fa
Feedback
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

رفتن به کانال در Telegram

« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

کانال 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀 (@https_asselefya1) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 292 مشترک است و جایگاه 6 167 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 369 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 292 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 21 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -52 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 16.86% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.12% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 2 410 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 160 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 22 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

14 292
مشترکین
+124 ساعت
+87 روز
-5230 روز
آرشیو پست ها
▶️ወንጀል ላደከማት ነፍስ! 📚 አድ-ዳእ ወድ-ደዋእ(ሙኽተሶር) ኪታብ ቀጥታ ስርጭት👇 https://t.me/Sle_qelbachn1?livestream=9076638e15deef94b7

~ አንዳንድ ፀሁፎች አንባቢ ለመሆን ሰበብ ይሆናሉ ! እና የመፃፍ ችሎታ ያለዉ ይፃፍ ማለቴ ነዉ። ችሎታችሁን ዝም ብላችሁ ለራሳችሁ አትያዙ ! አዉጡት ህዝቡ ይጠቀምበት! ሁሉም በችሎታዉ ይታገል! =

~ ወንጀል አንድን ባሪያ ራሱን እንድረሳ ያደርጋል! የሚል ሰማሁ ከአድ_ዳእ ወድ_ደዋእ ደርስ ላይ! ሀቂቃ ራሴ ላይ ተመላለሰብኝ እና ላካፍላችሁ "ቆይ ራሳችን መንከባከብ የሚከብደን ፀጉራችን አበጥሮ መስራት ራሳችን ፏ በተን ማለት ልክ ተራራ እንደመዉጣት የሚከብደን ግን ለአረቦች ሲሆን ቢደክመንም ጨክነን የምንሰራ ለገንዘብ ብለን የቱ ድብቅ ወንጀላችን ይሆን ራሳችንን እንዳንከባከብ ያገደን ? መቸም ስልካችን ነዉ የወንጀል መዳፈሪያ ሰበባችን እና በስልካችን ምን እንምንመለከት ምን እንደምንማ ከማን እንደምንፃፃፍ እንደምንደዋወል እስኪ ትኩረት እንስጠዉ ! እና ወደ ራሳችን እንመለስ። =

14 አድ-ዳእ ወድ-ደዋእ(ሙኽተሶር).mp311.15 MB

ይቀጥላል መልካም ንባብ 🙌

🔖​የሁለተኛ ሚስት ወግ! "ከሸሪዓ" እስከ ማህበራዊ "ውጥረት"1. ሸሪዓውና የቤት ውስጥ "ፓርላማ" ​በሸሪዓውማ ነገሩ ግልጽ ነው፤ አራት ድረስ ይፈቀዳል። ግን ቅድመ-ሁኔታው "ፍትህ" (Justice) የሚባል ትልቅ ተራራ ነው። ብዙ ወንዶች የፈቃዱን አንቀጽ እንደ "ብሔራዊ መዝሙር" በቃላቸው ያውቁታል። ​ወንዱ፤ "ሸሪዓው እኮ አራት ፈቅዶልኛል!" ይላል። ​ሚስት፡ "ፍትህ መስጠት ትችላለህ? መጀመሪያ የልጆቹን ደብተር አሟልተህ ግዛ!" ብላ የቤቱን "ቬቶ" ስልጣን ትጠቀማለች። ሸሪዓው ፍትህን በገንዘብ፣ በጊዜና በእንክብካቤ ሲያዝ፣ ወንዱ ደግሞ ፍትህን "ሁለቱንም እኩል እወዳቸዋለሁ" በሚል ስሜታዊ ስሌት ሊያቃልለው ይሞክራል። ​2. ማህበራዊ ተግዳሮት፡ "የሰፈር ራዳር" ​ሁለተኛ ለማግባት የወሰነ ወንድ ልክ እንደ ሰላይ ነው፤ እንቅስቃሴው ሁሉ በሚስጥር ነው። ☎️ስልኩ በፓስዎርድ ታጥሮ፣ ስም ሳይጻፍባቸው "A1", "B2" ተብለው የተቀመጡ ቁጥሮች ይበዛሉ። ​ሰውነቱ፦ ሽቶው ይቀየራል፣ ጂም መሄድ ይጀምራል፣ ድንገት "ስብሰባ በዛብኝ" ማለት ያዘወትራል። ሰፈሩ ግን ራዳር አለው። ገና እግሩን ሲያነሳ "እገሌ እኮ ደገመ" ተብሎ ወሬው ከቤቱ ቀድሞ ይደርሳል። እዚህ ጋር ነው እንግዲህ "የማህበራዊ ጦርነት" የሚጀምረው። የዘመድ አዝማድ ምክር፣ የጎረቤት ኩርፊያ፣ "የመጀመሪያዋን ሚስት ምን አጎደለችብህ?" የሚሉ ጥያቄዎች እንደ ናዳ ይወርዱበታል። ​3. "ፍትህ" ወይስ "የመደበቂያ ጨዋታ"? ​ሁለተኛ ያገባ ወንድ ህይወቱ እንደ "ሹፌር" ይሆናል። ​ሰኞና ማክሰኞ "ዋናው መሥሪያ ቤት" (የመጀመሪያዋ ቤት)፣ ​ረቡዕና ሐሙስ "ቅርንጫፍ ቢሮ" (ሁለተኛዋ ቤት)። የሚገርመው ግን፣ አንዷ ቤት የረሳውን ካልሲ ፍለጋ ሲሄድ የሚፈጥረው ድራማ ነው። "የአክስቴ ልጅ መጥታ ነው"፣ "መኪናዬ ተበላሽቶ ነው" የሚሉ ሰበቦች የፈጠራ ክህሎቱን ያሳድጉለታል። ​4. የአሁኑ ዘመን "ሁለተኛ ሚስት" ዓይነቶች ​በአሁኑ ጊዜ ሁለት ዓይነት "ሁለተኛ ሚስት" ፈላጊዎች አሉ፡- ​"የፌስቡክ ጀግና"፦ በየፖስቱ ስር "ሱናውን እናحي (እናንሳ)" እያለ የሚለፍፍ፣ ግን በተግባር ለሚስቱ ቂቤ መግዛት የሚፈራ። ​"ጸጥተኛው ገዳይ"፦ ምንም ሳይናገር፣ ድምጹን ሳያሰማ "ኒካህ" አስሮ፣ መጨረሻ ላይ በድንገት ድግስ የሚጠራ። ​በእርግጥ ሸሪዓው የፈቀደው ለጥበብና ለችግር መፍቻ ነው። ማህበራዊ ተግዳሮቱ ግን የሚመጣው ወንዱ "ፍትህ" የሚለውን ሚዛን ስቶ "ስሜት" ላይ ሲያተኩር ነው። ​ትልቁ ምክር፡ ሁለተኛ ለማግባት ስታስብ፣ ሸሪዓው የሰጠህን መብት ብቻ ሳይሆን፣ ትከሻህ የሚሸከመውን "የሁለት ቤት ጫጫታ" እና "የሁለት አማች ጦርነት" ችሎታህንም ፈትሽ! منقول

እንግድች በደንብ አስቡበት ! አግቢዎች እንድሁም የምትገቡትም ይሄ ሁሉ ጡዘት ያለ 🙌 1ድ ይዞ ሰላም መኖር አይሻል¡¡

ቀጣይም አለ በደንብ አንብቡ እለቃለሁ ሀቂቃ አጃኢብ የሆነ ፀሁፍ ነዉ ፈገግታ እያጫረ ትልቅ ቁም ነገር የያዘ ነዉ ፀሀፊ ወንድማችን አብዱረዛቅ አልሐበሺ አላህ ጀዛዉን ይክፈለዉ!

​ "የወንዱ መንከራተት - ከቤት እስከ ስደት"1. "የሻንጣ ፖለቲካ" (The Mobile Life) ​ሁለት ሚስት ያለው ወንድ የራሱ የሆነ ቋሚ ቁምሳጥን የለውም። ልብሱ ግማሹ "እዛኛው" ቤት፣ ግማሹ "እዚህኛው" ቤት ነው። ሰኞ ጠዋት ለስራ ሲነሳ የሚፈልገው ነጭ ሸሚዝ እዛኛው ቤት መቅረቱን ሲያስታውስ፣ ቀኑን ሙሉ "በግማሽ ልብስ" እንደተጓዘ ይሰማዋል። ​መኪናው ውስጥ ሁልጊዜ ትርፍ ካልሲ፣ ማበጠሪያና የጥርስ ብሩሽ ይዞ ይዞራል። መኪናው ልክ እንደ "ትንሽ ቤት" ትሆናለች። ጎረቤት ሲያየው "እገሌ ሁልጊዜ ጉዞ ላይ ነው" ይለዋል፤ እሱ ግን በሁለት ሰፈር መሃል የሚባዝን "የፍቅር ስደተኛ" ነው። ​2. "የመኖሪያ አድራሻ" መጥፋት ​ወንዱ መሬት ላይ ካለው መንከራተት በላይ፣ አእምሮው ይንከራተታል። ☝️ግራ መጋባቱ👇 ለምሳሌ አንደኛው ቤት ሆኖ "የጨው መጫሪያው የት ነው?" ብሎ ይጠይቃል። ሚስትየው "አምስት ዓመት ሙሉ እዚህ ቤት እየኖርክ ዛሬ ጠፋህ?" ብላ ስታፈጥበት፣ እሱ ግን የጨው መጫሪያው ያለበትን ቦታ "ከዛኛው ቤት" ጋር አደባልቆት መሆኑን በውስጡ ያውቀዋል። ✍​የስልክ ጥሪ አንድ ሰው ደውሎ "የት ነህ?" ሲለው፣ "ቆይ እስቲ..." ብሎ መስኮቱን ከፍቶ ሰፈሩን ማየት አለበት። "የካራ" ሰፈር ነው ወይስ "ላፍቶ"? ግራ መጋባት ማለት ይህ ነው! ​3. "የምግብ ሰለባ" (The Food Marathon) ​ይህ መንከራተት የሆድም ጭምር ነው። ​ አንደኛዋ ቤት በልቶ፣ ሁለተኛዋ ቤት ሲሄድ "ልዩ ምግብ ሰርቼልሃለሁ" ትለዋለች። "በልቻለሁ" ካለ "እሷ ጋር ስለበላህ እኔን ናቅኸኝ" የሚል ጦርነት ይነሳል። ​ ሆዱ እየፈነዳም ቢሆን "በጣም ይጣፍጣል" እያለ ይበላል። ወንዱ "ከቤት ወደ ቤት" ሲንከራተት፣ ሆዱም "ከውፍረት ወደ ውፍረት" ይንከራተታል። መጨረሻ ላይ ወንዱ ለስራ ሳይሆን ለምግብ ብቻ የሚንቀሳቀስ "ሞባይል ሬስቶራንት" ይመስላል። ​4. "የበዓላት ድራማ" (The Holiday Rush) ​የበዓል ቀን (ዒድ ወይም ሌላ) ሲመጣ ወንዱ እንደ "ማራቶን ተወዳዳሪ" ይሮጣል። ​ጠዋት አንደኛው ቤት መስዋዕት ያርዳል፣ ከሰዓት በኋል ደግሞ እዛኛው ቤት ሄዶ ሌላ ድግስ መሳተፍ አለበት። ​የአንዱ ቤት ዘመዶች "ለምን ቶሎ ትሄዳለህ?" ይሉታል፤ የሌላኛው ቤት ደግሞ "ለምን ዘገየህ?" ይሉታል። ​ ወንዱ በዓሉን የሚያሳልፈው በሁለት ቤቶች መሃል ባለው መንገድ ላይ "ትራፊክ" ውስጥ እየተጨናነቀ ነው። ለሰው በዓል ነው፣ ለእሱ ግን "የሩጫ ውድድር" ነው። ​5. "የሰላም ፍለጋ" (The Search for Sanctuary) ​በመጨረሻም ወንዱ ከሁለቱም ቤት ሲንከራተትና ሲደክመው፣ ሦስተኛ "ቤት" ይፈልጋል። ​ያ ቤት ግን ሚስት ያለበት ሳይሆን፣ "መኪናው" ውስጥ ወይም "መስጂድ" ውስጥ ነው። ​ብቻውን ሆኖ "ኧረ ለመሆኑ እኔ ማን ነኝ? ቤቴስ የት ነው?" ብሎ ራሱን ይጠይቃል። መንከራተቱ በሁለት ሚስት ብቻ ሳይሆን፣ በሁለት ዓለም መሃል መሆኑን ይረዳዋል። ​ወንዱ "ሁለት አገባሁ" ሲል በሁለት እግሩ መቆም አቅቶት በሁለት ቤት መሃል እንደ ፔንዱለም ይወዘወዛል። መንከራተቱ በገንዘብ ብቻ ሳይሆን በስሜት፣ በጊዜና በጤናም ነው። ​ለወንዶች የተላከ ማስታወሻ፦ "መንከራተቱ" እንዳይበዛብህ ካሰብክ፣ መጀመሪያ የልብህን "ኮምፓስ" አስተካክል። ፍትህ ከሌለ መንከራተቱ ወደ "መጥፋት" ይቀየራልና! ​ منقول

«በአንደኛዋ ሚስቱ ቤት ሆኖ የሁለተኛዋን ሚስቱን ስም የጠራ አለ!» ቀን የሚሳሳተው፣ ካልሲውን አንዷ ጋር ጥሎ አንዷ ጋር አልጋ ስር የሚፈልገው በርክቷል እየተባልኩ ነው።  እስኪ ስለዚህ ጉዳይ ሰፋ ያለ ወግ ብጤ አዘንባለሁ። cold war منقول

ለነበረን ቆይታ አመሰግናለሀ ብሎ ፍስታል ከኢትዮ ተሰናብቷል አሉ🙌
ለነበረን ቆይታ አመሰግናለሀ ብሎ ፍስታል ከኢትዮ ተሰናብቷል አሉ🙌

አንድ የቡና ሱሰኛ ባልና ሚስት ይጣላሉ። ሚስትየው ተናዳ "በቃ! ከዚህ በኋላ ካንተ ጋር መኖር አልችልም፣ ቤተሰቦቼ ጋር እሄዳለሁ!" ብላ ሻንጣዋን ትጭናለች። ባሏ በረጅሙ ተንፍሶ እንዲህ አላት፦ "እ
አንድ የቡና ሱሰኛ ባልና ሚስት ይጣላሉ። ሚስትየው ተናዳ "በቃ! ከዚህ በኋላ ካንተ ጋር መኖር አልችልም፣ ቤተሰቦቼ ጋር እሄዳለሁ!" ብላ ሻንጣዋን ትጭናለች። ባሏ በረጅሙ ተንፍሶ እንዲህ አላት፦ "እሺ የኔ እመቤት መሄድ መብትሽ ነው... ግን ከመሄድሽ በፊት የመጨረሻዋን አንድ ሲኒ ቡና አፍልተሽልኝ አትሄጂም? ታውቂዋለሽ የሌላ ሰው ቡና ራስ ምታት እንደሚሆንብኝ።" ➖እሷም ቡናውን አፈላች፣ በዛው ታረቁ ❕

والعاقِلُ لا يرَى لنَفسِهِ ثمنًا إلَّا الجنَّة... «ጮሌ (ብልጥ) ሰው ከጀነት በስተቀር ለራሱ ምንም ዋጋ አያይም...!»
والعاقِلُ لا يرَى لنَفسِهِ ثمنًا إلَّا الجنَّة... «ጮሌ (ብልጥ) ሰው ከጀነት በስተቀር ለራሱ ምንም ዋጋ አያይም...!»

Quran_recitation_minshawi_imitation_quran_quranrecitation_minshawi.mp36.34 KB