Teddy Hawassa
رفتن به کانال در Telegram
7 949
مشترکین
+624 ساعت
+107 روز
-4730 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
اوت '26
اوت '26
+7
در 0 کانالها
ژوئیه '26
+93
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '26
+71
در 0 کانالها
Get PRO
مه '26
+135
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+211
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '26
+79
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '26
+282
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '26
+164
در 1 کانالها
Get PRO
دسامبر '25
+794
در 1 کانالها
Get PRO
نوامبر '25
+1 350
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '25
+1 232
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '25
+1 212
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '25
+106
در 1 کانالها
Get PRO
ژوئیه '25
+92
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '25
+74
در 0 کانالها
Get PRO
مه '25
+323
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '25
+80
در 1 کانالها
Get PRO
مارس '25
+257
در 2 کانالها
Get PRO
فوریه '25
+185
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '25
+475
در 1 کانالها
Get PRO
دسامبر '24
+193
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+214
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+298
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+487
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '24
+3 184
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 01 اوت | +7 |
پستهای کانال
(ቴዲ ሀዋሳ)
ወደ ስዊድን ያቀኑ 20 የእግርኳስ ቡድን አባላት መጥፋታቸው ተሰማ።
ወደ ስዊድን ያቀኑ ዕድሜያቸው ከ 14 እስከ 17 የሚገመት 20 ታዳጊ የእግርኳስ ተጫዋቾች ከ መሪያቸው ጋር መጥፋታቸውን ስዊድን ሄራልድ ዘግቧል።
"ጎቲያካፕ" ለተሰኘ የእግር ኳስ ውድድር ከኢትዮጵያ የሔዱት ታዳጊዎች ካረፉበት ትምሕርት ቤት ሳያሳውቁ በመውጣት መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።እግር ኳስ ተጫዋቾቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠው ፖሊስ፤ በራሳቸው ፍላጎት ጠፍተው ሊሆን እንደሚችል አመላክቷል።
በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ የሰጠው ፌደሬሽኑ የቡድኑ አባላት መጥፋት እንዳሳዘነው እና ታዳጊዎቹ በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ ማምራታቸውን አሳውቋል።
በመሆኑም ታዳጊዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን ብሏል ፌደሬሽንኑ።
ፖሊስ የጠፉት ታዳጊዎች ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ወጣቶች ሲሆኑ፣ ከእነሱ ጋር አንድ ወይም ከዚያ በላይ የቡድን መሪዎች አብረው ጠፍተዋል ብሏል። ይህ የታወቀው በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ሲሆን ያረፉበት ትምህርት ቤት አስተዳዳሪ አባላቱ ያለ ምንም ማስታወቂያ ለቀው መሄዳቸውን ካረጋገጠ በኋላ ለፖሊስ ማሳወቁም ተዘግቧል።
| 2 | (ቴዲ ሀዋሳ)
ብልፅግናን ከጣልን በኋላ ከፋኖ ጋር መዋጋታችን አይቀርም..ሞንጆሪኖ
የሕወሓት ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር (ሞንጆሪኖ) ከሰሞኑ በአንድ መድረክ ላይ አነጋጋሪ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሁን ከተጣመርናቸው ኃይሎች ጋር መዋጋታችን አይቀርም ብለዋል፡፡ የሀላፊዋ ንግግር የጽምዶ ኃይሎችን የትብብር መሰረት የሚያናጋ ነው ተብሏል፡፡
ወይዘሮ ፈትለወርቅ ቃል በቃል የተናገሩ፡-
‹‹ዋናው ነገር ብልፅግናን ለመጣል ፍላጎት ያሳይ እንጂ የትኛውም ስብስብ እርስ በራሱ እሳትና ጭድ ቢሆንም እንኳን አብረን እንሰራለን። ብልፅግናን ከጣልን በኃላ ደግሞ የአሸናፊዎች አሸናፊ ለመለየት ሌላ ዙር ፍልሚያ ይኖረናል። ለዚህም እየተዘጋጀን ነው፤ ይህ በተለያየ መልክ የተጀመረውን ትብብራችንን ስናየው የተለያየ ፍላጎት ያለን ሃይሎች ሆነን ነው ትብብር እየፈጠርን ያለነው። በአላማ፣ በፕሮግም፣ ወደፊት በረዥም ጊዜ እቅድ ምናምን አንድ ነን ማለት አይደለም። ትብብራችን በዛች በምታገናኘን ነገር ብቻ ነው። እኛ ከፋኖ የምንለይበት የፖለቲካ አቋም አለን። ከሻዕቢያ ይሁን ከሌሎች የተለያዩ ሃይሎች የምንለያይባቸው መዓት ጉዳዮች አሉ። አንድ የሚያደርገን ግን የብልፅግና ስርዓት የሁላችንም ስጋት ነው የሚለው ነው። ይቺ ብቻ ናት የምታገናኘን። እንደ ተሞክሮ ልንወስደው የሚገባን ነገር ደግሞ እንኳን አሁን በብዙ ጉዳዮች ልዩነት ካለንና በዓላማ ከማንገናኛቸው የተለያዩ ሃይሎች ጋር የምንፈጥረው ትብብር ይቅርና ኢህአዴግም እኮ ፈርሷል። ኢህአዴግ እኮ የኦሮሞ፣የአማራ፣የደቡብ ኢትዮጵያ ሃይሎች አራት ድርጅቶች አንድ ላይ ሆነን የፈጠርነውና በፕሮግራም ወይም አላማ አንድ የነበረ ድርጅት ነበር። ግንኙነታችንም ስትራቴጂካዊ ነበር[ታክቲካል አልነበረም] ፣ በተለያየ ቋንቋ የተፃፈች አንዲት ፕሮግራም ነበር የነበረችን። ግንባር ከመሆናችን ውጭ አንድ ድርጅት ማለት ነበርን፤ በዚህ ደረጃ የነበርን ሰዎች እኮ ተካክደናል[እንኳን ይሄ በዓላማ ከማይመስሉን ሃይሎች ጋር የምንፈጥረው ትብብር ይቅርና]›› ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር | 1 791 |
| 3 | (ቴዲ ሀዋሳ)
የቀድሞ የሲዳማ ክልል የፀጥታ አመራሮች በጽኑ እስራት ተቀጡ።
የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞው የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስን በ10 ዓመት ከ5 ወር ጽኑ እስራት እና በ4,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ዛሬ ውሳኔ አስተላልፏል።
በተመሳሳይ የቀድሞው የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስም በ1 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት እና በ1,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል።
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን የሰጠው በሲዳማ ክልል ፍትህ ቢሮ በቀረበባቸው ክሶች ላይ የቀረቡ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ከመረመረ በኋላ መሆኑን ገልጿል።
በፍርድ ቤቱ ውሳኔ መሠረት፣ ተከሳሾቹ ሥልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም "የሲዳማ ነፃነት ሠራዊት (ሲነሠ)" የተባለ ታጣቂ ቡድን በማደራጀትና ተደራራቢ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በመፈጸም ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተዋል። | 1 651 |
| 4 | ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ እንገናኛለን
መሳተፍ ለምትፈልጉ በሀሳብ መስጫ ላይ ስማችሁን አስቀምጡ | 1 893 |
| 5 | (ቴዲ ሀዋሳ)
የ4 ዓመት ህጻን ልጅ በማገት 5 ሚሊዮን ብር የጠየቁ ባልና ሚስት በጽኑ እስራት ተቀጡ።
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም(አዲስ ፖሊስ)፦ወንጀሉ የተፈፀመው ነሐሴ 12 ቀን 2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 3 ሰአት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ቀጠና አራት እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪ መታደል ታደሰ ነሀሴ 2 ቀን 2017 ዓ/ም በአራት ሺ ብር የወር ደመወዝ በቤት ሰራተኝነት በአቶ መልካሙ ረዳቴ እና በወ/ሮ ጥጋብ ጌታሁን መኖሪያ ቤት ትቀጠራለች።
ግለሰቧ በተቀጠረች በ10ኛ ቀን የቀጣሪዎቿን ወደ ስራ መሄድን እንደ አጋጣሚ በመጠቀም የ4 አመት እድሜ ያለውን ህፃን ዮሴፍ መልካሙን ችብስ ልግዛልህ በማለት ይዛው ትሰወራለች።
የህፃኑ ወላጆች ስራ ውለው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ልጃቸውን እና የቀጠሯትን የቤት ሰራተኛ ከቤት ያጧቸዋል።
የቤት ሰራተኛቸው የትዳር አጋር የሆነው ግለሰብ ወደህጻኑ ወላጅ አባት ስልክ በመደወል ልጅህን አግተንዋል 5 ሚሊየን ብር አምጣ ብሎ ስልኩን ይዘጋል ።
የልጃቸውን መታገት ተደውሎ የተነገራቸው ወላጅ አባት እና እናትም ለአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ያመለክታሉ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያም የምርመራ ክፍሉና የክትትል ኦፕሬሽን ቡድን በመቀናጀት ባከናወኑት ጠንካራ ክትትል የቤት ሠራተኛዋ መታደል ታደሰ ከትዳር አጋሯ መሠረት አየለ ጋር በመሆን ወደ ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሀን ከተማ ጫጫ ክፍለ ከተማ ህፃኑን እንደወሰዱት ይደርስበታል።
ከደብረ ብርሀን ከተማ ፖሊስ ጋር በመተባበርም ሁለቱንም ተጠርጣሪዎች ቤት ተከራይተው ልጁን ከአስቀመጡበት ነሀሴ 17 ቀን 2017 ዓ/ም በቁጥጥር ስር በማዋል ታግቶ የነበረው ህፃን ዮሴፍ መልካሙን ከነሙሉ ጤንነቱ ለወላጆቹ በማስረከብ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምርመራውን ይቀጥላል።
ፖሊስ የምርመራ መዝገብ በማደራጀትና በማጠናቀቅ ለሚመለከተው የፍትህ አካል በመላክ ክስ እንዲመሰረት አድርጓል።
ጉዳዮን የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሾቹ ጥፋተኛ ሆነው በማግኘቱ 1ኛ:- ተከሳሽ መታደል ታደሰ በ8አመት ከ4ወር 2ኛ :-ተከሳሽ መሰረት አየለ ደግሞ በ7አመት ከ9ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ መወሰኑን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።
ሰዎች ሰራተኛ ሲቀጥሩ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል። | 2 523 |
| 6 | (ቴዲ ሀዋሳ)
ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት የ2 ዓመት ህፃን እንዳትጮህ አፉን በማፈን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
በአሶሳ ዞን ባምባሲ ወረዳ ኤዳ ዳቡስ ቀበሌ ጎጥ አንድ በሚባል አካባቢ ነው የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ተከሳሽ አወድ አልሀሪብ የተባለ ሲሆን ግንቦት 16 ቀን 2018 ከረፍዱ 4፡00 ሰዓት የወንጀል ድርጊቱን ፈፅሟል።
የ2 አመት ህፃን የሆነችውን ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት እናቷ ውሃ ልትቀዳ መሄዷን በማረጋገጥ ወደ ራሱ መኖሪያ ቤት ከወሰዳት በኋላ አፏን በማፈን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈፀሙን ተናግረዋል፡፡
የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች በማስደገፍ ለዐቃቤ ህግ ያቀርባል ዐቃቤ ህጉም ተከሳሹ በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 627(1) ስር በተደነገገው የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ክስ በመመስረት ለባምባሲ ወረዳ ፍርድ ቤት ያቀርባል፡፡
ፍርድ ቤቱ የቀረበውን ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ተከሳሹን ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ የወንጀሉን ክብደትና የቅጣት ማክበጃ እና ማቅለያ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋለው ችሎት በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ሲሉ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል | 2 706 |
| 7 | በእዓለም ዋንጫ ታሪክ አንድም ኳስ ወደ ጎል ያልሞከረ አርጀንቲና ተብሎ በታሪክ ተመዝግቧል
ስፔን ሻምፒዮን ሆነች 🇪🇸 | 2 952 |
| 8 | ስፔንንንንንንንንንንንንንንን እነዚህን ጥቁር ጠሎች አስለቅሱልኝ 💪🏾💪🏾💪🏾💪🏾💪🏾💪🏾💪🏾💪🏾 | 2 605 |
| 9 | የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ እስኪ ግምታችሁን አስቀምጡ እኔ በግሌ በፊፋ ላይ እምነት የለኝም አርጀንቲና እንድታሸንፍ የተቻላቸውን ሁሉ ያደርጋሉ አረ እንደውም አርጀንቲና ዋንጫውን አንስታለች ብል ይቀለኛል ለማንኛውም እስኪ ግምታችሁን አስቀምጡ።
እኛን ገምቱ ይሉናል ጨዋታው ግን የታየ ነው😂
በትክክል ከነ ውጤቱ ለገመተ ቲክቶክ ላይ 20ሺ ኮይን እነሰጠዋለን ለአድማጭ ተመልካች እናስተዋውቀዋለን።
አርጀንቲና 🇦🇷
ስፔን 🇪🇸
አር | 2 644 |
| 10 | አሁንም ደግመን እናስጠነቅቃለን
በ ሳውዲ፣ኳታር፣ባህሬን፣ኩዌት፣ዱባይ፣ኤምሬትስ፣ ባጠቃላይ በገልፍ ሀገራት የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ከቻላችሁ ሀገሪቱን ለቃችሁ ውጡ። | 2 841 |
| 11 | (ቴዲ ሀዋሳ)
አሁን የደረሰን ሰበር ዜና።
በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ ካናዳን ወክሎ ድንቅ ብቃቱን በማሳየት የተጫወተው አሊ አህመድ በቀጣይ ሰኞ ወደ ቤተሰቦቹ ሀገር ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው።
በክለብ ደረጃ በእንግሊዝ ሻምፒዮን ሺፕ ለሚገኘው ኖርዊች ሲቲ የሚጫወተው አሊ በኢትዮጵያ ቆይታው ለታዳጊ ወጣቶች እና ለእግርኳስ አፍቃሪን ልምዱን እንደሚያካፍል የሚጠበቅ ሲሆን። በቀጣይ ኢትዮጵያ ውስጥ መስራት ስለሚፈልጋቸው ስራዎችም ከከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች ጋር ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል። | 3 124 |
| 12 | (ቴዲ ሀዋሳ)
"ኦሮሚያ ክልል "ጠፍቶ" ለማየት የሚመኙ አካላት አሉ"
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ባለውና ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ የመንግሥት አመራሮች በሚሳተፉበት መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ኦሮሚያ ክልል "ጠፍቶ" ለማየት የሚመኙና ኦሮሚያ የሚለውን ቃል መስማት የማይፈልጉ አካላት አሉ ሲሉ ገልጸዋል። ይህ ምኞት "በፍጹም" ሊሳካ እንደማይችል የገለጹት ርዕሰ መሥተዳድሩ፣ ይልቁንም ክልሉ ወደፊት ይበልጥ እየጠነከረ፣ መሬት እየያዘና ውጤታማ እየሆነ እንደሚሄድ በኦሮምኛ ቋንቋ ባደረጉት ንግግር አመልክተዋል፡፡
ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ኦሮሚያ ክልል ጠፍቶ ማየት ይፈልጋሉ ያሏቸውን አካላት ማንነት ግን በስም ለይተው በንግግራቸው ውስጥ አልጠቀሱም። አቶ ሽመልስ ይህን የተናገሩት፣ የክልሎች አወቃቀር ጉዳይ ለአገራዊ ምክክር ጉባኤው በአጀንዳነት በቀረበበት ማግስት ነው። | 2 603 |
| 13 | አርጀንቲና ከ ስፔን ለ ዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ይገናኛሉ
ጨዋታውን እንዴት አገኛችሁት? | 2 662 |
| 14 | (ቴዲ ሀዋሳ)
በሚኒሶታ የሚገኘው የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ የእሳት አደጋ ተጎዳ።
በአሜሪካ ሚኒሶታ ግዛት ሮዝማውንት (Rosemount) ከተማ የሚገኘው የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በድንገት በተከሰተ የእሳት አደጋ ክፉኛ ተጎድቷል።
አደጋው የደረሰው ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. (ጁላይ 13፣ 2026) የቅድስት አርሴማ ወርሃዊ በዓል የቅዳሴ ሥርዓት ከተጠናቀቀ በኋላ ሲሆን፣ እሳቱ በህንጻው ጣሪያና በውስጣዊ ክፍሎች ላይ በፍጥነት ተዛምቶ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
በርካታ የእሳት አደጋ መከላከያ ቡድኖች እሳቱን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ርብርብ ቢያደርጉም፣ በህንጻው ላይ የደረሰው ውድመት እጅግ ከባድ መሆኑ ተገልጿል። በአደጋው ወቅት በህንጻው ውስጥ ሰው ባለመኖሩ የሕይወት መጥፋትም ሆነ የአካል ጉዳት አልተመዘገበም።
በሚኒሶታና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በአደጋው ቦታ በመገኘት ለደብሩ ካህናት፣ ለሰበካ ጉባኤ አባላትና ለምዕመናን አባታዊ ማጽናኛ ሰጥተው፣ ቤተክርስቲያኑን በድጋሚ ለማቋቋም በአንድነት እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ ቤተክርስቲያን በቅርቡ ከ2.2 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ ተገዝቶ፣ ለምዕመናን አገልግሎት መስጠት የጀመረ በመሆኑ አደጋው የበለጠ አሳዛኝ መሆኑ ተጠቁሟል።
በበኩላቸው የአካባቢው ፖሊስና የእሳት አደጋ መርማሪዎች የአደጋውን መንስኤ ለማወቅ ምርመራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል። | 3 800 |
| 15 | (ቴዲ ሀዋሳ)
አቶ ተወልደ ገብረማርያም የፓኪስታን አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሸሙ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት አቶ ተወልደ ገብረማርያም፣ የፓኪስታን ብሔራዊ አየር መንገድን (PIA) ከገጠመው ከፍተኛ ኪሳራ አውጥተው ወደ ትርፋማነት እንዲመልሱ በዋና ሥራ አስፈጻሚነት መመረጣቸውን ብሉምበርግ እና አረብኒውስ ዘግበዋል።
ይህ ሹመት የተሰማው አየር መንገዱን ወደ ግል የማዛወሩ ሂደት የመጀመሪያ ምዕራፍ መጠናቀቁን ተከትሎ ሲሆን፣ "አሪፍ ሀቢብ ኮርፖሬሽን" የተባለው የግል ጥምረት የአየር መንገዱን የሥራ አመራር ቁጥጥር ተረክቧል።
አዲሶቹ ባለቤቶች የአየር መንገዱን የፋይናንስ አቅም ለማጠናከር፣ የበረራ አውሮፕላኖችን ለማዘመንና የበረራ መዳረሻዎችን ለማስፋፋት በመጀመሪያ ዙር 80 ቢሊዮን የፓኪስታን ሩፒ ( ወጪ አድርገዋል።
አቶ ተወልደ ገብረማርያም የኢትዮጵያ አየር መንገድን በአፍሪካ ግዙፍና ስኬታማ አየር መንገድ በማድረግ ረገድ የነበራቸው ዓለም አቀፍ ዝና እና ልምድ ለዚህ ሹመት እንዳበቃቸው ተገልጿል።
ባለሀብቶቹ በአጠቃላይ 180 ቢሊዮን ሩፒ ለኢንቨስትመንት ያቀዱ ሲሆን፣ የአቶ ተወልደ መመረጥ አየር መንገዱን በክልላዊና በዓለም አቀፍ የኢንዱስትሪ ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ ለተያዘው ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ወሳኝ መሆኑ ታምኖበታል።
በአሁኑ ወቅት የአቶ ተወልደ ሹመት በይፋ ከመታወጁ በፊት የተለመደው የመንግስት የጸጥታ ማጣሪያ እየተከናወነ መሆኑን የአየር መንገዱ የሥራ ኃላፊዎች ማረጋገጣቸውን ብሉምበርግ እና አረብ ኒውስ ዘግበዋል፡፡ | 2 711 |
| 16 | (ቴዲ ሀዋሳ)
አንጋፋዋ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች።
በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ በተለይም በዘመን አይሽሬ (Oldies) እና በባህላዊ ስራዎቿ የብዙዎችን ልብ የማረከችው አንጋፋዋ ድምፃዊትና የዜማ ደራሲ ራሔል ዮሐንስ** ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷ ተሰምቷል።
የጥበብ አሻራ እና መንፈሳዊ ህይወት
የማይረሱ ስራዎቿ፦
"አራዳ"፣ "ምኒልክ"፣ "ይዳኘኝ ሰው" እና በርካታ ስራዎቿን ለህዝብ ያበረከተች ድንቅ አርቲስት ነበረች።
የህይወት ምዕራፍ ለውጥ፦
በቅርብ ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ከዓለማዊ ሙዚቃ ርቃ፣ ህይወቷን ሙሉ በሙሉ ለመንፈሳዊ አገልግሎት (ለመዝሙር) ሰጥታ እንደነበር ይታወሳል።
የቤተሰብ ህይወት
ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ የሁለት ወንድና የአራት ሴት ልጆች እናት እንዲሁም የበርካታ የልጅ ልጆች አያት ነበረች።
ለቤተሰቦቿ፣ ለአድናቂዎቿና ለመላው የጥበብ አፍቃሪያን መጽናናትን እንመኛለን። ፈጣሪ ነፍሷን በገነት ያኑርልን። | 4 092 |
| 17 | ቤልጅየም 3
ሴነጋል 2
ሴኔጋል በአጭሩ ተዘረች ማለት ይቀላል።
እግሩን ተክሎ ለወደቀ ሁሉ ፔናሊቲ ይሰጣል ማለት ነው?
ማነው ለኳሱ ቅድሚያ የነበረው ሚባል ነገር አይታይም ቀረ ማለት ነው? | 4 180 |
| 18 | (ቴዲ ሀዋሳ)
በደቡብ አፍሪካ ራሱን ለመከላከል ጦር መሳሪያ ታጥቆ የታየዉ "ኢትዮጵያዊ ነዉ" የተባለ ግለሰብ መነጋገሪያ ሆኗል
በደቡብ አፍሪካ የሚኖር ኢትዮጵያዊ ነዉ የተባለ አንድ ግለሰብ ከባድ መሳሪያ ታጥቆ ራሱን ከሰሞነኛዉ የመጤ ጠል እንቅስቃሴ አራማጆች ለመከላከል ጥረት ማድረጉ ከተሰማ በኋላ ደቡብ አፍሪካዊያን "በሀገራችን ይህ እንዴት ይደረጋል?" ሲሉ ተቃዉሟቸዉን እያሰሙ ነዉ።
"Put South Africans first" ከተሰኘ የትዊተር/ኤክስ ገጽ ላይ ዳጉ ጆርናል እንደተመለከተው ከሆነ አንድ ማንነቱ ያልተጠቀሰ ኢትዮጵያዊ ነዉ የተባለ ግለሰብ ራሱን ከሰሞነኛዉ ነዉጥ ለመከላከል ከባድ የጦር መሳሪያ ይዞ ይታያል። ግለሰቡ ከያዘዉ ጠብመንጃ በተጨማሪ ሁለት ዉሾችንም በመኪናዉ ላይ ይዞ መንገድ ላይ ቆሞ ይታያል።
ደቡብ አፍሪካዊያን ይህ ምስዕል ከወጣ በኋላ ታድያ በአስተያየት መስጫዉ ላይ "ይህ የሽብርተኝነት ተግባር ነዉ " ፣ "ባለስልጣናልት ይህንን ግለሰብ ይዘዉ ሊጠይቁት ይገባል" እንዲሁም "ይህ ግለሰብ ከሀገራችን በአፋጣኝ ይዉጣ" ሲሉ መጠየቃቸዉን ታዝበናል።
በአንጻሩ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ዜጎች የኢትዮጵያዊዉን ተግባር አድንቀዋል። ግለሰቡ ንብረቱን እና ራሱን የመከላከል መብት እንዳለዉ ተከራክረዋል።
የዚህ እንቅስቃሴ መሪዎች ንቅናቄዉ "ሰላማዊ ነዉ" ቢሉም በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ዜጎች የተያዙ በርካታ ንብረቶች ወድመዋል ፤ ሁለት ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ የሌሎች ሀገራት ዜጎች ስደተኞች ህይወትም ጠፍቷል። አዝማሚያው አስፈርቷቸዉም በርካቶች ሀገሪቱን ለቅቀዉ ወጥተዋል።
ዳጉ_ጆርናልአ | 3 561 |
| 19 | ካናዳ 1
ደቡብ አፍሪካ 0
ደቡብ አፍሪካውያን በቶሎ ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ሰኔ 30 ለሚደረገው አፍሪካውያን ጠል ሠልፍ ላይ መሳተፍ አለባቸው። | 3 039 |
| 20 | የኢራን እና የአሜሪካ ጦርነት ዳግም በአስከፊ ሁኔታ ሊቀጥል ነው። ስምምነታቸው ሙሉ ለሙሉ ከሽፏል። የአሜሪካንን ጥቃት ተከትሎ ኢራን በገልፍ ሀገራት የሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ቤዞች ላይ ጥቃት ፈፅማለች
ሳውዲ አረቢያ
ኩዌት
ባህሬን
ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ
ኳታር
ዱባይ ምትገኙ
ኢትዮጵያውያኖች ብትችሉ ለቃችሁ ውጡ ካልቻላችሁ ወደ ህዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎች አትሂዱ | 3 633 |
