1 256
مشترکین
+224 ساعت
+297 روز
+9330 روز
آرشیو پست ها
ለ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
የፊታችን ሀሙስ (18/10/18) የ online የልምምድ ፈተና(Noc examination ) ስለሚሰጥ ከጠዋቱ 2:00 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች እነዲሁም ከሰዓት 7:00 ደግሞ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ እንድትገኙ ሲል ትምህርት ቤቱ በጥብቅ ያሳስባል ።
ማሳሰቢያ
ወላጆች እና ትምህርት ቤቱ በተስማሙበት የትራንስፖርት ክፍያ መሰረት ተማሪዎች የተወሰነውን 1800 ብር ከፈተና በፊት እንድትከፍሉ ትምህርት ቤቱ ያሳስባል ።
ስማችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው ተማሪዎች አጠቃላይ የ 2018 ዓ.ም ውጤት ስላልተሰራላችሁ በአፋጣኝ ለትምህርት ቤቱ ሪፖርት እንድታደርጉ ትምህርት ቤቱ በጥብቅ ያሳስባል ።
ት/ቤቱ
ለ11ኛ እና ለ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
ነገ ማክሰኞ (16/10/18) የሚሰጠውን ፈተና የትምህርት ቤቱን መደበኛ ክፍያ ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ፈተናውን እንደማይወስዱ ትምህርት ቤቱ በጥብቅ ያሳስባል ።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+1
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል።
(ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞ በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል።
ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
ለ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
እስካሁን ባለው ሁኔታ የ 2 ተማሪዎች አድሚሽን ካርድ ላይ ስህትተት ተፈጥሮ ተማሪዎቹ ለትምህርት ብቱ ሪፖርት በማድረግ ሊያስተካክሉ ችለዋል። ስለሆነም እስካሁን አድሚሽን ካርድ ያልወሰዳችሁ ተማሪዎች አድሚሽን ካርዱን ከትምህርት ቤቱ በፍጥነት በመውሰድ check እንድታደርጉ ትምህርት ቤቱ በጥብቅ ያሳስባል ።
ሆኖም ግን ይህ ሳይሆን ቀርቶ አድሚሽን ካርዱ ላይ ችግር ቢኖርበት ከፊታችን ሀሙስ (11/10/2018) በኋላ ትምህርት ቤቱ ለሚፈጠረው ችግር ኃላፊነት እንደማይውስድ ትምህርት ቤቱ በአክብሮት ያሳውቃል
Repost from YFS general secondary school
4th Q 2018 Final Exam Program.pdf1.02 MB
ቀን 9/10/2018 ዓ.ም
ለህምዳር የቤተሰብ ት/ቤት ወላጆች በሙሉ:-
ወርሃዊ ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ ወላጆች ክፍያውን ከማጠቃለያ ፈተና በፊት ማለትም እስከ 11/10/2018ዓ.ም ድረስ ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ እያሳሰብን: ለ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ክፍያ ያላጠነቀቃችሁ ወላጆች በ10/10/2018ዓ.ም በፈተና ላይ ለሚደርስ እንግልት የተማሪው ወላጅ ኃላፊነቱን የሚወስድ መሆኑን ከወዲሁ ለመግለፅ እንወዳለን።
ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ለሆናችሁ ተማሪዎች በሙሉ!
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በተከታዮቹ መስኮች ራሳችሁን የምታንጹበት ታላቅ የክረምት ስልጠና አዘጋጅቶላችኋል።
🤖በፈንዳሜንታል ኦፍ ኤ.አይ፣
💻 ፕሮግራሚንግ፣
🧠 ማሽን ለርኒንግ፣
⚙️ በሮቦቲክስ እና IOT፣
📊 ዳታ ሳይንስ እና በሌሎችም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ዘርፎች ራሳችሁን የምታንጹበት ታላቅ የክረምት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።
እስከ ሰኔ 30፤ 2018 ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ በተከታዩ የጉግል ፎርም https://forms.gle/uDGPmQsiZcWWeNuRA በመጠቀም ይመዝገቡ።
ለ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች በሙሉ
የተስተካከለው አዲሱ አድሚሽን ካርድ ስለመጣ ከነገ አርብ(5/10/2018) ጀምሮ እስከ ፊታችን ሰኞ (8/10/2018) የግንቦት የጥናት ክፍያ እንዲሁም የትምህርት ቤቱን መደበኛ ክፍያ በማጠናቀቅ እንድትወስዱ ሲል ትምህርት ቤቱ በጥብቅ ያሳስባል ።
በተጨማሪም የፊታችን ቅዳሜ (6/10/2018) ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ከ 12ኛ ክፍል ወላጆች ጋር ስብሰባ ስለሚኖረን ወላጆች በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ እንድትገኙልን በአክብሮት እናሳውቃለን ።
ማሳሰቢያ
1.አድሚሽን ካርዱ ላይ የፎቶ እና የስም ስህተት ሊኖሮ ስለሚችል ተማሪዎች አድሚሽን ካርዱን በተጠቀሱት ጊዜ ወስደው ስህተት አለመኖሩን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል ።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
