ar
Feedback
Seid Al-jeylani

Seid Al-jeylani

الذهاب إلى القناة على Telegram

❤️‍🩹 وما من كاتـب إلا سـيفنى ويبقى الدهر ما كتبت يداه فلا تكتُـب بكفك غير شيء يسـرك في القيامة أن تراه ☘ . . For any comment 👇 📧 @Islamic_path_bot

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Seid Al-jeylani

تُعد قناة Seid Al-jeylani (@islamic_path1) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 10 951 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 375 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 3 039 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 10 951 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 04 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -370، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -23، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 1.40‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 0.41‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 153 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 45 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 1.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
❤️‍🩹 وما من كاتـب إلا سـيفنى ويبقى الدهر ما كتبت يداه فلا تكتُـب بكفك غير شيء يسـرك في القيامة أن تراه ☘ . . For any comment 👇 📧 @Islamic_path_bot

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 05 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

10 951
المشتركون
-2324 ساعات
-877 أيام
-37030 أيام
أرشيف المشاركات
የማይበጀኝን መንገድ ስመርጥ፣ እኔን ለማዳን ሲል እቅዴን የሚያበላሽብኝ እርሱ ምንኛ መሐሪ ጌታ ነው! አሁንም እዝነትህን የኔ ጌታ።
የማይበጀኝን መንገድ ስመርጥ፣ እኔን ለማዳን ሲል እቅዴን የሚያበላሽብኝ እርሱ ምንኛ መሐሪ ጌታ ነው! አሁንም እዝነትህን የኔ ጌታ።

ከሁሉም በፊት እራስህን አስተካክል!! ——— ኢብኑ ቁዳመህ አል-መቅዲሲይ (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- “እራስህን ከማስተካከልህ በፊት ሌሎችን በሚያስተካክል ነገር ከመወጠር busy ከመሆን ተጠንቀቅ!። ውስጥህን በማስተካከልና ከሚወገዙ ባህሪያት በማፅዳት ተወጠር!፣ እላይህን ከማስተካከልህ በፊት ለዱኒያ ከመጓጓት፣ ከምቀኝነት፣ ከይዩልኝ፣ በራስ ከመደነቅ ውስጥህን አፅዳ!።” [ሙኽተሶር ሚንሃጁ'ል ቃሲዲን ገፅ 20]

ነቢዩ ሙሳን عليہ السلام እና ተከታዮቻቸውን ከበዳዩ ፊርዐውን ግፍ ያዳነውና ባህሩን ያለመርከብ በሰላም ያሻገራቸው አላህ سبحانہ وتعالى ከሁሉም ዓይነት የዱኒያና የኣኺራህ ሃሳብ፣ ጭንቀትና ስጋት እራሳችን፣ ቤተሰብና ኡመታችንን በሙሉ ይገላግለን ሀገራችንም ሰላም ያድርግልን

🔷 ጓደኛህ ማን መሆን እንዳለበት ከወዲሁ እወቅ ኢማም ማሊክ - ረሂመሁሏህ - እንዲህ አሉ :- "ቃላቱ እውቀትን ከሚጨምርልህ ፣ ተግባሩ ወደ መጨረሻው አለም ከሚጠራህ ሰው ጋር መቀመጥ አለብህ። ቃላቱ ከሚያደናግርህ ፣ ሀይማኖቱ ጉድለት ካለበት እና ተግባሩ ወደዚህ አለም ከሚጠራህ ሰው ጋር ከመቀመጥ ተጠንቀቅ" ترتيب المدارك ١/٤٤٢

ኢላሂ... እኛ ሁላችንም ፈላጊዎችህ ነን። ሀብታሙም በውስጡ ድሃ ነው፤ ጤነኛውም በውስጡ ደካማ ነው። ያገኘውም ያጣውም፣ የተማረውም ያልተማረውም፣ ትልቁም ትንሹም... ሁላችንም በአንተ ፊት እኩል ድሆችና ያንተ እገዛ የሚያስፈልገን ፍጥረታትህ ነን። የውስጣችንን የማይነገረውን ምስጢር፣ ማንም የማያይልንን ስውር ስብራትና ጭንቀት የምታውቅ አንተ ብቻ ነህ። ኢላሂ... ◈​ያጣውና የቸገረው... ከአንተ ሰፊ ሲሳይ ስጠው። ◈​የታመመውና በአልጋ ላይ ያለው... በፈውስ እጅህ ዳስሰው። ◈​ልቡ የተሰበረውና የተገፋው... አንተ መጠጊያ ሁነው። ◈​መንገዱ የጠፋበትና የጨለመበት... ብርሃንህን አብራለት።

ያ ረብ! የኔ ባልኾነ ነገር ላይ ልቤን አታንጠልጥልብኝ፣ዓይኔም የኔ ያልኾነን አይከጅል፣በማላገኘው ነገር ላይ ሀሳቤ አይበታተን።

የእለተ ጁምዓ ሱንናዎችና ስርኣቶች ————— ① መታጠብና መቀባባት ከሰልማነል ፋሪሲይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል አለ:- “አንድ ሰው በእለተ ጁምዓ ታጥቦ፣ ከመፀዳዳትም የቻለውንም ተፀዳድቶ፣ ከሚቀባባ ነገርም ተቀባብቶ፣ ቤቱ ውስጥ ከሚገኝ ሽቶ ተቀብቶ፣ ከዚያም ከቤቱ ወጥቶ በሁለት ሰዎች መካከል ካልለያየ፣ ከዚያም የተፃፈለትን ከሰገደ፣ ከዚያም ኢማሙ በተናገረ ጊዜ ዝም ካለ፣ በዚያች ጁምዓ እና በቀጣዩዋ ጁምዓ መካከል ያለውን ወንጀል ይቅር ይባላል።” [ቡኻሪ 883 ላይ ዘግበውታል] ② ከሌላ ጊዜ የተሻለ ቆንጆ የሆነውን ልብስ መልበስ ከሙሀመድ ኢብን የህያ ኢብን ሂባን (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “አንዳችሁ ለእለተ ጁምዓ ከሌላ ጊዜ የተሻሉ ሁለት ልብሶችን ብይዝ የተሻለ ነው” [አቡዳውድ 1078 ላይ የተዘገበ ሲሆን አልባኒ ሶሂህ ብለውታል] ③ በጊዜ ወደ መስጂድ መግባት ከአቢሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “በእለተ ጁምዓ ለጀናባ የሚታጠብ አይነትን ትጥበት የታጠበ፣ ከዚያም (ወደ መስጂድ) የተጓዘ ሰው ልክ ግመል ለሶደቃ እንዳቀረበ ነው፣ በሁለተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ልክ ለሶደቃ ከብት (ላም) እንዳቀረበ ነው፣ በሶስተኛው ጊዜ የተጓዘ ሰው ልክ ቀንዳማ የሆነ ሙክት እንዳቀረበ ነው፣ በአራተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ለሶደቃ ዶሮ እንዳቀረበ ነው፣ በአምስተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ለሶደቃ እንቁላል እንዳቀረበ ነው፣ ኢማሙ  ሚንበር ላይ ከወጣ መላኢካዎች ኹጥባውን ለማዳመጥ ይሳተፋሉ።” [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል] ④ መስጂድ ከገቡ በኋላ በሁለት ሰዎች መካከል አለመለያየት (በሁለት ሰዎች ትከሻ ላይ አለመረማመድ) ጃቢር ኢብን ዐብደላህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ:- የአላህ መልእክተኛ ﷺ እየኾጠቡ እያለ አንድ ሰው ገባ፣ ሰዎች ላይ እየተረማመደ ነበርና የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ አሉት:- “ቁጭ በል! በእርግጥም አስቸግረሃል አርፍደሃልም።” [ኢብን ማጀህ 923 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ብለውታል] ⑤ ሱረቱል ከህፍን መቅራት (ማንበብ) ከአቢ ሰዒድ አል-ኹድሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “በእለተ ጁምዓ ሱረቱል ከህፍን ያነበበ ሰው በእርሱና በበይተል ዐቲቅ መካከል ብርሃን ይበራለታል።” [አልባኒ በሶሂሁል ጃሚዕ 6471 ላይ ሶሂህ ነው ብለውታል።] ⑥ ዱዓ ማብዛትና በእለተ ጁምዓ ዱዓ ተቀባይ የሚሆንባትን ሰኣት መጠባበቅ ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየላሁ ዐንሁ)  የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል አለ:- “የጁምዓ ቀን አስራ ሁለት ሰኣት ነው፣ ከእርሷ ውስጥ አንዲት ሰኣት አለች ሙስሊም የሆነ ባሪያ በዚያች ሰኣት አላህን ከጠየቀ አላህ የጠየቀውን ይሰጠዋል፣ (ያቺን ሰኣት) በመጨረሻ ሰኣት ከአስር በኋላ አካባቢ ፈልጓት።” [ሶሂሁል ጃሚዕ 8190 ላይ አልባኒ ሶሂህ ነው ብለውታል።] ከአነስ ኢብን ማሊክ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “የዱዓ ተቀባይነት የሚከጀልባትን ሰኣት ከአስር በኋላ ፀሀይ ወደ መግቢያዋ እስከምትቃረብ ድረስ ባለው ጊዜ ፈልጓት።” [ትርሚዚይ 1237 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ብለውታል።] ⑦ በነቢዩ ﷺ ላይ ሶለዋት ማብዛት ከሶፍዋን ኢብን ሱለይም (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “የጁምዓ ቀን እና የጁምዓ ሌሊት ከሆነ (ከገባ) በኔ ላይ ሶለዋት አብዙ።” [በሶሂሁል ጃሚዕ 776 ላይ አልባኒ ሶሂህ ብለውታል።] ማሳሰቢያ:- ይህ ተግባር የሚመለከተው ወንዶችን ነው። በተለይ ሽቶ ተቀብቶ መውጣት ለሴት ልጅ ሙሉ በሙሉ ሀራም ነው። ሴቶች ምንም አይነት ጌጣጌጥ ያለውን እና ወንዶችን ሊፈትን የሚችል ልብስም ሆነ ሽታ ያለው ቅባትና ሽቶ ሳይጠቀሙ ሙሉ በሙሉ የሴቶችን ሸሪዓዊ ስርኣት ያሟላ አለባበስ ለብሰው በአደብ ወደ መስጂድ መሄዱ አይከለከሉም።

🚫 በሶስት ነገር ጊዜ ከማባከን ተጠንቀቅ ! ➖ ባለፈ ነገር በመፀፀት አይመለስምና ! ➖ ራስህን ከሌላ ጋር በማወዳደር አይጠቅምህምና ! ➖ ሁሉንም ለማስደሰት በመሞከር አይቻለረምና !

ቁርዓን ቲላዋ #أحمد_بن_طالب ለምትወዱት ሰው ሼር አድርጉለት🙌 https://t.me/QuranForQalb https://t.me/QuranForQalb

የኢማን መዳከም ምልክቶች፦ * አዛን እየሰማህ ምላሽ አለመስጠትህ። * የፈጅር ሶላት አምልጦህ ግድ የለሽ መሆንህ። * ቁርኣንን ትተህ (ርቀህው) ሳለህ አለመፍራትህ። * መልካም ነገር ስትነፈግ ግድ የማይሰጥህ መሆንህ። * ከመልካም ጓደኞች ስትነጠል (ስትርቅ) እረፍት ማጣት አለመሰማትህ። * ወንጀልን ሰርተህ አለማዘንህ። * የዕለት ተዕለት የቁርኣን እና የአዝካር ዊርድ የሌለህ መሆንህ። ተጠንቀቅ! ሞት ቅርብ ነው፤ የሚመጣውም በድንገት (ሳይታሰብ) ነው።

“የምስጋና ዝቅተኛው ደረጃ አላህን በሰጠህ ፀጋዎች አለማመጽህ ነው፤ የአካል ክፍሎችህ (ህዋሳቶችህ) በሙሉ አላህ በአንተ ላይ የዋለልህ ፀጋዎች ናቸውና በእነሱ እርሱን አታምፅበት።” ​ ሰህል ቢን አብ
“የምስጋና ዝቅተኛው ደረጃ አላህን በሰጠህ ፀጋዎች አለማመጽህ ነው፤ የአካል ክፍሎችህ (ህዋሳቶችህ) በሙሉ አላህ በአንተ ላይ የዋለልህ ፀጋዎች ናቸውና በእነሱ እርሱን አታምፅበት።” ​ ሰህል ቢን አብደላህ (ረሒመሁላህ) ምንጭ፦«ሱነን አስ-ሷሊሒን ሊል-ባጂ» (394)

በምድር ላይ ሁሉንም ነገር አጥተህ አላህ ከአንተ ጋር ከሆነ ምንም አላጣህም። አላህን ካጣህ ግን ሁሉንም ነገር አጥተሃል። ስለዚህ አላህን አትጣ እንጂ ያጣኸውን ነገር ሁሉ በሌላ መልክ ታገኘዋለህ።
በምድር ላይ ሁሉንም ነገር አጥተህ አላህ ከአንተ ጋር ከሆነ ምንም አላጣህም። አላህን ካጣህ ግን ሁሉንም ነገር አጥተሃል። ስለዚህ አላህን አትጣ እንጂ ያጣኸውን ነገር ሁሉ በሌላ መልክ ታገኘዋለህ።

አንዳንዴ መጨከን ግድ ይላል ~ አንዳንድ ዉሳኔዎችን ለመወሰን ጨካኝ መሆን ግድ ይለናል፡፡ ዱንያ ላይ ስንኖር ተወዶ አይደለም እኮ የሚጨከነው፡፡ ካልጨከኑ የሚጠበቀው ፍሬ አይገኝም፤ ከሚታለመው ዉጤት አይደረስም፡፡ በድሎት ላይ ተሁኖ ከድሎት አይደረስምና መጨከን ግድ ይላል፡፡ ምቾት ላይ ተሁኖ ምቾት አይመጣምና መራራ ዉሳኔ መወሰን ያስፈልጋል፡፡ ኮረኮንች ላይ ሳይሄዱ ከአስፋልት መድረስ የለም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ራሣችንን ለመቻል ከሰው መነጠል፣ ዉጤታማ ለመሆን ከአገር መራቅ፣ የኢኮኖሚ አቅማችንን ለማሳደግ ያለ እረፍት መሥራት ግዴታ ይሆናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ዕውቀታችንን ለማሳደግ እንቅልፍ ማጣት፣ ተሻሽሎ ለመምጣት መሰደድ፣ ከድህነት ለመውጣት ብዙ መሥራት፣ ለመለወጥ መከራን መጋፈጥ፣ ለመጥገብ ሲሉ መርራብ፣ ከፍ ያለ ሰው ለመሆን መዋረድ ግድ ይላል፡፡ አንዳንዴማ እንደገና ለመታደስ መሰበር፣ የተሻለ ነገር ለማግኘት ከታች መነሳት፣ በዘላቂነት ለመዳን መርዝ መጠጣት፣ ቆሞ ለመሄድ ብዙ መታገስ፣ ነገን ለማየት ዛሬን መቸገር፣ በእጅ ያለን ነገር ዋጋ ለማወቅ ማጣት፣ ጠንክሮ ለመውጣት መውደቅ፣ ተነፋፍቆ ለመገናኘት መለያየት፣ ሁሉ ነገር እንደማይዘልቅ ለመረዳት መደሕየት እና ሌላም ሌላም ያስፈልጋል፡፡ ሕይወት እንዲህ ናት፡፡ መቸገር፣ መክሰር፣ መጎዳት፣ መቁሰል፣ የሕይወት አካል ነው፡፡ ይበርደኛል፣ ይርበኛል፣ ይጠማኛል፣ ይቸግረኛል፣ አልቋቋምም፣ አልችልም ... እያሉ ሁሌም እትት ብትት ማለት፤ ከምቾት ክልል ዉስጥ ላለመውጣት ሰበብ መደርደርዉድቀትን ያፋጥናል እንጂ ስኬትን አያመጣም፡፡ ትርፉም ራስን መጉዳት ነው የሚሆነው፡፡ አለመጀገን፣ አለመወሰን፣ መፍራት፣ መግደርደር፣_ መጠራጠር፣ አለመጀመር ዋጋ ያስከፍላል፡፡ ሰንደል ሲያቃጥሉት መልካም ሽቶ ወጣው፡፡ ብረት ሲያቀልጡት ጠነከረ፡፡ የረጋ ዉሃ ሳይሆን ትልቅ ማዕበል ነው ብርቱ ዋናተኛን የሚፈጥረው፡፡ ጀግና በጦርነት መሃል ነው የሚወለደው፡፡ መቃጠልን፣ መቅለጥን፣ መገፋትን አትፍራ፡፡ መከራን ያሳወቀ ጦርነት ጠቀመን፡፡ ችግርን ላስለመደን ስደት ምስጋና ይገባል፡፡ ፅናትን ከነርሱ ተማርን፡፡ ዱንያ የልፋት አገር ናት፡፡ በየቀኑ ከመኝታህ ስትነሳ መጀመርያ ላይ ማስታወስ ያለብህ ሙሉ ቀኑን ብቻ ሳይሆን ዕድሜ ልክህን ልፋት እንደሚጠብቅህ ነው፡፡ ~ ከ"ሰባሐል ኸይር " መፅሀፍ  ከገፅ 70 🙌

🌹እንኳን አደረሳችሁ🌹 تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال وعيد مبارك أعاده الله عليكم وأنتم في صحة وعافية وإيمان እንኳን ለ1447 ኛው የዒድ አል_አድሃ  በዓል በሰላም አደረሳችሁ !!! EID MUBAREK ኢድ ሙባረክ  🕊

«ቀልብ ዉስጥ አላህን ማውሳት ብቻ እንጂ ሌላ ምንም ነገር የማይሞላቸው ክፍተቶች አሉ። »ይላሉ ኢብኑል ቀይም―ሱብሓነላህ! አልሐምዱ ሊላህ! ላ ኢላሀ ኢልለላህ! አላሁ አክበር!―ማለትን አብዙ። ከሰብሒ
«ቀልብ ዉስጥ አላህን ማውሳት ብቻ እንጂ ሌላ ምንም ነገር የማይሞላቸው ክፍተቶች አሉ። »ይላሉ ኢብኑል ቀይም―ሱብሓነላህ! አልሐምዱ ሊላህ! ላ ኢላሀ ኢልለላህ! አላሁ አክበር!―ማለትን አብዙ። ከሰብሒ በፊት ጥቂት ቀደም ብሎ ያለው ጊዜ የኢስቲግፋር ነው። ረጋ፣ ሰከን ያለ ወቅት ነው። በሁለት ረከዓ ሶላትም ይሁን በሁለት ዘለላ እንባ ዱዓ ማድረግ መመረጥም መታደልም ነው።

ያለ ቁርአን ሕይወት ባዶ ናት። ወላሂ ባዶ።ተማሩት አጣጥሙት።
ያለ ቁርአን  ሕይወት ባዶ ናት። ወላሂ ባዶ።ተማሩት አጣጥሙት።

እኔ አልችልበትም...
ለጊዜያዊ ጥቅም ብዬ ቃላቶቼን በውሸት ማር ለውሼ ሰውን ማባበል፣ በሐሰት አሳምኖ ሰውን ከጎን ማቆየት፣ እውነትን ደብቆ ውሸትን ማንገስ፣የሌለ ማንነትን እንደ ጌጥ ተከናንቦ መታየት፣ አዎ እኔ አልችልበትም! ሰውን አታልዬ በዙሪያዬ ከማሰባሰብ፣ በእውነተኛነቴና በቅንነቴ አጥቼ ከራሴ ጋር በሰላም ብቻዬን ብቀር እመርጣለሁ፡፡

ራስህ ለራስህ የገባኸውን ቃል ስንቴ እንደካድከው ካስታወስክ ፤ የሰዎች ታማኝ ሆኖ አለመገኘት ብዙ አይገርምህም።

ምኞት አየለና ቀደሩን አስረሳን፣ ለጥቂት ቀን ፈተና ሰላምን አጣን። የነገው ሲጨንቀን የዛሬው ሲገፋን፣ የዓለሙ ጌታ መኖሩን ዘነጋን።

ለጊዜው ተሸሽጎ የቆየ ማንነት ፍጻሜው ሲቃረብ መጋለጡ አይቀሬ ነው፤ ጭንብል ተለብሶ ቢኖርም እውነተኛው ባሕሪ አንድ ቀን አፈትልኮ ይወጣል። ሰው በሕይወት ዘመኑ ሲያዘወትረው በነበረው ተግባር ላይ ሕይወቱ ያልፋል፤ በዚያው በለመደው ማንነቱም ለፍርድ ይቀርባል። ስለሆነም፣ የነገውን ውርደት ለማስቀረት ዛሬውኑ ራስን መመርመርና መጥፎ አመሎችን ማረም ብልህነት ነው።