Grade 8 Info & Materials
رفتن به کانال در Telegram
▶ ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች፦ ➤ በተለያቱ ትምህርት ቤቶች የተዘጋጁ:- ➢ Models ➢ Worksheets ➢ Short notes ➢ ከምትማሩት ትምህርት ጋር የሚሄዱ ቪድዮዎችን ➢ Ministry Exams ➤ የአጠናን ስልትና የፈተና ጊዜ ሲቃረብ በአላህ እገዛ ጭንቀትን ለማስወገድ የሚረዱ ጥቆማዎችን እንለቃለን። ◉ የቂያማ እለት ከምንጠየቀው ጥያቄ አንዱ ❝በአወቅከው ነገር ምን ሰራህበት❞ ነው❗️
نمایش بیشتر2 249
مشترکین
-224 ساعت
-197 روز
+5130 روز
آرشیو پست ها
ወላጅ እናቱን የሚኒስትሪ ፈተናው ቀን በሞት ያጣው ተማሪ ኻሊድ የባንክ አካውንት ይፋ ሆኗል።
ተማሪ ኻሊድን መርዳት የምትፈልጉ የሲንቄ ባንክ እና የአዋሽ ባንክ አካውንት ተከፍቷል። ተማሪ ኻሊድ እድሜው 18 ስላልሞላውና ዘመድም ስለሌለው፤ ብቻውን ገንዘብ አውጥቶ መጠቀም ስለማይችል፣ አካውንቱ በአካባቢው መስጅድ ኡስታዝ፣ ከሀገር ሽማግሌ እና ከራሱ ጋር በጋራ በመሆን አካውንት ተከፍቶለታል።
①) ስንቄ ባንክ
11 14385901915
②) አዋሽ ባንክ
013201115433100
የድል ብስራት! የስኬት ማማ! 🏆
📖 «...ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ጨምርልኝ በል፡፡» (ሱረቱ ጣሃ: 114)
አልሃምዱሊላህ! የቻናላችን ቤተሰቦች ሆይ፣ ዛሬ ሰኔ 12/2018 ዓ.ል የሀገራችን የዓይን ብርሃን የሆኑት የ8ኛ ክፍል አበቦቻችን፣ የሀገር ድምቀቶች እና አንፀባራቂ ኮከቦቻችን የከተማ አቀፍ የሚኒስትሪ ፈተናቸውን በላቀ የዲሲፕሊን መንፈስ እና በታላቅ ስኬት አጠናቀዋል።
ውድ ልጆቻችን! የለፉበት የጥናት ምሽቶች፣ የደከሙበት የመማሪያ ክፍሎች ውጤት ዛሬ በፈገግታችሁ መታተሙ ያስደስተናል። እናንተ የነገዋ ሀገር ተስፋ፣ የቤተሰባችሁ የኩራት ምንጭ ናችሁ። ይህ ጉዞ ለትልልቅ ስኬቶች መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ አይደለም። ገና ብዙ የስኬት ማማዎችን ትረግጣላችሁ፤ የላቀ ታሪክም ትሰራላችሁ! 🚀
ለወላጆች፣ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አስተዳደርና ለመላው ማህበረሰብ፦
ለዚህ ክብር ያበቃችሁ፣ ሌት ተቀን የደከማችሁ፣ በሀሳብ፣ በምክርና በዱዓ ከልጆቻችሁ ጎን የቆማችሁ ሁሉ፤ አላህ ውለታችሁን በጀነት ይክፈለው። የአንድ ልጅ ስኬት የመላው ማህበረሰብ ድልና ኩራት ነው። ✨
🤲 ዱዓችን፦ ሁሉም እጁን አንስቶ አሚን ይበል!
🔷 ያ አላህ! ያጠናቀቁትን ፈተና ለልጆቻችን የላቀ ውጤት እና የደስታ ማብሰሪያ አድርግላቸው፤ ድካማቸውን ከንቱ አታድርግባቸው።
🔷 ያ ረብ! ለእነዚህ የሀገር ድምቀቶች በምድራዊ ሕይወታቸው ጠቃሚ ዕውቀትን፣ በወዲያኛው ዓለም ደግሞ መዳንንና ስኬትን ለግሳቸው።
🔷 ያ አላህ! ለልጆቻቸው ስኬት ደፋ ቀና ለሚሉ ወላጆች፣ ዕውቀታቸውን ለሚለግሱ መምህራንና ለአስተዳደር አካላት በሙሉ ኸይር ጀዛቸውን አብዝተህ ክፈላቸው፤ ማህበረሰባችንንም በዕውቀትና በሰላም ገንባው።
🔷 ያ አላህ! አሁን ላይ የማጠቃለያ ፈተና (Final Exam) መፈተን ለጀመሩ፣ ለቀጣይ የትምህርት ምዕራፍ ሌት ተቀን ለሚተጉ አበቦቻችንና አንፀባራቂ ኮከቦቻችን ሁሉ አእምሯቸውን አብራልን፣ የረሱትን አሳስባቸው፣ የፈሩትን አስወግድላቸው። በዕውቀት አሳድጋቸው፣ በስኬት አስውባቸው፣ በውጤት አበሽብሻቸው!
አሚን ያ ረበል ዓለሚን! 🤲
📚 የዕውቀት ጎዳና፤ ለዘላለም የተባረከ ነው!
✍️ ረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
ውድ ተማሪዎች እንዲሁም መላው የቻናላችን ቤተሰቦች
ሰላም፣ ጤና እና የአላህ እዝነት በእናንተ ላይ ይሁን፤
አልሃምዱሊላህ! የሀገር ተስፋዎች፣ የ6ኛ ክፍል አበቦቻችን እና አንፀባራቂ ኮከቦቻችን ከተማ አቀፍ የሚኒስትሪ ፈተናቸውን ዛሬ በሰላም፣ በስኬት እና በታላቅ የዲሲፕሊን መንፈስ አጠናቀዋል።
ልጆቻችን ይህንን ምዕራፍ በልበ ሙሉነት እንዲሻገሩ በሃሳብ፣ በምክርና በዱዓ ከጎናቸው ለነበራችሁ ውድ ወላጆች እና መላው ማህበረሰብ አላህ ኸይር ጀዛችሁን አብዝቶ ይክፈላችሁ። 🤲
ቀጣዩ የተስፋ ምዕራፍ፦ የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና
ነገ ሐሙስ፣ ሰኔ 11/2018 ዓ.ል ደግሞ ሌላኞቹ የቤታችን ድምቀቶች፣ የ8ኛ ክፍል አበቦች እና አንፀባራቂ ኮከቦቻችን የከተማ አቀፍ ሚኒስትሪ ፈተናቸውን በይፋ ይጀምራሉ። እነዚህ ልጆቻችን የደከሙበትን የጥናት ፍሬ የሚያዩበት፣ የተመኙትን የላቀ ውጤት የሚያስመዘግቡበት እንዲሆን ሁላችንም በዱዓ እና በቅን ምኞት ከጎናቸው እንቁም!
🤲 ለተማሪዎቻችን ዱዓ
ያ አላህ! ነገ ፈተና ለሚጀምሩት የ8ኛ ክፍል ልጆቻችን አእምሯቸውን አብርቶላቸው፣ ያጠኑትን አሳስባቸው፤ የፈሩትን አስወግደህ ልባቸውን በሰኪና (በረጋ መንፈስ) ሙላው። ብዕሮቻቸውን ቀጥ አድርግላቸው፣ ፈተናውን አግራልላቸው፤ የድካማቸውን አምረውና ደምቀው እንዲያዩ፣ የወላጆቻቸውም የኩራት ምንጭ እንዲሆኑ መልካም ውጤትን ለግሳቸው።
ያ ረብ! ዛሬ ፈተናቸውን በሰላም ያጠናቀቁትን የ6ኛ ክፍል አበቦቻችንንም ድካማቸውን ከንቱ አታድርግባቸው፤ የለፉበትን ውጤት አሳምረህ በመልካም የምስራች ልባቸውን አስደስት። ለቀጣዩ የትምህርት ህይወታቸውም በርካታ ስኬቶችንና ብሩህ ተስፋን ስጣቸው።
አሚን ያ ረበል ዓለሚን! 🤲
📚 አላህ ልጆቻችንን ለታላቅ ስኬት ያብቃቸው!
✍️ ረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
📚 📚 ርዕስ: የድል ዋዜማ ማሳሰቢያ፦ የመጨረሻ ጥሪ ለወደፊቱ የሀገር ብርሃኖች!
ለንጋቱ ፀሐዮች፣ ለውድ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ አበቦቻችን በሙሉ፤
የፊታችን ሰኞ ሰኔ 8 (ለ6ኛ ክፍል) እና ሰኔ 11 (ለ8ኛ ክፍል) የምትወስዱት የከተማ አቀፍ ሚኒስትሪ ፈተና ደርሷል። ይህ ዕለት የድካማችሁ ዋጋ የሚከፈልበት፣ የተስፋችሁ ማማ የሚቆምበት ወርቃማ ቀን ነው። አሁን መደናገጥና ፍርሃትን አውርዳችሁ፣ ሙሉ እምነታችሁን በአላህ ላይ ጥላችሁ፣ በፈገግታና በውስጥ ሰላም ወደ ፈተናው አዳራሽ የምትገቡበት ጊዜ ነው።
የአንድ ዓመት ሙሉ ልፋታችሁ ፍሬ እንዲያፈራ፣ በአላህ ፈቃድና እገዛ የሚከተሉትን ወሳኝና ጥብቅ መመሪያዎች በንቃት ተግብሩ፡
❶. የፈተናው ዋዜማ እና የጠዋት ዝግጅት
የመግቢያ ካርድ እና ቁሳቁስ፡ የመግቢያ ካርዳችሁን (Admission Card)፣ HB ወይም 2B እርሳስ፣ ጥሩ ላጲስ እና መቅረጫ በዋዜማው ምሽት አዘጋጅታችሁ አስቀምጡ።
እረፍትና አመጋገብ፡ በፈተናው ዋዜማ በቂ እንቅልፍ ተኙ። ጠዋት ላይ ቀለል ያለ ቁርስ፣ ከሰዓት ደግሞ ቀለል ያለ ምሳ ተመገቡ፤ በቂ ውሃም መጠጣታችሁን አትርሱ።
በሰዓቱ መገኘት፡ ሳይጣደፉና ሳይደናገጡ፣ አእምሮአችሁ እንዲረጋጋ ከፈተናው መጀመሪያ 30 ደቂቃ ቀድማችሁ በጣቢያው ተገኝታችሁ ተረጋጉ።
❷. የኦፕቲካል (OMR) መልስ መስጫ ወረቀት ጥንቃቄ (እጅግ ወሳኝ!)
የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ፡ የፈተና ወረቀት እንደደረሳችሁ ከAdmission Card ላይ አይታችሁ ስማችሁን፣ የትምህርት ቤቱን ስም፣ የመለያ ቁጥራችሁን (Registration Number) እና የትምህርት አይነት መለያ ኮዱን (Subject Code) በየሳጥኑ በትክክል ፃፉ።
ሳጥኖችን ማጥቆር፡ ከፃፋችሁት ቁጥር እና ፊደል ትይዩ ያለውን አራት ማዕዘን ቅንፍ [ ] በእርሳስ ብቻ በጥንቃቄ አጥቁሩ።
ምርጫ መቀየር ሲፈልጉ፡ መጀመሪያ ያጠቆራችሁትን ቦታ በላጲስ ምንም አይነት የእርሳስ ዱካ ሳይቀር በደንብ አጥፉት።
የወረቀቱ ደህንነት፡ ወረቀቱ ላይ ምንም አይነት ትርፍ ጭረት፣ ስዕል ወይም ነጥብ አታድርጉ፤ ማዕዘኖቹን አታጥፉ። ማሽኑ (OMR) እንዳያነበው ሊያደርግ ስለሚችል በከፍተኛ ንፅህና ያዙት።
እገዛ መጠየቅ፡ በአጋጣሚ ወረቀቱ ቢቀደድ ወይም ቢበላሽባችሁ፣ ምንም ሳትደነግጡ እጅ በማውጣት ፈታኙን መምህር በአክብሮት ጠይቁ።
❸. ከፈተና በኋላ...
ፈተናው እንደተጠናቀቀ "ምን አገኘሁ? ስንት ጥያቄ ተሳሳትኩ?" በማለት ጥያቄዎችን ከጓደኞቻችሁ ጋር አትወያዩ። ይህ ጭንቀትን ስለሚጨምር ለቀጣዩ ፈተና አእምሮአችሁን ያደክማል። ከአላህ እገዛ ቀጥሎ የተረጋጋ አእምሮ ለቀጣዩ ፈተና ትልቅ ስኬት ነው።
ውድ ተማሪዎቻችን፤ እኛ በበኩላችን ሙሉ እምነት ጥለንባችኋል። እናንተ ሰበቡን (ምክንያቱን) በሚገባ አድርሳችኋል፤ ቀሪውን ነገር ግን ሙሉ በሙሉ ሁሉንም ነገር ማድረግ በሚችለው በፈጣሪያችሁ በአላህ ላይ ጥሉት (ተወኩል አድርጉ)። ጥረታችሁን አምኖ በአላህ ላይ የተደገፈ ተማሪ መቼም አይወድቅም። ከፊት ለፊታችሁ ድልና ስኬት ይጠብቃችኋል!
የግጥም ግብዣ ✍️ ረሻድ 👇
ንፁዎችን አደራ
በተወኩል ልመሳጠር - ከጌታዬ ጋራ
መጥፎን አርቅላቸው - ከሚቀማመጡበት ስፍራ
ወዳጅ አበርክትላቸው - አላህን የሚፈራ፤
ሰውን የሚያከብር - የማያውቅ ጎራ፤
ህይወቷቸው ይመር - ኑሮአቸውም ይብራ፤
በተውሒድ ይሞላ - የህይወታቸው ጎተራ፤
በአላህ ይጠበቁ - ከመጥፎ አሻራ
እባክህ የአላህ - ተማሪዎችን አደራ፤
እባክህ የአላህ - ንፁዎችን አደራ።
🤲 አጭር ዱዓ ለአንፀባራቂ ኮከቦቻችን ⭐
ያ አላህ! አንተ እውቀትን ሰጪ፣ ልብን ከፋች እና ጥበብን መጋቢ አምላክ ነህ። እነዚህን ውድ ልጆቻችንን በፈተና ወንበር ላይ በሚቀመጡበት ወቅት ልባቸውን አስፋላቸው፤ ያጠኑትን ወደ አእምሯቸው መልስላቸው፤ ያልገባቸውን አብራራላቸው። በፈተና ወቅት የሚመጣን ጭንቀት እና መደናገር አንሳላቸው፤ ብዕሮቻቸውን ወደ ትክክለኛው መልስ አቅናላቸው። በጥረታቸው ብቻ ሳይሆን በአንተ ሰፊ እዝነት፣ ልፋታቸውን አሳምረህ አስደሳች እና ያማረ ውጤት ወፍቃቸው። አሚን! ያ ረበል ዓለሚን! 🤲
✍️ ረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
📚 Review English Questions from Grade 6, 7 and 8
✅ Part 3 (Last)
📚For Grade 8 Students
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
✅ አላህ ይርዳችሁ!! 🤲🤲
📚 Review English Questions from Grade 6, 7 and 8
✅ Part 2
📚For Grade 8 Students
📚 Review English Questions from Grade 6, 7 and 8
✅ Part 1
📚For Grade 8 Students
📚 ርዕስ: ከፈተና በፊትና በኋላ ማድረግ የሚገቡን ነገሮች
ውድ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች፤ የፊታችን ግንቦት 10 እስከ 12/2018 ዓ.ል ለምትወስዱት የሞዴል ፈተና እንዲሁም ለቀጣዩ የሚኒስትሪ ፈተና ስንቅ ይሆን ዘንድ፣ ይህንን አጭር እና ጠቃሚ ምክር በጥንቃቄ አንብቡት።
የፈተና ጊዜ ሲቃረብ ሁላችንም በመጠኑ መጨነቅ እና ከወትሮው ከፍ ባለ መጠን ውጥረት ውስጥ መግባታችን የተለመደ እና ተፈጥሯዊ ነገር ነው። ይህንን አይነቱን ከፍተኛ ውጥረት መቆጣጠር የምትችሉበትን መንገድ አንድ በአንድ እንመልከት።
1. ከፈተና በፊት ማድረግ የሚገቡን ወርቃማ ዘዴዎች
♦️አመለካከትን ማስተካከል፡ ፈተና ማለት ከዚህ ቀደም ከተማርነው ነገር የተረዳነውን እና የቀሰምነውን እውቀት የምንለካበት መመዘኛ እንጂ የኛ የህይወት ምዕራፍ ማብቂያ ወይም አጠቃላይ ችሎታችንን የሚያመላክት አለመሆኑን መረዳት ያስፈልጋል። መሳሳትን አትፍሩ፤ ሁሌም ለማወቅ እና ራስን ለማሻሻል ዝግጁ መሆን የብልህ ተማሪ መገለጫ ነው።
♦️የጋራ ጥናት፡ ከጓደኞቻችን ወይም ከወላጆቻችን ጋር ያጠናነውን ነገር በጋራ ሆነን መጠያየቅ እና እርስ በርስ ያወቅነውን ነገር መለዋወጥ ትልቅ ጥቅም አለው። ይህ ዘዴ የማስታወስ ብቃታችንን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚጨምር እና የተጠያየቅነው ነገር እንዳይረሳን ያደርጋል።
♦️በቂ እረፍት እና እንቅልፍ፡ የፈተና ቀን ሲቃረብ እንደ ወትሮው ዘና ማለት እና በቂ እረፍትና በቂ እንቅልፍ መተኛት ጭንቀትን ይቀንስልናል፤ እንዲሁም ተረጋግተን ያጠናነውን ነገር አስበን እንድንሰራ ይረዳናል።
💡የሳይንቲስቶች እይታ፡ "እንቅልፍ የተማርነውን አዲስ እውቀት ወደ ዘላቂ ማህደረ-ትውስታ (Long-term memory) የምናሸጋግርበት ወርቃማ ድልድይ ነው።" ስለዚህ በቂ እንቅልፍ ማግኘት ያጠናነውን እንዳንረሳ ያደርገናል።
2. በፈተና ወቅት መከተል ያለብን ጥበቦች
♦️ቅድመ ዝግጅት፡ ወደ ፈተና ከመሄዳችን ቀደም ብለን ለፈተና የሚረዱንን መሳሪያዎች እና የመፈተኛ ቁሶችን ማዘጋጀት አለብን።
♦️ድንገተኛ ጭንቀትን ማሸነፍ፡ በፈተና ጊዜ ድንገተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ ከገጠመን ወዲያው የምንሰራውን ገታ አድርገን በጥልቀት አየር በአፍንጫችን ስበን ወደ ሳንባ እያስገባን መልሰን ማስወጣት ይኖርብናል። ይህንንም እስክንረጋጋ መደጋገም ወሳኝ ነው።
📖 ነቢዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) ከባድ ሀላፊነት ሲገጥማቸው አላህን እንዲህ ብለው ተማጸኑ፦ ❝ጌታዬ ሆይ! ልቤን አስፋልኝ፤ ነገሬንም ለእኔ አግራልኝ።❞ (ሱረቱ ጣሀ፡ 25-26)። እናንተም በፈተና ወንበር ላይ ስትቀመጡ ይህንን በማሰብ አላህ ነገራችሁን እንዲያገራላችሁ ጠይቁ።
♦️ራስን ማረጋጋት፡ "እኔ የምችለውን አድርጌያለሁ (ሰበብ አድርሼያለሁ)፣ የቀረውን ለአላህ ሰጥቼዋለሁ!" በማለት የማረጋጊያ ቃላትን ለራሳችሁ ንገሩ።
♦️የጥያቄ አያያዝ ስልት፡ ግራ ያጋባንን እና እርግጠኛ ያልሆንበትን ጥያቄ በይለፍ ማቆየት እና ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ጊዜያችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። ፈተናውን ወደ ማገባደድ ስንደርስ በይለፍ ያስቀመጥናቸውን ግራ ያጋቡንን ጥያቄዎች ጥቂት አስበንበት መልስ መስጠት፤ ካልሆነም ደግሞ ብልሀት ተጠቅመን የግምት መልስ ሰጥተን ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ይገባናል። በተደጋጋሚ ሰአት በቃን አልበቃን እያልን መጨነቅ የለብንም።
🔴 መሰረዝና መደለዝን መቀነስ፡ ስንደነግጥ እና ስንጨነቅ የምናውቀውን መልስ ትተን ሌላ መልስ እንድንሰጥ ስለሚያረግ፣ በተመሳሳይ እርግጠኛ ያልሆልንበትን መልስ ላይ ተደናግጠን መሰረዝ እና መደለዝን መቀነስ አለብን።
3. ከፈተና በኋላ...
አብዝተን ፈተናን እና የምናመጣውን ነጥብ ስሌት መገመት አይገባንም።
ፈተና ስንጨርስ የተሳሳትነውን ጥያቄ አብዝቶ ማሰብ እና ሌላ ተማሪ መጠየቅ ጭንቀት ውስጥ ስለሚከተን፣ ከዚህ ይልቅ እረፍት ማድረግ እና ለቀጣይ ፈተና መዘጋጀት ይመከራል። አሁን የምንፈተነው ፈተና እንዳሰብነው እንኳን ውጤቱ ባያስደስት ለቀጣይ ማስተካከል እና ማሻሻል እንደሚቻል ማመን አለብን።
⭐💫 ማጠቃለያ
ሁሌም ልናስታውሰው የሚገባን ትልቁ እውነት፡- ፈተና ማለት ለጀነት ማለፊያ ትኬት እንዳልሆነ እርግጠኛ መሆን ነው። ሁሉም ነገር አላህ ከወሰነው ውጭ እንደማይሆን ማመን አለብን። ከኛ የሚጠበቀው የአቅማችንን ያህል ማድረግ፣ ሌላውን ለአላህ መተው ነው። አላህ በናንተው ጥረት ብቻ ሳይሆን በሱ እዝነት መልካም የሆነ ውጤትን ይሰጣችኋል።
🤲 ዱዓ
ያ አላህ! አንተ እውቀትን ሰጪ፣ ልብን ከፋች አምላክ ነህና ለእነዚህ ልጆች ልባቸውን አስፋላቸው። ያጠኑትን ወደ አእምሮአቸው መልስላቸው፤ ያልገባቸውን አብራራላቸው። በፈተና ወቅት የሚመጣን ጭንቀት እና መደናገር አንሳላቸው። በጥረታቸው ብቻ ሳይሆን በአንተ ሰፊ እዝነት፣ ልፋታቸውን አሳምረህ አስደሳች እና ያማረ ውጤት ወፍቃቸው። ያረብ... ቀጣዩን የህይወት ዘመናቸውንም በስኬት፣ በኢማን እና በጥበብ የተሞላ አድርግላቸው! አሚን! 🤲
═══════════════
◆ ጥረት ካለ ስኬት አይርቅም፤ ትጋት ካለ ድል አይታጣም!!
✅ ስኬት ለልጆቻችን፣ ለአበቦች፣ ለአንፀባራቂ ኮከቦች!
✨━━━━━━━━━━━━✨
✍️ ረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
📌 የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የከተማ አቀፍ ሚኒስትሪ ፈተና መልስ መስጫ ወረቀት (Answer Sheet) አጠቃቀም መመሪያ
ውድ ተማሪዎች፤ ለዚህ ትልቅ ፈተና ያደረጋችሁት ጠንካራ ዝግጅት እና የለፋችሁበት ውጤት በትክክል ተመዝግቦ ስኬታማ እንድትሆኑ፣ የመልስ መስጫ ወረቀታችሁን አጠቃቀም በጥንቃቄ ማወቅ አለባችሁ። የሚከተሉትን መመሪያዎች በትኩረት አንብባችሁ ተግብሩ።
ክፍል 1፡ መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት አሞላል
መለያ ቁጥር፦ የተማሪ መለያ ቁጥራችሁን (ID) እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥርን ከላይ ወደ ታች በተሰጣቸው ሳጥኖች ውስጥ በትክክል ፃፉ።
ማጥቆር፦ በፃፋችሁት ቁጥር ትይዩ ያለውን አራት ማዕዘን ቅንፍ [ ] (Square Bracket) ብቻ በጥንቃቄ አጥቁሩ።
ክፍል 2፡ መልስ አሰጣጥ እና የቁጥር ማስተያየት
ቁጥርን ማስተያየት (ወሳኝ)፦ የምታነቡትን የጥያቄ ቁጥር እና በወረቀቱ ላይ ያለውን የመልስ መስጫ ቁጥር ሁልጊዜ እያስተያያችሁ አጥቁሩ። (የአንዱን ጥያቄ መልስ ሌላ ቁጥር ላይ በማጥቆር ሙሉ ረድፍ እንዳይሳሳትባችሁ ተጠንቀቁ!)
የመልስ ምርጫ፦ ትክክል ነው ብላችሁ የመረጣችሁትን መልስ ፊደል ትይዩ ያለውን አራት ማዕዘን ቅንፍ [ ] በትክክል አጥቁሩ።
እርሳስ ብቻ ይጠቀሙ፦ ማጥቆር ያለባችሁ በእርሳስ ብቻ ነው! በእስክሪብቶ መፃፍ ፈጽሞ የተከለከለ በመሆኑ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ ይዛችሁ መቅረብ አትዘንጉ።
የጥንቃቄ እርምጃ፦ ሲያጠቁሩ እርሳሱ ከተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ በጥንቃቄ አጥፉት።
መልስ ስለመቀየር፦ ያጠቆራችሁትን መልስ መቀየር ብትፈልጉ፣ መጀመሪያ ያጠቆራችሁትን ቦታ በላጲስ ምንም ዱካ ሳያስቀር በደንብ አጥፉት።
አንድ ምርጫ ብቻ፦ በአንድ ረድፍ (ለአንድ ጥያቄ) ከአንድ በላይ መልስ ማጥቆር አይቻልም፤ ከአንድ በላይ ከጠቆረ ጥያቄው ውድቅ ይደረጋል።
ክፍል 3፡ የወረቀት ደህንነት ጥንቃቄ (በጣም አስፈላጊ!)
ፅሁፍ እና ጭረት ክልክል ነው፦ ከመፃፊያ እና ማጥቆሪያ ቦታ ውጭ በወረቀቱ ፊትም ሆነ ጀርባ ምንም አይነት ፅሁፍ፣ ስዕል ወይም ጭረት ማድረግ ፈጽሞ የተከለከለ ነው። ትንሽ ጭረት ወይም ነጥብ ካለ ወረቀቱ በኮምፒውተር ላይነበብ ስለሚችል ሙሉ በሙሉ ውድቅ ሊሆን ይችላል!
ጠርዞችን አለመንካት፦ በመልስ መስጫ ወረቀቱ ማዕዘኖች ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች (Corners) መንካትም ሆነ ማበላሸት ፈጽሞ የተከለከለ ነው።
ንፅህና እና ጥንቃቄ፦ ወረቀታችሁን በከፍተኛ ንፅህና ያዙ! እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፣ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅ አለባችሁ። በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ ስትጠቀሙ ደግሞ ወረቀቱ እንዳይቀደድ እጃችሁን አቅልሉ ዘንድ ይመከራል።
ክፍል 4፡ ተጨማሪ አጠቃላይ ማሳሰቢያዎች እና እገዛ
ቅድመ-ማረጋገጥ፦ ፈተናውን ከመጀመራችሁ በፊት የጥያቄ ወረቀቱ ሙሉ መሆኑን እና የተሰጣችሁ የፈተና ዓይነት ትክክል መሆኑን አረጋግጡ።
ወረቀት ቢበላሽባችሁ፦ በአጋጣሚ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ቢበላሽባችሁ ወይም ቢቀደድባችሁ፣ ምንም ሳትደነግጡ እጅ በማውጣት ፈታኙን መምህር ወረቀት እንዲቀይርላችሁ በአክብሮት ጠይቁ።
እገዛ መጠየቅ፦ ማንኛውንም የቁጥጥራችሁ ውጭ የሆነ ነገር ሲያጋጥም በፈተና ክፍሉ ውስጥ ያሉትን ፈታኝ መምህራን እጅ አውጥታችሁ በትህትና ከመጠየቅ ወደኋላ አትበሉ።
የመጨረሻ መልዕክት
ውድ ተማሪዎች፤ በቂ ዝግጅት አድርጋችኋል፣ ደክማችኋል፣ ለፍታችኋል። አሁን የቀረው በራስ መተማመንን ሰንቆ፣ በረጋ መንፈስ ፈተናውን መስራትና ውጤቱን በአላህ ላይ መጣል (መመካት) ብቻ ነው። ስኬት ይጠብቃችኋል!
✅ አላህ ይርዳችሁ!! 🤲🤲
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
✍️ ረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
♦️ የሰዓት እና የፈተና አያያዝ ስልት፦ ፈተናው ሲጀምር መጀመሪያ የምታውቋቸውን ጥያቄዎች በፍጥነት በመስራት በራስ መተማመናችሁን አሳድጉ። በአንድ አስቸጋሪ ጥያቄ ላይ ከሁለት ደቂቃ በላይ በማባከን ሰዓታችሁን አትጨርሱ። የከበዳችሁን ጥያቄ ምልክት አድርጋችሁ አልፉት፤ ሁሉንም ከሰራችሁ በኋላ ወደ እሱ ትመለሳላችሁ።
♦️ በሰዓቱ መገኘት፦ ጥዋት ሳይደናገጡና ሳይጣደፉ በሰዓቱ (ከተቻለ 30 ደቂቃ ቀድሞ) በመፈተኛ ጣቢያ መገኘት አእምሮ ሰላም እንዲሆን ያደርጋል።
🏅 ክፍል ➓፦ መዝጊያ፦ ወደ ድል አደባባይ ሂዱ!
ውድ አበቦቻችን! ይህ ምናልባትም ከፈተናው በፊት የምንለዋወጠው የመጨረሻው ትልቅ መልዕክታችን ሊሆን ይችላል። እኛ በበኩላችን ሙሉ እምነት ጥለንባችኋል። እናንተ የታሪካችን አዲስ ምዕራፎች ናችሁ።
ሰኔ 8 (ለ6ኛ ክፍል) እና ሰኔ 11 (ለ8ኛ ክፍል) ወደ ፈተና ክፍሉ ስትገቡ፣ ትከሻችሁን ቀና አድርጋችሁ፣ ፈገግ ብላችሁ፣ በፈጣሪ ስም ተማምናችሁ ግቡ። ይህንን ያህል የለፋችሁለት ስኬት በእጃችሁ ላይ ይወድቃል።
የስኬት ቃል ኪዳን፦ "ያለፈውን ጊዜ በሚገባ ተጠቅሜያለሁ፤ አሁንም ያለኝን ጊዜ እጠቀማለሁ። ፈጣሪዬን አምኜ የላቀ ውጤት አመጣለሁ!"
መልካም የፈተና እና የድል ቀናት ይሁኑላችሁ! እናንተ የነገዎቹ አሸናፊዎች ናችሁ! 🏆 ያ አላህ ተፈታኝ ተማሪዎቻችንን በድል አጅባቸው! አሚን።
🤲 ያ አላህ! ያ ረብ! 🤲
እነዚህ የነገው ንጋት ብሩህ ፀሐዮች የሆኑት ውድ ተማሪዎቻችን ላለፉት ዓመታት የለፉበትን ድካም ከንቱ አታድርግባቸው። በፍርሃት ፈንታ ፍጹም መረጋጋትን በልባቸው ውስጥ አስፍር።
ያ አላህ! በፈተናው ዕለት አእምሯቸውን አብራው፤ ማህደረ-ትውስታቸውን ክፈትላቸው። ያጠኑትን ነገር ሁሉ በፈተናው ወረቀት ላይ በትክክለኛው ሰዓት እንዲያስታውሱት ቀናውን መንገድ ምራቸው። ብዕሮቻቸውን ወደ ትክክለኛው መልስ አቅናላቸው።
ፈጣሪ ሆይ! ከፈተናው አዳራሽ በታላቅ ድልና በፈገግታ እንዲወጡ አድርጋቸው። የወላጆቻቸውን ልብ በደስታ አርስ፤ የትምህርት ቤታቸውን እና የአስተማሪዎቻቸውን ድካም በላቀ ውጤት አጅበው። የወደፊት ጉዟቸውን የከፍታና የብርሃን ማማ አድርገው!
አሚን! ያ ረበል ዓለሚን! 🤲
══════════════
✍️ ረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
🎯 የክብር ዘመቻው የመጨረሻው 10 ሜትር፦ ከጭንቀት ወደ ንግስና!
ለንጋቱ ፀሐዮች፣ ለ2018 ዓ.ል የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የከተማ አቀፍ ሚኒስትሪ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ! 🎓✨
🔶 ክፍል ❶፦ ታላቁ መግቢያ፦ ለውድድር ሳይሆን ለታሪክ የተፈጠራችሁ የነገው አበቦች!
ውድ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል አንፀባራቂ ኮከቦች! ዛሬ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ል ላይ ቆመን ወደፊት ስንመለከት፣ የቀሩን ቀናት ከ10 አይበልጡም። የ6ኛ ክፍል ሰኔ 8፣ 9 እና 10፤ የ8ኛ ክፍል ደግሞ ሰኔ 11 እና 12 የውሳኔ ቀናቶቻችሁ ናቸው። ይህ ፈተና እናንተን ለመመዘን የሚመጣ ጠላት ሳይሆን፣ ለአመታት የለፋችሁበትን የድካም ፍሬ የምታጭዱበት፣ የታላቁ ስኬታችሁ ባለቤት የምትሆኑበት የክብር መድረክ ነው።
ይህ መልዕክት የመጨረሻ የጦር ሜዳ መመሪያችሁ ነው! እንደ ሰይፍ የሳለ፣ እንደ ሚሳኤል ግቡን የሚመታ። እናንተ የምድር ጨው፣ የሀገር ተስፋ ናችሁ። ይህንን የመጨረሻ 10 ሜትር እንዴት በድል እንደምትሻገሩት እነሆ በተግባር የተፈተኑ መመሪያዎች።
📚 ክፍል ❷፦ የቀሩትን 10 ቀናት "መጨቅለቅ" (The Ultimate Crunch Time)
ጊዜው የሰከንድ ሳንቲሞች የሚቆጠሩበት ወርቃማ ወቅት ነው። አሁን አዲስ መጽሐፍ የምታገላብጡበት ሳይሆን፣ የነበራችሁን እውቀት የምታጠቁሩበት ጊዜ ነው።
◆ የጊዜ አጠቃቀም (Time Compression): የቀሩትን ቀናት በሰዓታት ከፋፍሏቸው። በእያንዳንዱ ሰዓት ላይ ምን እንደምታነቡ ግልጽ እቅድ ይኑራችሁ።
◆ የአንበሳው ድርሻ ለዋናው ርዕስ: ከፍተኛ ማርክ ሊያስገኙ የሚችሉ ዋና ዋና አርዕስቶችን ለይታችሁ አጥኑ።
◆ ትኩረትን ሰብሰብ ማድረግ: ማህበራዊ ሚዲያ እና ትኩረት የሚሰርቁ ነገሮችን ለነዚህ 10 ቀናት በቁልፍ አስቀምጧቸው። ታላቁ ሳይንቲስት አልበርት አንስታይን እንደተናገረው፦
"በጣም ብልህ ስለሆንኩ ሳይሆን፣ ከችግሮች ጋር ረዘም ላለ ጊዜ አብሬ ስለማቆይ ነው!"
አሁን ካጠኑት ርዕስ ጋር ብቻ አብሮ የመቆያ ጊዜ ነው።
🔄 ክፍል ❸፦ የክለሳ ጥበብ እና የሞዴል ፈተናዎች ስልታዊ ውጊያ
ማንበብ ብቻውን አይበቃም፤ ያነበቡትን ማስታወስና ለፈተናው ማዋቀር የድል ቁልፍ ነው።
✅ በማጠቃለያ መክለስ (Active Recall): የያዛችኋቸውን አጫጭር ማስታወሻዎች (Summary Notes) ብቻ በዓይን እያነበቡ በፍጥነት መሮጥ።
✅ የሞዴል ጥያቄዎች ጋጋታ: ላለፉት ጥቂት ወራት የተሰጡ የሞዴል ፈተናዎችን እና ያለፉት ዓመታት የሚኒስትሪ ጥያቄዎችን ሰዓት እያዩ መስራት። ይህ ፈተናው ላይ የሚመጣውን ድባብ በጭንቅላታችሁ ውስጥ አስቀድሞ ይቀርጻል።
✅ ስህተትን ማረሚያ ደብተር: በሞዴል ጥያቄዎች ላይ የተሳሳታችሁትን ነጥብ ደግማችሁ እዩት። ስህተት አሁን ሲታረም ለፈተናው ዕለት ትልቅ ስጦታ ይሆናል።
🧠 ክፍል ❹፦ በራስ መተማመን እና በአላህ መመካት (Effort + Trust)
በራስ መተማመን የሚመጣው ካለምክንያት አይደለም። ለአመታት ካፈሰሳችሁት ላብ፣ ካደራችሁበት ሌሊት እና ካደረጋችሁት ከፍተኛ ጥረት የሚቀዳ ነው።
🔶 ከትጋት በኋላ መመካት፦ ሙሉ አቅማችሁን አውጥታችሁ ካጠናችሁ፣ ከለፋችሁና ከደከማችሁ በኋላ፣ በራሳችሁ ጥረት ላይ ሙሉ እምነት ይኑራችሁ።
🔶 ቀሪውን ለባለቤቱ መስጠት፦ ሰበቡን (ምክንያቱን) በሚገባ ካደረሳችሁ በኋላ፣ ቀሪውን ነገር ሙሉ በሙሉ በአላህ ላይ ጣሉት (ተወኩል አድርጉ)። ጥረታችሁን አምኖ ፈጣሪ ላይ የተደገፈ ተማሪ መቼም አይወድቅም። ያኔ ፍርሃት ቦታውን ለውስጥ ሰላም ይለቃል።
🛡️ ክፍል ❺፦ የጭንቀትና የውጥረት ሚሳኤል መከላከያ (Psychological Armor)
ፈተናው ሲቃረብ የልብ ትርታ መጨመርና "ሁሉንም ነገር የረሳሁት መሰለኝ" የሚል ስሜት መፈጠሩ ተፈጥሯዊ ነው። ይህ የውሸት ስሜት ነው። ጭንቅላታችሁ መረጃዎችን እያደራጀ መሆኑን ማሳያ እንጂ የመርሳት ምልክት አይደለም።
♦️ አዎንታዊ ንግግር (Positive Self-Talk): "እችላለሁ! ተዘጋጅቻለሁ! የለፋሁበትን ውጤት አገኛለሁ!" እያላችሁ ለራሳችሁ ንገሩ።
♦️ የኢማሙ አሕመድ ድንቅ ምክር: ታላቁ ሊቅ ኢማሙ አሕመድ የተረጋጋ አእምሮ ስላለው ስኬት ሲናገሩ፦
❝በጎ ነገርን አስብ፤ ሁልጊዜም በበጎ ነገር ላይ ትሆናለህ።❞
ጭንቀትን በአዎንታዊ አስተሳሰብ አሸንፉት።
♦️ ከአሉታዊ ሰዎች መራቅ: "ፈተናው ይከብዳል" የሚሉ፣ ፍርሃትን የሚዘሩ ጓደኞችን ለነዚህ ቀናት በሩቁ በሏቸው። አሁን የሚጠቅማችሁ ብርታትና ተስፋ ብቻ ነው።
🕋 ክፍል ❻፦ የሰበብ ማድረስ ትርጉም (የአላህ ቃል ማጠናከሪያ)
ሙስሊም ተማሪዎችም ሆናችሁ የሌላ እምነት ተከታዮች፣ የሰው ልጅ ግዴታ መጣርና መጣር ብቻ ነው። ውጤቱን የሚወስነው ግን ፈጣሪ ነው። አላህ በቁርዓኑ እንዲህ ይላል፦
❝...በአላህም ላይ የሚጠጋ ሰው እርሱ በቂው ነው፤ አላህ ትዕዛዙን አድራሽ ነው...❞ (ሱረቱ አጥ-ጠላቅ፡ 3)
እናንተ ሰበቡን አድርሱ፤ ቀሪውን ለፈጣሪ ተዉት፣ ፍጹም ሰላምና መረጋጋት ያቅፋችኋል።
🤲 ክፍል ❼፦ የዒባዳ፣ የዱዓ እና የወላጆች ምርቃን ኃይል
እውቀት የፈጣሪ ስጦታ ነው፤ ያንን ስጦታ ደግሞ በዱዓ እና በጸሎት እንለምነዋለን። የወላጆቻችሁ ምርቃን ደግሞ የተዘጋውን በር ሁሉ የመክፈት ምስጢራዊ ኃይል አለው።
◆ በዒባዳ መበርታት: ፈርደ ሰላቶቻችሁን በወቅቱ ስገዱ፤ በሱጁድ ላይ እውቀትንና መረጋጋትን ለምኑ።
◆ የነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰልም) መመሪያ: የአላህ መልክተኛ እንዲህ ብለዋል፦
❝ለአንተ የሚጠቅምህን ነገር ላይ ጉጉ ሁን (ትጋ)፤ በአላህም ታገዝ፤ አትስነፍም!❞ (ሶሒሕ ሙስሊም፡ 2664)
◆ የወላጆች ዱዓ: ዛሬውኑ ወደ ውድ ወላጆቻችሁ ሂዱና ዱዓና ምርቃታቸውን ለምኑ። የወላጆች ዱዓ በቀጥታ ተቀባይነት አለው፤ መንገድን ያቀናል፣ አእምሮን ይከፍታል።
💤 ክፍል ❽፦ በቂ እረፍት እና የእንቅልፍ ወሳኝነት (The Brain Recharge)
ብዙ ተማሪዎች የሚሳሳቱበት ትልቁ ስህተት ሌሊቱን ሙሉ ባለመተኛት አእምሯቸውን ማድከማቸው ነው። የተዳከመ አእምሮ ፈተና ላይ መረጃዎችን ማውጣት አይችልም።
✅ ከ6-8 ሰዓት እንቅልፍ: በእነዚህ 10 ቀናት ውስጥ በተለይም በፈተናው ዋዜማ በቂ እንቅልፍ መተኛት ግዴታ ነው።
✅ የአንጎል ሳይንስ: እንቅልፍ ስትተኙ ያጠናችሁት ነገር ከአጭር ጊዜ ማህደረ-ትውስታ ወደ ረጅም ጊዜ ማህደረ-ትውስታ ይሸጋገራል።
✅ የኢብኑ ተይሚያህ ድንቅ ጥቅስ: ታላቁ ሊቅ ኢብኑ ተይሚያህ ስለ ነፍስና አካል እረፍት ሲናገሩ፦
"ነፍስ እረፍት ስታገኝ ትበረታለች፤ ስትደክም ግን ትጠፋለች።"
አካላችሁንና አእምሯችሁን በቂ እረፍት በመስጠት አድሱት።
📝 ክፍል ➒፦ የፈተና ዕለት ተግባራዊ ስነ-ስርዓት (Exam Day Readiness)
♦️ ቁሳቁሶችን ማዘጋጀት፦ የእርሳስ፣ የላጲስ፣ የመቅረጫ እና የመግቢያ ካርዳችሁን (Admission Card) በዋዜማው ምሽት አዘጋጅታችሁ አስቀምጡ።
♦️ አመጋገብና ውሃ፦ በፈተናው ጥዋት ቀለል ያለ ቁርስ መመገብን አትርሱ። አእምሯችሁ ንቁ እንዲሆን በቂ ውሃ ጠጡ።
+1
🔠🔠🔠
🟰በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
(ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
📌በዚህ መሰረትም ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም እንዲሁም የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሰጥ ይሆናል፡፡
📌ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሰጠው በዚህ ከተማ አቀፍ ፈተና በ6ኛ ከፍል 84,882 ተማሪዎች 199 የመፈተኛ ጣቢያዎች እንዲሁም በ8ኛ ከፍል 86,808 ተማሪዎች 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናዉን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡
መልካም ፈተና✅
🔠🔠🔠🅰️
🔤🔤🔤🔤
🔠🔠🔠
🔤🔤🔤
ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇👇
❤️❤️❤️❤️❤️
https://t.me/dam76
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
