ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
رفتن به کانال در Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
نمایش بیشتر2 955
مشترکین
+1424 ساعت
+247 روز
+38330 روز
آرشیو پست ها
104ኛ ኮርን ለመክበብ የሞከረዉ የአገዛዙ ሰራዊት ራሱ ተከቦ ሲቀጠቀጥ ዉሏል!!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ስር የሚገኘውን 104ኛ ኮርን "አፍናለሁ" በሚል ትዕቢትና ቅዠት ተሞልቶ ወደ ግንባር ያመራው የአገዛዙ ሠራዊት በጀግኖች ክንድ ራሱ ታፍኖ ሲቀጠቀጥ አርፍዷል።
ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም የአገዛዙ ጦር በ104ኛ ኮር፣ 23ኛ ክፍለጦር ስር የሚገኘውን 1ኛ ሻለቃን በብዛትና በኃይል ለመክበብ አስቦ ሰፊ እንቅስቃሴ ያደረገ ቢሆንም በጀግኖቹ ስልታዊ ዝግጅትና የንቃት ደረጃ የጠላትን ዕቅድ አስቀድመዉ አክሽፈዉታል።
የአገዛዙ ሠራዊትም በተንታ ወረዳ ልዩ ስሙ "ኮረት" በተባለ ስፍራ ላይ ሲደርስ፣ ገና ከጅምሩ ባልጠበቀው አስደንጋጭ ጥቃት የተሰነዘረበት ሲሆን የ1ኛ ሬጅመንት ተናዳፊዎቹ የጠላትን ከበባ በመስበር ፈጣንና ኃይለኛ የፊት ለፊት ዉጊያ በማድረግ በጠላት ላይ ድልን ተጎናጽፈዋል።
በዚህ እልህ አስጨራሽ ዉጊያም አጥቂ የነበረው የአገዛዙ ሰራዊት ተጠቂ በመሆን ራሱን መከላከል አቅቶት ታፍኖ ሲቀጠቀጥ ዉሏል።
በዚህም ዉጊያ በርካታ የአገዛዙ ሠራዊት አባላት ሙትና ቁስለኛ ሲሆኑ በርካታ የጦር መሳሪያዎችና ትጥቆች ሲገኙ የጠላት ስልታዊና ወታደራዊ ዕቅድ ሙሉ በሙሉ እንዲከሽፍ አድርገዉታል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ
የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!
ግንቦት 30/2018ዓ.ም
የእነ አረጋ ከበደ ሙሴዎች መሪ መገደሉ ተሰማ።
በጠላት የ36ኛ ሻለቃ የድማ ብተና አዛዥ ሻለቃ በርይሁን ጨምሮ 16 አድማ ብተና አባላት ተደመሰሱ።
23 የአድማ ብተና አባላትን በመያዝ ከደብረ ማርቆስ ከተማ ተነስቶ ወደ ሊባኖስ ሲንቀሳቀስ በነበረው ሻለቃ በርይሁን ላይ የቦ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ላይ መብረቃዊ ጥቃት የፈፀሙት በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር የጅበላ ሙተራ ሬጅመንት አርበኞች አንፀባራቂ ድል ተቀዳጅተዋል።
በዚህ የቆረጣ ማጥቃት፡ የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎችን በጅምላ በማሰር በመደብደብ፣ በመረሸንና ዘረፋ በመፈፀም አሰቃቂ ድርጊት ይፈፅም የነበረው ሻለቃ በርይሁን ጨምሮ 16 የአድማ ብተና አባላት ሲደመሰሱ።
ሰባት የሚሆኑት በፅኑ ቆስለው ለሕክምና ወደ ደብረ ማርቆስ ሆስፒታል መግባታቸው ተረጋግጧል ሲል የ206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል።
ሰበር ዜና!
ሰራዊታችን ለተከታታይ ሁለት ቀናት ባደረገው ልዩ የተቀናጀ ኦፕሬሽን ጀግናው የራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር የደብረ ሊባኖስ ወረዳ ሁለት ከተሞችን ተቆጣጠረ።
አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነውየራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ከአርበኞች ጦር ሰራዊት ጋር በቅንጅት በተሰራ ልዩ ኦፕሬሽን በግራርያ (ፍቼ ሰላሌ) አውራጃ የደብረ ሊባኖስ ወረዳ ዋና ከተማን ጨምሮ ሴት ደብር እና ውሻ ገደል የሚባሉ ሁለት የወረዳ ከተሞችን ዛሬ ረፋዱ ላይ በቁጥጥር ስር ማድረጉን ኮሩ በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል።
የደብረ ሊባኖስ ወረዳ የሆኑ በርካታ ነዋሪዎችን "የፋኖ ደጋፊ ናችሁ" በሚል ብዙዎችን ለሞትና ለስደት እንዲሁም ለከፍተኛ እስርና እንግልት የዳረጉ የወረዳው የብልፀሰግና አመራሮች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ሲፈፀም የፀጥታ ዘርፍ ኃላፊውና ሌሎች ቁስለኛ ሆነው ወደ ፍቼ ከተማ ሆስፒታል የተወሰዱ ሲሆን፣ ለአገዛዙ ቅጥረኛ በመሆን የመረጃ ስራ ላይ ሆነው ሲያገለግሉ በተገኙ ባንዳዎች ላይ ክፍለጦሩ የማያዳጋም ርምጃ በመውሰድ ከተማውን ተቆጣጥሯል።
የህዝብ ልጅ የሆነው ጀግናው ሰራዊታችን ትላንት ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ግንቦት 30 ቀን 2018ዓ.ም ዕኩለ ቀን ድረስ በሞርተርና ዙ-23 ታጅቦ ከገጠመው አገዛዝ ጋር ባደረገው ልዩ ተጋድሎ ከተሞቹን ሲቆጣጠር እስከ ጫጋል ከተማ ድረስ አድማሱን ባሰፋው ውጊያ ሽንፈቱን የተከናነበው የብልፅግናው የግለሰቦች ታዛዢ ዘራፊ ሰራዊትና ጥምር ጦር ወደ ፍቼ ከተማ መፈርጠጡን ዕዙ በመረጃው አረጋግጧል።
''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 30/2018ዓ.ም
የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በአርሲ ምድር በተፈጸመው ጥቃት ላይ ፍትህ ጠይቀዋል።
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን አህጉረ ስብከት ስር በሚገኙት የአሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች በንጹሐን ምዕመናንና በቤተ ክርስቲያናት ላይ ተፈጽሟል የተባለውን ጥቃት በመቃወም ምዕመናን፣ ወጣቶች እና የማኅበረሰብ ክፍሎች ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ፍትህ እየጠየቁ መሆኑ ተገልጿል።
በተመሳሳይ ምዕመናንና ወጣቶች “እኛ የአቡነ ጴጥሮስ ልጆች ነን፤ የአባቶቻችንን ሃይማኖት በጽናት እንጠብቃለን” በማለት ለተጎዱ ወገኖች ፍትህ እንዲሰጥ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል።
#ፍትህ_ለአርሲ_ኦርቶዶክሳውያን #አርሲ #ኢትዮጵያ
ወጣቱን በማደራጀት አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ እየፈፀመ ያለውን አረ* መኔዊ ተግባር በተመለከተ ግንዛቤ የመስጠት ስራ እንደቀጠለ ነው።
በእነማይ ወረዳ ስር- እየሱስ፣ እንደሽኝት እና አካባቢው ቀበሌ ከሚገኙ ወጣቶች ጋር የ64ኛ ክ/ጦር እና የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች በወቅታዊ ጉዳዩች ጋር ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።
ይህን የህልውና ትግል ትላት ወጣቱ ደረቱን ለጥይት በመስጠት እዚህ እንዳደረሰው ሁሉ ዛሬም የአማራን ህዝብ የትጥቅ ትግል ከፊት በመሆን ይህንን ስረዓት መገርሰስ እንዳለበት በስብሰባ መድርኩ ለተገኙ ወጣቶች በሰፊው ግንዛቤ ተሰጥቷል።
በውይይት መድርኩ የተገኙት ወጣቶች እንደተናገሩት ይህ ስረዓት አናቱን በድንጋይ እንደተመታ እባባ ላለመሞት እየተፈራገጠ እንደሚገኝ በማስረዳት የአማራን ህዝብ እየጨፈጨፉ፣ እየዘረፉ ፣በጅምላ እየገደሉ እና በጅምላ እያሳደዱ የሚቀጥሉበት ግዜ እያበቃ እንደሆነ በማስረዳት ወጣቱ ይህንን አረ* መኔዊ ስረዓት ለመገረሰስ በፋይናስ፣ በመረጃ በመሳሰሉት ድጋፎች ከፋኖ ጎን እንደሆኑ አሳውቀዋል።
አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!!
ግንቦት29/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
አማራ መሆን» ምን ማለት እንደሆነ የሚገባህ... ልክ እንደ እኔ የግፍ ጽዋ ሲተርፍህና መከራው ደጃፍህ ድረስ መጥቶ ሲያንኳኳ ብቻ ነው። እውነት ለመናገር፣ እኔ ዛሬም ድረስ በገዛ ወገኖቼ፣ በሆዳምና አስመሳይ ባንዳዎች የውሸት ስም እየተለጠፈልኝ፣ ህይወቴን ለማጥፋት የሚሸረብን ሴራ በየቀኑ የምጋፈጥ የዚሁ ግፍ ቀጥተኛ ሰለባ ነኝ።
የሚያሳዝነው ግን፣ የዚህ ህዝብ የመኖር ነፃነትና የህልውናው ህመም የሚሰማችሁ... ልክ እንደ እኔ ቀስቱ ውስጣችሁን ሲያደማውና የነፍስ ዋጋችሁ ሲረክስ ብቻ መሆኑ ነው። ህመሙ ከቤታችሁ እስካልደረሰ ድረስ፣ የሩቅ ለቅሶ ሆኖባችሁ ሊቀጥል ይችላል። እኔ ግን... በእኔ የደረሰው መከራና ስቃይ በምንም ተአምር በእናንተ ላይ እንዳይደርስ እመኛለሁ።
ትናንት በአርሲ ንጹሃን ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው አረመኔያዊ በደል ልብን የሚሰብር፣ ነፍስን የሚያደማ እና እጅጉን የሚያም ክስተት ነው።
ይህ የታሪክ ጠባሳ ግን አንድ ትልቅ እውነት ያስተምረናል። ከእንግዲህ በልቅሶና በዋይታ የምንሻገረው ወንዝ የለም። አማራጭ የሌለው ብቸኛው መፍትሔ መደራጀት እና አንድ መሆን ብቻ ነው። ለአንድ ህዝብ አንድነት ማለት... የመኖር ነፃነቱን የሚያረጋግጥበት ብቸኛው የህልውና መንገድ ነው! #Dawit #Amhara ከንጉሶች መንደር!!
ጀግኖች የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ የአብይ አህመድ አረመኔያዊ ኃይል አሁን በዚህ ስዓት እየለበለቡት ይገኛሉ አፋብን ወደ ፊት!!
Dawit #Amhara ከንጉሶች መንደር ቀጥታ ከግንባር #አማራ #ፋኖ #Amhara #Fano #ኢትዮጵያ #Ethiopia #Share
#የቴሌግራም ገፃችን ይወዳጁ!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!
https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ኮር 81ኛ ክፍለጦር በጠላት ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀናጁ!
ምኒልክ ዕዝ የ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር አሃድ የሆነችው 81 ኛ ክፍለጦር በመቄት ወረዳ ወደ አግሪት መስመር በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ ከባድ የደፈጣ ጥቃት ፈፅማለች። በዙ-23 እና ሌሎች የቡድን መሳሪያዎች ታጅቦ ሲግተለተል የነበረው የአፓርታይዱ ስርዓት ወንበር አስጠባቂ ሰራዊት በቁጥር እና በመሳሪያ ብዛት በነበልባሎቹ የፋኖ ኃይሎች ከመገረፍ አልተረፈም።
በጦር ጠበብቱ ኮማንዶ አማን ጎበዜ በተመራው አውደ ውጊያ 8 የአገዛዙ ሰራዊት ሲደመሰስ 12 ቁስለኛውን ታቅፎ ወደ ተለመደው ጉድጓዱ ፍላቂት ከተማ ምሽግ ገብቷል። የፋኖን ክንድ መቋቋም ያቃተው ደመነፍሳዊ የአፓርታይዱ ስርዓት ወንበር አስጠባቂ በፍላቂት ከተማ ንፁሃንን እያንገላታ መሆኑ የ303ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 29/2018ዓ.ም
+3
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒሊክ ዕዝ 101ኛ ኮር ታላቅ ድል ተጎናፀፈ!
የ101ኛ ኮር አሃድ የሆነችዉ 35ኛ(ባለሽርጡ) ክፍለጦር የብአዴን ምንጣፍ ጎታች ሚኒሻ ላይ ደፈጣ በመያዝ ዶግ አመድ አድርገዉታል። 35ኛ(ባለሽርጡ) ክፍለጦር 2ኛ ሻለቃ 1ኛ ሻንበል በደቡብ ወሎ ተሁለደሪ ወርዳ ሰግለን ሮቢት አካባቢ በተደረገ የደፈጣ ጥቃት በጥቁር አማራ ሚሊሻ ባንዳዎችን ዶግ አመድ የሆኑ ሲሆን ከነበልባሎቹ ምት የተረፉት በየአቅጣጫው ነፍሴ ብለው ፈርጥጠዋል።
በሌላ በኩል ሁለት መከላከያ ሰራዊት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ከደቡብ ዕዝ 205ኛ ኮር 41ኛ ክፍለ ጦር በመክዳት ባለሽርጡ ክፍለጦርን የተቀላቀሉ ሲሆኑ የመከላከያ አባሎቹ ወደ ፋኖ ሲመጡ የ35ኛ ክፍለጦር አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል ሲል የ101ኛ ኮር ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 29 2018።
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር ጥልቅ ግምገማና ወይይት አደረገ!
የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ሚኒሊክ ዕዝ ስር የሚገኘው 101ኛ ኮር፣ ለተከታታይ ሦስት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የሰራዊትና የአመራር አባላት ጥልቅ የግምገማና የውይይት መድረክ በስኬት በዛሬዉ ዕለት አጠናቋል።
ግንቦት 29 ቀን ድረስ በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ የኮር እና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች፣ የ15ኛ እና 11ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች እንዲሁም ከመቶ መሪ በላይ የሆኑ የሰራዊት አባላት ተሳትፈዋል።
በውይይቱ ላይ የአማራ ሕዝብ ትግል በአሁኑ ወቅት የደረሰበት ደረጃ በጥልቀት የተገመገመ ሲሆን፣ እስካሁን በተከናወኑ ወታደራዊ ግዳጆች የተመዘገቡ ታላላቅ ድሎችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችም የተቀመጡ ሲሆኑ በግምገማው ላይ በተለይም ጠላት የደረሰበት ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ እንዲሁም በአሁኑ ወቅት የሚገኝበት የውድቀት ደረጃ በሰፊው የተዳሰሰ ሲሆን፣ ይህንን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ቀሪ የትግል ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ በሚቻልበት ስልት ላይ ጠንከር ያሉ መመሪያዎችና የወደፊት አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
በዚህም ግምገማ እና ዉይይት ላይ አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ም/ ሰብሳቢ ረዳ ዉበቱ (አባ አዝማራ) ፣የዕዙ ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ወንድሙ ማሩ ፣የዕዙ ዘመቻ መምሪያ አርበኛ በለጠ ሸጋዉ ፣ ልዩ ዘመቻ መምሪያ አርበኛ ተሾመ ፈንታዬ እንዲሁም ሌሎች የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን በትግሉ ሂደት ውስጥ ሌት ተቀን በቁርጠኝነት እየሰሩ መሆናቸውን ያብራሩ ሲሆን የአገዛዙ ብልፅግናዉን ስርዓት ለመጣል ከወትሮዉ በተለዬ መልኩ እራሳቹህን አዘጋጁ ሲሉ ለሰራዊቱ አሳስበዋል።
በዚህም የሦስት ቀን ጥልቅ የግምገማ መድረክ በምኒልክ ዕዝ ወታደራዊ አማካሪ በሆኑት ኮረኔል ሞገስ ዘገዬ ማጠቃለያ ንግግር ተቋጭቷል።
ኮለኔል ሞገስ በንግግራቸው አጠቃላይ የትግሉን ነባራዊ ደረጃና ቀጣይ የአፈጻጸም አቅጣጫዎችን በማስመር፣ ሰራዊቱና አመራሩ የተጣለባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት በንቃት እንዲወጡ አሳስበዋል ሲል የ101ኛ ኮር ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ
የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮምኒኬሽን መምሪያ
ግንቦት 29 2018
ወጣቱን በማደራጀት አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ እየፈፀመ ያለውን አረ* መኔዊ ተግባር በተመለከተ ግንዛቤ የመስጠት ስራ እንደቀጠለ ነው።
በእነማይ ወረዳ ስር- እየሱስ፣ እንደሽኝት እና አካባቢው ቀበሌ ከሚገኙ ወጣቶች ጋር የ64ኛ ክ/ጦር እና የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች በወቅታዊ ጉዳዩች ጋር ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።
ይህን የህልውና ትግል ትላት ወጣቱ ደረቱን ለጥይት በመስጠት እዚህ እንዳደረሰው ሁሉ ዛሬም የአማራን ህዝብ የትጥቅ ትግል ከፊት በመሆን ይህንን ስረዓት መገርሰስ እንዳለበት በስብሰባ መድርኩ ለተገኙ ወጣቶች በሰፊው ግንዛቤ ተሰጥቷል።
በውይይት መድርኩ የተገኙት ወጣቶች እንደተናገሩት ይህ ስረዓት አናቱን በድንጋይ እንደተመታ እባባ ላለመሞት እየተፈራገጠ እንደሚገኝ በማስረዳት የአማራን ህዝብ እየጨፈጨፉ፣ እየዘረፉ ፣በጅምላ እየገደሉ እና በጅምላ እያሳደዱ የሚቀጥሉበት ግዜ እያበቃ እንደሆነ በማስረዳት ወጣቱ ይህንን አረ* መኔዊ ስረዓት ለመገረሰስ በፋይናስ፣ በመረጃ በመሳሰሉት ድጋፎች ከፋኖ ጎን እንደሆኑ አሳውቀዋል።
አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!!
ግንቦት29/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
+1
እንወያያለን!
እንመካከራለን!
እናሸንፋለን!
ቀን 29/09/18
የ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር በመቀጠዋ ወረዳ ካሉ ሁሉም ትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን እና ከሚመለከታቸው የትምህርት አካላት ጋር ውይይት አድርገናል!!
🕯🕯🕯🕯🌲🌲🕯🕯🕯🕯
204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር በተቆጣጠራቸው ቀጠናወች ሁሉን አቀፋ የማህበረሰብ የውይይት መድረኮችን በመፍጠር ትግሉን ወደ ፊት ማራመድ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ግንዛቤ ተፈጥሯል!!
➡️ በትግሉ ዙሪያ ከመምህራን ስለሚጠበቁ ጉዳዮች
➡️ ስለ ትግሉ አሁናዊ ቁመና
➡️ ፋኖ የትምህርትን ዘርፍ አስጀምሮ አስካሁኑ ድረስ ያሉ ተግዳሮቶች እና ውጤቶች
➡️ በቀጠይ መደረግ ስላለባቸው ሁኔታወች!!
♨️ አጠቃላይ የትምህርቱ ዘርፍ እና የፋኖ ትግል በሰፊው ተወያይተናል!!
🗡 እንወያያለን!
🗡 እንመካከራለን!
🗡 እናሸንፋለን!
ድል ለአማራ ፋኖ!!
የ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!!
በጦር ጠበብቶች የሚመራው ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ ታሪክ በደሙ እየፃፈ ይገኛል!!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ106ኛ ኮር 22ኛ ክፍለጦር ረፋዱን የጠላትን ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አይቀጡ ቅጣት ቀጥተውታል።
ከጋሸና ተነስቶ ወደ ገረገራ ሊሻገር በነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ላይ የቀኝአዝማች ተበጀ ወርቁ ትንፋሾች ዶግ አመድ አድርገውታል።
ንስሮቹ የጠላትን እንቅስቃሴ በማፈንፈን ከቋና ሮቢት እንደ አቦ ሸማኔ ተምዘግዝገው ዛሬ ማለትም ግንቦት 29/2018 ከረፋዱ 2:00 ሰዓት ላይ አርቢት ኪዳነ-ምህረት ጋሸና አፍንጫ ስር ላይ የስርዓቱ ወንበር አስጠባቂዎች ከባድ ጥቃት ፈፅመዉበታል።
በዚህ ጥናታዊ ኦፕሬሽን ከ09 በላይ የተደመሰሱ እና ከ17 በላይ ከባድ ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል።
የተወሰደበት ጥናታዊ እርምጃ አስከፊ በመሆኑ ወደ መጣበት የፈረጠጠ ሲሆን ባጃጅ በማስገደድ ቁስለኛና ሙቱን ጭኖ ሲፈረጥጥ የአርቢት ኪዳነምህረት ምድር አስከሬናቸው በተገተቱ የጠላት ሰራዊቶች ደም ጨቅይቷል።
በርካታ ቁስለኛውን ወደ ኮን ሆስፒታል እያሳከመ የሲቃ ድምፁን እያሰማ ይገኛል ሲል 106ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርአድርሷል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ግንቦት 29/2018 ዓ/ም
+1
ሰበር ዜና!
አንዳቤት ወረዳ በአናብስቶች አንዳቤት ብርጌድ በልዩ ቀዶ ጥገና የውጊያ ስልት የብልጽግና መንደርተኛ ባንዳ የከተማ ሽፍታ ተቀነደሽ!
=======================
ግንቦት (29/2018 ዓ.ም)
አፋብን ሰሜን አማራ በላይ ዕዝ ሜ/ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ ኮር በልማደኛዋ ጉና ክፍለ ጦር ስር አንዳቤት ብርጌድ መብረቃዊ ጥቃት በመፈፀም በጠላት ሃይል ላይ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሳቸው ተገለፀ!!
ግንቦት 29/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 1ሰዓት አንዳቤት ብርጌድ አናብስቶች ከአገዛዙ ሰራዊት ጋር ትንቅንቅ በማድረግ አኩሪ ድል ፈፅመዋል። ጀግኖች በተጠና ልዩ የከተማ የውጊያ ስልት በጠላት ላይ መብረቃዊ ጥቃት በማድረግ በአስገራሜ ሁኔታ የብልጽግና አንባገነኑን ሰራዊት በመደምሰስ ሰባት (7) የሚሆኑትን የአገዛዙ ወንበር ጠባቂ ታጣቂ ሃይል ሙት፣ ስምንት( 8) ኮቭ ክላሽ፣ አንድ አብራረው(1)፣ አንድ (1) አድማ ብተና እጅ ከፈንጅ፣ ሁለት(2) የደረት ትትቅ ገቢ በማድረግ በአስደናቂ የመናበብ ችሎታ ድል ማድረግ ተችሏል።
በአውደ ውጊያው የጠላት ሻንበል መሪ ጨምሮ የተደመሰሰ ሲሆን አስከሪኑን ሳያነሳ ጥሎ በመፈርጠጥ ከተለመደው የቀበሮ ጉድጓድ እንዲመሽግ አድርገውታል።
ህልውናችን በተባባረ ክንዳችን!
የጉና ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ
ፋኖ መምህር ያሬድ ገደፍው
በሕገ-መንግሥቱ የተደነገገው መብት እና በገሃድ እየታየ ያለው ማኅበራዊ ቀውስ!!
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት በአንቀጽ 27 ላይ ማንኛውም ሰው የመረጠውን ሃይማኖት የመከተል፣ የመያዝ ወይም የመቀበል ሙሉ መብት እንዳለው በግልጽ ይደነግጋል። ሆኖም ግን፣ በአገሪቱ ውስጥ በተግባር እየታዩ ያሉ ክስተቶች ይህ ሕጋዊ መብት በወረቀት ላይ ብቻ ተወስኖ መቅረቱንና በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ከፍተኛ የሕሊና ስብራትና ቁስል በግልጽ ያሳያሉ።
በተለይም ሰሞኑን በአርሲና በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የተፈጸሙት ዘግናኝ ድርጊቶች በዜጎች ላይ ከፍተኛ የሕሊና ስብራትና ቁስል ጥለው አልፈዋል። በዐቢይ አሕመድ፣ በአዳነች አቤቤ እና በሽመልስ አብዲሳ የሚመራውና የኦሮምማው ሥርዓት" አማራ ጠሉ መዋቅር፣ በአማራ ብሔርና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ያነጣጠረ መገለልና ጥቃት እያደረሰ መሆኑን የሚታወቅ ሃቅ ነው።
ከእነዚህ ጥቃቶች መካከል እጅግ ልብ ሰባሪ የሆነው ገና የሃይማኖትንና የዓለምን ፖለቲካ ምንነት ጠንቅቀው ባላወቁ ሕፃናት ላይ የተፈጸመው ድርጊት ነው። ከሞትና ከማንነት ማጽዳት ጥቃት የተረፉ ንጹሐን የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ሕፃናት፣ በአንገታቸው ላይ ያሰሩትንና በሃይማኖታዊ ሥርዓት ከእመቤታችንና ከክብር ልጇ የተቀበሉትን የክር መስቀል በኃይልና በጭካኔ ሲበጠስ ማየት፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ የሃይማኖት ነፃነት መደፈርን ያሳያል። ይህ ትዕይንት የማኅበረሰቡን የውስጥ ሕመም ይበልጥ ያበረታውና ሕጉ ዜጎችን ለመጠበቅ አለመቻሉን ያረጋገጠ ክስተት ሆኗል።
የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች ከሕዝቡ ጎን ከመቆም ይልቅ በሆዳቸው አድረው ከሥልጣንና ከጥቅም ጋር በማበር ሚናቸውን እንደዘነጉ የሚታይ ሲሆን አሁን ላይ የሚደረጉ ጥቃቶች በአንድ ብሔር ላይ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን ስልታዊ በሆነ መልኩ የእምነት ተቋማትንም ጭምር መሠረት ያደረገ ነው።
ስለሆነም፣ ከእንግዲህ "እንደ አማራ ብቻ መደራጀት በቂ አይደለም። ምክንያቱም እየተካሄደ ያለው ስልታዊ አጀንዳ መጀመሪያ አማራውን በማጥፋት ላይ ያነጣጠረ ቢሆንም፣ ቀጥሎም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነትን መዋቅርና መኖር አደጋ ላይ የመጣል ስውርና ሰፊ ስትራቴጂ አካል መሆኑን በግልጽ የሚያሳይ እቅድና እስትራቴጂ ጨምር ነው።
