4 996
مشترکین
+1024 ساعت
+377 روز
+24030 روز
آرشیو پست ها
4 995
አባት ለልጁ ሲመክር
...
ልጄ ሆይ ነገ በሕይወትኽ ለምታጣቸው የትኞቹም ዕድሎች ኀላፊነቱን የምትወስደው አንተና አንተ ብቻ ነኽ።
በየትኛውም የዕድሜኽ እረከኖች ውስጥ የሳትኸውን የስኬት ግብ ማንም ሊያሳካልኽ እንደማይችል እየተነፈስኽ ከመኾንኽ በላይ ዕርግጠኛ ኹን።
በዛ ፈንታ ግን ክሽፈትኽን ሌላው ሰው እንደ ራሱ ስኬት ቆጥሮ ሊዘባበትብኽና ሐሴት ሊያደርግብኽ እንደሚችል እመን።
ለራስኽ ኹሌም ክብር ይኑርኽ! ምክንያቱም ሰዎች አንተ ለራስኽ የሰጠኸውን ቦታ ይሰጡኻል እንጂ አዲስ ስብዕና አላብሰው ዙፋን ላይ አይሰቅሉኽም።
በየትኛውም አጋጣሚ ክብረኽን ዝቅ የሚያደርጉ አካላት እንዳሉ ከተረዳኽ የክብርኽን ጽዋ ከፍ አድርግ። እነርሱን ደግሞ በዝቅታ ዕያየኽ ዝለላቸው።
ብላቴናው! ማወቅ ያለብኽ ነገር በጣም ግልጽና እንክብካቤኽም ገደብ የለሽ ከኾነ ሰዎች እንደ ጧፍ አንጠፍጥፈው ጨለማቸውን ያበሩኻል።
ተንጠፍጥፈኽ ያበቃኽ ጊዜ ዕዳ ስለምትኾንባቸው በየትኛውም መስመር ሊያገኙኽ አይወዱም።
ዕውነት ነው ሕይወት ማካፈል ናት፤ ግን ስታካፍል ለነማንና ለምን የሚለውን አስብ።
እንደ ልብ ስላገኙኽ የኾነ ጊዜ በመኖርኽም ባለመኖርኽም መካከል በነርሱ ዘንድ ለውጥ ከሌለ አንተ በትክክል ረክሰኽ እንደቀረብካቸው እመን።
ስለዚህ ከነዚህ አካላት ራስኽን አሽሸኽ ለራስኽ ቦታ መስጠትን ተማር።
ብላቴናው! ወደ ዱንያ ብቻኽን መጥተኻል።
ዱንያ ላይም ብቻኽን እንደምትጓዝ፣ብቻኽንም ከአፈር እንደምትገባ አምነኽ ተቀበል።
ስለዚህ ከወዲኹ በራስኽ ቆመኽ በራስኽ ለመራመድ በርታ።
መድረስ ያለብኽን የመጨረሻውን ነጥብ አኹኑኑ ከፊትለፊትኽ አስቀምጠኽ ብቻኽን እንደኾነክ ሙሉ በሙሉ ዕርግጠኛ ኾነኽ ጉዞኽን ጀምር።
መልካም ጉዞ!!!
https://t.me/E_M_ahmoud
4 995
4 995
ዕውነተኛነት
...
አንድ ሰው በምንም መልኩ ሆሳእ ስብዕና ቢኖረው ዕውነተኛ ከኾነና ውሸትን የሚጠነቀቅ ከኾነ ክፉ ባሕሪዎቹን በሙሉ ዕውነኛነቱ ይሸፍንለታል።
በተቃራኒው ደግሞ አንድ ሰው ምንም ዓይነት ከሩቅ የሚጣራ ስብዕና አለው ቢባል ውሸትን ግን በጉያው ይዞ የሚንቀሳቀስ ከኾነ፣ያ "አቤት እሱ...!" የተባለለት ማንነቱ በኔጌቲቭ የሚባዛ ይኾናል።
ወዳጄ ከሰዎች መካከል ከሩቅ ዐይተን በመልዐክ ምስልና በነብያት ስብዕና ልክ የምንሰፍራቸው ብዙ ይኖራሉ።
ግን ደግሞ እነዚያ ሰዎች ኾን ብለው በሰዎች ላይ ለሚተላለፏቸው ስሕተቶች ውሸተን መደበቂያ ማድረጋቸው በጊዜ ሒደት ከሰዎች ዘንድ ያገኙትን ቦታ ኹሉ እንዲያጡ ያደርጋቸዋል።
በውሸት የሚገነባ ማንነት በሙሉ ሳይታለብ ታስሮ የከረመ የላም ግት ብጤ ነው።
ከሩቅ ስታየው ግቱ በወተት የተሞላ ይመስላል። ፈተሕ ስታልበው ግን ከእንጥፍጣፊ ውጪ የሌለው የሕጻን ርሓብን እንኳ የማያስታገስ ቁርበት ብቻ ይኾናል።
ስንቶች በተለሳለሰ አንደበት ጉምቱና አንቱ የሚባሉትን ቀርበው ቆንጥር በኾነው ውሸታም ስብዕናቸው በሰዎች መካከል እየተመላለሱ የተገለሉና ገዳም የገቡ አሉ!!!
ስንቶችስ በውሸት የገነቡት ቤት በዕውነት ነፋስ ፈርሷል!
ወዳጄ ወሽካታና ውሽታምነትን ኢስላም በብርቱ የሚዋጋው እንደኾነ ለመረዳት መልዕክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ገና ነብይነትን ሳይቀቡ ሙሐመዱል አሚን ይባሉ እንደነበረ ማወቅ በቂ ነው።
አላህ (ሱብሓነሁ ወተዓላ) መልዕክተኛውን ከሐሺም ቤተሰቦች መካከል ከመረጠበት መስፈርት መካከል አንዱ ዕውነተኛነታቸው ነው።
መልዕክተኛው ነብይነትንም ከተቀቡ በኋላ ዕውነተኛነት ላይ አበክረው ሲናገሩ፦
"ዕነተኛነት ላይ በርቱ፤ ዕውነተኛነት ወደ መልካም ስራ ይመራል።መልካም ስራ ደግሞ ወደ ጀነት ይመራል። አንድ ሰው ዕነተኛ ከመኾን አይወገድም፣ ዕውነትንም አያዝወትርም/አይጠብቅም አላህ ዘንድ ዕውነተኛ ተብሎ እስኪጻፍ ድረስ" ብለዋል።
ይሕ የመልዕክተኛው ቃል አላህ "እናንተ ያመናችኹ ሰዎች ሆይ አላህን ፍሩ ከዕውነተኞችም ኹኑ" ብሎ ከተናገረው ጋር ይስማማል።
ዕውነተኛነት አላህን ከመፍራት ጋር በቀጥታ እንደሚያያዝ ልብ ይሏል!!!
ታዲያ ወዳጄ አኹን ላይ ወጣቱ ጎልማሳውም ከዛም ከፍ ያለው
ከሰዎች ፊት ምክንያታዊ ለመምሰል ውሸትን መከለያ ማድረጉ እጅግ እየበዛ ነው።
ትልቁ የረሳነው ነገር ሰዎችን በውሸት ያተለልን ይመስለን ይኾናል ግን አላህን ማታለል አይቻልም፦
"ከሰዎች ይሸሸጋሉ አላህ ግን ከእነርሱ ጋር ኾኖ ሳለ የማያወደውን ንግግር ሲያሳድሩ ከርሱ አይደበቁም"
ይሕ ማለት ሰዎችን አመክንዮአዊ ኾኖ በተሽሞነሞኑ ወይም አሳዛኝ በኾኑ ቃላት ማታለል ይቻል ይኾናል።
በዕውቀቱ ከእኛ ዘንድ ያለውን አላህን ግን ማታለል አይቻልም።
ሰውንም ቢኾን አንዴ ማታለል ይቻል ይኾናል፤ለመደጋገም መሞከር ግን ግለሰቡን መናቅና ጅልነትም ጭምር ነው።
...
ይታሰብበት ጓዶቼ!!!
https://t.me/E_M_ahmoud
4 995
ይሄ video 3 ሰአት አልፎታል እስካሁን ግን እንደሚፈለገው ሰው ጋር አልደረሰም። ስነ-መለኮትን እንዲህ ረጋ ብለን አጢነን መማር ካልጀመርን እጅግ ጥቃቅን ሹቡሀዎች ያወዛውዙናል፥ዛሬ ኡስታዝ ይህንን video የለቀቀው በዚህ ጥናት ዘርፍ ቡዙዎች ባለመማራቸው ምክንያት ሹቡሀ ውስጥ ስለሚሆኑ ነው ዛሬስ አንማርም? በሉ ገብታቹህ video እስከመጨረሻ እዩ ኮመንት ፃፉ ሪፖስት አድርጉ(ዳዕዋው ተደራሽ እንዲሆን ብቻ)።
የvideo ሊንክ:- https://vt.tiktok.com/ZSxEG5SGS/
4 995
ስሕተትን ስናርም
..
ከሰሞኑን አንድ በፍልስፍና ውስጥ የተዘፈቀ ወንድም የኾነ ሚዲያ ላይ ቀርቦ የተናገረውን ነገር ብዙዎቻችን እንዳየን አምናለኹ፡፡ የልጁን ንግግር ተከትሎ በቁጥር ቀላል የማይባሉ ሰዎች ልጁን ከኢስላም አጠድ ውጪ ሲያስወጡት፣ገሚሱ ደግሞ አፈንጋጭ (ሙልሒድ) ነው ሲሉትም ዐይተናል፡፡
ግለሰቡ የተሳሳተውን ነገር ማረምና ማስተካከያ መስጠት ግዴታ ነው፡፡ እንዴት ነው የምናርመው?የሚለው ጥያቄው ግን በሰከነ መንፈስ ሊታይ ይገባዋል፡፡
በተለይ ደግሞ ገፊ ስሜቱን መቆጣጠር የማይችል ሰው፣በሰዎች ላይ መልስ ለመስጠት ባይንደረደር መልካም ነው፡፡ ምክንያቱም መሰል ሰዎች መልስ እንሰጣለን ብለው ሲነሱ ከመልሱ ይልቅ የግል ጥላቻና አቋማቸውን ጮክ አድርገው ስለሚናገሩ የሚያዳምጣቸው ሰው ከንግግራቸው መካከል ተሳሳተ የተባለው ግለሰብ ስሕተቱ ምኑ ጋር እንደኾነ በቅጡ መረዳት ይሳነዋል፡፡
በሌሎች ላይ መልስ ለመስጠት የሚነሳ ማንኛውም ሰው በመጀመሪያ በኢስላማዊ አደብ ሊጸበየት ይገባል፡፡ አንዳንዴ መልስ ከመስጠት ይልቅ ግለሰቡን ማነጋገር ሊሻል ይችላል፡፡
አንዳንዴ ደግሞ መልስ መስጠቱ በራሱ ጉዳዩን የበለጠ ማስተዋወቅ ይኾናል፡፡ ለዚህም ምርጥ ማሳያችን የሰልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (The satanic verses) መጽሐፍ ነው፡፡
ሰልማን ሩሽዲ በሳላፍነው መጽሀፍ ያልሰደበው፣ያላዋረደው ማሕበረሰብ አለ ማለት ይከብዳል፡፡ ከዚህም መሐል ቁርኣንን ጨምሮ ኢስላምን አብጠልጥሏል፡፡
ይሕን ተከትሎ በወቅቁ የኢራን መሪ የነበረው አያቱላህ ኹመይኒ ሰልማን ሩሽዲን የገደለ ኢራን ወሮታውን እንደምትከፈል ተናገረ፡፡ ይሕ ንግግሩ ብቻ የሰላምን ሩሽዲ መጽሐፍ በዓለም ላይ እንዲተዋወቀቅ አደረገው፡፡
ወዳጄ በየጊዜው በኢስላም ላይ የሚጻፉ በርካታ አጓጉል መጽሐፎች እንዳሉ ልብ ይሏል፡፡ሩቅ ሳንሄድ የሐገራችን የኦርቶ ቤተክርስቲያን ታቅፋ የምትሞቃቸው ጥቂት የማይባሉ ኢስላምንና መልዕክተኛውን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የሚያነውሩ መጽሐፍት አሉ፡፡ ከነዚህ መጽሐፍት አኳያ የሰልማን ሩሽዲ መጽሐፍ ምንም ላይኾን ይችላል፡፡ ኾኖም ግን የኹመይኒ ንግግር በዓለም ላይ እንዲገን አድርጎታል፡፡
ብዙም ሳይቆይ ሼኽ አሕመድ ዲዳት ( ረሒመሁ ላህ) ``Can you stomach the best of Rushdi`` በሚል ርዕስ ድንቅ መጽሐፍ ጽፎ ለሰልማን ጥገኝነት የሰጠችው እንግሊዝ ጭምር በስራዋ እንድታፍር አድርጓል፡፡
ምን መሰሎት ወዳጄ? ሰልማን በመጽሀፉ እንግሊዞች ከእህታቸው ጋር ይዘሙታሉ ብሎ ተናሯል፡፡ የራሱ የሰልማን ሚስት ደግሞ በጊዜው አንግሊዛዊት ነበረች፡፡ ዲዳት ሲጠይቅ “ሰልማን እንግሊዞች ይሕንን ነውር እንደሚፈጽሙ ከየት አወቀ?ø ይልና…ራሱ ሲመልስ “ያው ሚስቱ ነግራው ነው ማለት ነው” ካለ በኋላ፣ “ሚስቱም ብትኾን የዚህ ነውር ተጋሪ ናት ማለት ነው” በማለት ሰልማንን በራሱ ጥይት ገድሎታል፡፡
ወደ ኋላ ተንደርድረን ሌላ ምሳሌ ብንወስድ፣የኢማሙ አቢ ሓኒፋ መዝሃብ ላይ ኢማሙ አልቡኻሪ በተለያዩ መጽሐፎቹ ውስጥ መልስ ሰጥቷል፡፡ ኾኖም ግን ቡኻሪ መልሱን ሲሰጥ በፍጹም አክብሪትና አደብ ውስጥ ኾኖ ነበር፡፡ ለዚህም ማሳያው አልቡኻሪ የአቡ ሓኒፋን ስም በፍጹም ሳይጠቅስ “አንዳንድ ሰዎች እንዲሕ ይላሉ” ብቻ በማለት ስሕተቱ ላይ አተኩሮ መናገሩ ነው፡፡
በትክክል የአቡ ሓኒፋን መዝሃብ አስቀድሞ ያላወቀ ወይም ቡኻሪ በማን ላይ መልስ እንደሰጠ የከሌሎች ዑለማእ ካልሰማ፣ ቡኻሪ እናምንን አስቦ እንደሚናገር ማወቅ አይችልም፡፡
ይሕንን ለማየት የፈለገ በራሱ በቡኻሪ የሐዲስ መጽሐፍ ውስጥ “ኪታቡል ሒል” በሚል ርዕስ የሰጠውን ክፍል ማንበብ ይችላል፡፡ ኢማሙ አልቡኻሪ በአቡ ሓኒፋ መዝሐብ ላይ መልስ እንደሰጠ ራሱ ኢብኑ ሐጀር “ፈትሑል ባሪ” ላይ ይናገራል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ሐነፊይ የነበረው ኢማሙል ዓይኒይ “ዑመዱል ቃሪእ” ላይ ተናግሯል፡፡
ኢማሙል ቡኻሪ ከሐዲስ መድብሉ ባሻገር “አልቂራኣት ኸልፈል ኢማም” በሚል መጽሐፉ፣”ረፍዑል የደይን ፊ አሰሏት” በሚባለውም መጽሐፉ ጭምር በሓነፊያ መዝሀብ ላይ መልስ ሰጥቷል፡፡
ወደ ተነሳንበት ወግ ስንመለስ፣ ግለሰቡ ያለፈበትን የፍልስፍና ውጣ-ውረድ ልብ ብሎ የተረዳ ሰው፣ግለሰቡ በትክክል ከባድ ፊትና ውስጥ የነበረና እስከ አኹንም በዛ ፊትና ውስጥ እየዋለለ እንደኾነ መረዳት አይከብደውም፡፡
ወዳጄ ፍልስፍና ማለት በተለይ የተዘራባቸውን ኹሉ ለሚያበቅሉ ተደራሲ ለኾኑ ሰዎች በመርዝ የተለወሰ ማር ነው፡፡ ቀስ እያለ እየጣፈጠ ይገባና የማይወጣ በሽታ ኾኖ ይቀራል፡፡
እስከማውቀው ድረስ ግለሰቡ የራሴ የሚለው አቋምና ተቋም የለውም፡፡ ባለው አቋም ላይም ዕርግጠኛ አይመስለኝም፡፡ ቀረብ ብሎ ለሚያናግረውና እዚህ ጋር ተሳስተሃል ለሚለው ሰው ደግሞ ስሕተቱን የሚቀብል እንጂ ተከራካሪ ግለስብ እንዳልኾነ በቅርብ ዐውቃለኹ፡፡
ልጁ በተሳሳተው ነገር በሙሉ ባለማወቅ ዑዝር ሊሰጠው ((عذر بالجهل ይችላል፡፡ በርግጥም ከኢስላም አኳያ ጀማሪ የሚባል እንኳ ዕውቀት ያለው ሰው አይደለም፡፡ ዕውቀት ፈላጊም ((طالب العلم አይደለም፡፡
እንደኔ በረጋ መንፈስ ስሕተቱን ማረሙ የግድ ኾኖ፣ግን ደግሞ ጨርሶ ልጁን ከማጣታችን በፊት የሚመለከታቸው አካላት ቀርበው ቢያናግሩትና ካለበትም የችግር ሕይወት እስከ መጨረሻው መውጣት የሚችልበትን የስራ ዕድል ቢያመቻቸቹለት ማለፊያ ነው፡፡
ግለሰቡ ያለውን የንባብና የማሰላሰል አቅም ወደ ኢስላም ገልብጠን ለመጠቀም ልጁን ወደ ሕይወት መመለስና መስራት የሚችልበትን ከባቢ ማመቻቸት የኹሉም ኃላፊነት ነው ብዬ አምናለኹ፡፡
https://t.me/E_M_ahmoud
4 995
ስሕተትን ስናርም
..
ከሰሞኑን አንድ በፍልስፍና ውስጥ የተዘፈቀ ወንድም የኾነ ሚዲያ ላይ ቀርቦ የተናገረውን ነገር ብዙዎቻችን እንዳየን አምናለኹ፡፡ የልጁን ንግግር ተከትሎ በቁጥር ቀላል የማይባሉ ሰዎች ልጁን ከኢስላም አጠድ ውጪ ሲያስወጡት፣ገሚሱ ደግሞ አፈንጋጭ (ሙልሒድ) ነው ሲሉትም ዐይተናል፡፡
ግለሰቡ የተሳሳተውን ነገር ማረምና ማስተካከያ መስጠት ግዴታ ነው፡፡ እንዴት ነው የምናርመው?የሚለው ጥያቄው ግን በሰከነ መንፈስ ሊታይ ይገባዋል፡፡
በተለይ ደግሞ ገፊ ስሜቱን መቆጣጠር የማይችል ሰው፣በሰዎች ላይ መልስ ለመስጠት ባይንደረደር መልካም ነው፡፡ ምክንያቱም መሰል ሰዎች መልስ እንሰጣለን ብለው ሲነሱ ከመልሱ ይልቅ የግል ጥላቻና አቋማቸውን ጮክ አድርገው ስለሚናገሩ የሚያዳምጣቸው ሰው ከንግግራቸው መካከል ተሳሳተ የተባለው ግለሰብ ስሕተቱ ምኑ ጋር እንደኾነ በቅጡ መረዳት ይሳነዋል፡፡
በሌሎች ላይ መልስ ለመስጠት የሚነሳ ማንኛውም ሰው በመጀመሪያ በኢስላማዊ አደብ ሊጸበየት ይገባል፡፡
አንዳንዴ ግሞ መልስ ከመስጠት ይልቅ ከግለሰቡ ጋር በግል መነጋገርና መወያየት ሊሻል ይችላል፡፡
አንዳንዴ ደግሞ መልስ መስጠቱ በራሱ ጉዳዩን የበለጠ ማስተዋወቅ ይኾናል፡፡
ለዚህ ምርጥ ማሳያችን የሰልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (The satanic verses) መጽሐፍ ነው፡፡
ሰልማን ሩሽዲ በሳላፍነው መጽሀፍ ያልሰደበው፣ያላዋረደው ማሕበረሰብ አለ ማለት ይከብዳል፡፡ ከዚህም መሐል ቁርኣንን ጨምሮ ኢስላምን አብጠልጥሏል፡፡
ይሕን ተከትሎ በወቅቁ የኢራን መሪ የነበረው አያቱላህ ኹመይኒ ሰልማን ሩሽዲን የገደለ ኢራን ወሮታውን እንደምትከፈል አወጀ፡፡ ይሕ ንግግሩ ብቻ የሰልማን ሩሽዲን መጽሐፍ በዓለም ላይ እንዲተዋወቅ አደረገው፡፡
ወዳጄ በየጊዜው በኢስላም ላይ የሚጻፉ በርካታ አጓጉል መጽሐፎች እንዳሉ ልብ ይሏል፡፡ሩቅ ሳንሄድ የሐገራችን የኦርቶ ቤተክርስቲያን ታቅፋ የምትሞቃቸው ጥቂት የማይባሉ ኢስላምንና መልዕክተኛውን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የሚያነውሩ መጽሐፍት አሉ፡፡ ከነዚህ መጽሐፍት አኳያ የሰልማን ሩሽዲ መጽሐፍ ምንም ላይኾን ይችላል፡፡ ኾኖም ግን የኹመይኒ አዋጅን ተከትሎ የሰልማን መጽሐፍ በወቅቱ በዓለም ላይ እንዲገን ኾኗል፡፡
ብዙም ሳይቆይ ሼኽ አሕመድ ዲዳት ( ረሒመሁ አላህ) ``Can you stomach the best of Rushdi`` በሚል ርዕስ ድንቅ መጽሐፍ ጽፎ ለሰልማን ጥገኝነት የሰጠችው እንግሊዝ ጭምር በስራዋ እንድታፍር አድርጓል፡፡
ምን መሰሎት ወዳጄ? ሰልማን በመጽሀፉ እንግሊዞች ከእህታቸው ጋር ይዘሙታሉ ብሎ ተናግሯል፡፡ የራሱ የሰልማን ሚስት ደግሞ በጊዜው አንግሊዛዊት ነበረች፡፡ ዲዳት ሲጠይቅ “ሰልማን እንግሊዞች ይሕንን ነውር እንደሚፈጽሙ ከየት አወቀ?ይልና…ራሱ ሲመልስ “ያው…
4 995
አወወ " ስሕተትን ስናርም"በሚል ርዕስ የጻፍኹት የመጨረሻ ጽሑፌን ኮፒ ወይም ሼር ያደረገ ካለ በውስጥ ቢያቀብለኝ። ባልታወቀ ምክንያት ከዚህ ግርግዳ ላይ ተሰርዟል
4 995
ስሕተትን ስናርም
..
ከሰሞኑን አንድ በፍልስፍና ውስጥ የተዘፈቀ ወንድም የኾነ ሚዲያ ላይ ቀርቦ የተናገረውን ነገር ብዙዎቻችን እንዳየን አምናለኹ፡፡ የልጁን ንግግር ተከትሎ በቁጥር ቀላል የማይባሉ ሰዎች ልጁን ከኢስላም አጠድ ውጪ ሲያስወጡት፣ገሚሱ ደግሞ አፈንጋጭ (ሙልሒድ) ነው ሲሉትም ዐይተናል፡፡
ግለሰቡ የተሳሳተውን ነገር ማረምና ማስተካከያ መስጠት ግዴታ ነው፡፡ እንዴት ነው የምናርመው?የሚለው ጥያቄው ግን በሰከነ መንፈስ ሊታይ ይገባዋል፡፡
በተለይ ደግሞ ገፊ ስሜቱን መቆጣጠር የማይችል ሰው፣በሰዎች ላይ መልስ ለመስጠት ባይንደረደር መልካም ነው፡፡ ምክንያቱም መሰል ሰዎች መልስ እንሰጣለን ብለው ሲነሱ ከመልሱ ይልቅ የግል ጥላቻና አቋማቸውን ጮክ አድርገው ስለሚናገሩ የሚያዳምጣቸው ሰው ከንግግራቸው መካከል ተሳሳተ የተባለው ግለሰብ ስሕተቱ ምኑ ጋር እንደኾነ በቅጡ መረዳት ይሳነዋል፡፡
በሌሎች ላይ መልስ ለመስጠት የሚነሳ ማንኛውም ሰው በመጀመሪያ በኢስላማዊ አደብ ሊጸበየት ይገባል፡፡ አንዳንዴ መልስ ከመስጠት ይልቅ ግለሰቡን ማነጋገር ሊሻል ይችላል፡፡
አንዳንዴ ደግሞ መልስ መስጠቱ በራሱ ጉዳዩን የበለጠ ማስተዋወቅ ይኾናል፡፡ ለዚህም ምርጥ ማሳያችን የሰልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (The satanic verses) መጽሐፍ ነው፡፡
ሰልማን ሩሽዲ በሳላፍነው መጽሀፍ ያልሰደበው፣ያላዋረደው ማሕበረሰብ አለ ማለት ይከብዳል፡፡ ከዚህም መሐል ቁርኣንን ጨምሮ ኢስላምን አብጠልጥሏል፡፡
ይሕን ተከትሎ በወቅቁ የኢራን መሪ የነበረው አያቱላህ ኹመይኒ ሰልማን ሩሽዲን የገደለ ኢራን ወሮታውን እንደምትከፈል ተናገረ፡፡ ይሕ ንግግሩ ብቻ የሰላምን ሩሽዲ መጽሐፍ በዓለም ላይ እንዲተዋወቀቅ አደረገው፡፡
ወዳጄ በየጊዜው በኢስላም ላይ የሚጻፉ በርካታ አጓጉል መጽሐፎች እንዳሉ ልብ ይሏል፡፡ሩቅ ሳንሄድ የሐገራችን የኦርቶ ቤተክርስቲያን ታቅፋ የምትሞቃቸው ጥቂት የማይባሉ ኢስላምንና መልዕክተኛውን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የሚያነውሩ መጽሐፍት አሉ፡፡ ከነዚህ መጽሐፍት አኳያ የሰልማን ሩሽዲ መጽሐፍ ምንም ላይኾን ይችላል፡፡ ኾኖም ግን የኹመይኒ ንግግር በዓለም ላይ እንዲገን አድርጎታል፡፡
ብዙም ሳይቆይ ሼኽ አሕመድ ዲዳት ( ረሒመሁ ላህ) ``Can you stomach the best of Rushdi`` በሚል ርዕስ ድንቅ መጽሐፍ ጽፎ ለሰልማን ጥገኝነት የሰጠችው እንግሊዝ ጭምር በስራዋ እንድታፍር አድርጓል፡፡
ምን መሰሎት ወዳጄ? ሰልማን በመጽሀፉ እንግሊዞች ከእህታቸው ጋር ይዘሙታሉ ብሎ ተናሯል፡፡ የራሱ የሰልማን ሚስት ደግሞ በጊዜው አንግሊዛዊት ነበረች፡፡ ዲዳት ሲጠይቅ “ሰልማን እንግሊዞች ይሕንን ነውር እንደሚፈጽሙ ከየት አወቀ?ø ይልና…ራሱ ሲመልስ “ያው ሚስቱ ነግራው ነው ማለት ነው” ካለ በኋላ፣ “ሚስቱም ብትኾን የዚህ ነውር ተጋሪ ናት ማለት ነው” በማለት ሰልማንን በራሱ ጥይት ገድሎታል፡፡
ወደ ኋላ ተንደርድረን ሌላ ምሳሌ ብንወስድ፣የኢማሙ አቢ ሓኒፋ መዝሃብ ላይ ኢማሙ አልቡኻሪ በተለያዩ መጽሐፎቹ ውስጥ መልስ ሰጥቷል፡፡ ኾኖም ግን ቡኻሪ መልሱን ሲሰጥ በፍጹም አክብሪትና አደብ ውስጥ ኾኖ ነበር፡፡ ለዚህም ማሳያው አልቡኻሪ የአቡ ሓኒፋን ስም በፍጹም ሳይጠቅስ “አንዳንድ ሰዎች እንዲሕ ይላሉ” ብቻ በማለት ስሕተቱ ላይ አተኩሮ መናገሩ ነው፡፡
በትክክል የአቡ ሓኒፋን መዝሃብ አስቀድሞ ያላወቀ ወይም ቡኻሪ በማን ላይ መልስ እንደሰጠ የከሌሎች ዑለማእ ካልሰማ፣ ቡኻሪ እናምንን አስቦ እንደሚናገር ማወቅ አይችልም፡፡
ይሕንን ለማየት የፈለገ በራሱ በቡኻሪ የሐዲስ መጽሐፍ ውስጥ “ኪታቡል ሒል” በሚል ርዕስ የሰጠውን ክፍል ማንበብ ይችላል፡፡ ኢማሙ አልቡኻሪ በአቡ ሓኒፋ መዝሐብ ላይ መልስ እንደሰጠ ራሱ ኢብኑ ሐጀር “ፈትሑል ባሪ” ላይ ይናገራል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ሐነፊይ የነበረው ኢማሙል ዓይኒይ “ዑመዱል ቃሪእ” ላይ ተናግሯል፡፡
ኢማሙል ቡኻሪ ከሐዲስ መድብሉ ባሻገር “አልቂራኣት ኸልፈል ኢማም” በሚል መጽሐፉ፣”ረፍዑል የደይን ፊ አሰሏት” በሚባለውም መጽሐፉ ጭምር በሓነፊያ መዝሀብ ላይ መልስ ሰጥቷል፡፡
ወደ ተነሳንበት ወግ ስንመለስ፣ ግለሰቡ ያለፈበትን የፍልስፍና ውጣ-ውረድ ልብ ብሎ የተረዳ ሰው፣ግለሰቡ በትክክል ከባድ ፊትና ውስጥ የነበረና እስከ አኹንም በዛ ፊትና ውስጥ እየዋለለ እንደኾነ መረዳት አይከብደውም፡፡
ወዳጄ ፍልስፍና ማለት በተለይ የተዘራባቸውን ኹሉ ለሚያበቅሉ ተደራሲ ለኾኑ ሰዎች በመርዝ የተለወሰ ማር ነው፡፡ ቀስ እያለ እየጣፈጠ ይገባና የማይወጣ በሽታ ኾኖ ይቀራል፡፡
እስከማውቀው ድረስ ግለሰቡ የራሴ የሚለው አቋምና ተቋም የለውም፡፡ ባለው አቋም ላይም ዕርግጠኛ አይመስለኝም፡፡ ቀረብ ብሎ ለሚያናግረውና እዚህ ጋር ተሳስተሃል ለሚለው ሰው ደግሞ ስሕተቱን የሚቀብል እንጂ ተከራካሪ ግለስብ እንዳልኾነ በቅርብ ዐውቃለኹ፡፡
ልጁ በተሳሳተው ነገር በሙሉ ባለማወቅ ዑዝር ሊሰጠው ((عذر بالجهل ይችላል፡፡ በርግጥም ከኢስላም አኳያ ጀማሪ የሚባል እንኳ ዕውቀት ያለው ሰው አይደለም፡፡ ዕውቀት ፈላጊም ((طالب العلم አይደለም፡፡
እንደኔ በረጋ መንፈስ ስሕተቱን ማረሙ የግድ ኾኖ፣ግን ደግሞ ጨርሶ ልጁን ከማጣታችን በፊት የሚመለከታቸው አካላት ቀርበው ቢያናግሩትና ካለበትም የችግር ሕይወት እስከ መጨረሻው መውጣት የሚችልበትን የስራ ዕድል ቢያመቻቸቹለት ማለፊያ ነው፡፡
ግለሰቡ ያለውን የንባብና የማሰላሰል አቅም ወደ ኢስላም ገልብጠን ለመጠቀም ልጁን ወደ ሕይወት መመለስና መስራት የሚችልበትን ከባቢ ማመቻቸት የኹሉም ኃላፊነት ነው ብዬ አምናለኹ፡፡
https://t.me/E_M_ahmoud
4 995
ከግንዛቤ ቢገባ
....
ብዙ ጊዜ ሴቶች የማይገነዘቡት ነገር ቢኖር ወንዶች ከቤታቸው የሚሸሹት ወይም ሌላ ቤት ለመገንባት ከሚፈልጉት ምክንያቶች መካከል አንዱ ከቤታቸው ክብርን ማጣታቸው ነው።
ኹሉም አባወራ ዉሎውን የሚወጣጥረውና የሚያደክመው ብሎም የሚያጨናንቀው ከባቢ ውስጥ አሳልፎ ነው የሚገባው።
ውጪ ያጣውን ሰላምና ክብካቤ ቤት ውስጥ ካላገኘ፣ይልቁንም ቤቱ የጋላ ምጣድ ኾኖ ከጠበቀው፣ሌላ ቤት መገንባት አሊያም ቤቱን አፈራርሶ ከራሱ ጋር ሰላሙን መፍጠር ያሰኘዋል።
ከዚህም ዕውነታ አኳያ እየተንገዳገዱ ያሉ በርካታ ቤቶችን እናውቃለን።
ከምንም በላይ መሰል ቤቶችን ቀጥ ለማድረግ ሚስቶች ከፍተኛ ሚና መጫወት አለባቸው።
ሚስቶች የመሰል ችግሮች መንስዔ መኾናቸውን አለማወቃቸውና መኾናቸውንም ለመቀበል ፈቃደኛ አለመኾናቸው ችግሩን መፍትሔ አልባ እንዲኾን ያደርገዋል።
ሚስቶች በቻሉት ልክ የባላቸው የሰላም ምንጭ መኾን አለባቸው።
ባሎች በሰላም ቤቷ ትኖር የነበረችን ልጅት ከቤቱ አምጥቶ ኩነኔ ሊፈጥርባት አይገባም።
መልዕክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ባሎች ሚስቶቻቸውን በማኗኗር ላይ አላህን እንዲፈሩ አሳስበው ተናግረዋል፦
اتقوا الله في النساء فَإِنَّكُمْ أَخَذْتُمُوهُنَّ بِأَمَانِ اللَّهِ
"ከሚስቶቻችኹ አኳያ አላህን ፍሩ። ያገባችዃቸው በአላህ ቃል ኪዳን ነው"
ይሕ የመልዕክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ንግግር ሚስቶችን በአላህ (ሱብሓነሁ ወተዓላ) ፊት ባሎች ቃል ገብተው ከወሊይ ዕጅ ተቀብለዋልና ቃላቸውን እንዲጠብቁ አበክሮ ያሳስባል።
ስለዚህ ወዳጄ መታወቅ ያለበት ኹሉም እንደ ሰው የራሱ ክፍተት አለበት።
ዱንያ ላይ የወንድም ኾነ የሴት ምሉዕ በፍጹም የለም።
ዱንያ ላይ የመጨረሻ ደስታም ከቶ አይገኝም። ያማ ቢኾን ኖሮ አላህ (ሱብሓነሁ ወተዓላ) ጀነትን ባልፈጠረ ነበር።
ሰው ኹሌም ሰውን ተቀብሎ ሲኖር ዕዳውንም ተሸክሞ ነው።
ወዳጄ ኹላችንም የባሕሪ አሊያም ሰው የመኾን ዕዳ አለብን።
ዕዳ እንዳለባቸው የሚያምኑ፣ዕዳቸውን እያቃለሉ የአጋራቸውንም ዕዳ አሚን ብለው ተቀብለው ይኖራሉ።
ቤት በማፍረስና ሌላ ቤት በመገንባት የተከፈሉ ዕዳዎች ካሉ ግን ኹሉም በሚባል መልኩ ሌላ የሕሊና ዕዳ ያውም በአራጣ የታጨቀ ተከፍሎ የማያልቅ ሸክም ያመጣሉ እንጂ ደስታን አይፈጥሩም።
...
ለማንኛውም በኣያም አተሽሪቅ ሰላም ያጡ ቤቶች ኹሉ በሰላም እንዲያበሩ ተመኘኹ!!
4 995
Emotional Advice for Those Who Missed Hajj | Ibn Rajab al-Hanbali ابن رج...
https://youtube.com/watch?v=J-1VoDCFVRU&si=ZdT8DxE7rP_usavl
4 995
አልባጢኒያ (11)
..
ዮጋና ኢኣማኝነት
…
ቀደም ሲል ዮጋ በሚባል የሚታወቀው “አካላዊ እንቅስቃሴ” ከሂንዱ እምነት ጋር ብቻ የማያያዝ እሳቤዎች እንደነበሩ ይታወቃል፡፡ ሒንዱ እንደ ማንኛውም ሃይማኖት በውስጡ የአምልኮ እንቅስቃሴዎች፣ጾምና ጸሎትን ያካትታል፡፡
በኢስላም ሶላት ሲፈጸም የራሱ አምልኮአዊ እንቅስቃሴዎች አሉት፡፡ በሂንዱም ሃይማኖት እንደዚሁ የስግደት እንቅስቃሴዎች አሉ፡፡ እነዚህ የስግደት እንቅስቃሴዎች በአጭሩ “ዮጋ” በሚል ይጠራሉ፡፡
በየትኛውም ሃይማኖት ውስጥ ያሉ የዬጋ እንቅስቃሴ ተለማማጆችም አሰልጣኞችም በምልዓት ጠዋትና ማታ ለጸሐይ ሰላምታ ይሰጣሉ፡፡ ይሕ የጻሐይ ሰላምታ ሱርያ ናማስካር ( Surya Namaskar ) በመባል ይታወቃል፡፡
በሱርያ ናማስካር የሚመላለሱ የዮጋ አፍቃሪዎች እግራቸውን በማጣመር መሬት ላይ ይቀመጣሉ፡፡ይሕ አቀማመጥ ሙድራ (Mudra ) በመባል ይታወቃል፡፡ ሙድራ ላይ እያሉም አውራ ጣታቸውን ከጠቋሚ ጣታቸው ጋር አቆላልፈው ቀለበት የሚመስል ሰፋ ያለ ክብ ይሰራሉ፡፡
አውራ ጣት “ሺቫ” የሚባለውን “የሒንዱ አምላክ” ያመላክታል፡፡ ጠቋሚ ጣት ደግሞ የግለሰቡን ውስጠት (ነፍስ) ያመለክታል፡፡ ጠቋሚ ጣት እጥፍ ብሎ አውራ ጣትን ሲነካ፣ግለሰቡ ውስጠቱን (ነፍሱን) “ከአምላኩ” (አውራ ጣት) ጋር እንዳገናኘና በዚህ ልምምድ ውስጥ እሱና አምላኩ ተጣምረው አንድ አካል እንደሰሩ የሚጠቁም ነው፡፡ በኹለቱ ጣቶች የተሰራው ቀለበት በሌላ መልኩ መለኮታዊው ሃይል በእኔ ውስጥ አለ የሚል ትርጉምም አለው፡፡
ይህ ደግሞ እንደ ኢስላም ዐቂደት አልሑሉል (عقيدة الحلول) በመባል የሚታወቀው ሲኾን አስተምህሮው አላህ(ሱብሓነሁ ወተዓላ) በኹሉም ነገር ውስጥ ሰርጧል፤ኹሉም ነገር ውሰስጥ አለ፤እኛም ውስጥ አለ፤ስለዚህ አንድ ሰው ራሱን ቢያመለክ ምን ችግር አለው የሚል ጥያቄ የሚያስነሳ የኩፍር አቋም እንደኾነ ይታወቃል፡፡
በዮጋ አቀማመጥ ኹለቱ ጣቶች እርስ በርስ ሲጣመሩ የተቀሩት ሶስቱ ጣቶች ደግሞ ተዘርግተው ይቀራሉ፡፡ ሶስቱ የተዘረጉት ጣቶች ቁሳዊው ዓለምን፣ቁሳዊ ስሜቶችንና ጠፊ የኾነውን ጊዜ ያመልክታሉ፡፡ የኹለቱ ጣቶች መጣመርና የተቀሩት ሶስቱ መዘርጋት “ከዚህ ቁሳዊው ዓለም ውጥንቅጥ ወጥቼ ውስጠቴን ከመለኮታዊው ኣካል ጋር አቆራኝቻለኹ” የሚል ትርጉም አለው፡፡
የዮጋ መዘዞች
….
ከአንድ ዓመት በላይ ዮጋ በተለማመዱ ሰዎች ላይ በተደረገ ጥናት ሐምሳ በመቶ የሚኾኑት ከልምምዱ በፊት ያልነበራቸውን ዓይነት እንግዳ ሓሳቦችን ማሰላሰል እንደጀመሩ ተናግረዋል፡፡ 82 በመቶ የሚኾኑት ደግሞ ፍርሓት፣ጭንቀትና መርበትበት ወይም “ሊገድሉኝ ነው የሚል የስጋት መንፈስ እንደተጠናወታቸው ተዘግቧል፡፡
በተደረጉ መሰል ጥናቶች ላይም 18 በመቶ የሚኾኑ በዬጋ ልምምድ ውስጥ የሚመላለሱ ሰዎች ራሳቸውን የማጥፋት ሙከራ አድረገው ተገኝተዋል፡፡
በዮጋ ልምምድ ወቅት ባዕድ ሕሳቦ የሚጀምርበት ምክንያት ልምምዱ ከፍ ያለ የአተነፋፈስ ፍጥነት የሚያስፈልግበት ደረጃ ላይ ሲደርስ ከሰውነት በርካታ ካርበን ዳኦክሳይድ ይወገዳል፡፡ ይሕ ደግሞ ሃይፖካፕኒያ (hypocapnia) የሚባል ኹኔታ እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡
ሰውነታችን ካርበን ዳይኦክሳይድን በመጠቀም ስለኾነ ካርበኒክ አሲድ የሚሰራው፣የካርቦን ዳይኦክሳይድ ማነስ ሰውነት በተወሰነ ደረጃ አልካላይን እንዲኾን ያደርገዋል፡፡ ይህ ሂደት ሬስፒራትሪ አልካሎሲስ (respiratory alkalosis) በመባል ይታወቃል፡፡
ደማችን ካልሺየምን የሚሸከሙ በአብኛው አልቡሚን የሚባሉ ፕሮቴኖችን ይይዛል፡፡ ቀደም ሲል በጠቀስነው ምክንያት ደም አልካላይን በሚኾንበት ጊዜ የነዚህ ፕሮቴኖችን ቅርጽ ይለወጣና በብዛት በደም ውስጥ ከሚገኙ ነጻ የካልሺየም አዮኖች ጋር እንዲጣበቁ ያደርጋቸዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በደም ውስጥ ንቁ የኾነ የካልሺየም አዮን ክምችት ይቀንሳል፡፡
ይሕ ኹኔታ ደግሞ በተዘዋዋሪ ለነረቮችና ለጡንቻዎች መድረስ ያለበት አስፈላጊ የካልቺየም ክምችት እንዲቀንስ ስለሚያደርግ ነርቮች በጣም ይታወካሉ፡፡ የዚህ የካልሺየም ክምችት እጥረት (hypocalcemia) በስተመጨረሻ አዕምሮ ከተለመደው ውጪ ባዕድ ነገር እንዲያስብ ያስገድደዋል፡፡
….
ይቀጥላል
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
