fa
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

رفتن به کانال در Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

نمایش بیشتر
2 955
مشترکین
+1424 ساعت
+247 روز
+38330 روز
آرشیو پست ها
አዳጊ እና በየጊዜው የሚሻሻል መዋቅራዊ አሰራርን እየተገበረ የሚገኘው የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ የሕግና ሥነ ሥርዓት ጉባኤ የድርጅቱ አንድ ክፍል ሆኖ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስ
+6
አዳጊ እና በየጊዜው የሚሻሻል መዋቅራዊ አሰራርን እየተገበረ የሚገኘው  የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ የሕግና ሥነ ሥርዓት ጉባኤ የድርጅቱ አንድ ክፍል ሆኖ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት የፍትሕ ክፍል  በማቋቋም ለድርጅታችንና ለሕዝባችን የፍትሕ አገልግሎት እየሰጠን እንገኛለን። ይህን የፍትሕ አሰጣጥ ከምንጥለው አገዛዝ የተሻለ የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት የሚያግዝ የሕግን ሕዝብ አስተዳደር ስልጠና መስጠት አስፈላጊ መሆኑን በማመን  ቀደም ሲል በቴዎድሮስ ዕዝ ስር የሚገኙ 206 ኮር፣105ኮር፣109ኮር ስር የሚገኙ የኮር ፣የክፍለ ጦር የሕግ ክፍሎችን እንዲሁም በኮሮች ስር የሚገኙ ወረዳዎች የጊዜያዊ መንግስት የፍትሕ አካላትን  በሁለት ማዕከል በማሰልጠን ወደ ግዳጅ ቀጠናዎች ያሰማራን ሲሆን ይህን ስልጠና በማስቀጠል በ201ኮር ስር የሚገኙ የኮር ፣የክፍለ ጦርና በቀጠናው ውስጥ የሚገኙ የወረዳ ጊዜያዊ መንግስት የፍትሕ  አካላትን በአጠቃላይ በቁጥር 36 የሆኑትን ለተከታታይ 5 ቀናት በማሰልጠን የተሻለ ፍትህ ይሰጡ ዘንድ ወደ ግዳጅ ቀጠናቸው አሰማርተናል።                አዲስ  ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!

የአብይ አህመድ አረመኔያዊ አገዛዝ ሳይቨሮች የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ህዝብ ግኑኝነት ኃላፊ አርበኛ አማር ታዘዘን የፊስቡክ አካውንት አዘግተውብታል ስለዚህ
የአብይ አህመድ አረመኔያዊ አገዛዝ ሳይቨሮች የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር ህዝብ ግኑኝነት ኃላፊ አርበኛ አማር ታዘዘን የፊስቡክ አካውንት አዘግተውብታል ስለዚህ የአርበኛው አዲሱን የፊስቡክ አካውንት ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ በመጫን  ይወዳጁት!!! https://www.facebook.com/share/1AcrCEzm4C/

የአማራ ሕዝብ ደምና እንባ ባልደረቀባት ምድር በምስጢር የተሸረበው የብልፅግና የሴራ ፖለቲካና የመሬት ቅርጫ!! ደጋግማ የፈረሰች፣ ልጆቿ በየሜዳው የወደቁባት፣ በሕመም ላይ ያለችው የምስኪኖቹ ከተማ አጣዬ፤ ዛሬም ከኦሮምማው አብይ አህመድ ብልፅግ መራሹ ስርዓት ከሚመጣባት መከራ በላይ ከውስጥ በብአዴን አማራሮች የክህደት አለንጋ እየተገረፈች ነው። ​የቆሰሉትን ልታክም፣ የተፈናቀሉትን ልታስጠልልና የፈረሱትን ቤቶቿን ልትጠግን የሚገባት ታሪካዊቷ ስምጥ ሸለቆ፤የአኤፍራታዋ አጣዬ ከተማ ዛሬ ግን በአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂና በብአዴን ቅጥርኛ የዞንና የከተማ አመራሮች ምስጢራዊ የኪስ ማደለቢያ ሆናለች። ገና የንጹሐን ዜጎች ደምና ዕንባ ባልደረቀባት በዚህች ምስኪን ከተማ ውስጥ፣ አማራን ከምድር ገፅ ለማጥፋት ለዘመቱት የመከላከያ ጦር አዛዦች፣ ለጄነራሎች፣ ለኮሎኔሎችና ለባለሥልጣናት መሬት “በውስጥ መስመር” ተሸንሽኖ የመስጠት አሳዛኝና ልብ የሚሰብር ዘረፋ እየተካሄደ ይገኛል። ​ የባለሥልጣናቱ ስግብግብነት በሕዝብ መቃብር ላይ ​ከተማዋ በጦርነትና በሰቆቃ እየታመሰች ባለበት በዚህ ጨለማ ወቅት፣ የስግብግቦቹ ባለሥልጣናት ምስጢራዊ ስብሰባና ንግግር ግን የሰሙትን ሁሉ የሚያስለቅስ ነው። ​ለብልፅግናው አማራ ጠሉ ስርዓት ታማኝ ለሆኑ የጦር አዛዦችና የብአዴን ቅጥርኞች የዞን መሪዎች መሬት በምስጢር ሲታደል፣ “ሁለት ቦታ ይበቃችኋል” ሲባሉ ለአካባቢው ስቃይና መከራ ደንታ የሌላቸው ግፈኞች፦ “ለምን ሁለት ብቻ? ሦስት ለምን አይደረግልንም?” በማለት በስግብግብነት ሲከራከሩ እንደነበር የውስጥ መርጃዎች አድርሰውናል። ሆኖም ​የማዘጋጃ ቤት ሠራተኞችና አመራሮችም ይሄንን ታላቅ ክህደትና ምስጢር ማንም እንዳይሰማው በጥብቅ ተደብቀውና ተባብረው እንዲሠሩ ተደርጓል። ይህ ድርጊት ከዚህ ቀደም በሸዋሮቢት አካባቢ ተሞክሮ በአካባቢው ጀግኖችና በፋኖ ኃይሎች ብርቱ ተቃውሞ የሄዱትን ሠራተኞች በማባረር የከሸፈ ቢሆንም፤ አጣዬ ላይ ግን በሕዝብ ስም እየማሉ ሕዝብን በሚያርዱ ባለሥልጣናት አማካኝነት በምስጢር ተጠናቆ ሊፈጸም ጫፍ ላይ ደርሷል። በዚህም "ባለቤቱ የሌለውን መሬት እየተቀራመቱት ነው! ​ይህንን ዘግናኝ ምስጢር በዋይታና በቁጭት የገለጹት የቅርብ መረጃ አቀባዮች በከፍተኛ ኃዘን ሆነው እንዲህ ይላሉ፦ ሕዝባችን መውጫና መግቢያ አጥቶ፣ ታሪካዊቷ ከተማችን ደም እያለቀሰች ባለችበት ሰዓት፣ መሬታችንን በምስጢር እየተቀራመቱት ነው። ይህንን ግፍና ክህደት ማጋለጥ ካልቻልን፣ ለነገ የምናስተላልፋት አጣዬ አትኖርም። እባካችሁ በሚዲያ ድምፅ ሁኑን! ይህንን አሳዛኝ ሴራ ለዓለም አሳውቁልን ​ይህንን መረጃ ይፋ ማድረጋችን የአጣዬን መሬትና የወደፊት ዕድል ለመታደግ የሚደረግ ሕዝባዊ ትግል አካል ነው። የሕዝብ ዕንባ ሳይታበስ፣ የሰማዕታት አፅም ሳይከበር፣ በአጣዬ መሬት ላይ የሚደረግ ማንኛውም የምስጢር ንግድና ዘረፋ የታሪክ ተጠያቂነትን አያመልጡም።

በእነ አቶ ሉዑል ሰዉነት(ሀብታሙ ዘለቀ) የተከሰሱ ተከሳሾች ዛሬ ፍ/ቤት ቀርበዋል ።፤ በእነ አቶ ሉዑል ሰዉነት(ሀብታሙ ዘለቀ)  መዝገብ ጉዳያቸውን በእስር ቤት ሆነው ከሚከታተሉ 16 ተከሳሾች መካከል 12ቱ ግዛሬ ግንቦት 28/2018 በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የሕገ መንግስት እና የፀረ ሽብር ወንጀል ችሎት ቀርበው ነበር። የዐቃቤ ሕግ ምስክር እና የሰነድ ማስረጃ ክርክሩን መርምሮ ለመበየን ፍ/ቤቱ ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል በማለቱ ቀጠሮው ለሰኔ 23/2018 ተራዝሟል። አማራነትን እና ፋኖነትን እንደ ወንጀል በቆጠረው የኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ በሽብር ወንጀል ተከሰው በግፍ እስር ላይ ከሚገኙት መካከል በእነ ሉዑል ሰዉነት መዝገብ ዉስጥ የተከሰሱት 16 ተከሳሾች 1.ሉዑል ሰዉነነት(ሀብታሙ ) 2.ይመስላል የእኔአባት 3.በላይ አለባቸው 4.ብርሀኑ ዳኛቸው 5.ፍቅሩ መለሰ 6.አማኑኤል ደምላሽ 7.ቢኒያም አስቻለ 8.ሙሉጌታ አብርሀም 9.አድማሱ ጌታሁን 10.ሰሎሞን 11.ጌታመሳይ 12.እንዳልክ ጌቱ 13.በላይ አለም 14.የኔአባት ስንሻዉ 15. በዋስ የወጡ 16.በዋስ የወጡ ጥፋተኛ በሚል ተከሰዋል ። መዝገቡ የቀጠረው ፍርድቤቱ የተከሳሾቹን የግል ስልክ ጠለፋ  በተመለከተ ከኢትዮ ቴሌኮም ፍቃድ ማስመጠታን በተመለከተ እና የዐቃቤ ሕግ የሰነድ ማስረጃ አስተያየትን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለሰኔ 23/2018 ዓ.ም ተራዝሟል።

​አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒሊክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ መምሪያ በተጓደሉ አዳዲስ የስራ ኃላፊዎችን ሾመ‼️ ​ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ መምሪያ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ለ 2 ቀናት የፈጀ  ስብሰባና ግምገማ ካደረገ በኋላ ክፍት በነበሩ ቦታወች ላይ አመራር መድቧል። 2ቀን በፈጀዉ በዚህዉ ስብሰባ፣ እየተደረገ ለሚገኘው የህልውና ተጋድሎ ይበልጥ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠርና የአደረጃጀት ጥንካሬን ለመጨመር ይረዳ ዘንድ የአዳዲስ የሥራ ኃላፊዎች ሹመትና የሥራ ሽግሽግ አድርጎ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ​በዚሁ መሠረት በ ልዩ ዘመቻ መምሪያዉ ውስጥ ክፍት የነበሩ የሥራ ቦታዎች ላይ የተመደቡ አዳዲስ የሥራ ኃላፊዎች ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦ 1. ልዩ ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ .........አርበኛ  ተሾመ ፈንታየ 2. ወታደራዊ አዛዥ........አርበኛ መ/አለቃ ግርማ አብየ 3. ም/ወታደራዊ አዛዥ.........አርበኛ አሻግሬ ሙሉ 4. ዘመቻ መምሪያ.......አርበኛ አሸናፊ ዳኜ 5.ወታደራዊ አስተዳደር ና ፋይናስ ..አርበኛ በላይ ተሾመ 6.ፖለቲካ መምሪያ ........አርበኛ አባተ ካሳ 7.ህ/ግንኙነት ና ሀብት አፈላላጊ .....አርበኛ ሀብታሙ ታደሰ 8.ሎጆስቲክ ክፍል ........ አርበኛ  አማረ  ተገኘ 9.ኦርዲናስ ክፍል ........አርበኛ በቀለ ቢራራ 10.ህግ ክፍል ..........አርበኛ ዘገየ ገሰሰ 11. መረጃ ክፍል*አርበኛ*** 12.ንብረት አስተዳደር......አርበኛ መርጌታ ሀይለማርያምን አድርጎ ሹሟል ሲል የልዩ ዘመቻ ህ/ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ©አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮምኒኬሽን መምሪያ!!            28/ዐ9/2018 ዓ.ም

ቀን 28/09/2018 ዓም                   =======+++======= " ከጋይንት  እስከ ደብረ ዘቢጥ የአብይ  ዙፋን ጠባቂ በፅኑ ተመታ"   በጋይንት ነፋስ መውጫ  ከተማ ዘር ጨፍጫፊው የአብይ  ወምበር ጠባቂ  ንፁሀን ሲረሽን : ካህናትን ሲገድል :  ህፃናትን ሲደፍር : ቤተ ክርስትያናትንና አጥቢያዎችን ሲረግጥ   የቆየው  የስርዓቱ ምንጭር ቆራጭ ሰራዊት  የጥፋት ግዳጁን  ጨርሶ ወደ ወሎ ግምባር ከሌሊቱ 11:00  ጀምሮ  ባደረገው  የእግር ጉዞ  የራስ ጋይንት ልዩ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር  በየ መንገዱ እያራገፈ  ከ12 በላይ የተሰውቱን  በየ አስፓልት ጠርዝ ሲቀብር በርካታ ቁስለኞችን  በአምቡላንስ   ከነፋስ መውጫ ጨጨሆ አባሶበር  እያነሳ በራሱ የህክምና  አገልግሎት አስገብቷል።           ረመጡ የራስ ጋይንት  ልዩ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር  ውጊያ ረግረግ  የሆነበት እልፍኝ አሽከር  በዙ 23 :ሞርተር እና ዲሽቃ  የታገዘ  የአውራጅት  : የጋንጋና ጨጨሆ ተራሮችን ከለሊት ጀምሮ  እስከ 8:00  ሲደበድብ ውሏል። @ ድል ለአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ @ ድል ለአማራ ህዝብ @ ራስ ጋይንት ልዩ ተወርዋሪ ክ/ ጦር ሻምበል ተስፋ  ቃል አቀባይ

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ለወራት ያሰለጠናቸውን የኮማንዶ አባላት በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ ​ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ​የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እየተዋጋን እንሰለጥናለን እየሰለጠንን እንዋጋለን በሚል መርህ፤ ለረጅም ወራት በጽናት፣ በልዩ ሁኔታና በከፍተኛ ዲሲፕሊን ሲያሰለጥናቸው የቆያቸውን የኮማንዶ አባላት በዛሬው ዕለት የዕዙ ዋና መሪ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ ና ሌሎች የዕዝና የኮር ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል። ​ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ወታደራዊ ስልጠናው ንድፈ ሀሳብን በተግባር በማጣመር በበቂ ሁኔታ በብቁ አሰልጣኞች ሁሉንም አይነት ውጣውረድ ተቋቁመው በቂ ስልጠና የወሰዱ ሲሆን፣ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በአስተማማኝ ሁኔታ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል። ​በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት የተገኙ ሲሆን፣ የዕለቱ ክቡር እንግዳ ባስተላለፉት መልዕክት፦ ​"ይህ የኮማንዶ ኃይል የአማራን ህልውና ከማስከበር ባለፈ፣ ለሕዝባችን መከታና ጋሻ በመሆን ረገድ ትልቅ አቅም የሚፈጥር እና ጠንካራ አሸናፊ ሀይልም ነው" ብለዋል። ​በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ተመራቂዎቹ የሰለጠኑበትን ጥበብና ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን የሚያሳይ ልዩ ልዩ ትዕይንቶችንና የማርሽ ትርኢቶችን ያቀረቡ ሲሆን፣ በስልጠናቸው ከፍተኛ ውጤትና አርአያነት ላሳዩ የኮማንዶ አባላትም የዕውቅናና የሽልማት አሰጣጥ ተከናውኗል። ​የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የተጣለበትን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣትና የሕዝቡን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ መሰል የሰው ኃይል ግንባታዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በዕለቱ ተገልጿል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን አፋብን ሸ/ጠ/ግ አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

ባንዳው ተቀንድሿል "ፋኖን የከዳ አለበት እዳ" ፋኖን ከድቶ ወደ ስርዓቱ የገባው እርምጃ ተወሰደበት ➡️ ከዚህ በፊት ፋኖ የነበረ ነገር ግን በባንዳነት ፋኖን በመክዳት አምኖት የነበረውን ፋኖ ዋርድያ
+1
ባንዳው ተቀንድሿል "ፋኖን የከዳ አለበት እዳ" ፋኖን ከድቶ ወደ ስርዓቱ የገባው እርምጃ ተወሰደበት ➡️ ከዚህ በፊት ፋኖ የነበረ ነገር ግን በባንዳነት ፋኖን በመክዳት አምኖት የነበረውን ፋኖ ዋርድያ ሁኖ ሲጠብቅ በተኛበት ገድሎ ወደ ስርዓቱ የገባው ከሀዲው አማረ መብሬ በ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ጀኔራል ፈንታ በላይ ክፍለ ጦር የደፈጣ ስፔሻሊስቶቹ  በአርበኛ ዋለ ደጀን የምትመራው ወብእናት ብርጌድ ማታ ከምሽቱ 3:20 ላይ እብናት መሀል ከተማው ላይ ከተማው ሰርጎ በመግባት እርምጃ ተወስዶበታል!!! "ከተማውም ገጠሩም የፋኖ ነው" ማምለጥ አይቻልም! "ከንስሮቹ ማምለጥ ያልቻለው እባብ" የከሀዲ መጨረሻው የውሻ ሞት መሞት ነው!! ፋኖን ክዶ መኖር አይቻልም ሌሎች ከሀዲወችም ትምህርት ውሰዱበት ምክራችን ነው!! "በጠላት መቃብር ላይ አሸናፊነታችን እናረጋግጣለን" ድል ለአማራ ፋኖ! የ204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!

Can an election be considered genuinely democratic when major regions are engulfed in conflict, millions of citizens are effectively excluded from participation, political competition is severely constrained, and substantial portions of the country are beyond the reach of normal electoral administration? If the answer is yes, then the standards articulated in the African Charter on Democracy, Elections and Governance lose their meaning. The implications extend far beyond Ethiopia. When continental institutions endorse elections that fail to meet fundamental democratic standards, they unintentionally weaken the very principles they were created to defend. Such endorsements risk sending a dangerous message throughout Africa—that democratic legitimacy can be achieved through procedural symbolism rather than genuine political participation; that conflict and exclusion are compatible with democracy; and that elections need only occur, rather than be truly competitive, inclusive, and credible. Africa's democratic future depends upon the willingness of its institutions to apply democratic principles consistently and without fear or favor. The African Union has historically played a vital role in advancing constitutional governance, electoral accountability, and democratic norms across the continent. That legacy should not be compromised by assessments that appear disconnected from realities experienced by millions of citizens. No institution benefits from validating a process that large segments of the population view as neither representative nor legitimate. In the long run, honest assessments strengthen democracy; diplomatic convenience weakens it. We therefore respectfully urge the African Union, IGAD, and the international community to undertake a more comprehensive review of the electoral environment in Ethiopia and to evaluate the process against the full standards contained within the African Charter on Democracy, Elections and Governance rather than relying primarily on observations made on election day itself. The people of Ethiopia deserve peace, justice, accountability, and the opportunity to determine their future through a genuinely free and inclusive democratic process. Equally important, the people of Africa deserve continental institutions that defend democratic principles consistently, regardless of political circumstance. History will judge our institutions not by how readily they certified elections, but by how faithfully they defended democracy. Respectfully,

Ref,No. አፋብን/00203/9/18 June 05, 2026 H.E. Mahmoud Ali Youssouf Chairperson of the African Union Commission African Union Headquarters Addis Ababa, Ethiopia CC: H.E. Uhuru Kenyatta, Former President of Kenya and Head of the AU Election Observation Mission H.E. António Guterres, Secretary-General, United Nations Subject: The Endorsement of Ethiopia's 2026 Election Undermines the Principles of Democracy. Your Excellency, I write to express profound concern regarding the public assessments issued by the African Union Election Observation Mission and other regional observers following Ethiopia's June 2026 general election. While the mission's statement acknowledged the conduct of voting in areas it observed and commended aspects of the electoral process, the broader conclusion risks legitimizing an election that falls far short of the democratic standards enshrined in the African Union's own governing principles. This letter is not merely about Ethiopia. It is about the credibility of African institutions and the future of democracy on our continent. The African Charter on Democracy, Elections and Governance establishes clear standards for democratic legitimacy. Elections must be free, fair, transparent, inclusive, competitive, and conducted within an environment where citizens can freely exercise their political rights. The Charter emphasizes political pluralism, independent institutions, citizen participation, respect for human rights, freedom of expression, freedom of association, and equal political opportunity. Measured against these standards, serious questions arise regarding the legitimacy of Ethiopia's 2026 election. The election was conducted while significant portions of the country remained affected by armed conflict. Entire regions faced severe security challenges, political opposition remained constrained, and millions of citizens were unable to participate under conditions that could reasonably be described as free and competitive. International media organizations, independent analysts, and human rights advocates documented an electoral environment marked by conflict, displacement, restrictions on political activity, and the absence of meaningful national political competition. The concerns become even more troubling when examining the available data from conflict-affected regions. According to reports compiled by local observers and civic actors in the Amhara Region, there were approximately 11,902 polling stations across the region. Of those, only 326 polling stations—approximately 2.7 percent—were reported to have conducted voting activities. The remaining 11,576 polling stations, representing approximately 97.3 percent of the total, did not conduct meaningful voting due to conflict, security conditions, or lack of government control. Furthermore, reports indicate that active military engagements occurred in approximately 146 towns and administrative centers during the election period, including more than 100 locations within the Amhara Region alone. Whether one accepts every aspect of these figures or not, the scale of the reported disruption should have prompted extreme caution before declaring the election broadly successful or representative. Equally concerning is the fact that Ethiopia's political environment leading up to the election lacked many of the characteristics associated with genuine democratic competition. Opposition leaders, journalists, civic activists, and independent voices have repeatedly reported intimidation, detention, restrictions on political activity, and limitations on freedom of expression. Elections cannot be evaluated solely by what occurs inside polling stations on election day; they must also be judged by the political environment that precedes them. The fundamental question therefore remains:

ለ201ኛ ኮር 54ኛ እና 74ኛ ክ/ጦር  ስር ለሚገኙት ለሕግ አካላት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ። ============================= ግንቦት28/2018ዓ.ም የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ ሕግና ሥነ-ሥርዓት ጉባኤ፤ ለ201ኛ ኮር እና በሥሩ ለሚገኙ የክፍለ-ጦር እንዲሁም የወረዳ ጊዜያዊ መንግሥት የሕግ አካላት ለተከታታይ 8ቀናት  ከግቦት 21_28/2018 ዓ.ም የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል። ይህ ስልጠና በዋናነት በሕግ ግንዛቤና በድርጅታዊ መመሪያዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን የፍሬ ነገር ህግ እና የስነ ሰርዓት ህጎች ነው። የስልጠናው ዋና ዋና ነጥቦችና የተላለፉ መልዕክቶች፦ 1. የኃላፊዎች መልዕክትና ማሳሰቢያ: ጠበቃ ምንያምር አዲስ (የጉባኤው ም/ሰብሳቢ)፦ ስልጠናው  ድርጅታዊ መመሪያን መሠረት ያደረገ ከመሆኑም በላይ የተቀላጠፈ የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ሰልጣኞችም የተሰጣቸውን ጥራት ያለው እንዲሁም ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪን የሚቆጥብ የፍትሕ አገልግሎት የመስጠት ኃላፊነት በትጋት እንዲወጡ አሳስበዋል። አርበኛ ላይችሉህ ገበየሁ (የ201ኛ ኮር ሰብሳቢ) እና አረበኛ ሻለቃ ዘላለም ጥላሁን የኮሩ ወታደራዊ አስተዳደር  ፦ ሰልጣኞች በስልጠናው ባገኙት የሕግ ግንዛቤ መሠረት የሕዝባቸውን ማኅበራዊ ፍትሕ ማረጋገጥ እንዳለባቸው አሳስበው፤ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በቅንነትና በታማኝነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። 2. የሰልጣኞች ቁርጠኝነት: የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው የተሻለ የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ከፍተኛ የሕግ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም ቀልጣፋና ፈጣን የፍትሕ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት