ru
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Открыть в Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Больше
2 924
Подписчики
+10524 часа
+3357 дней
+33630 дней
Архив постов
እንዲገባህ ነው የፃፍኩልህ እዛው በጎጥህ ዝምታ የነፃነት መንገዴ እንጅ እንደ አንተ በእየቤቱ እየሔድኩኝ ማውራት እችል ነበር ስለዚህ አርፈህ ተቀመጥ የመጨረሻ ነው የምነግርህ አንተ እና እኔ እንለያያለን!! #dave #Amhara

አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር  ''እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር ''በጠላት ላይ የማያዳግም እርምጃ ወሰደ!!         ነሐሴ  24/12/2018 ዓ.ም  ፀረ-ህዝብ የሆነው ስርዓት ብልፅግና፣ ያደራጀው አድማ ብተና ኃይል በቀን 24/12/2018 ከቀኑ 6፡00 ሰዓት አካባቢ መነሻውን ከአንኮበር ከተማ በማድረግ በፓትሮል ተጭኖ ወደ ቁንዲ በመጓዝ ላይ እያለ፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር 3ኛ ሻለቃና የኮሩ ቃኝዎች በቅንጅት ድንገተኛ እርምጃ ወስደውበታል። ይህ እርምጃ የተወሰደው ልዩ ቦታው ቁንዲ ጊዮርጊስ ላይ ሲሆን ወጤታማ ምት በመሆኑ የጠላት ኃይል መከላከል ሳይችል በርካታ አድማ ብተና ተጎድቷል ሲል የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ገልጿል።  የወገን ኃይል በወሰደው የደፈጣ ጥቃት፣ መቋቋም ያቀተው የጠላት ስብስብ፣ ወደ አንኮበር ከተማ ለመፈርጠጥ ጥረት ቢያደርግም፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለጦር የ2ኛ ሻለቃ እና የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ቃኝዎች ልዩ ቦታው አሸዋ መድፊያ አካባቢ መንገዱን ዘግተው በመፈርጠጥ ላይ የነበረውን ጠላት በጨበጣ ውጊያ በርካታ ኃይሉ ላይ መጠነ ሰፊ ርምጃ ተወስዷል።  በዚሕም የጠላት መመላለሻ የነበረው ፓትሮል መኪና በወገን ጥይት ተመትቶ ከጥቅም ውጪ ሲሆን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ሙትና በርካታ ቁስለኞች በሌላ መኪና ተጭኖ ወደ መጣበት ከተማ ለመመለስ ተገዷል ሲል አክሎ ገልጿል።  " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

​አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር 23ኛ ነበልባሉ ክፍለ ጦር አይበገሬዋ 3ኛ መብረቅ ሻለቃ በዘረ ፈጁ ስርዓት ጦር ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አደረሰ። ነሐሴ 24/2018
​አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር 23ኛ ነበልባሉ ክፍለ ጦር  አይበገሬዋ 3ኛ መብረቅ ሻለቃ  በዘረ ፈጁ ስርዓት ጦር ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አደረሰ። ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም መነሻውን ከወረታ ከተማና እና ከዓለም በር ከተማ ያደረገው የጠላት ኃይል ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት በአሲቃ ከተማ ላይ ሙሉ ከበባ በማድረግ ከንጋቱ 11:30 ላይ ተኩስ የከፈተ ቢሆንም፣ 3ኛ መብረቅ ሻለቃ በተለመደው ጀግንነቷና በላቀ ወታደራዊ ጥበብ በጠላት ላይ መብረቃዊ ምት እንዲያርፍበት ሆኗል። ከፍተኛ ኪሳራ የደረሰበት  የጠላት ኃይልም እየተዝረከረከ ወደመጣበት  እንዲመለስ ተገዷል። ​በሌላ በኩል 23ኛ ነበልባሉ ክፍለ ጦር 1ኛ ተከዜ ሻለቃ እና ተወርዋሪ ሻለቃ ከሀገረ ሰላምና ከመነጉዘር በመነሳት ወጂ አርባ አምባን እና ወጂ ጊዮርጊስን በማካለል ሌሊቱን ወጂ ከተማ ላይ ምሽግ ይዞ የነበረውን የጠላት ኃይል ከበባ ውስጥ በማስገባት ቀኑን ሙሉ ሲቀጠቅጡት ውለዋል። ይህ የድል ውሎ የጀግኖች ሰማዕታት የሻለቃ ሙሉዬ ፈጠነ 3ኛ ዓመት፣ የኮማንዶ በለጠ ሙጨ 2ኛ ዓመት እንዲሁም የሻለቃ ሰለሞን 3ኛ ወር መታሰቢያ ቀን በመሆኑ ዕለቱን ልዩ ያደረገ የአውደ ውጊያ ውሎ ነበር። በተመሳሳይ በሌላኛው አውደ ውጊያ በታች ፎገራ ቀጠና ሻጋ ቀበሌ ሶስት ፓትሮል ጦርና የወረዳ አመራሮችን ይዞ በመንቀሳቀስ ሻጋ ማርያም ቤተክርስቲያን ማህበረሰብ ሰብስቦ የፕሮፓጋንዳ ስራ ለመስራት  ቢያስብም  በ2ኛ ሻለቃ አባላት ውጊያ ተከፍቶበት ከፍተኛ ኃይሉ ሙትና ቁስለኛ ሆኖ ተመልሷል ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ነው። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

#ሴት_ፋኖ፦ #የትግሉ_ሞተር #የነፃነቱ_ማገር አርበኛ ፍቅርተ ​የታሪክ ማህደር ሲገለጥ፣ የድል አውድማው ሲቃኝ፣ በጀግንነት ስም ዝርዝር ውስጥ የሴት ፋኖ አሻራ የጎላ ነው። እርሷ ለትግሉ ድምቀት ብቻ ሳትሆን፣ መላውን እንቅስቃሴ ወደፊት የምታስፈነጥር "ሞተር" ናት። ​በአንድ እጇ ቤቷን፣ በአንድ እጇ ነጻነቷን የጨበጠችው ሴት ፋኖ፤ በቁጭት ስትነሳ ተራራ የምታንቀጠቅጥ፣ ስትራመድም ምድርን የምታናውጥ የጽናት ተምሳሌት ናት። ሰንቀው ለሚዘምቱት ወንድሞቿ ስንቅ ብቻ ሳትሆን፣ ለውጊያው ወኔ፣ ለድሉም ተስፋ የምትዘራ የብርታት ምንጭ ናት። ​የእርሷ የትግል ሞተርነት በሁለት መልክ ይገለጣል፦ #በግንባር፦ እንደ ጥይት ተኳሽነቷና እንደ ስትራቴጂ ነዳፊነቷ፣ ጠላትን የምታስበረግግ ቆራጥ ተዋጊ ናት። #በጀርባ፦ እንደ እናትነቷና እንደ እህትነቷ፣ የትግሉን ማገዶ አቀጣጥላ፣ ተስፋው እንዳይከስም የምታደርግ የህልውና ዋስትና ናት። #ሴት_ፋኖ ስትታጠቅ፣ ትጥቁ የብረት ብቻ ሳይሆን የሞራልና የማንነት ጭምር ይሆናል። እርሷ በሌለችበት ትግል ውስጥ ትንፋሽ የለም፤ እርሷ ባልቆመችበት አውድማ ላይም ፅናት አይታሰብም። በእውነትም፣ የነፃነት ጉዞው ጋሪው ህዝብ ከሆነ፣ ያንን ጋሪ አድካሚውን ዳገት አስወጥታ ለድል የምታበቃው ብቸኛዋ ሞተር "ሴት ፋኖ" ናት! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አሳምነው 5ኛ ዕዝ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር የሴት ጅግና ታጋይ የሻለቃ ቃኘ አርበኛ ፍቅርተ

ቆሎ መሸጫ እና ገመሱ ላይ የሎቬድ ሹፌሩ ሲሰናበት ተሽከርካሪው እና የአብይ ጀበና ሰባሪወች አስክሬን መንገዱን ዘግተውታል። === ===================== .......ነሐሴ24/2018 ዓ.ም አስደናቂ ጥምረት እና መናበብ የታየበት ድንቅ ኦፕሬሽን በዛሬው እለት ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ ከሞጣ14 መኪና 4ኮንቲነሮች የጫኑ በዙ=23 ታጅቦ የመጣውን ጠላት እና ከአዴት እና ከገረገራ 4 መኪና የአብይ ጀበና ሰባሪ ሀይል በማምጣት ሽፋን በመስጠት አጅቦ ወደ ባህርዳር ለመጎዝ የተነሳውን ሀይል ድንቅ ጥምረት በመፍጠር በተጠና በተናበበ መልኩ አይበገሬወች 54ኛ ክፍለ ጦር ሻለቃ ሁለት (መብረቅ ሻለቃ) እና 33ኛ ክፍለ ጦር ዮሀንስ አለማየሁሻለቃ እና አበረ አዳሙ ሻለቃ በግራ እና በቀኝ በዲሽቃ እና በብሬንአጣድፈው አንድ የሎቬድ ሹፌሩ በአልሞ ተኳሾች የተሰናበተ ሲሆን ተሽከርካሪው ላይም ጉዳት በማድረስ ልዩ ስሙ ገመሶ ከርቩ ላይ ጥቃት በመፈፀም እጀባ ላይ የነበረው ጀበና ሰባሪ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን የፋኖ ሐይሎች የሞት ሽረት ትግል በማድረግ ቆሎ መሸጫ ላይ በሁለት አቅጣጫ ገዥ መሬቶችን ቀድመው በመያዝ መሀል መስመሩ በአስክሬን የተዘረከረከ ሲሆን አስክሬኑን እና ከሞት የተረፈውን ቁስለኛውን ለማንሳት ለ7ሰዓት ያህል ተሽከርካሪወችን በማገድ ወደ አዴት ሆስፒታል ቁስለኞችን ሲያመላልስ  ውሏል። የአፋብን 2ኛ ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

#ጥቆማ_ለንጉስ_ተክለኃይማኖት_ሺ_አለቃ‼️ ይድረስ ለጀግኖቻችን ለንጉስ ተ/ሀይማኖት ሺ - አለቃ! ይህ አረመኔ ጨቃኝ ሌባ በደ/ማርቆስ ከተማ ምኒሻ በመሆን የደ/ማርቆስን ማህበረሰብ በመደብደብ በመዝረፍ የፋኖ ደጋፊ በማለት በመረሽን ድፍን ሁለት አመት ለደ/ማርቆስ ህዝብ ስቆቃ ሁኖብን የቆየ ሲሆን ታህሳስ 19 /2017 ዓ.ም ብሬን በመያዝ ፋኖን ሲቀላቀለ ለእኛ ለደ/ማርቆስ ህዝብ እንደ አይን ብሌን ለምናያቸው የንጉስ ተ/ሀይማኖት ሺ - አለቃ ይበትንብናል በማለት ስጋት ኖሮብን ተጠንቀቁ ከማለት ውጪ ምንም ማምጣት አልቻልንም ነበረ። ብዙም ሳይቆይ ንጉስ /ተሀይማኖት ለሁለት ተከፈለች ይህም የሱ ስራ ነው ከከፈለ በኃላ ሺ - አለቃ ብኔን በሱ መረጃ በደ/ማርቆስ አስገደለ፣ በስንት ስቃይ ንጉስ አንድ ሆነች እሱም አመራር ሁኖ ተመረጠ ፣ በሚሊሻ ስም ሲያሰቃየን የነበረ ሌባ ማልያ ቀይሮ በፋኖ ስም ደግሞ ዘረፈን፣ አንገራገርን ፣አስቃያን ፣አድማ እየላከ ፋኖ ነኝ እያለ አዘረፈን የምንነግረው ሰው አጣን እየዘርፈን በተስፋ ቆየን በስተመጨረሻ ንጉሶን ደ/ዘይት የሚባል ቀበሌ አስከባባት የፈጣሪ ስራ ሆኑ ንጉሷ ወጣች በስተመጨረሻ የፀድ የምትባል ቀባሌ በተኙበት አስከበባቸው ስራውን ሲጨርስ ተምልሶ ወደ ብልፅግና መጣ። ነግሩ እንዲህ ነው ደ/ማርቆስ በመግባት እያሰቃየን ነው ድጋሚ የፋኖ ደጋፊ ነበራቸው በማለት እያንገራገረ እየዘርፉን ነው እባካቸው ንጉሶች እናተ ጀግኖች ብዙ ባንዳዎችን ያጠፋችሁ ኩራታችን ናችሁና ይህን ሰውየ አስወግዱልን እኛም በምንችለው እየለፋን ነው ይህን የምታነብ አማራ በየ ሚዲያው አሰራጭ፣ ንጉሶች ይህንን ሌባ እርምጃ ውሰዱልን ሲሉ ከንስር አማራ ጋር ቆይታ ያደረጉ በደል እየደረሰባቸው ያሉ የደብረማርቆስ ኗሪዎች ለንጉስ ተክለኃይማኖት ሺ አለቃ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል:: #Dave #Amhara 24/12/2018 ዓ.ም

​የፍኖተ ሰላም አደባባይ ምዕራብ ጎጃም ነሐሴ 2015 ዓ.ም ከ40 በላይ ንጹሃን በአንድ ጊዜ ረግፈዋል። በከተማዋ መሀል ህዝብ በተሰበሰበበት አደባባይ ላይ የተፈጸመ የድሮን ጥቃት ነው። በተለይም በመላው አማራ በስም ላልተጠቀሱ እና ​የመርሳ ገበያ (ሰሜን ወሎ) እና ሸዋ ሮቢት፣ ቢቸና፣ ደብረ ማርቆስ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሲቪሎች በተለያዩ ጊዜያት። በገበያ ቀናት እና በህዝብ መንደሮች ላይ የሚወርዱ የከባድ መሳሪያ ድብደባዎች እና ከተሞች በተያዙ ማግስት የሚደረጉ የቤት ለቤት ፍተሻዎች ንጹሃንን ሰለባ አድርገዋል። ​በ​ቋሪት ወረዳ (ፈረስ ቤት ከተማ 2016 ዓ.ም)፦ በአብይ አህመድ መከላከያ ሰራዊት በተፈጸመ የከባድ መሳሪያ ድብደባ በአንድ የመኖሪያ መንደር ውስጥ ከ18 በላይ ንጹሃን እናቶችና ህጻናት በቤታቸው ውስጥ እያሉ ተገድለዋል። ​በምስራቅ ጎጃም ህዳር 2016 ዓ.ም ከባድ ውጊያዎችን ተከትሎ በተደረገ የቤት ለቤት ፍተሻ ከ25 በላይ ንጹሃን ወጣቶች ያለ ምንም ፍርድ በአደባባይ ተረሽነዋል። ​ዋሸራ ማርያም አዊ ዞን በቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ ተጠልለው የነበሩ ከ15 በላይ አዛውንቶችና ምዕመናን በግጭቱ ሳቢያ ህይወታቸውን እንዲጠፋ ተደርጓል። በአዲስ አበባ ከተማ (ስልታዊ ማግለል እና የጅምላ እስራት ​በዋና ከተማዋ የተፈጸሙት ወንጀሎች ህዝቡ ድምፅ አልባ እንዲሆን ለማድረግ ታቅደው የተከናወኑ የመዋቅር ጥቃቶች ናቸው። ​መደበኛ ያልሆኑ የጦር ሰፈሮች አዋሽ ሰባት፣ ገላን፣ ኮልፌ ማሰልጠኛ)፦ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከ100,000 በላይ ታሳሪዎች የአማራ ተወላጅ የሆኑ ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች፣ የቪዲዮ ባለሙያዎችና ወጣቶች ያለ ምንም የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ታድነው በእነዚህ በረሃማ ካምፖች ውስጥ ለእንግልት ተዳርገዋል። ​የአዲስ አበባ መግቢያ በሮች ሰንዳፋ፣ ሱሉልታ፣ ቡራዩ ​ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ተጓዦች ተጎድተዋል። ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተፈናቀሉና በሰላማዊ መንገድ ወደ ዋና ከተማዋ ለመግባት የሞከሩ ዜጎች በማንነታቸው ብቻ መታወቂያቸው እየታየ ወደ ከተማዋ እንዳይገቡ ተከልክለዋል። ​ፖለቲካዊ እና ህሊናዊ ማጠቃለያ ​ተጠያቂነትን ማድበስበስ፦ በእነዚህ ሁሉ ቦታዎች የተፈጸሙትን የጅምላ ጭፍጨፋዎች አስቀድሞ መከላከል ያልቻለው፣ ሲፈጸምም ዜጎቹን ጥሎ የሸሸው እና እስካሁንም ለተጎጂዎች ፍትህን ያልሰጠው ይኸው ስልጣን ላይ ያለው የብልፅግና መራሹ ስርዓት ነው። ዛሬም ድረስ በአማራ ግዛቶች ከተሞችና ገጠር ቀበሌዎች የሚዘንበው የድሮን እሳት፣ በአዲስ አበባ ከተማ መግቢያ በሮች ላይ የሚፈጸመው ስልታዊ ማግለል እና የሺዎች ዜጎች የጅምላ እስራት የብልፅግና ስርዓት ቀጥተኛ ፖሊሲ ውጤቶች ናቸው። ​ስለሆነም፣ ይሄንን የአማራን ህዝብ የህልውና አደጋ ወደ ጎን በመተው እና የተፈሰሰውን የንጹሃን ደም በመርሳት የብልፅግናን ስልጣን በምርጫ ለማደስ መሞከር ከተገደሉት ንጹሃን በላይ የታሪክና የህሊና ተጠያቂነትን የሚያስከትል ነው። ይህ ጉዳይ ለፖለቲካ የድጋፍ ስምምነት የሚቀርብ ሳይሆን፣ የንጹሃን ዜጎችን የመኖር መብት እና የሀገርን ህልውና የማዳን ስር ነቀል ጥያቄ ነው። #Dave #Amhara

የማይሻረው የታሪክ ጠባሳ፦ የንጹሃን ደም እና አማራ ጠሉ የብልፅግና ስርዓት ምርጫ!! ​ባለፉት ስምንት ዓመታት በአብይ አህመድ የሚመራው የብልፅግና ስርዓት ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ፣ በመላው ሀገሪቱ በማንነታቸው (በአማራነታቸው) ብቻ ተለይተው በግፍ የተጨፈጨፉት፣ የተፈናቀሉት እና የታሰሩት ውድ የሆኑ የአማራ ልጆች መከራ የታሪክ ጥቁር ማህደር ነው። ​በዚህ እጅግ አሳዛኝ እና አስከፊ ሁኔታ ውስጥ፣ ዛሬ ላይ ቆሞ የአብይ አህመድ የብልፅግና ስርዓት በድጋሚ መምረጥ ማለት በማንነታቸው ምክንያት ህይወታቸውን ባጡት ውድ በሆኑት የእነዚህ ሁሉ ሚሊዮኖችን የአማራ ልጆች ደምና ሰቆቃ ላይ መቀለድ ነው። ​ይህንን የታሪክ እውነታ ከዚህ ቀደም ባልተጠቀሱ ተጨማሪ ቦታዎች፣ ቀበሌዎችና አሃዞች ጭምር በሰፊው እንደሚከተለው ቀርቧል ቀሪ እና የምታውቁት እናንተ በውስጥ አድርሱኝ!!! ​ በኦሮሚያ ክልል የተፈጸሙ ስልታዊ የጅምላ ጭፍጨፋዎች እና ማፈናቀሎች ​በዚህ ክልል ውስጥ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ለትውልድ የኖሩባቸው የገጠር መንደሮች የጅምላ መቃብር ተደርገዋል። ጥቃቶቹ የተፈጸሙት የአብይ አህመድ ጸጥታ ኃይሎች አካባቢውን ጥለው በወጡ ማግስት በሚል ማግስት ሲሆን በዚህም ​የቶሌ ቀበሌ ፍጅት (ምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ) ሰኔ 2014 ዓ.ም በይፋ ከ338 በላይ (የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እንደገለጹት ደግሞ እስከ 500 የሚጠጉ) ንጹሃን። ​የሽመልስ አብዲሳ ኃይል መንደሩን በመክበብ ምንም መከላከያ የሌላቸውን ህጻናት፣ እናቶችና አረጋውያንን በአንድ ቀን ጨፍጭፈው በጅምላ ቀብረዋል። ​የሃዋ ገላን ወረዳ (ቂለም ወለጋ፣ ቲቾ ቀበሌ ሰኔ 2014 ዓ.ም መጨረሻ ከ200 በላይ ሰላማዊ አርሶ አደሮች ተገድለዋል። ከቶሌ ፍጅት ጥቂት ቀናት በኋላ የተፈጸመ የቤት ለቤት እረሸና ሲሆን፣ ንብረታቸው በሙሉ እንዲወድም ተደርጓል። ​የኪረሙ እና ጊዳ አያና ወረዳዎች ምስራቅ ወለጋ ህዳር 2015 ዓ.ም ​ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሟቾች እና ከ500,000 (ግማሽ ሚሊዮን) በላይ ተፈናቃዮች። በዚህም በተደራጀ መልኩ የተከፈተ ጥቃት ሲሆን፣ በተለይ በሀሮ ቀበሌ የተፈጸመው ጭፍጨፋ አካባቢውን ሙሉ በሙሉ ከአማራ ተወላጆች የማጽዳት (Ethnic Cleansing) ስራ የተካሄደበት ነው። ​በአጋምሳ ከተማ እና ጮቢ መንደር ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ነሐሴ 2014 ዓ.ም ከ100 በላይ ንጹሃን አማራ ተገደዋል። ሰላማዊ አርሶ አደሮች በማሳቸው ላይ እና በቤታቸው ውስጥ እያሉ ድንገተኛ ጥቃት ተሰንዝሮባቸዋል ተገድለዋል። ​የጋዋ ቃንቃ ትምህርት ቤት ጭፍጨፋ ምዕራብ ወለጋ ጉሊሶ ወረዳ ጥቅምት 2013 ዓ.ም፦ ከ54 በላይ ንጹሃን አማራዊያን ተገድለዋል። በተናበበ ሲራ የአብይ አህመድ መከላከያ ሰራዊት አካባቢውን ለቆ በወጣ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ የሽመልስ አብዲሳ ኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ የተጠለሉ አማራዎችን ለይተው ረሽነዋል። ​የሰኔ 2012 ዓ.ም የከተሞች ሁከት (ሻሸመኔ፣ ባቱ/ዝዋይ፣ አሰላ፣ ሮቤ፣ አጋርፋ እና ጭሮ ከ200 በላይ ሰዎች በጭካኔ ተገድለዋል። ​የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ሞት ፖለቲካዊ መነሻ በማድረግ፣ በማንነታቸውና በሃይማኖታቸው በተለይ ኦርቶዶክስ የሆኑ አማራዎች ተለይተው በዱላና በሰይፍ ተጨፍጭፈዋል፤ ታሪካዊቷ የሻሸመኔ ከተማ የንግድ ተቋማት ወድመዋል። ​አሙሩ ወረዳ (ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ነሐሴ 2014 ዓ.ም)፦ በዚሁ በመከላከያ እና በሸኔ በተቀናጀ ወረራ ቡድን በአንድ ሳምንት ውስጥ ከ80 በላይ ንጹሃን አርሶ አደሮች የተገደሉ ሲሆን፣ ከ20,000 በላይ ዜጎች መኖሪያ ቤታቸው ተቃጥሎ ተፈናቅለዋል። ​ኑኑ ኢንፓር ቀበሌ (ምስራቅ ወለጋ 2015 ዓ.ም)፦ በማንነታቸው ብቻ ተለይተው ከ35 በላይ የሚሆኑ የአማራ ተወላጆች በቤት ውስጥ ተዘግቶባቸው በህይወት እያሉ የተቃጠሉበት አሰቃቂ ቀጠና ተደርጓል። ​ፈንታሌ ወረዳ ምስራቅ ሸዋ መተሃራ ዙሪያ በ2014 ዓ.ም በስኳር ፋብሪካ እና በአካባቢው እርሻዎች ላይ በቀን ሰራተኝነት እና በነዋሪነት ይኖሩ የነበሩ ከ40 በላይ የአማራ ተወላጆች ተለይተው ተረሽነዋል። ​በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመተከል ማጽዳት ዘመቻ ​በመተከል ዞን የነበረው ጥቃት ዋነኛ ዓላማ በሰፈራ ፕሮግራም ለዘመናት የኖሩትን የአማራ አርሶ አደሮች በማስፈራራት መሬታቸውን እንዲቀሙ ተደርጓል። ​የቢኩጂ ቀበሌ ጭፍጨፋ (ቡለን ወረዳ ታህሳስ 2013 ዓ.ም ከ207 በላይ ንጹሃን አማራ ተጨፍጭፈዋል።በዚህም በአንድ ሌሊት የተፈጸመ ጥቃት ሲሆን፣ ሰለባዎቹ በገጀራና በጥይት ተለይተው ተረሽነዋል። ​የባቡሊስ ቀበሌ (ጉባ ወረዳ) መቃብር ፶" ተብሎ የሚጠራው ልዩ ቦታ፦ በቁጥር ያልታወቁ ነገር ግን በርካታ የአማራ ልጆች በህይወት እያሉ በቡድን ወደ እሳት ተጥለው የተቃጠሉበት እና እጅግ አሰቃቂ የቪዲዮ ምስክርነት ለዓለም የወጣበት ቦታ ነው። ​የዳንጉር፣ ድባጤ እና ማንቡክ ወረዳዎች ከ2012 እስከ 2014 ዓ.ም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሟቾች ተከታታይ የቤት ማቃጠል ንብረት መዝረፍ እና የመንገድ ላይ አድብቶ መግደል ወንጀሎች የተፈጸሙባቸው ቦታዎች ናቸው። በዚህ ሳቢያ ከ100,000 (አንድ መቶ ሺህ) በላይ ተፈናቃዮች በቻግኒ ማረፊያ ካምፕ ውስጥ ተጠልለው ሲሰቃዩ ነበር ​ ​የምዛ ቀበሌ ድባጤ ወረዳ መስከረም 2013 ዓ.ም የወረዳው ባለስልጣናት ባሳዩት ቸልተኝነት ታጣቂዎች በከፈቱት ድንገተኛ ተኩስ ከ45 በላይ ንጹሃን የአማራ አርሶ አደሮች በአንድ ጀንበር ተገድለዋል። ​የቻግኒ ዙሪያ እና ባንቡዋሲ ቀበሌዎች፦ ከቤኒሻንጉል ክልል ተገፍተው የወጡ በአጠቃላይ ከ120,000 በላይ የአማራ ተወላጆች ለዓመታት ያለ መጠለያና ያለ ምግብ በሜዳ ላይ ተጥለው የቆዩበት ታላቅ የሰብአዊ ቀውስ ማዕከል እንዲሆን አድርገውት ነበር። ​ ከሰሜኑ ጦርነት ጋር ተያይዞ የተፈጸሙ የበቀል ፍጅቶች ​የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ በሰላማዊ አማራዎች ላይ መጠነ-ሰፊ ጥቃቶችን ፈጽመዋል። ​የማይካድራ ከተማ ጭፍጨፋ ህዳር 2013 ዓ.ም፦ ከ600 በላይ ንጹሃን አማራ በጦርነቱ መጀመሪያ ሰሞን "ሳምሪ" በተባለ ቡድንና በአካባቢው ሚሊሺያዎች አብዛኞቹ የአማራ ተወላጅ የሆኑ የቀን ሰራተኞች በዱላ፣ በሰይፍና በገመድ ታንቀው የተጨፈጨፉበት እጅግ ዘግናኝ ክስተት ነው። ​የጭና መንደር ፍጅት ደቡብ ጎንደር፣ ዳባት ወረዳ ነሐሴ መስከረም 2013 ዓ.ም ከ120 በላይ ንጹሃን። የሳምሪ ኃይሎች አካባቢውን ጥለው ከመውጣታቸው በፊት የሃይማኖት አባቶችን፣ አረጋውያንንና ህጻናትን በየደጃፋቸው የረሸኑበት የበቀል ጥቃት ነበር። ​የቆቦ ከተማ መንዲዳ እና ፍልኪት መንደሮች ሰሜን ወሎ ነሐሴ 2013 ዓ.ም፦ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሲቪሎች። ወደ ከተማዋ የገቡ ኃይሎች በነዋሪው ላይ ሰፊ የጅምላ ግድያ እና የተቋማት ማውደም ወንጀል ፈጽመዋል። ​[​የጋሸና እና አግሪት አካባቢዎች (ዋድላ ወረዳ ጥቅምት 2014 ዓ.ም ከ80 በላይ ንጹሃን አርሶ አደሮች በጅምላ ተረሽነዋል። ​የአጋምሳ እና ኡርጌሳ ቀበሌዎች ሰሜን ወሎ ጦርነቱ በተፋፋመበት ወቅት በአካባቢው በነበሩ የመኖሪያ መንደሮች ላይ በተፈጸሙ ጥቃቶች ከ50 በላይ ሴቶችና ህጻናት ተገድለዋል። ​በአሁኑ ወቅት በአማራ ግዛት​ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የአብይ አህመድ መከላከያ ሠራዊት የድሮንና የከባድ መሳሪያ ቴክኖሎጂን በከተሞች ላይ በመጠቀም ንጹሃንን እየገደለ ይገኛል።

በመቅደላ ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች ህዝባዊ ውይይትና የመዋቅር ማስተካከያ ተደረገ!! ​በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ በሚገኙ ሁለት ቀበሌዎች የፖለቲካ ግንባታ፣ የአመራር ግምገማና የመዋቅር ማስተካከያ ያተኮሩ ህዝባዊ መድረኮች ተካሂደዋል ። ​በዚሁ መሰረት በቀን 22/12/2018 ዓ.ም በመቅደላ ወረዳው 023 ቀበሌ ህዝባዊ መድረክ የተካሄደ ሲሆን፣ በተመሳሳይ መልኩ በቀን 23/12/2018 ዓ.ም በ022 ኮሬብ ታዳጊ ከተማ ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተካሂዷል። ​በሁለቱም ቀበሌዎች በተካሄዱት በእነዚሁ መድረኮች የምኒልክ 1ኛ ዕዝ ምክትል አደራጃጅ እና የወረዳው ሲቪል መዋቅር አመራሮች የተገኙ ሲሆን፣ ለህዝቡ በፖለቲካ ግንባታ ዙሪያ ሰፊ ገለጻና ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ተሰርቷል። ​በተጨማሪም የነበሩ የቀበሌ መዋቅሮች የስራ አፈፃፀም በጥልቅ ተገምግሞ በተገኙ ክፍተቶች ላይ የእርምት እርምጃዎች የተወሰዱ ሲሆን፣ ክፍተት በነበረባቸው የሃላፊነት ቦታዎች ላይ አዳዲስ አመራሮችን በመመደብ መዋቅሮቹ ሙሉ እንዲሆኑ ተደርጓል። ​ይህ የተካሄደው ውይይትና የተወሰደው የማስተካከያ እርምጃ በአካባቢው መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና ለህዝቡ የሚሰጠውን የአገልግሎት ጥራት ይበልጥ ለማሻሻል ያለመ መሆኑ ተጠቅሷል። የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ ነሃሴ 24/2018ዓ.ም

ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የሲቪል አስተዳደር የተሰጠ ጥብቅ የማስጠንቀቂያ መግለጫ ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ሰዴ ወረዳ መግባት እና ማንኛውም እንቅስቃሴ ማድረግ ላይ የተጣለን ሙሉ ክልከላ እና ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ይመለከታል የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የሲቪል አስተዳደር በሰዴ ወረዳ እና በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ አካላትን እንቅስቃሴ በሚመለከት የሚከተለውን ጥብቅ የማስጠንቀቂያ መግለጫ አውጥቷል። በሰዴ ወረዳ ሥር ለተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች ከተመደባችሁ አመራሮች ጀምሮ እስከ ታችኛው እርከን ድረስ ያላችሁ አካላት በሙሉ፣ ወደ ወረዳው ወሰን ፈጽሞ መግባትም ሆነ ማንኛውንም ዓይነት እንቅስቃሴ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን እናሳውቃለን። ይህ መመሪያ ቀጥተኛ ማኅበራዊ አገልግሎት የሚሰጡ መምህራንን እና የግብርና ባለሙያዎችን ብቻ አይጨምርም። ከእነዚህ ከሁለቱ የሙያ ዘርፎች ውጭ ያለ ማንኛውም ባለሙያም ሆነ አመራር ወደ ወረዳው ግዛት መረገጥ እና መግባት አይችልም፤ ይህንን አልፎ ለሥራም ሆነ ለሌላ ጉዳይ ወደ ሰዴ ወረዳ የሚገባ ማንኛውም አካል ላይ 54ኛ ክፍለ ጦር የማያወላውል እርምጃ የሚወስድ ይሆናል። ለሚከተለው ማንኛውም ዓይነት አደጋ እና ጉዳት ግለሰቡ ራሱ ሙሉ ኃላፊነቱን የሚወስድ መሆኑን እናስነብባለን። ባለፉት ጊዜያት በተለይም ከመጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በተከናወኑ ክስተቶች የአካባቢውን እውነታ በመረዳት፣ ከጓዶቻችሁ የደረሰ ከንቱ መስዋዕትነት እና ውድቀት በቂ ትምህርት እንድትወስዱና ወደ ወረዳው ከመግባት እንድትቆጠቡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ይህ መግለጫ ከወጣበት ከዛሬ ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በጥብቅ ተፈጻሚ የሚሆን ሲሆን፣ መመሪያውን ተላላፎ ወደ ወረዳው በሚገባ ማንኛውም አካል ላይ አስፈላጊው እርምጃ የሚወሰድ ይሆናል። ነሐሴ 24/2018 ዓም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የሲቪል አስተዳደር

አፋብን፤ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፣ አዲሱ ስራ አስፈፃሚ አባላት፤ ለተከታታይ ቀናት ሲያካሄድ የነበረውን ስብሰባ አጠናቀቀ! ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ አዲሱን የስራ አስፈፃሚ አዋቅሮ ይፋ ካደረገበት ሐምሌ 2018 ዓ.ም ጀምሮ ጠንካራ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። የተጓደሉ የኮር አመራሮችን ማሟላት፣ የሦስት ወራት የእቅድ ዝግጅትና የሚዲያና ፕሮፖጋንዳ ስራዎች በአጭር ጊዜ  ከተከናወኑት መካከል ናቸው። ከእነዚህ ስራዎች ጎን ለጎን አዲሱ የስራ አስፈፃሚ አባላት ለተከታታይ 10 ቀናት በአካል በመገናኘት፣ በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሄዷል። ወይይቱ የዕዙን ያለፉት ሦስት ዓመታት የትጥቅ ትግል ጠንካራና ደካማ ሂደቶችን በጥልቀት ዳሷል። የቀድሞው የዕዙ ስራ አስፈፃሚ አባላት ባለፉት ሶስት ዓመታት ያላከናወኗቸውን ተግባራት በጥልቀት በመፈተሽና በመገምገም ለይቶ አስቀምጧል። በዚህ መሰረት፣ ከዚህ ቀደም በዕዙ ስራ አስፈፃሚ ደረጃ ያልተሰሩ ስራዎችን ጨምሮ ሌሎች አዳዲስ ግዳጆችን ድርጅታዊ መርህና አሰራርን በመከተል አዳዲስ ግዳጆችን በብቃት ለመፈፀም ጠንካራ አቋም ላይ እንደሚገኙ አባላቱ በውይይቱ ገልፀዋል። ከዚህ በተጨማሪ በቀጣይ የስራዊታችንንና የማኀበረሰባችንን መሰረታዊ ጥያቄዎች ድርጅታዊ መስመር በማስያዝ በየደረጃው  ወርዶ እንደሚሰራና ያለማዛነፍ እንደሚያስፈፅም በስብሰባው አረጋግጧል። የቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፣ አዲሱ የስራ አስፈፃሚ አባላት፤ ላለፉት 10 ቀናት በአካል ተገኝቶ ያካሄደውን ውይይት አጠቃላይ የጋራ ውሳኔና የአቋም መግለጫ እንደደረሰን ይፋ እናደርጋለን። አፋብን፤ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፣ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!