ar
Feedback
Seid Al-jeylani

Seid Al-jeylani

الذهاب إلى القناة على Telegram

❤️‍🩹 وما من كاتـب إلا سـيفنى ويبقى الدهر ما كتبت يداه فلا تكتُـب بكفك غير شيء يسـرك في القيامة أن تراه ☘ . . For any comment 👇 📧 @Islamic_path_bot

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Seid Al-jeylani

تُعد قناة Seid Al-jeylani (@islamic_path1) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 10 647 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 564 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 3 099 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 10 647 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 28 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -382، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 1.80‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 0.39‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 192 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 42 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 2.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
❤️‍🩹 وما من كاتـب إلا سـيفنى ويبقى الدهر ما كتبت يداه فلا تكتُـب بكفك غير شيء يسـرك في القيامة أن تراه ☘ . . For any comment 👇 📧 @Islamic_path_bot

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 29 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

10 647
المشتركون
-824 ساعات
-977 أيام
-38230 أيام
أرشيف المشاركات
አላህዪ! ወዴት ልሂድ? የማንንስ በር ላንኳኳ? ከአንተ ውጪ ማን አለኝ? መጠጊያዬም፣ መሸሸጊያዬም አንተ ብቻ ነህ። የሁሉ ነገር ባለቤት ሆነህ ሳለ እንዴት ከበርህ እመለሳለሁ? የአዛኞች ሁሉ አዛኝ ሆነህ ሳለ እንዴት ተስፋ እቆርጣለሁ?

ከማህበራዊ ሚዲያ እብደትና ሱስ ስታገግም... በርካቶች ቀድመውህ የራቀ ጉዞ እንደተጓዙ ታያለህ። አንደኛው ቁርዓን ሲሃፍዝ፣ ሌላው መሠረታዊ የእስልምና እውቀቶችንና ልዩ ልዩ ጥበቦችን ሲቀስም አንተ ግን ስልክህ ላይ እንደተደፋህ ጊዜህ በከንቱ ያልፋል፤ ዕድሜህ ሲነጉድ እንኳ አይሰማህም። በአንተና በመቃብርህ መካከል ግን የቀረችው አንዲት እርምጃ ብቻ ልትሆን ትችላለች!

ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለሁት ብለህ አትዘናጋ፡፡ ከጀነት የበለጠ ጥሩ ቦታ የለም፡፡ አባታችን አደም በሷ ዉስጥ ሆነው ጭምር ፈተና አግኝቷቸዋል። በዒባዳህ ብዛትም አትጃጃል፣ ኢብሊስ ከዚያ ረጅም የዒባዳ ሕይወት በኋላ ምን እንዳጋጠመው ይታወቃል፡፡

ከአላህ በስተቀር ሁሉም ምትክ አለው! የሰው ልጅ ላጣቸው ነገሮች ሁሉ ይብዛም ይነስ ምትክ ( አማራጭ ) ሊያገኝ ይችላል፤ አላህን ያጣ ( ከርሱ የራቀ፣ እሱን ያስቆጣ ) ሰው ግን ምንም ዓይነት ምትክና አማራጭ መቼም ማግኘት አይችልም። ስለዚህ መቼም ቢሆን፣ ለማንም ለምንም ብለህ አላህን እንዳታጣ ተጠንቀቅ

በርካታ የዱንያን ፈተናዎች እና ደስ የማይሉ የሚረብሹ ስሜቶችን በየቀኑ እንታገላለን ። በዚህ ሁሉ መሀል ደህና መስለን ለመታየት የምናደርገው ጥረትም ሌላው ከባድ ትግል ነው።
በርካታ የዱንያን ፈተናዎች እና ደስ የማይሉ የሚረብሹ ስሜቶችን በየቀኑ እንታገላለን ። በዚህ ሁሉ መሀል ደህና መስለን ለመታየት የምናደርገው ጥረትም ሌላው ከባድ ትግል ነው።

ያ አላህ! የልቤን መረጋጋት አትቀማኝ፤ የተስፋዬን በር አትዝጋብኝ። ከጭንቀት ይልቅ ሰኪናህን፣ ከጥርጣሬ ይልቅ የቂን በልቤ ውስጥ ሙላልኝ። ከአንተ ውጭ ሌላ ደጋፊ የለኝምና ልቤን በአንተ ውሳኔ ወዳጅ አድርገው።

አንዳንዶቻችንም ምንም የማይጠቅም የእርዳታ ጩኸት ይጮኻሉ። አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿قال رَبِّ ارْجِعُونِ لَعَلِّي أَعْمَلُ صَالِحًا فِيمَا تَرَكْتُ ۚ كَلَّا ۚ إِنَّهَا كَلِمَةٌ هُوَ قَائِلُهَا ۖ وَمِنْ وَرَائِهِمْ بَرْزَخٌ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ﴾ እንዲሁም አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿وَأَنْفِقُوا مِنْ مَا رَزَقْنَاكُمْ مِنْ قَبْلِ أَنْ يَأْتِيَ أَحَدَكُمُ الْمَوْتُ فَيَقُولَ رَبِّ لَوْلَا أَخَّرْتَنِي إِلَىٰ أَجَلٍ قَرِيبٍ فَأَصَّدَّقَ وَأَكُونَ مِنَ الصَّالِحِينَ﴾ እንዲሁም አላህ እንዲህ ይላል፦ ﴿يَقُولُ يَا لَيْتَنِي قَدَّمْتُ لِحَيَاتِي﴾ ስለዚህ ገና ዕድሜ እያለን ሳለ፣ እንመከር፣ እንለወጥ።

ያለ ስራ ምኞት ቂልነት ነው ። قال يحيى بن معاذ -رحمه الله - : أعظمُ الاغترَار: التمادِي في الذنُوبِ معَ رجَاء العَفْو مِن غير ندامَة ، وتوقّع القُرب من الله بغير طاعَة ، وانتظَار زرْع الجنّة بِبَذر النار ، وطلَبُ دَار المطيعينَ بالمعاصِي ، وانتظار الجزاء بغير عمَل ، والتمنّي علَى الله مَعَ الإفرَاط. تزكية النفوس(١١٤). 🔷  የሕያ ኢብኑ ሙዓዝ የተባሉ ታላቅ ሊቅ እንዲህ ይላሉ :- " በጣም ትልቁ መታለል በወንጀል መዘውተር ነው ። ያለ ፀፀት የአላህን ምህረት , መከጀል ትእዛዙን ሳይፈፅሙ ወደ አላህ ለመቃረብ መጠበቅ , የእሳት ዘር እየዘሩ የጀነት ፍሬ መጠባበቅ , ወንጀል እየሰሩ የአላህን ታዛዦች ሀገር መፈለግ , ያለ ሥራ ምንዳ መፈለግ , ምንም ሣይሠሩ በአላህ ላይ ተስፋ ማድረግ " ናቸው ።

በቢሊዮን ከሚቆጠሩ የዓለም ሕዝቦች መሃል ሙስሊም ሆኖ መገኘትን የመሰለ ታላቅ ጸጋ ይዞ ማማረር እንዴት ይሆናል? ሙሊም ከመሆን በላይስ ምን ፀጋ አለ!? ኧረ አልሐምዱ ሊላህ እንበል!

በቢሊዮን ከሚቆጠሩ የዓለም ሕዝቦች መሃል ሙስሊም ሆኖ መገኘትን የመሰለ ታላቅ ጸጋ ይዞ ማማረር እንዴት ይሆናል? ሙሊም ከመሆን በላይስ ምን ፀጋ አለ!? ኧረ አልሐምዱ ሊላህ እንበል!

ወንጀል ከሰራህ በኋላ ምንም እንኳን ትንሽ ገንዘብ ቢሆን ሰደቃ ስጥ፤ ምክንያቱም ሰደቃ የኃጢአቱን መጥፎ ተጽእኖና መዘዝ በአላህ ፈቃድ ታስወግዳለች። — ሸይኽ ዐብዱስሰላም አሽ-ሹወይዒር
ወንጀል ከሰራህ በኋላ ምንም እንኳን ትንሽ ገንዘብ ቢሆን ሰደቃ ስጥ፤ ምክንያቱም ሰደቃ የኃጢአቱን መጥፎ ተጽእኖና መዘዝ በአላህ ፈቃድ ታስወግዳለች። — ሸይኽ ዐብዱስሰላም አሽ-ሹወይዒር

ኢላሂ...ፍጡራን ሁሉ ቢወዱኝም ሆነ ቢጠሉኝ ግድ የለኝም፤ የእኔ ትልቁ ጭንቀት በአንተ ዘንድ ያለኝ ስፍራ ብቻ ነው። ኢላሂ! ሰዎች ከሚያዩት ውጫዊ ማንነቴ ይልቅ በአንተና በእኔ መካከል ያለውን አሳምርልኝ!

ትልቁ ኪሳራ ማለት...ጀናዛው ላይ ሊሰገድበት ብቻ ተብሎ መስጊድ የገባ ሰው ነው። ልትቀበር ተብላ በከፈን ጊዜ ብቻ ሒጃቧን ፀጉሯን የሸፈነ ሴት ናት።ጌታዬ ሆይ በዲንህ ላይ አጽናን።መልካም መመለስን ወዳንተ መልሰን።

ኢማም ፉደይል ቢን ዒያድ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ "ሙእሚን ንግግሩ ጥቂት ነው፣ ሥራው ግን ብዙ ነው። ሙናፊቅ ደግሞ ንግግሩ ብዙ ነው፣ ሥራው ግን ጥቂት ነው።" እንዲሁም እርሳቸው (ረሒመሁላህ
ኢማም ፉደይል ቢን ዒያድ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ "ሙእሚን ንግግሩ ጥቂት ነው፣ ሥራው ግን ብዙ ነው። ሙናፊቅ ደግሞ ንግግሩ ብዙ ነው፣ ሥራው ግን ጥቂት ነው።" እንዲሁም እርሳቸው (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ "ከጁምዐ እስከ ጁምዐ ድረስ የተናገረውን ቃል በጥንቃቄ የሚቆጥር ሰው አውቃለሁ።"

ኢላሂ! ~ ባንተ ታውቀን ባንተ ከሚያምፁት አታድርገን፣ለሰው ጠቁመን ተቃራኒውን ከሚጓዙ አታድርገን፣ በአፍ ቀርበውህ በተግባር ከሚርቁህ አታድርገን፣ በምላስ ከሚያመልኩህ በልቦና ከሚሸሹህ አታድርገን፣አለባበሣችንን እንዳሳመርክ ዉስጣችንን አሳምርልን!

وَلَا تُخْزِنِي يَوْمَ يُبْعَثُونَ በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡ يَوْمَ لَا يَنفَعُ مَالٌ وَلَا بَنُونَ ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡ إِلَّا مَنْ أَتَى اللَّهَ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡» [سورة الشعراء]

ከማንም ምንም አለመጠበቅ ከአንገት እንጂ ከአንጀት የሚያወራ ቁምነገረኛ ሰው በጠፋበት በዚህ ዘመን፤ ካንተ ጋር ቃል ገብቶ ዘወር ብሎ ከሌላ ጋር የሚደራደር በሞላበት በዚህ መጣሁ ብሎ ቀረሁ እኮ ማለት እጅግ ተራ ነገር በሆነበት በዚህ ወቅት፤ ብቻ በአጠቃላይ መልካም እሴቶች እየተሸረሸሩ ባሉበት ዘመን ሕይወታችሁን ቀጥ አድርጋችሁ ለራሣችሁ ኑሩ እንጂ ወደ ሰዎች ብዙ አትመልከቱ፡፡ ማንንም አትጠብቁ፤ ከማንም አትጠብቁ። ብዙዎቻችን ወደኋላ ያስቀረን መጠበቅ ነው፡፡ መጠበቅ ያደኅያል፣ መጠበቅ ከሰው ያስከጅላል፣ መጠበቅ አላህን ያስረሳል፣ መጠበቅ ያሰንፋል፣ ልብን ያንጠለጥላል፣ ሞራልን ይሰብራል ... አንዳንድ ጊዜ መጠበቅ መልካም ቢሆንም ግና ፍፁም በሆነ መልኩ ሰው ላይ በመደገፍ መሆን የለበትም። ነብዩ ዩሱፍ ዐ.ሰ. ለአላህ አደራህን አምላኬ ማለት የነበረባቸዉን ነገርእረስተው ከእስር ለተፈታው ባልደረባቸው እንዳትረሳኝ አሉት፡፡ ግና እሱ ጉዳያቸዉን ረሳ፡፡ አላህ ግን አልረሣቸዉም። አባታችን ሊሞትልን ነው ብለው የአባታቸውን ሀብት ለመውረስ ሲጠብቁ ስንቶች ድሆች ሆነው ሞተዋል! ያገባኛል / ታገባኛለች ብለው ሲጠብቁ ስንቶች ተከዳን ብለው እሪ ብለዋል፡፡ በርግጠኝነት መጠበቅና _ በርሱ ላይ እራሣችንን ልንጥል የምንችለው አምላካችንን አላህን (ሱ.ወ.) ብቻ ነው፡፡ እሠጣለሁ ብሎ ቃሉን የማያጥፍ፣ እመጣለሁ ብሎ የማይቀር ከርሱ ወዲያ ማን አለ!!።

❝አላህን በማያስደስት መንገድ የተጀመረ መጀመሪያ፣ ፍጻሜው ባለቤቱን አያስደስተውም።❞
❝አላህን በማያስደስት መንገድ የተጀመረ መጀመሪያ፣ ፍጻሜው ባለቤቱን አያስደስተውም።❞

የማይበጀኝን መንገድ ስመርጥ፣ እኔን ለማዳን ሲል እቅዴን የሚያበላሽብኝ እርሱ ምንኛ መሐሪ ጌታ ነው! አሁንም እዝነትህን የኔ ጌታ።
የማይበጀኝን መንገድ ስመርጥ፣ እኔን ለማዳን ሲል እቅዴን የሚያበላሽብኝ እርሱ ምንኛ መሐሪ ጌታ ነው! አሁንም እዝነትህን የኔ ጌታ።

ከሁሉም በፊት እራስህን አስተካክል!! ——— ኢብኑ ቁዳመህ አል-መቅዲሲይ (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- “እራስህን ከማስተካከልህ በፊት ሌሎችን በሚያስተካክል ነገር ከመወጠር busy ከመሆን ተጠንቀቅ!። ውስጥህን በማስተካከልና ከሚወገዙ ባህሪያት በማፅዳት ተወጠር!፣ እላይህን ከማስተካከልህ በፊት ለዱኒያ ከመጓጓት፣ ከምቀኝነት፣ ከይዩልኝ፣ በራስ ከመደነቅ ውስጥህን አፅዳ!።” [ሙኽተሶር ሚንሃጁ'ል ቃሲዲን ገፅ 20]