fa
Feedback
Seid Al-jeylani

Seid Al-jeylani

رفتن به کانال در Telegram

❤️‍🩹 وما من كاتـب إلا سـيفنى ويبقى الدهر ما كتبت يداه فلا تكتُـب بكفك غير شيء يسـرك في القيامة أن تراه ☘ . . For any comment 👇 📧 @Islamic_path_bot

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Seid Al-jeylani

کانال Seid Al-jeylani (@islamic_path1) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 10 127 مشترک است و جایگاه 8 937 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 3 275 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 10 127 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 13 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -330 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -10 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 1.57% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً N/A% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 159 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 0 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
❤️‍🩹 وما من كاتـب إلا سـيفنى ويبقى الدهر ما كتبت يداه فلا تكتُـب بكفك غير شيء يسـرك في القيامة أن تراه ☘ . . For any comment 👇 📧 @Islamic_path_bot

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 14 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

10 127
مشترکین
-1024 ساعت
-707 روز
-33030 روز
آرشیو پست ها
ምን ይሻላል?! -በምቾት ጊዜ አላህን እየረሳን፣ በችግር ስንፈተን ብቻ ወደ እርሱ እንሮጣለን። አምልኳችን የዘመቻ ሆኗል፤ ፆምም ሆነ የሌሊት ሶላት በጉጉት ጀምረን እናቋርጣለን። ውስጣችን ከውጫችን ተጋጭቷል፤ አፋችን ቢያምርም ምግባራችን የከፋ፣ እውቀት ቢኖረንም ተግባር የለሽ ሆነናል። ጉድለታችን በዝቶ የሰውን ነውር ከማውራት ባለፈ መልካሙን ማድነቅ ተስኖናል። ኢላሂ... ለዚህ ሁሉ መዋዠቅና ግራ መጋባት ብቸኛው መፍትሄ አንተው መሆንህን አውቄያለሁ። ጌታዬ ሆይ፤ ከውድቀቴ አንስተህ ቀጥ አድርገህ አቁመኝ፣ ቀሪ ዕድሜዬንም በተቅዋ አስውብልኝ። ፍሬ አልባ ዛፍና ዝናብ አልባ ደመና ከመሆን ጠብቀህ፣ ለራሴም ለሌላውም ብርሃን እንድሆን እርዳኝ። ያ ረቢ! ከእዝነትህ ፈፅሞ ተስፋ አልቆርጥም!

ትልቅ መስለን ለመታዬት ሌሎችን ለማሳነስ ስንሞክር እናንሳለን ! በየትኛዉም መስክ ራስህን እወቅ ፤ ራስህን ተቀበል ፤ ራስህን ሁን፤ ራስህን አሻሽል እንጅ ከፍ ብለህ ለመታየት ሰዎችን ያለአግባብ ማሳነስህ የአንተን ትንሽነት እንጅ ታላቅነትህን አያሳይም ወዳጄ !

የሰዎችን መሄድ አትፍሩ፤ መሸኘትን በፀጋ ተለማመዱት። ማንም ይምጣ፣ ማንም ይሂድ—ሰላማችሁ በማንም መኖርና አለመኖር ላይ እንዳይመሠረት አድርጉ። ሰው ብቻውን ወደዚህች ምድር መጣ። ብቻውንም ይህችን ም
የሰዎችን መሄድ አትፍሩ፤ መሸኘትን በፀጋ ተለማመዱት። ማንም ይምጣ፣ ማንም ይሂድ—ሰላማችሁ በማንም መኖርና አለመኖር ላይ እንዳይመሠረት አድርጉ። ሰው ብቻውን ወደዚህች ምድር መጣ። ብቻውንም ይህችን ምድር ይሰናበታል። ብቻውን ቢኖር ታዲያ ምኑ ይገርማል!

ጌታዬ ሆይ! ● የኔ ባልሆነ ነገር ላይ አታባክነኝ ● የኔ ያልሆነን ሰው ከጃይ አታድርገኝ ● አንተ በማትወደው ነገር ቀልቤ አይሰረቅ ኢላሂ!
ጌታዬ ሆይ! ● የኔ ባልሆነ ነገር ላይ አታባክነኝ ● የኔ ያልሆነን ሰው ከጃይ አታድርገኝ ● አንተ በማትወደው ነገር ቀልቤ አይሰረቅ ኢላሂ!

ኢላሂ! ከተውበተኞች አድርገህ ካኖርከኝ ይበቃኛል። ሙስሊም ሆኜ ከሞትኩም በታላቁ ችሮታህ ነው።ኢላሂ! ወዳንተ መልሰኝ።በመንገድህ ላይ አፅናኝ።

ሁሌም ካንተ ጋር ነኝ፣ ፈፅሞ አልለይህም ለሚሏችሁ ...ሁሌም ከኛ ጋር የሚሆነው አላህ ብቻ ነው በሏቸው። በዚህች አጭር የዱንያ ላይ ዕድሜያችን ከስንቱ ጋር ወዳጅነት ጀምረን፤ ስንትና ስንት ሰው ወደኋላ ጥለን እዚህ ደርሰናል።ሰው ይረሳል። ይረሳና ሁሉንም ነገር ይረሳል።

በዚህ ዘመን...ስሜትህን የሚረዳልህ፣ ብሶትህን የሚያዳምጥልህ፣ እንባህን የሚጠርግልህ፣ እጅህን ይዞ የሚያነሳ ወዳጅ ካገኘህ ብዙ ነገር አገኘህ፡፡
በዚህ ዘመን...ስሜትህን የሚረዳልህ፣ ብሶትህን የሚያዳምጥልህ፣ እንባህን የሚጠርግልህ፣ እጅህን ይዞ የሚያነሳ ወዳጅ ካገኘህ ብዙ ነገር አገኘህ፡፡

ኻሊድ ቢን በርመክ እንዲህ ይላል፦ ❝ዝሙት የክፋት ፀባዮችን በሙሉ አጠቃልሎ የያዘ ነው። አንድ ዝሙተኛ ዘንድ አላህን መፍራት፣ ቃል ኪዳን ማክበርም ሆነ ለጓደኛ ታማኝ መሆንን አታገኝም። — ከኢብኑል ጀውዚ «አኽባሩ-ኒሳእ» ኪታብ የተወሰደ

አላህዪ! ወዴት ልሂድ? የማንንስ በር ላንኳኳ? ከአንተ ውጪ ማን አለኝ? መጠጊያዬም፣ መሸሸጊያዬም አንተ ብቻ ነህ። የሁሉ ነገር ባለቤት ሆነህ ሳለ እንዴት ከበርህ እመለሳለሁ? የአዛኞች ሁሉ አዛኝ ሆነህ ሳለ እንዴት ተስፋ እቆርጣለሁ?

ከማህበራዊ ሚዲያ እብደትና ሱስ ስታገግም... በርካቶች ቀድመውህ የራቀ ጉዞ እንደተጓዙ ታያለህ። አንደኛው ቁርዓን ሲሃፍዝ፣ ሌላው መሠረታዊ የእስልምና እውቀቶችንና ልዩ ልዩ ጥበቦችን ሲቀስም አንተ ግን ስልክህ ላይ እንደተደፋህ ጊዜህ በከንቱ ያልፋል፤ ዕድሜህ ሲነጉድ እንኳ አይሰማህም። በአንተና በመቃብርህ መካከል ግን የቀረችው አንዲት እርምጃ ብቻ ልትሆን ትችላለች!

ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለሁት ብለህ አትዘናጋ፡፡ ከጀነት የበለጠ ጥሩ ቦታ የለም፡፡ አባታችን አደም በሷ ዉስጥ ሆነው ጭምር ፈተና አግኝቷቸዋል። በዒባዳህ ብዛትም አትጃጃል፣ ኢብሊስ ከዚያ ረጅም የዒባዳ ሕይወት በኋላ ምን እንዳጋጠመው ይታወቃል፡፡

ከአላህ በስተቀር ሁሉም ምትክ አለው! የሰው ልጅ ላጣቸው ነገሮች ሁሉ ይብዛም ይነስ ምትክ ( አማራጭ ) ሊያገኝ ይችላል፤ አላህን ያጣ ( ከርሱ የራቀ፣ እሱን ያስቆጣ ) ሰው ግን ምንም ዓይነት ምትክና አማራጭ መቼም ማግኘት አይችልም። ስለዚህ መቼም ቢሆን፣ ለማንም ለምንም ብለህ አላህን እንዳታጣ ተጠንቀቅ

በርካታ የዱንያን ፈተናዎች እና ደስ የማይሉ የሚረብሹ ስሜቶችን በየቀኑ እንታገላለን ። በዚህ ሁሉ መሀል ደህና መስለን ለመታየት የምናደርገው ጥረትም ሌላው ከባድ ትግል ነው።
በርካታ የዱንያን ፈተናዎች እና ደስ የማይሉ የሚረብሹ ስሜቶችን በየቀኑ እንታገላለን ። በዚህ ሁሉ መሀል ደህና መስለን ለመታየት የምናደርገው ጥረትም ሌላው ከባድ ትግል ነው።

ያ አላህ! የልቤን መረጋጋት አትቀማኝ፤ የተስፋዬን በር አትዝጋብኝ። ከጭንቀት ይልቅ ሰኪናህን፣ ከጥርጣሬ ይልቅ የቂን በልቤ ውስጥ ሙላልኝ። ከአንተ ውጭ ሌላ ደጋፊ የለኝምና ልቤን በአንተ ውሳኔ ወዳጅ አድርገው።

አንዳንዶቻችንም ምንም የማይጠቅም የእርዳታ ጩኸት ይጮኻሉ። አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿قال رَبِّ ارْجِعُونِ لَعَلِّي أَعْمَلُ صَالِحًا فِيمَا تَرَكْتُ ۚ كَلَّا ۚ إِنَّهَا كَلِمَةٌ هُوَ قَائِلُهَا ۖ وَمِنْ وَرَائِهِمْ بَرْزَخٌ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ﴾ እንዲሁም አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿وَأَنْفِقُوا مِنْ مَا رَزَقْنَاكُمْ مِنْ قَبْلِ أَنْ يَأْتِيَ أَحَدَكُمُ الْمَوْتُ فَيَقُولَ رَبِّ لَوْلَا أَخَّرْتَنِي إِلَىٰ أَجَلٍ قَرِيبٍ فَأَصَّدَّقَ وَأَكُونَ مِنَ الصَّالِحِينَ﴾ እንዲሁም አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿يَقُولُ يَا لَيْتَنِي قَدَّمْتُ لِحَيَاتِي﴾ ስለዚህ ገና ዕድሜ እያለን ሳለ፣ እንመከር፣ እንለወጥ።

ያለ ስራ ምኞት ቂልነት ነው ። قال يحيى بن معاذ -رحمه الله - : أعظمُ الاغترَار: التمادِي في الذنُوبِ معَ رجَاء العَفْو مِن غير ندامَة ، وتوقّع القُرب من الله بغير طاعَة ، وانتظَار زرْع الجنّة بِبَذر النار ، وطلَبُ دَار المطيعينَ بالمعاصِي ، وانتظار الجزاء بغير عمَل ، والتمنّي علَى الله مَعَ الإفرَاط. تزكية النفوس(١١٤). 🔷  የሕያ ኢብኑ ሙዓዝ የተባሉ ታላቅ ሊቅ እንዲህ ይላሉ :- " በጣም ትልቁ መታለል በወንጀል መዘውተር ነው ። ያለ ፀፀት የአላህን ምህረት , መከጀል ትእዛዙን ሳይፈፅሙ ወደ አላህ ለመቃረብ መጠበቅ , የእሳት ዘር እየዘሩ የጀነት ፍሬ መጠባበቅ , ወንጀል እየሰሩ የአላህን ታዛዦች ሀገር መፈለግ , ያለ ሥራ ምንዳ መፈለግ , ምንም ሣይሠሩ በአላህ ላይ ተስፋ ማድረግ " ናቸው ።

በቢሊዮን ከሚቆጠሩ የዓለም ሕዝቦች መሃል ሙስሊም ሆኖ መገኘትን የመሰለ ታላቅ ጸጋ ይዞ ማማረር እንዴት ይሆናል? ሙሊም ከመሆን በላይስ ምን ፀጋ አለ!? ኧረ አልሐምዱ ሊላህ እንበል!

በቢሊዮን ከሚቆጠሩ የዓለም ሕዝቦች መሃል ሙስሊም ሆኖ መገኘትን የመሰለ ታላቅ ጸጋ ይዞ ማማረር እንዴት ይሆናል? ሙሊም ከመሆን በላይስ ምን ፀጋ አለ!? ኧረ አልሐምዱ ሊላህ እንበል!

ወንጀል ከሰራህ በኋላ ምንም እንኳን ትንሽ ገንዘብ ቢሆን ሰደቃ ስጥ፤ ምክንያቱም ሰደቃ የኃጢአቱን መጥፎ ተጽእኖና መዘዝ በአላህ ፈቃድ ታስወግዳለች። — ሸይኽ ዐብዱስሰላም አሽ-ሹወይዒር
ወንጀል ከሰራህ በኋላ ምንም እንኳን ትንሽ ገንዘብ ቢሆን ሰደቃ ስጥ፤ ምክንያቱም ሰደቃ የኃጢአቱን መጥፎ ተጽእኖና መዘዝ በአላህ ፈቃድ ታስወግዳለች። — ሸይኽ ዐብዱስሰላም አሽ-ሹወይዒር

ኢላሂ...ፍጡራን ሁሉ ቢወዱኝም ሆነ ቢጠሉኝ ግድ የለኝም፤ የእኔ ትልቁ ጭንቀት በአንተ ዘንድ ያለኝ ስፍራ ብቻ ነው። ኢላሂ! ሰዎች ከሚያዩት ውጫዊ ማንነቴ ይልቅ በአንተና በእኔ መካከል ያለውን አሳምርልኝ!