ ሁለት ወታደራዊ ፓትሮል እና ሁለት አይሱዙ ተሽከርካሪ ሙሉ ሬሽን፣ የህክምና ቁሳቁስና መድሀኒት፤ ሁለት የዲሽቃ አፈሙዝ፤ አንድ የብሬን አፈሙዝ፤ ዘጠኝ መገናኛ ሬድዮ፤ 200 የክላሽ ካዝና፣ 93 የወገብና የደረት ትጥቅ፤ ሦስት የጦር ሜዳ መነፀር፤ 65 የውሃ ኮዳ በአርበኞቹ ተማርኳል።
በዚህ ተጋድሎ 16 የአገዛዙ ወታደሮች እጅ ከፈንጅ ሲማረኩ፡ 52 ወታደሮች ደግሞ ወደ ጫካ ተበትነው ደብዛቸው ጠፍቶ መቅረቱ ታውቋል ሲል በአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር የህዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል።
23/12/2018 ዓ.ም
የፖሊስ አዛዡ ከአገዛዙ በመኮብለል ጀብደኛው ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 15ኛ ኮርን ተቀላቀለ!
ነሀሴ 22/2018 ዓ.ም የመሃል አምሓራ ሳይንት ወረዳ ፖሊስ ዋና አዛዥ የነበረው ዋና ሳጅን ዓለምነው ገረመው ከአገዛዙ በመኮብለል 154ኛ አትሮንስ ክፍለጦርን ተቀላቅሏል።
የግለሰብን ሥልጣን ለማፅናት ከእፉኝት ልጆች ጋር ሲተባበሩ የነበሩ አካላት ከመሠረታዊ ወታደር እስከ አዛዥ ድረስ እየፈረሱ ወደ ወገን መግባታቸው ግፈኛውን ቡድን (ኦህዴድ/ብልፅግና) እረፍት የለሽ ተቅበዝባዥ አድርጎታል። ዋና ሳጅን ዓለምነው ገረመው ከጨፍጫፊውና ስርዓት አልበኛው ቡድን ጋር በማበር ለዓመታት የቆየ ቢሆንም እውነቱ ሲገለጥለትና የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ ለመከላከልና ለመቀልበስ የሚደረገው ተጋድሎ ፍትሐዊና ተፈጥሯዊ ግዴታ መሆኑን በመረዳቱ እነሆ ወደ አማናዊው የትግል ሜዳ ለመግባት ተገዷል።
ዋና ሳጅን ዓለምነው ስለ ኦህዴድ/ብልፅግና ወንጀለኛ ቡድን ሲናገር "አገዛዙ በሚያደርገው እብደት ላይ የተመሠረተ አንድ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ የማግለል፣ የመበደል፣ የማሳደድ፣ የመዝረፍና የመግደል ሰይጣናዊ ስራ ስላንገሸገሸኝ፣ ይህን ጭራቃዊ ገዳይ ቡድን ለመታገል ወስኜና ቆርጨ መጥቻለሁ" ሲል ምሬቱንና የስርዓቱን ሁለንተናዊ የጭካኔ ባህሪ ገልጿል።
የሽንፈቱንና የውርደቱን መራራ ፅዋ በግድ እየተጋተ ያለው ደመ-ነፍሳዊው አገዛዝ ብቸኛ መመኪያ የነበረው ወታደራዊ ኃይሉ ወኔው መሰለቡ፣ ሞራሉ መዋዤቁና ሀሞቱ የመፍሰሱ ነገር ሥልጣኑን የዛፍ ላይ እንቅልፍ አድርጎበታል። የባንዳነት ስነልቦና ተጣብቷቸው የተከበረውንና መተኪያ የሌለውን አማራዊ ማንነታቸውን ሽርፍራፊ ጥቅም ለመመፅዎት ሲሉ የሸጡ፤ ለኦህዴድ/ብልፅግና ወንጀለኛ ቡድን በማጎብደድና በማሸርገድ፣ ግፍ የወለደውን አብዮት በማደናቀፍ ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ከሞራላዊና ሰብዓዊ እሴቶች መካከል ይቅር ባይነትና ሆደ-ሰፊነት የአማራ መገለጫዎቹ በመሆናቸው ከጥፋታቸው የተማሩትን በመቀበል ስም ከሌለው የውሻ ሞት ራሳቸውን እንዲያተፉ መልካም አጋጣሚ ስለተፈጠረላቸው ብዙዎች ወደ ትክክለኛው መንገድ እየተመለሱ ነው።
መዳረሻው ድል እና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ነሃሴ 23/2018 ዓ.ም
+1
22ኛ ክ/ጦር በባህር ዳር ከተማ ድል ተቀናጅቷል።
አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ እዝ 102ኛ ኮር 22ኛ ክ/ጦር ራሱን አድሶ ወትሮ ዝግጁነቱን በማረጋገጥ ባህር ዳር ከተማ ላይ የሰፈረውን የጠላት ሀይል መደምሰስ ጀምሯል። በዛሬው እለት (23/12/2018 ዓ/ም) በባህርዳር ከተማ አስተዳድር ዳግማዊ ሚሊሊክ ክ/ከተማ አዲስ አለም ቀበሌ ላይ ሰፍሮ የነበረው የጠላት ሀይል 07 የሰው ሀይል ሲማረክ ቀሪውን ሙሉ በሙሉ በመደምሰስ ስራውን አሀዱ ብሎ ጀምሯል። በተደረገው አውደ ውጊያ ብሬን ፣በርካታ ክላሾች ፣የብሬና እና የክላሽ ተተኳሾች ፣የብሬን ሸንሸልና ኪት እንዲሁም ወታደራዊ ሻጣዎች መማረክ ተችሏል።
163ኛ ክፍለጦር የምስረታ ቀኑን ምክንያት በማድረግ የተሃድሶ መድረክ አከናወነ!!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 16ኛ ኮር 163ኛ ክ/ጦር የምስረታ ቀኑን ምክንያት በማድረግ የተሃድሶ ፕሮግራም በዛሬዉ ዕለት ማለትም በቀን 23/2018 ዓ.ም ያደረገ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይም የኮሩ እና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በዚህም ፕሮግራም ላይ የተገኙ የ16ኛ ኮር ከፍተኛ አመራሮች ለሰራዊቱ ለቀጣይ ድርጅታዊ ግዳጆችን ለመወጣት ዝግጁ እንድሆኑ እና የቀጣይ የግዳጅ አፈፃፀም አቅማቸውን ለማሳደግ ያመች ዘንድ የግንዛቤ ማስጨበጫ በአመራሮቹ በኩል ተሰጥቷቸዋል።
የ16ኛ ኮር አመራር አርበኛ አለበል ተካልኝ በፕሮግራሙ ላይ "ክፍለ ጦሩ ከምስረታ እስከ አሁናዊ የአመጣጥ ቁመና ምን ይመስላል የሚለውን ታሪካዊ ዳራ በሰፊው ለአባላቱ አብራርተዋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ የክፍለጦሩ የፓለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ መኩሪያ አጋዥ ክፍለጦሯ "ጥቅምት 27/2016 ዓ.ም በዋድላ ወረዳ ቋና ላይ መመስረቱን ያወሱ ሲሆን ፤ ክፍለጦሩ በበርካታ ቦታዎች እየተንቀሳቀሱ የሰውና የትጥቅ ኃይላቸውን ማጠንከርና ማጎልበት እንደተቻለ በመግለፅ ይህ እንዲሆን ጠንክረው 24 ሰዓት ለሰሩ አመራሮች እና አባላት የላቀ ምስጋና አቅርበዉ ይህ ታህድሶ ታሪካዊ ቀን መሆኑን ገልፀዉ የአማራ ህዝብ እንዲጠፋ ከተፈረደበት አደጋ
በማውጣትና የትግሉን የመጨረሻ አሸናፊነታችንን ለማረጋገጥ ከመቸውም በላይ ጠንክረን የምንሰራበት ጊዜ ነዉ" ሲሉም መልክታቸውን አስተላልፈዋል ።
የክፍለጦሩ ወታደራዊ አዛዥ ጌታቸው ጉቸ ለቀጣይ ግዳጅ ራሳችንን በማዘጋጀት ህዝባችን ልክ እንደስካሁኑ ከጎናችን በማሰለፍ ጠላትን መደምሰስ ይገባል ብለዋል።
በመቀጠል የስራ መመሪያ እና የግዳጅ ተልዕኮ በመስጠት መልዕክት ያስተላለፉት የክፍለጦሩ ም/ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ በረከት ያለው "ኮራችን በግዳጅ ጥሩ ውጤት እንዳመጣና ታሪካዊ ኃላፊነታችንን በአግባቡ እንድንወጣ ጠንካሮች ሆነን መገኘት ይገባል ብለዋል ሲል 16ኛ ኮር ቃል አቀባይ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!
ነሀሴ :- 23/ 2018 ዓ/ም
ህዝባዊ መድረኮች ተጠናክረው ቀጥለዋል ----------
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ጀኔራል ኃይሌ ዘ ውባንተ ክፍለ ጦር በስማዳ ወረዳ የኳሳ ከተማ እና የአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ የትግሉ ሁኔታ እና በድርጅታዊ አደረጃጀት ዙሪያ የመከረ ሰፊ ሕዝባዊ ውይይት አካሂደዋል።
ነሐሴ 23 /2018 ዓ.ም
በተካሄደው በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የዕዙ የአደረጃጀት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አበበ መልኬ፣ የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ ምክትል ኃላፊ አርበኛ ዋሴ ታደሰ፣ የዕዙ ገንዘብ ያዥ አርበኛ መላክ ተስፋ እና ሌሎች የክፍለ ጦሩ አመራሮች ተገኝተዋል።
በውይይቱ ወቅት የአደረጃጀትና የአንድነት ሂደቱን ማፋጠን፣ የትግል እንቅፋቶችን በጋራ ማስወገድ፣ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመገምገም ማስተካከል እንዲሁም ሕዝባዊ ድጋፍን በማጠናከር ትግሉን ማፋጠን በሚሉ ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ በስፋት ተመክሮ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
በመድረኩ የተሳተፉት የኳሳ ከተማ ነዋሪዎች በበኩላቸው የጎንደር ፋኖ ወደ አንድነት መምጣቱ ታላቅ ደስታና ተስፋ እንደፈጠረላቸው ገልፀው፣ ዕዙ ወደ አንድ ወጥ አደረጃጀት መሰብሰቡ ወታደራዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን በተቀናጀ መልኩ ለመምራት የሚያስችል በመሆኑ ነው ብለዋል።
ይህ የውስጥ ጥንካሬና ቅንጅት ቀደም ሲል ይስተዋል የነበረውን የኃይል መበታተን በማስቀረት የትግሉን ስትራቴጂካዊ አካሄድ ያጠናክረዋል፤ በተበታተነ እንቅስቃሴ ምክንያት በህዝቡ ዘንድ ይፈጠር የነበረውን ስጋትና ተስፋ መቁረጥ አስወግዶ የተሻለ የወደፊት ዕይታ እንዲኖር ያደርጋል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በሌላ በኩል ነዋሪዎቹ የተጀመረውን የአንድነት አደረጃጀት ውጤታማ ለማድረግ የደጀንነት ሚናቸውን በተግባር ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ማረጋገጣቸው፣ በህዝቡና በፋኖ መካከል ያለውን ጠንካራ ቁርኝት ያሳያል። የደጀንነት ተሳትፎው በሎጅስቲክስ ፣የግንባር ተሳትፎና እና በወታደራዊ መረጃ አቅርቦት ላይ የተመረኮዘ በመሆኑ፣ ህዝቡ ትግሉን የራሱ አድርጎ መውሰዱንና ለውጤታማነቱም ቀጣይነት ያለው ቁሳቁሳዊና ሞራላዊ ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን ያረጋገጠበት አጋጣሚ ነበር ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ነው።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በዛሬው ዕለት በምዕራብ ጎንደር ዞን በገንዳውሃ ከተማ ፣ በኩመር አውላላ ቀበሌ ፣ ኮሎኔል አለሙ የተባለ የመከላከያን አዛዥ ጨምሮ 28 ወታደሮች አዞበር ኪዳነምህረት ቤ/ክ፣ ያለምንም ወታደራዊ ስነስርዓት፣ በስካቫተር ተቆፍሮ በጅምላ በአንድ ጉድጏድ መቀበራቸውን ቦታው ላይ የነበሩ እማኞች ነግረውኛል።
17 አካላቸው በከፍተኛ ሁኔታ የቆሰሉ ወታደሮች ደግሞ ህክምና እየተደረገላቸው ነው።
አብይ አህመድ ስልጣኑ የተከለለው በየ 3 ወሩ አሰልጥኖ በሚያስገባቸው መቶሺ ወጣቶች ደም እንደሆነ ለማንም ግልፅ ነው።
ተጠናክሮ የቀጠለው የንፁኋን የዘር ማጥፋት ዘመቻ!!!
ነሐሴ22/2018ዓም
የኦሮሞ ፅንፈኛ ኃይሎች የጭካኔ ጥግ፣የሰው በላነት ማንነት አዉሪያዊ ባህሪና ድርጊት በገሀድ አፍጥጦ ወጥቷል።
ሰሞኑን በተለይም በዚህ ሳምት በርካታ ካህናቶች ፣ መለኮሳት ፣ አይነስውራን ፣ አዛውንቶች እናቶች ፣ አባቶች እና ህፃናት እድሁም እናቷ በግፍ ተገላባት በአራተኛ ቀን የተገኘች ህፃን እናት ጨምሮ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገለዋል።አብያተ ቤተክርስቲያኖች ተቃጥለዋል። ሀብት ንብረታቸውን በመዝረፍና ቤታቸውን በማቃጠል በርካታ በሺዎች የሚቆጠሩ ንፁኋኖች ተፈናቅለው በጫካ ይገኛሉ።
በምስራቅ ወለጋ ጊዳ አያና ወረዳ አንገር ጉትን ከተማ ነዋሪዎች እና አመራር ይህን እየተሰራ ያለን ግፍ በመቃወማቸው እዲቆም በማሳሰባቸው በግፍ እየታሰሩና እየተረሸኑ ይገኛሉ።በሌላኛው ከባለፈው አውደ ውጊያ ወደኋላ ከተመለሱት አራት ተሽከርካሪዎች ውስጥ የነበረው የማዕከላዊ ዕዝ ኮለኔል መግስቱ ለምን ንፁኋን የጨፈጨፋል እና የሃይማኖት ተቋማት ይቃጠላል ብሎ በመናገሩ ወደ አስር አስገብተውታል።
በተጨማሪም ትናት አንገር ጉትን ከተማ ላይ ሶስት ጥቋቁር በሬዎችን በማረድ የጉምዝን ፣ የትግራይንና አድሁም በከፈተኛ የአማራን ህዝብ ለመጨፍጨፍ ተማምለው መነሳታቸውን ከአከባቢው ያገኘነው ምንጭ ያሳያል።
ይህ በእድህ እዳለ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ከማሽ ዞን ሶጌ ወረዳ ሜጢ ቀበሌ ላይ ለበርካታ ወራቶች ይህ ገዳይ ሀይል የጉሙዝ ንፁኋኖች ተጨፍጭፈዋል። የህን ግፍ ያየ የጉሙዝ ታጣቂዎች በመልሶ ማጥቃት የደረሰበትን ምት መቋቋም ሲያቅተው ት/ቤቶችን እና መደሮችን አቃጥሎ ወደኋላ ፈርጧል።
በሌላኛው ዛሬ ከጠዋቱ 2:00ሰዓት መነሻውን ከአንገር ጉትን በማድረግ ይህ የክልሉ ገዳይ ሃይል እደተለመደው አሰቃቂ ግፎችን ለመስራት ወደ ምስራቅ ወለጋ ጊዳ አያና ወረዳ ልዩ ቦታዋ "ዋጀ" እምትባል አከባቢ እየሄደ ባለበት ሁለት ክፍለጦሮች ቀድመው ቦታውን በመያዝ አይቀጡ ቅጣት ተቀቶ ወደኋላ በመመለስ አቦ ሰፋር ላይ የአቦ ቤተክርስትያን ደብርን በማቃጠል እና ከዚህ በፊት ያቃጠለውን ፋድቃ ከተማን አልፎ አልፎ የተረፉትን ቤቶች እያቃጠለ ይገኛል።
ግፍ የወለደን:ግፈኞችን የምቀጣ የአንሻ ሰይድ ወድሞች ነን‼️
አፋብን አንሻ ሰይድ 4ኛ ዕዝ
ህ/ግንኙነት መምሪያ
ሕዝብን የማንቃትና የማደራጀት ስራዎች በወሎ ቤተ-አማራ ተጠናክረው ቀጥለዋል!
የአፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ከጠላት ነፃ ባወጣቸውና በተቆጣጠራቸው ቀጠናዎች ሕዝባዊ አደረጃጀት የመስራትና ማህበረሰቡን ፓለቲካዊ ትጥቅ የማስታጠቁ ተግባር በአናብስቶቹ የምኒልክ 1ኛ እዝ አመራሮች ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ከተቆጣጠራቸዉ ወረዳዎች መካከል በሰሜን ወሎ ዞን ዉስጥ አንዱ የሆነዉ ዳውንት ወረዳ 011፣ 012 እና 013 ቀበሌዎች ጋር ህዝባዊ የንቅናቄ መድረክ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።
በዚህ መድረክ በርካታ የቀጠናዊ ማህበረሰብ ተሳታፊ የሆነ ሲሆን በአማራ ሕዝብ የትግል አላማና ግብ፣ አሁናዊ የትግሉ ቁመና ፣ ስለ ትብብርና አጋርነት እንዲሁም ከሕዝቡ ስለሚጠበቀው አብይ ጉዳይ ሰፊ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ፍፁም መግባባት ላይ ተደርሷል።
"የብልፅግናውን አገዛዝ ለመቅበር እና ከፋኖ ጎን ለመቆም የቀበሌው ማህበረሰብ በልበ-ሙሉነት የተናገረ ሲሆን በሃሳብ፣ በፀሎት፣ በፋይናንስ እና በሎጀስቲክ ትግሉን ለማገዝ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልፀዋል"።
የአደረጃጀት፣ የሃሳብና ወታደራዊ ጥራት ባላቸው መሪዎች የሚመራው ጀብደኛው ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ለአማራነት እየከፈለ ያለውን ዋጋ ያደነቁ ሲሆን "ዕዛችሁ በአማራነት ውሃ-ልክ የተሰፋ በመሆኑ ኮርተንባችኋል ሲሉ ሃሳባቸውን ገልፀዋል"።
ተሳታፊዎቹ አክለውም "መንግስት ለመሆን የሚታገል ሃይል እንዲሁም መዋቅር አፍርሶ መዋቅር እየተከለ የሚገኘው ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ ካለው አቅምና ስብስብ አንፃር ከዚህ በላይ እንጠብቃለን ብለዋል"።
በውይይቱ ላይ የምኒልክ 1ኛ ዕዝ አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አሰፋ መሰለ፣ የምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ብርሃን አረጋ ፣ የዳውንት ወረዳ ሲቨል አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አርበኛ ገቨርመንት ደስታው እንዲሁም የወረዳው ሲቨል አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል።
በመጨረሻም የአማራን ትግል እስከአሁንም ያለመሰሰት ልጆቻችንን መርቀን በመስጠት፣ ሎጀስቲክና ፋይናንስ በማሰባሰብ እያገዝን ቢሆንም የአገዛዙን እድሜ ለማሳጠር እና የእኛንም የስቃይ ዘመን ለማሳጠር ከዚህ በላይ ስለሚበቅብን ሁሉንም ነገር ለመስጠት ዝግጁነታቸውን አሳይተዋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ነሃሴ 22/2018 ዓ.ም
በምንጃር ከሰም ግንባር የአገዛዙ ሪፐብሊካን ጋርድ ክፍለ ጦር እየፈረሰ ፋኖን እየተቀላቀሉ ይገኛሉ!!
ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም
የፋኖን ህዝባዊ ትግል እና የህዝብን በደል የተረዱ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት አረመኔውን ስርዓት ማገልገል አንፈልግም በማለት የህዝብን ትግል በስፋት መቀላቀላቸውን ቀጥለውበታል።
አገዛዙ ያለበትን ከፍተኛ ውጥረት እና ሽንፈት ለመሸፈን ወጣቶችን በአፈሳ፣ ነጋዴውን ደግሞ በከባድ የግብር ጫና በማስጨነቅ ላይ ይገኛል። በከፍተኛ አመራሮች እና በአክቲቪስቶቹ አማካኝነት የጦርነት ቅስቀሳ በሚያፋፍምበት በዚህ ወቅት፣ በህዝብ ላይ የሚፈጸመውን ግፍና በደል የተቃወሙ የሰራዊቱ አባላት መከላከያውን በመክዳት ከህዝባዊ ኃይሉ ጎን መሰለፍን አፋጥነውታል።
በዚህም መሰረት፣ የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮርን መቀላቀላቸውን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ገለፀ። የአገዛዙ ሪፐብሊካን 5ኛ ክፍለ ጦር እየፈረሰ የሚገኝ ሲሆን፣ የዚሁ ክፍለ ጦር አባል የሆነው ወጣት አስር አለቃ መኳንንት ከሀገር አፍራሹና ህዝብ ጨፍጫፊው ስርዓት ጋር ከመቆም፣ የህዝብን ወገንተኝነት መምረጥ ይበልጣል በማለት ነበልባል ክፍለ ጦርን ተቀላቅሏል።
አስር አለቃ መኳንንት ወደ ነበልባል ክፍለ ጦር ሲቀላቀል፦
➢ 1 ዘመናዊ ጥቁር AK-103 ክላሺንኮቭ
➢ 1 ሙሉ የደረት ትጥቅ ከነሙሉ ተተኳሽ ጥይቱ
➢ 1 የጦር ሜዳ መነጽር (ቢኖኪዩላር)
እነዚሕን ንብረቶች በመያዝ የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦርን በክብር ተቀላቅሏል ሲል የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት አክሎ ገልጿል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
+1
ሰበርርር ባንዳ የማፅዳት ዘመቻው
ተጠናክሮ ቀጥሏል💪💪
#_4ክላሽ_እናአንድ_እስኬስ_ገቢተደርጎል።
ንስሮቹ ሞጣ ቀራኒዮ ኬላ ላይ5ሚሊሻወችን እና በማስወገድ #_4ክላሽ እና1እስኬስ ገቢ ማድረግ ችለዋል።
►►►►►►►►►►►►►►►►►►
...... ነሐሴ22/2018 ዓ.ም
ሞጣ ማርያም ሰፈር ጩኸቱ በርክቷል ከስርዓቱ ጋር በመመሳጠር ያሉ ሎሌወች የከተማውን ሰላማዊ ህዝብ ምክኒያት በመፍጠር አንግልት ሲፈፅሙ የነበሩ የእንግዴ ልጆች ለሆዳቸው ያደሩ የሚሊሻ አባላትን በዛሬው እለተ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም በ54ኛ ክፍለ ጦር በንስሮች እስከወዲያኛው ተሸኝተዋል።
በዛሬው እለት የተሰናበቱት፦
1.መንግስቴ ሽታው...........ሚሊሻ
2.ሐብታሙ መንግስቴ......ሚሊሻ
3.ይታየው .......ሚሊሻ
4.መኳንት...........ሚሊሻ 5.የሽዋስ..........የተባሉ ሚሊሻወች ሙት እና ቁስለኛ ሲሆኑ ከሞት የተረፉት 3ቱ ከፍተኛ ቁስለኛ ሆነው ነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ ላይ መሆነቻውን ከአካባቢው ነዋሪወች ማረጋገጥ ችለናል።
ለከርሳቸው ብለው አማራን ከድተው ለብልፅግና ሲያጎበድዱ የነበሩ ሲሆን በዛሬው እለት በአዳኞች ተሸኝተዋል። ወደ ትክክለኛ ማንነታቸህ ተመለሱ ኑ የሚል ጥሪያችን እናቀርባለን።
የአፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የራስን ችግሮች በራስ አቅም መፍታትና በጠንካራ መሠረት ላይ መቆም ለዘላቂ ውሳኔ እና ነፃነት ዋናው መሠረት ነው።
ትናንት በወንድሞችህ ላይ እንድትዘምትና ደም እንድትቃባ ስምሪትና ግዳጅ የሰጠ አካል፣ ነገ ደግሞ በሌላ ምክንያት በገዛ ራስህ ላይ ላለማዝመቱና እሚፈልገውን ዓላማ ላለማስፈፀሙ ምንም ዓይነት ዋስትና የለም።
በመሆኑም ከውጭ ከሚመጣ ጊዜያዊ ትብብር እና የወደፊቱን ዕድል በማያስተማምን አካል ላይ መጣልና የሩቅ ናፋቂ መሆን ተገቢ አይደለም፤ የሩቅ እገዛ ከውጭ ሲያዩት የቀረበና አጋር የሚመስል ቢሆንም፣ ውስጡ ግን በራስ ጥቅም ላይ የተመሠረት ያደረገ ታማኝነት የሌለው ሊሆን ይችላል።
በእውነትና በተግባር አብሮህ የሚቆመውና ሊደርስልህ የሚችለው ከጎንህ ያለው ወንድምህ ብቻ ነው። የደም፣ የባህልና የጋራ ታሪክ ቁስልም ሆነ ደስታ በጋራ የሚጋራው ቅርብህ ያለው ወንድም ስለሆነ፣ ልዩነቶችን በውይይትና በውስጥ አቅም መፍታት ይበልጥ አስፈላጊ ይሆናል።
የውጭ ተፅዕኖዎችና ጊዜያዊ ወዳጅነቶች ሲቀያየሩ፣ የደምና የቅርብ ወንድምነት ትስስር ግን ዘላቂ ነው። በመሆኑም መፍትሔውን ከውጭ ከሚመጣ የሩቅ ናፍቆት ይልቅ በመካከላችሁ ባለው እውነተኛ ወንድማማችነትና የጋራ ውይይት ውስጥ መፈለግ የመጨረሻውና አስተማማኙ መንገድ ነው።
አሸናፊነታችን አድነታችን ላይ ነው!
በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ የአማራ ተወላጆች በሚኖሩባቸው በሁለት መንደሮች ብቻ በተፈፀመ ጭፍጨፋ የተገደሉ ከ67 በላይ የንፁኋን አስከሬን ስርዓተ ቀብር መፈፀሙ ታወቀ!
ጭፍጨፋው የተፈፀመው በጊዳ አያና ወረዳ መንደር 3 ላይ እና መንደር 22 ላይ ሲሆን፡ በዚህም በተለይ በመንደር 3 አከባቢ የ27 ንፁኋኖች ስርዓተ ቀብር ሲፈፀም ጥቃቱ ባለመቆሙ የሌሎቹን አስከሬን ስርዓተ ቀብር መፈፀም እንዳልተቻለ ነው ምንጮች የገለፁት።
በተመሣሣይ በመንደር 22 አከባቢ ነሀሴ 19/2018 ዓ/ም የ17 ንፁኋን አስከሬን ስርዓተ ቀብር የተፈፀመ ሲሆን፡ ትናንት እና ዛሬ ነሀሴ 21/2018 ዓ/ም ደግሞ ከ23 በላይ የንፁኋን አስከሬን ስርዓተ ቀብር ተፈፅሟል።
በመንደር 22 በተከፈተው ጥቃት ከተገደሉት መካከል በስለታማ መሣሪያ ተቆራርጠው የተገደሉት የ85 ዓመት አዛውንቱ አባ አየለ አረጋ እና ባለቤታቸው እማሆይ እስከዳር ገላው ይገኙበታል።
በወረዳው ፈንደቃ ቀበሌንና አንዶዴ ዲቾ ሻሾበር ከተማን ጨምሮ በመንደር 3 በመንደር 22ና በሌሎች የወረዳው አከባቢዎች ላይ በተፈፀመውና አሁንም ተባብሶ በቀጠለው በዚህ ዘግናኝ መንግስት መር ጭፍጨፋ፡ እስካሁን ባለው 200 የሚደርሱ የአማራ ተወላጆች መገደላቸውን ምንጮች አክለው ገልፀዋል።
መከላከያ ሠራዊትን ጨምሮ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይል፣ ገዳ ኮማንዶ፣ ጋቸና ሲርና፣ ረፔሎላና የሚኒሻ ኃይሉ በቅንጅት በምስራቅ ወለጋ ዞን በአማራ ተወላጆች ላይ የከፈቱት ጭፍጨፋ አድማሱን አስፍቶ ተባብሶ ቀጥሏል።
