Seid Al-jeylani
前往频道在 Telegram
❤️🩹 وما من كاتـب إلا سـيفنى ويبقى الدهر ما كتبت يداه فلا تكتُـب بكفك غير شيء يسـرك في القيامة أن تراه ☘ . . For any comment 👇 📧 @Islamic_path_bot
显示更多📈 Telegram 频道 Seid Al-jeylani 的分析概览
频道 Seid Al-jeylani (@islamic_path1) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 10 134 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 8 934,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 3 278 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 10 134 名订阅者。
根据 13 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -330,过去 24 小时变化为 -10,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 1.57%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 159 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“❤️🩹 وما من كاتـب إلا سـيفنى ويبقى الدهر ما كتبت يداه
فلا تكتُـب بكفك غير شيء يسـرك في القيامة أن تراه ☘
.
.
For any comment 👇
📧 @Islamic_path_bot”
凭借高频更新(最新数据采集于 14 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
10 134
订阅者
-1024 小时
-707 天
-33030 天
帖子存档
10 131
ትልቅ መስለን ለመታዬት ሌሎችን ለማሳነስ ስንሞክር እናንሳለን !
በየትኛዉም መስክ ራስህን እወቅ ፤ ራስህን ተቀበል ፤ ራስህን ሁን፤ ራስህን አሻሽል እንጅ ከፍ ብለህ ለመታየት ሰዎችን ያለአግባብ ማሳነስህ የአንተን ትንሽነት እንጅ ታላቅነትህን አያሳይም ወዳጄ !
10 131
የሰዎችን መሄድ አትፍሩ፤ መሸኘትን በፀጋ ተለማመዱት። ማንም ይምጣ፣ ማንም ይሂድ—ሰላማችሁ በማንም መኖርና አለመኖር ላይ እንዳይመሠረት አድርጉ።
ሰው ብቻውን ወደዚህች ምድር መጣ።
ብቻውንም ይህችን ምድር ይሰናበታል።
ብቻውን ቢኖር ታዲያ ምኑ ይገርማል!
10 131
ጌታዬ ሆይ!
● የኔ ባልሆነ ነገር ላይ አታባክነኝ
● የኔ ያልሆነን ሰው ከጃይ አታድርገኝ
● አንተ በማትወደው ነገር ቀልቤ አይሰረቅ
ኢላሂ!
10 131
ኢላሂ!
ከተውበተኞች አድርገህ ካኖርከኝ ይበቃኛል።
ሙስሊም ሆኜ ከሞትኩም በታላቁ ችሮታህ ነው።ኢላሂ! ወዳንተ መልሰኝ።በመንገድህ ላይ አፅናኝ።
10 131
ሁሌም ካንተ ጋር ነኝ፣ ፈፅሞ አልለይህም ለሚሏችሁ ...ሁሌም ከኛ ጋር የሚሆነው አላህ ብቻ ነው በሏቸው።
በዚህች አጭር የዱንያ ላይ ዕድሜያችን ከስንቱ ጋር ወዳጅነት ጀምረን፤ ስንትና ስንት ሰው ወደኋላ ጥለን እዚህ ደርሰናል።ሰው ይረሳል። ይረሳና ሁሉንም ነገር ይረሳል።
10 131
በዚህ ዘመን...ስሜትህን የሚረዳልህ፣ ብሶትህን የሚያዳምጥልህ፣ እንባህን የሚጠርግልህ፣ እጅህን ይዞ የሚያነሳ ወዳጅ ካገኘህ ብዙ ነገር አገኘህ፡፡
10 131
ኻሊድ ቢን በርመክ እንዲህ ይላል፦
❝ዝሙት የክፋት ፀባዮችን በሙሉ አጠቃልሎ የያዘ ነው። አንድ ዝሙተኛ ዘንድ አላህን መፍራት፣ ቃል ኪዳን ማክበርም ሆነ ለጓደኛ ታማኝ መሆንን አታገኝም።
— ከኢብኑል ጀውዚ «አኽባሩ-ኒሳእ» ኪታብ የተወሰደ
10 131
አላህዪ! ወዴት ልሂድ? የማንንስ በር ላንኳኳ? ከአንተ ውጪ ማን አለኝ? መጠጊያዬም፣ መሸሸጊያዬም አንተ ብቻ ነህ። የሁሉ ነገር ባለቤት ሆነህ ሳለ እንዴት ከበርህ እመለሳለሁ? የአዛኞች ሁሉ አዛኝ ሆነህ ሳለ እንዴት ተስፋ እቆርጣለሁ?
10 131
ከማህበራዊ ሚዲያ እብደትና ሱስ ስታገግም... በርካቶች ቀድመውህ የራቀ ጉዞ እንደተጓዙ ታያለህ።
አንደኛው ቁርዓን ሲሃፍዝ፣ ሌላው መሠረታዊ የእስልምና እውቀቶችንና ልዩ ልዩ ጥበቦችን ሲቀስም አንተ ግን ስልክህ ላይ እንደተደፋህ ጊዜህ በከንቱ ያልፋል፤ ዕድሜህ ሲነጉድ እንኳ አይሰማህም። በአንተና በመቃብርህ መካከል ግን የቀረችው አንዲት እርምጃ ብቻ ልትሆን ትችላለች!
10 131
ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለሁት ብለህ አትዘናጋ፡፡ ከጀነት የበለጠ ጥሩ ቦታ የለም፡፡ አባታችን አደም በሷ ዉስጥ ሆነው ጭምር ፈተና አግኝቷቸዋል።
በዒባዳህ ብዛትም አትጃጃል፣ ኢብሊስ ከዚያ ረጅም የዒባዳ ሕይወት በኋላ ምን እንዳጋጠመው ይታወቃል፡፡
10 131
ከአላህ በስተቀር ሁሉም ምትክ አለው!
የሰው ልጅ ላጣቸው ነገሮች ሁሉ ይብዛም ይነስ ምትክ ( አማራጭ ) ሊያገኝ ይችላል፤ አላህን ያጣ ( ከርሱ የራቀ፣ እሱን ያስቆጣ ) ሰው ግን ምንም ዓይነት ምትክና አማራጭ መቼም ማግኘት አይችልም።
ስለዚህ መቼም ቢሆን፣ ለማንም ለምንም ብለህ አላህን እንዳታጣ ተጠንቀቅ
10 131
በርካታ የዱንያን ፈተናዎች እና ደስ የማይሉ የሚረብሹ ስሜቶችን በየቀኑ እንታገላለን ። በዚህ ሁሉ መሀል ደህና መስለን ለመታየት የምናደርገው ጥረትም ሌላው ከባድ ትግል ነው።
10 131
ያ አላህ!
የልቤን መረጋጋት አትቀማኝ፤ የተስፋዬን በር አትዝጋብኝ። ከጭንቀት ይልቅ ሰኪናህን፣ ከጥርጣሬ ይልቅ የቂን በልቤ ውስጥ ሙላልኝ። ከአንተ ውጭ ሌላ ደጋፊ የለኝምና ልቤን በአንተ ውሳኔ ወዳጅ አድርገው።
10 131
አንዳንዶቻችንም ምንም የማይጠቅም የእርዳታ ጩኸት ይጮኻሉ።
አላህ እንዲህ ይላል፦
﴿قال رَبِّ ارْجِعُونِ لَعَلِّي أَعْمَلُ صَالِحًا فِيمَا تَرَكْتُ ۚ كَلَّا ۚ إِنَّهَا كَلِمَةٌ هُوَ قَائِلُهَا ۖ وَمِنْ وَرَائِهِمْ بَرْزَخٌ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ﴾
እንዲሁም አላህ እንዲህ ይላል፦
﴿وَأَنْفِقُوا مِنْ مَا رَزَقْنَاكُمْ مِنْ قَبْلِ أَنْ يَأْتِيَ أَحَدَكُمُ الْمَوْتُ فَيَقُولَ رَبِّ لَوْلَا أَخَّرْتَنِي إِلَىٰ أَجَلٍ قَرِيبٍ فَأَصَّدَّقَ وَأَكُونَ مِنَ الصَّالِحِينَ﴾
እንዲሁም አላህ እንዲህ ይላል፦
﴿يَقُولُ يَا لَيْتَنِي قَدَّمْتُ لِحَيَاتِي﴾
ስለዚህ ገና ዕድሜ እያለን ሳለ፣
እንመከር፣ እንለወጥ።
10 131
ያለ ስራ ምኞት ቂልነት ነው ።
قال يحيى بن معاذ -رحمه الله - :
أعظمُ الاغترَار: التمادِي في الذنُوبِ
معَ رجَاء العَفْو مِن غير ندامَة ،
وتوقّع القُرب من الله بغير طاعَة ،
وانتظَار زرْع الجنّة بِبَذر النار ،
وطلَبُ دَار المطيعينَ بالمعاصِي ،
وانتظار الجزاء بغير عمَل ،
والتمنّي علَى الله مَعَ الإفرَاط.
تزكية النفوس(١١٤).
🔷 የሕያ ኢብኑ ሙዓዝ የተባሉ ታላቅ ሊቅ እንዲህ ይላሉ :-
" በጣም ትልቁ መታለል በወንጀል መዘውተር ነው ። ያለ ፀፀት የአላህን ምህረት , መከጀል
ትእዛዙን ሳይፈፅሙ ወደ አላህ ለመቃረብ መጠበቅ , የእሳት ዘር እየዘሩ የጀነት ፍሬ መጠባበቅ , ወንጀል እየሰሩ የአላህን ታዛዦች ሀገር መፈለግ , ያለ ሥራ ምንዳ መፈለግ ,
ምንም ሣይሠሩ በአላህ ላይ ተስፋ ማድረግ " ናቸው ።
10 131
በቢሊዮን ከሚቆጠሩ የዓለም ሕዝቦች መሃል ሙስሊም ሆኖ መገኘትን የመሰለ ታላቅ ጸጋ ይዞ ማማረር እንዴት ይሆናል? ሙሊም ከመሆን በላይስ ምን ፀጋ አለ!?
ኧረ አልሐምዱ ሊላህ እንበል!
10 131
Repost from ስለ ቀልባችን
በቢሊዮን ከሚቆጠሩ የዓለም ሕዝቦች መሃል ሙስሊም ሆኖ መገኘትን የመሰለ ታላቅ ጸጋ ይዞ ማማረር እንዴት ይሆናል? ሙሊም ከመሆን በላይስ ምን ፀጋ አለ!?
ኧረ አልሐምዱ ሊላህ እንበል!
10 131
ወንጀል ከሰራህ በኋላ ምንም እንኳን ትንሽ ገንዘብ ቢሆን ሰደቃ ስጥ፤ ምክንያቱም ሰደቃ የኃጢአቱን መጥፎ ተጽእኖና መዘዝ በአላህ ፈቃድ ታስወግዳለች።
— ሸይኽ ዐብዱስሰላም አሽ-ሹወይዒር
10 131
ኢላሂ...ፍጡራን ሁሉ ቢወዱኝም ሆነ ቢጠሉኝ ግድ የለኝም፤ የእኔ ትልቁ ጭንቀት በአንተ ዘንድ ያለኝ ስፍራ ብቻ ነው። ኢላሂ! ሰዎች ከሚያዩት ውጫዊ ማንነቴ ይልቅ በአንተና በእኔ መካከል ያለውን አሳምርልኝ!
10 131
ትልቁ ኪሳራ ማለት...ጀናዛው ላይ ሊሰገድበት ብቻ ተብሎ መስጊድ የገባ ሰው ነው።
ልትቀበር ተብላ በከፈን ጊዜ ብቻ ሒጃቧን ፀጉሯን የሸፈነ ሴት ናት።ጌታዬ ሆይ በዲንህ ላይ አጽናን።መልካም መመለስን ወዳንተ መልሰን።
