1 737
مشترکین
+1724 ساعت
+167 روز
+23130 روز
آرشیو پست ها
✔️የ6ኛ 8ኛ ክፍል ተፈታኞችን ኦረንቴሽን ይመለከታል
➡️የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች እና አስፈጻሚ ፈታኞች ሱፐርቫይዘሮችና ሌሎች አካላት( አርብ 5/10/2018)ከጠዋቱ 2:00-4:00 ኦረንቴሽን የሚሰጥ ሲሆን
➡️የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች እና አስፈጻሚ ፈታኞች ሱፐርቫይዘሮችና ሌሎች አካላት አርብ (5/10/2018)ከጠዋቱ 4:00-6:00 ኦረንቴሽን የሚሰጥ ስለሆነ ተፈታኝ ተማሪዎቻቹህ በተጠቀሰ ሰአት በፈተና ጣቢያቸው እንዲገኙ መልክት ይተላለፍ!
➡️ማሳሰቢያ:-በኦረንቴሽን ያልተገኘ ማንኛውም ፈተና አስፈጻሚ በፈተናው የማይሳተፍ ሲሆን በተጠባባቂ የሚተካ ይሆናል!!
+9
የጥያቄና መልስ ዉድድር ተካሄደ፤
✅ሴነ 2/2018 በየካ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት በክፍለ ከተማዉ ደረጃ የ2018 ዓ.ም የሁለተኛ ወሰነ ትምህርትእና የ አመቱ መጨረሻ የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ዉድድር በደማቅ ስነ-ስረዓት በወንድራድ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በዛሬዉ እለት ተካህዷል፡፡
✅በፕሮግራሙ ላይ የክ/ከተማ ት/ጽቤት ባለሙያዎች፣ የት/ቤት ርዕሰ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች እንዲሁም ታማሪዎች ተሳትፏል፡፡
➡️ ባዉድድሩም ፤ተማሪ ስምኦን ባዩ ከ ወንድራድ ት/ቤት 1ኛ
➡️ተማሪ ፋስካ መንግስቱ ከኮከብጽባህ ት/ቤት 2ኛ
✅ ተማሪ አማኑኤል በንቲ ከካራ ት/ቤት 3ኛ
✔️ በመሆን ያጠናቀቁ ሲሆን ትምህርት ቤቶቹም በዚሁ መሰረት ከ 1ኛ- 3ኛ ይዞ ዉድድሩን ሲያጠናቅቁ የማበረታቻ ሽልማት ፤-የወንጫ፣ የሜዳልያ እና የሰርትፊኬት ስጦታወቾ ተበርክቶላቸዉ ሮግራሙ ተጠናቋል፡፡
👏ምስጋና፤-ለዚህ ፕሮገራም ዉበትና ስኬት ተዋናይና ግንባር ቀደም ለሆኑት ለወንድራድ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በክፍለከተማችን ስም ላቅ ያለ መስጋናችን እናቀርባለን👏👏👏👏
Repost from Yeka Education
✔️የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም ዙሪያ ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮች
✅የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡
✅ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ብቻ ማጥቆር አለበት፡፡
✅ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
✅ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን የአራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
✅በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ መልስ (የአራት ማዕዘን ቅንፍ/Square Bracket) ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
✅ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
✅ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
✅ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።
✅መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
✅ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
✅ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ
✅ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም።
✅ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።
#️⃣ሸር
📌 ለሁሉም ተፈታኞች
መልካም የጥናትና የፈተና ጊዜ!
👏👏👏👏👏
🔠🔠🔠🔠
🔠🔠🔠
Our Channel
⬇️⬇️⬇️
https://t.me/dam76
Repost from Yeka Education
✅የፈተና ጊዜ ሲቃረብ ሁላችንም በመጠኑ መጨነቅ እና ከወትሮው ከፍ ባለ መጠን ውጥረት ውስጥ መግባታችን የተለመደ ነገር ነው
።
📌 ይህም ጤናማ ፍርሀት ለፈተና እንድንተጋ ስለሚረዳን በተሻለ ለመዘጋጀት እንዲሁም ጥሩ ትኩረት ለማድረግ ያስችለናል።
✔️ ሆኖም ግን ይህ ጭንቀት ወይም ቴንሽን መጠነኛ ካልሆነ ወደ መደናገር እና ከፍተኛ ለሆነ ውጥረት ይዳርገናል ። በዚህም የተነሳ ፈተናችንን በጥሩ እንዳናስኬድ እና ተገቢውን ትኩረት እንዳንሰጥ ያደረፈርገናል ።
✔️ከዚህም ሀሳብ ጋር በተያያዘ ለዚህ አይነቱ #ጭንቀት እና ውጥረት ውስጥ #እንድንገባ አስተዋጽኦ ከሚያደርጉ #ምክንያቶች ውስጥ #ጥቂቶቹ:
➡️ አሉታዊ ሀሳቦች ወደ አዕምሮ በመምጣት ሀሳባችን በሙሉ ስለ ፈተናው አስከፊነት እና ስለውጤት መበላሸት አብዝተን ስናስብ ።
➡️ በቂ እና ምክንያታዊ ያልሆነ ግመታ እና ድምዳሜ አጠቃሎ ስለፈተናው ማሰብ ።
➡️ የውጫዊ ተፅእኖ እንደ ቤተሰብ ፣ መምህራን እና ጓደኛ የሚመጡ ጫናዎች አስተሳሰባችን ላይ ይህ መሆን አለበት ወይም መሆን የለበትም የሚል አቋም መያዝ ስህተትን እንዳንቀበል እና መሳሳትን እንድንፈራ ስለሚያረግ በፈተና መዳረሻ ከፍተኛ ለሆነ ውጥረት ይዳርገናል ።
➡️ሙሉ ሀሳብን ወደ ፈተናው ይዘት እና ሁኔታ ከማተኮር ይልቅ ወደ ውጤት እና ነጥብ ብቻ ላይ ማተኮር እና ማስላት። እነዚህ ዋና ዋናዎቹ በፈተና ወቅት ውጥረትን እና ጭንቀትን የሚያስከትሉ ምክንያቶች ናቸው።
✅ ስለዚህ ተፈታኞች የተወሰነ ዘዴን በመጠቀም ይህን አይነቱን ከፍተኛ ውጥረት መቆጣጠር የምትችሉበትን መንገድ አንድ በአንድ እንመልከት፤
⭐️ ከፈተና በፊት ማድረግ የሚገባን ዜዴዎች፤ -
➡️ ፈተና ሲመጣ መጠነኛ ውጥረት እና ጭንቀት ተፈጥሮአዊ እና ሁሉም ተፈታኝ ተማሪ እንደሚያጋጥመው መረዳት።
➡️ ለፈተና ስንዘጋጅ አዎንታዊ እና በጎ ሀሳቦችን ማሰብ፡፡ ይህ ማለት ስለፈተናው ክብደት እና አስከፊነት ከማሰብ በተቃራኒው በአይነ ህሊና (visualization) ዘና ብለን ስንፈተን እና ፈተናውን በተገቢ መንገድ ስንፈተን በአእምሮችን መሳል ።
✅ከዚህ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም በክፍል ውስጥ በብቃት የሰራናቸውን ፈተናዎች እና የገኘነውን ጥሩ ውጤቶች ማሰብ። እናም ምን አይነት ፈተና ሊመጣ ይችላል ብለን አብዝተን አለመጨነቅ ይልቅ የሚመጣው ፈተና ከዚህ በፊት ከተማርነው የተለየ አለመሆኑን መረዳት እና መጪውም ፈተና በተመሳሳይ እንደምንሰራው ማሰብ።
➡️ፈተና ማለት ከዚህ ቀደም ከተማርነው ነገር የተረዳነውን እና የቀሰምነውን እውቀት የምንለካበት መመዘኛ እንጂ የኛ የህይወት ምዕራፍ ማብቂያ ወይም አጠቃላይ ችሎታችንን የሚያመላክት አይደለም ።
✅ምክንያቱም ከላይ እንደ ምክንያት ለተቀመጡት ነጥቦች ከዚህ ሀሳብ በተያያዘ አንድ ተማሪ በፈተና ጥሩ ውጤት ባያገኝ እና ቢሳሳት ቀድሞውኑ ወደ ጭንቅላቱ የሚመጣው አለማወቁ ዋጋ እንደሚያስከፍለው እና ቤተሰቦቹም ሆነ መምህራን እንደ ሰነፍ እና ዋጋ እንደሌለው ስለሚገመት ስህተትን አስተካክሎ ለቀጣይ ለማሻሻል እና ለመማር መሰናክል ይፈጥራል።
✅ ስለዚህ ማወቅ ያለብን አንድ ነገር ቢኖር መሳሳትን አለመፍራት እና ሁሌም ለማወቅ እና ራስን ለማሻሻል ዝግጅ መሆንን ነው ። እንዲሁም አሁን የምንፈተነው ፈተና እንዳሰብነው እንኳን ውጤቱ ባያስደስት ለቀጣይ ማስተካከል እና ማሻሻል እንደሚቻል ማመን።
➡️ከጓደኞቻችን ጋር ያጠናነውን ነገር በጋራ ሆነን መጠያየቅ እና እርስ በርስ ያወቅነውን ነገር መለዋወጥ፡፡ ይህ ዘዴ ይበልጥ የማስታወስ ብቃታችንን እንደሚጨምር እና የተጠያየቅነው ነገር እንዳይረሳን ያረጋል ።
📌ከዚህም በተጨማሪ የተሳሳትነውን ነገር ድጋሚ እንድንከልስ እና እርማት እንድናረግ ያግዘናል።
➡️ የፈተና ቀን ሲቃረብ እንደ ወትሮው ዘና ማለት እና በቂ እረፍትና በቂ እንቅልፍ መተኛት ። ይህም ጭንቀትን ይቀንስልናል፣ እንዲሁም ተረጋግተን ያጠናነውን ነገር አስበን እንድንሰራ ይረዳናል።
✔️ ፈተና ከጀመርን በኋላ መድረግ የሚገቡን ነገሮች (ፈተና ላይ እያለን)፤
➡️ ወደ ፈተና ከመሄዳችን ቀደም ብለን ለፈተና የሚረዱንን መሳሪያዎች እና የመፈተኛ ቁሶችን ማዘጋጀት።
➡️አብዝተን ፈተናን እና የምናመጣውን ነጥብ ስሌት አለመገመት ።
➡️ ፈተና ስንጨርስ የተሳሳትነውን ጥያቄ አብዝቶ ማሰብ እና ሌላ ተማሪ መጠየቅ ጭንቀት ውስጥ ስለሚከተን ከዚህ ይልቅ ቤት ሄደን እረፍት ማድረግ እና ለቀጣይ ፈተና መዘጋጀት ።
✅በፈተና ጊዜ ድንገተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ ከገጠመን ወዲያው የምንሰራውን ገታ አድርገን በጥልቀት አየር በአፍንጫችን ስበን ወደ ሳንባ እያስገባን መልሰን ማስወጣት ይህንንም እስክንረጋጋ መደጋገም ።
➡️ ፈተና በምንሰራ ጊዜ ግራ ያጋባንን እና እርግጠኛ ያልሆንበትን ጥያቄ በይለፍ ማቆየት እና ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ይህም ጊዜያችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። ነገር ግን ምልክት አድርገን ማለፍ፤ •
✔️በተመሳሳይ እርግጠኛ ያልሆልንበትን መልስ ላይ ተደናግጠን መሰረዝ እና መደለዝን መቀነስ
✅ ይህም ስንደነግጥ እና ስንጨነቅ የምናውቀውን መልስ ትተን ወደ ሌላ መልስ እንድሰጥ ስለሚያረግ መሰረዝና መደለዝን መቀነስ ።
✅ፈተናውን ወደ ማገባደድ ስንደርስ በይለፍ ያስቀመጥናቸውን ግራ ያጋቡንን ጥያቄዎች ጥቂት አስበንበት መልስ መስጠት ፤ ካልሆነም ደግሞ ብልሀት ተጠቅመን የግመታ መልስ ሰጥተን ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ።
📌በተደጋጋሚ ሰአትን አለመመልከት ወይም ሰአት በቃን አልበቃን እያልን አለመጨነቅ።
✅ ይልቅ በጣም ሳንንቀራፈፍ ተረጋግተን ፈተናውን መስራት እና ፈተናውን ከጨረስን በኋላ ተመልሰን የሰራነውን ጥያቄ አጠቃላይ ማየት ያስፈልጋል።
⭐️የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከ10ቀናት ያልበለጡ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1 ወር ያነሱ ቀናት ይቀሩታል!
#️⃣Share
⭐️ ለሁሉም ተፈታኞች
መልካም የጥናትና የፈተና ጊዜ!⭐️
🔠🔠🔠🔠
🔠🔠🔠
Our Channel
⬇️⬇️⬇️
https://t.me/dam76
Repost from Yeka Education
✔️ለብሔራዊና ከተማ አቀፍ ፈተና የሚዘጋጁ ልጆቻችንን እንዴት እናግዛቸው?
✅ የብሔራዊ እና ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ በጣም ተቃርበዋል። በዚህ ወሳኝ ወቅት ልጆቻችን ከምንም በላይ የቤተሰብ ድጋፍ፣ ፍቅር እና መረጋጋት ያስፈልጋቸዋል።
✔️ ፈተናን በራስ መተማመን እንዲጋፈጡ በቤት ውስጥ ልናደርግላቸው የምንችላቸው 3 ወሳኝ ነገሮች፦
1️⃣/ የተረጋጋ የጥናት ከባቢ መፍጠር፦
➖ በቤት ውስጥ ረብሻና የድምፅ መረበሽ እንዳይኖር በማድረግ፣ ልጆቹ ትኩረታቸውን ሰብስበው የሚያነቡበት ጸጥ ያለ የጥናት ቦታ ማዘጋጀት አስፈላጊ ነው።
2️⃣/ ከጭንቀት ነፃ የሆነ ማበረታቻ መስጠት፦
➖ "ውጤትህ ምን ሊሆን ነው?" በሚል ጫና ከመፍጠር ይልቅ፣ እያደረጉት ያለውን ጥረት በማድነቅ "ጠንክረህ አንብብ፤ እኛ ካንተ ጋር ነን" በማለት ስነ-ልቦናቸውን ይገንቡ።
3️⃣/ የሞዴል ጥያቄዎችን እንዲሰሩ ማገዝ፦
➖የተለያዩ የሞዴል ጥያቄዎችን በተለይም https://t.me/dam76/5612 የተለቀቁ የብዙ አመታት ሞዴል ፈተናዎችን ፕሪንት አድርገው እንዲሰሩና እንዲለማመዱ ያድርጉ
🔠🔠🔠🔠
🔠🔠🔠
⭐️#ሸር
🔤የተማሪዎች አለኝታ
Our Channel
⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/dam76
Repost from Yeka Education
✅ለ12ኛ
✅ ለ8ኛ
✅ ለ6ኛ ክፍል
📌 ብሔራዊና ከተማ አቀፍ ተፈታኞች ከዛሬ ጀምሮ ከ2016 ዓ.ም -2018 ዓ.ም ያሉ የተለያዩ ሞዴል ፈተናዎችንና ሌሎች ወሳኝ መረጃዎችን በተደራጀ መልኩ የምናደርስ ይሆናል!!
✔️ከናንተ የሚጠበቀው ትብብር ቻናላችንን ለሌሎች ሸር በማድረግ 42k እንዲደርስ ተደራሽ ማድረግ ነው!!
⭐️አስኪ ለቻናሉ ያላቹህን ፍቅር ቻናሉን ለጓደኞቻቹህ ሸር በማድረግ አሳዩን!!
✅42k እንደደረስን መልቀቅ እንጀምራለን!!
🔠🔠🔠🔠
🔠🔠🔠
የተማሪዎች አለኝታ‼️
ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇👇
❤️❤️❤️❤️❤️
https://t.me/dam76
Repost from Yeka Education
+2
🔠🔠🔠
✔️በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
(ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
📌በዚህ መሰረትም ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም
✅እንዲሁም የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሰጥ ይሆናል፡፡
📌ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሰጠው በዚህ ከተማ አቀፍ ፈተና በ6ኛ ከፍል 84,882 ተማሪዎች 199 የመፈተኛ ጣቢያዎች እንዲሁም በ8ኛ ከፍል 86,808 ተማሪዎች 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናዉን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡
መልካም ፈተና✅
🔠🔠🔠🅰️
🔤🔤🔤🔤
🔠🔠🔠
🔤🔤🔤
ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇👇
❤️❤️❤️❤️❤️
https://t.me/dam76
+9
ቀን 12/9/2018ዓ.ም
✔️በየካ ክፍለ ከተማ የ2018ዓ.ም የ2ኛ ግማሽ አመት የ6ኛ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና በሁሉም የመንግስትና የግል ት/ቤቶች መስጠት ተጀምሯል
✔️በሞዴል ፈተናው በክፍለ ከተማው 6274 የ6ኛ ክፍል 6981 የ8ኛ ክፍል እና 4863 የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናውን እየወሰዱ ይገኛሉ::
ከትምህርት ቢሮ በተቀመጠው ቀነገደብ መሰረት የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኞች መረጃ ማስተካከያ ያላደረጉ ትምህርት ቤቶች
1.ኮተቤ ብርሀነ ህይወት
2.ደ/ወንድራድ
3.ልዕልት ዘነበ ወርቅ
4.ዳንሴ
5.መካነ ህይወት
6.ኪዳነ ምህረት
7.ማሪፍ
8.የካ ተራራ
9.ሊቦሮ
10.ቀበና አድቬቲስት
11.የካ ግሎባል
12.ራዕይ
13.እማዋይሽ
በተማሪዎች መረጃ ላይ ለሚፈጠረው ችግር ት/ቤቱ ሀላፊነቱን ይወስዳል!
Repost from Yeka Education
✅ለ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና የኦንላይን ልምምድ ያድርጉ!
✔️የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ተፈታኞች ፈተና የሚለማመዱበት አድራሻ ይፋ አድርጓል።
✅ተፈታኞች በተደለደሉበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ያለውን ሊንክ በመጠቀም፣ User Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Password በሚለው ላይ 1234 በማስገባት
✔️ በዴስክቶፕ ኮምፒውተር፣ በላፕቶፕ፣ በታብሌት፣ በስልክ እና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሳሪያዎች ማንኛውንም አይነት የኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም
✔️ ከዛሬ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከፈተናው ድረስ መለማመመድ እንደሚችሉ ተገልጿል።
🔠🔠🔠🅰️
🔤🔤🔤
⭐️Our Channel
⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/dam76
👆👆👆👆
+3
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ፣ የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል የሁለተኛ ሴሚስተር ከተማ አቀፍ ሞዴል ፈተና መስጫ ጊዜ ሰሌዳ
(ግንቦት 6/2018 ዓ.ም)
✔️የሞዴል ፈተና ፕሮግራም ለውጥ
🫰🏻 የ6ኛ፤ 8ኛና 12ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ የሞዴል ፈተና የቀን ለውጥ ተደርጎበታል፡፡
✔️ ከግንቦት 12-14/2018 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል ::
🖍በመሆኑም በዚህ አግባብ ትምህርት ቤቶች ዝግጁ እንድትሆኑ እናሳስባለን ፡፡
✅ለ12ኛ ክፍል የድጋሜ ተፈታኞች
✅በ2018ዓ.ም በየካ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት በደ/ወንድራድ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ስር የተመዘገባቹህ የድጋሚ ተፈታኞች አድሚሽን ካርድ የካ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት 7ኛ ፎቅ እየመጣቹህ እንድትወስዱ እናሳስባለን
🔤🔤🔤🔤
🔤🔤🔤
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/dam76
+6
✔️በ2018 ትምህርት ዘመን በበይነ መረብ የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የማስፈጸሚያ እቅድ ላይ ውይይት ተካሂዷል::
✅( ግንቦት 03/2018 ዓ.ም) የየካ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ውጤታማ ለማድረግ በተዘጋጀ የማስፈጸሚያ ዕቅድ ላይ ከኮማንድ ፖስት አባላት ጋር ውይይት አካሂዷል።
✅የየካ ክ/ከተማ ዋና ስ/አስ/ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታሪኩ ደሳለኝ በ2018 ዓ.ም የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በየደረጃው የሚገኙ የኮማንድ ፖስት አባላትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት ስራ ከወዲሁ መስራት የሚጠበቅበት መሆኑን አስገንዝበዋል።
✅ የፈተና መስጫ ጣቢያዎች የኢንተርኔት መሰረተ ልማትን ጨምሮ በቂ ኮምፒውተሮች ዝግጁ መሆናቸውን ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው በመግጽ ክ/ከተማው ይህን ለማሳካት የበኩሉን ሚና እንደሚወጣ አመላክተዋል።
✅የየካ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ወዳጆ በበኩላቸው በ2018 ዓ.ም በክ/ከተማው በድምሩ 5155 ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ በበይነ መረብ መመዝገባቸውን ጠቁመው ፈተናው ከሰኔ 24/2018 ዓ.ም እስከ ሀምሌ17/2018 ዓ.ም በ6 ዙር የሚሰጥ መሆኑን በመጥቀስ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ በማሳሰብ በቀጣይ ስራዎች እየተገመገሙ የሚሄዱ መሆኑን አስታውቀዋል።
✅የማስፈጸሚያ ዕቅዱ በስርዓተ ት/ት ትግበራና ክትትል ቡድን መሪ አቶ አዱኛው ባምላኩ የቀረበ ሲሆን ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
Repost from Yeka Education
📌እንዴት እናጥና❓
⭐️የሚከተሉትን ምክሮች በመተግበር የማስታወስ ችሎታችሁንና የትኩረት አቅማችሁን ማዳበር ትችላላችሁ:-
✅ 1. ቁርስና ጠቃሚ ምግቦች
✅ሰውነታችን በአግባቡ ሥራውን እንዲሰራ ኃይል ያስፈልገዋል፤ አንጎላችን ደግሞ ትኩረት እንዲኖረውና የማስተዋል አቅማችን እንዲጨምር በቂ የሆነና ያልተቆራረጠ የኃይል አቅርቦት ይፈልጋል።
✅ጥናቶች እንደሚያሳዩት ቁርሳቸውን ተመግበው ወደፈተና የሚገቡ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘግባሉ። የተመጣጠነ ምግብ ተመግበው ለፈተና የሚቀርቡት ደግሞ የበለጠ የማስታወስና የማስተዋል አቅም ይኖራቸዋል።
✅ስለዚህ ሁሌም ቢሆን ፈተና ያለባቸው ተማሪዎች እንደ የገብስ ገንፎ፣ ዳቦ፣ ሩዝና ድንች ያሉ በካርቦሃይድሬት የበለጸጉ ምግቦችን በቁርስ ሰዓት ተመግበው ቢወጡ ይመከራል።እርጎ፣ እንቁላል፣ አሳ፣ ጎመን፣ ቲማቲምና አቮካዶ ዓይነት ምግቦችም እጅጉን ጠቃሚ ናቸው።
✅2. በጠዋት ወደ ጥናት መግባት
⭐️ሁሌም ቢሆን ነገሮችን አስቀድሞ መጀመርን የመሰለ ነገር የለም። ለፈተናም ቢሆን ጥናት በጠዋት ተነስቶ መጀመር በፈተና ወቅት የተረጋጋ መንፈስ እንዲኖረን ይረዳል።
⭐️ጠዋት ላይ ጭንቅላታችን እረፍት አድርጎ በአዲስ መንፈስ ሁሉንም ነገር ስለሚጀምር፤ በዚህ ሰዓት ማጥናት ውጤታማ ያደርጋል። በተለይ ደግሞ የክለሳ ጥናቶችን ለከሰዓት ማሸጋገር ተገቢ አይደለም።ጠዋት ጥናት የምንጀምርበትና የምናበቃበት ሰዓት ከፈተናው በፊት ባሉት ሁለት ወይም ሦስት ሳምንታት ውስጥ ተመሳሳይ ለማድረግ መሞከርም ውጤታማ ያደርጋል።
✅ 3. ምን ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባችሁ ወስኑ
በመጀመሪያ ፈተናው የጽሁፍ ነው ወይስ የተግባር? ወይስ ቃለመጠይቅ ነው የሚለውን መለየት ወሳኝ ነው።
🔋ሁሉም ዓይነት ፈተናዎች የራሳቸው የሆነ የተለያየ አይነት አቀራረብ አላቸው። በምሳሌ አስደግፎ ማብራሪያ መስጠት የሚጠይቅ ዓይነት ፈተና ከሆነ ከዚህ በፊት የተሠሩ ፈተናዎችን እያመሳከሩ ጥቂት ቦታዎች ላይ በትኩረት መዘጋጀት።
✅ምናልባት ፈተናው ምርጫ አልያም አጭር መልስ የሚፈልግ ዓይነት ከሆነ ቀለል ያለና አጠቃላይ መረጃዎችን ለመያዝ መሞከር።
✅4. እቅድ ማዘጋጀት
✅ምናልባት ነገሮችን ቦታ ቦታ ለማስያዝና እቅድ ለማውጣት የምናጠፋው ጊዜ የባከነ መስሎ ሊሰማን ይችላል። ነገር ግን እውነታው በተቃራኒው ነው። ምክንያቱም ምን ማጥናት እንዳለባችሁና መቼ ማጥናት እንዳለባችሁ እቅዳችሁ ይነግራችኋል። ከዚህ በተጨማሪም ምን ያክል እንደተጓዛችሁ ለመመዝገብና ለመከታተል ይረዳል።
✅የትኞቹን ማስታወሻ ደብተሮች መቼ መመልከት እንዳለባችሁ፣ የትኞቹን መጻህፍት ለተጨማሪ ማብራሪያ እንደምትጠቀሙ እንዲሁም የፈተና ጥያቄዎችን መቼ መለማመድ እንዳለባችሁ በእቅድ ውስጥ ማስገባት ውጤታማ ያደርጋል።እዚህ ጋር መርሳት የሌለብን ለእረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴም ቦታ መስጠት እንዳለብን ነው።
✅5. ከፋፍሎ ማጥናት
✅የክለሳ ጥናትን ከፋፍሎ ማካሄድን የመሰለ ነገር የለም። አንድ የትምህርት ዓይነት ላይ 10 ሰዓት ሙሉ ከማሳለፍ በየቀኑ አንድ ሰዓት በማጥናት በ10 ቀን መጨረስ ይበልጥ ውጤታማ ያደርጋል።
✅ያጠናነውን ነገር ለማስታወስና በቀላሉ ለመሸምደድ ጭንቅላታችን ጊዜ ይፈልጋል። ከፋፍሎ ማጥናት ደግሞ ለዚህ ፍቱን መድሃኒት ነው። ከፋፍሎ ማጥናት እጅግ ውጤታማው መንገድ እንደሆነም በመላው ዓለም የተሰሩ የተለያዩ ጥናቶች ያለመክታሉ።
✅ 6. ራሳችሁን ቶሎ ቶሎ ፈትኑ
✅የሥነ አዕምሮ ጥናት ባለሙያዎች እንደሚሉት የማስታወስ ችሎታን ለማዳበርና በራስ መተማመናችንን ለመጨመር ራስን መፈተን ውጤታማ ያደርጋል።
✅ከዚህ በተጨማሪ እየተዘጋጀንበት ያለነውን ጉዳይ በደንብ እንድናውቀው ከማድረጉ በተጨማሪ የረሳናቸው ።የረሳናቸው አልያም የዘለልናቸው ርዕሶችን ለመለየት ይረዳናል።
✅7. መምህር መሆን
✅ከባዱን የክለሳና ራሳችሁን የመፈተን ሥራውን ካከናወናችሁ በኋላ ጓደኞቻችሁን ሰብሰብ አድርጋችሁ በጭንቅላታችሁ የሚመጣውን ነገር በሙሉ ንገሯቸው። ራሳችሁን በመምህር ቦታ አድርጋችሁ እውቀታችሁን ለማካፈል ሞክሩ።ምን ያህል እንደምታስታውሱ ለማወቅ ከመርዳቱ በተጨማሪ ጓደኞቻችሁንም ትጠቅሟቸዋላችሁ።
✅8. ከተንቀሳቃሽ ስልካችሁ ራቅ በሉ
✅ስልኮች በጣም ብዙ ጥቅም አላቸው። ነገር ግን በጥናት ወቅት ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው ነው የሚያመዝነው። በተለይ ደግሞ ማህበራዊ ሚዲያዎችን የምትጠቀሙ ከሆነ።
✅ብዙ ጥናቶች እንዳረጋገጡት ብዙ ጊዜያቸውን ስልካቸው ላይ የሚያሳልፉ ተማሪዎች የትምህርት ውጤታቸው ሁሌም ቢሆን ዝቅ ያለ ነው።ብትችሉ ስልካችሁን አጠገባችሁ እንኳን አታድርጉት።
✅9. ሙዚቃ መቀነስና በጸጥታ ማንበብ
✅በጸጥታ ውስጥ ሆነው ጥናታቸውን የሚያከናወኑ ተማሪዎች ሙዚቃ እየሰሙ ከሚያጠኑት ጋር ሲወዳደሩ በእጅጉ የተሻለ የማስታወስና የትኩረት አቅም እንዳለቸው ማረጋገጥ ተችሏል።
✅10. ቋሚ እረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴ
✅ውጤታማ የክለሳ ጥናት ማለት እረፍት አልባ ጥናት ማለት አይደለም። በጥናታችን መሀል መሀል ላይ ጥሩ አየር ለማግኘትና ሰውነታችንን ለማፍታታት ወጣ ብሎ እንቅስቃሴ ማድረግ የማስታወስ ችሎታችንን በደንብ ከፍ ያደርገዋል።
✅ከዚህ በተጨማሪ ሰውነታችን እና ጭንቅላታችን በእጅጉ የተሳሰሩ በመሆናቸው እንቅስቃሴ ስናደርግ የደም ዝውውራችን ይስተካከላል፤ ይህ ደግሞ በቂ ኦክስጅን ወደ ጭንቅላታችን እንዲሄድ ይረዳል።
✅አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ተዘርዝሮ የማያልቅ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን ጭንቀትን መከላከልና በራስ መተማመንን መጨመር ከነዚህ መካከል ይጠቀሳሉ።
✅11. እንቅልፍ
✅ከፈተና በፊት ያለችውን ምሽት ጥሩ እንቅልፍ አግኝቶ ማሳለፍ ተገቢ እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ። ነገር ግን ጥሩ እንቅልፍ ፈተናው ሲቃረብ ብቻ ሳይሆን ከሳምንታት በፊት ገና ዋናው ጥናት ሲደረግና ክለሳ በሚደረግበት ወቅትም እጅግ ወሳኝ ነው።
✅በጠዋት ተነስቶ ውጤታማ የክለሳ ጥናት ካደረጉ በኋላ በጊዜ ተኝቶ ጥሩ እንቅልፍ ማግኘት ሰውነታችንና ጭንቅላታችን በደንብ ተግባብተው እንዲሰሩ ይረዳቸዋል። ሌሊቱን በሙሉ ለማጥናት ሙከራ አታድርጉ ይላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች። ምክንያቱም ራሳችን ላይ ጫና እያሳደርን ስለሆነ።
⭐️መልካም ጥናት⭐️
🔤Share
🔤🔤🔤🅰️
🔤🔤🔤
ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇👇👇
🪐🪐🪐🪐🪐🪐
https://t.me/dam76
+7
✅የከተማ ግብርና እና የአረንጓዴ ልማት ስራ ቀጣይነት ለማረጋገጥ በኮከበጽባህ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በአዲስ መልክ እየተሰራ ያለ ስራ በከፊል
👏👏👏👏👏
Repost from Yeka Education
🔤🔤🔤🔤🔤 1️⃣2️⃣
📌ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዝግጅት እያደረጉ ነው?
✅በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጁ አጋዥ የትምህርት ይዘቶች እና የመለማመጃ ጥያቄዎችን የያዙ ቪዲዮዎች በድረ-ገፅ ያገኛሉ።
ይለማመዱ
⬇️⬇️⬇️
https://examinfo.moe.gov.et/guides
➡️የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።
መልካም ጥናት✅
🔠🔠🔠🅰️
🔤🔤🔤
⭐️ቻናላችን ይህ ነው
https://t.me/dam76
👆👆👆👆
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
