2 528
مشترکین
-124 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-730 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
የ2016 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና መርሃ ግብር ይፋ ሆነ፡፡
(ግንቦት 3 ቀን 2016 ዓ.ም) ከትግራይ ክልል ውጭ በሁሉም ክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች ላሉ ተፈታኞች በወረቀትና በበይነ መረብ የሚሰጠው የፈተና መርሃ ግብር የሚከተለው መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የገለጸ ሲሆን ተፈታኞችና የሚመለከታቸው ሁሉ ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስባል፡፡
የቡታጅራ ከተማ ደም ባንክ ስራ ማስጀመሪያ ልዩ የደም ልገሳ ፕሮግራም በቡታጅራ አጠቃላይ ሆስፒታል አዘጋጅቶ ይጠብቆታል።
#ግንቦት 2/2016 አርብ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ
#ግንቦትን ለወገኔ በሚል መሪ ቃል እኔም፣አንተም፣ አንቺም ለወገናችን ደም እንለግስ።
#ማንም የማይቀርበት ልዩ የደም ልገሳ ፕሮግራም "ኑ በሚተካ ደም የማይተካ የሰው ህይወት እንታደግ"።
ኑ ደም በመለገስ ለሞት የቀረበችን ህይወት እንታደግ
የፊታችን አርብ 2/09/2016 ዓ.ም በቡታጅራ አጠቃላይ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ ከጠዋቱ 2:00 ጀምር የደም ልገሳ መርሃ ግብር ይከናወናል።
ደም በመለገስ ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሂወት መታደግ መታደልም መመረጥም ነው።
ደም መለገስ ከየትኛውም የደግነት ጥግ የላቀ ደግነት ነው።
ደም ስንለግስ ለሞት የቀረበችን ህይወት እንደመታደግ ይቆጠራል።
ይሄን በጎ አላማ ማንኛውም ሰው በእለቱ መካፈል ይችላል
#የቡታጅራ ከተማ ነዋሪዎች በሙሉ በዚህ መልካም ተግባር እንድትሳተፋ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የቡታ/ከ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወላጆች ባደረጉት አስተዋጽኦ የተነገባ ግንባታ ገለጻ እና ጉብኝት።
30/08/20ዓም
በዛሬው እለት 30/08/2016ዓም. የቡታ/ከ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወላጆች ውይይት የት/ቤቱ የ9ወራት አፈጻጸም በማቅረብ ሰፊ ውይይት በማድረግ ተጠናቆዋል።
በውይይቱ ውስጥ ከዚህ በፊት ወላጆች አዋጥተው የተከናወኑ የግንባታ ስራዎች አበረታች በመሆናቸው በቀጣይም የማጠናቀቅ ስራው ተሰርቶ በ2017ዓም የት/ዘመን ለስራ እንዲውል በወላጅ 1000.00 አንድ ሺ ብር እስከ ሰኔ30/2016ዓም ተጠናቆ እንዲገባ መግባባት ላይ በመድረስ ውይይቱ ተጠናቆዋል።
Photo unavailableShow in Telegram
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
የባለፈው የወላጆች ውይይት ወደ 30/08/2016ዓም የተዛወረ መሆኑን ከጠዋቱ 2:30 ት/ቤቱ ግቢ ውስጥ እንዲገኙ እንድታደርጉ መልዕክታችንን እናስተላልፉለን።
Photo unavailableShow in Telegram
ለመላው የክረስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ።
እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው በሰላምና በጤና አደረሳችሁ እያልን። በዓሉ የሰላም የፍቅር የመረዳዳት በዓል እንዲሆን እየተመኘን በተለይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሳትዘናጉ እንድታጠኑ እንጠይቃለን።
የቡታጅራ ከ/አሰ/ት/ት ጽ/ቤት እና
የቡታጅራ ከ/አስ/ፐ/ሲ/ሰ ጽ/ቤት
የመ/ራን እና አሰተዳደር ሰራተኞች
የት/ት መረጃ የሚጣራበት ፕሮግራም
በቀን 24/8/16 አቱ1ኛ ደ/ት/ቤት
በቀን 29/8/16 ቡታጅራ መጀመሪያ
በቀን 30/8/16 መቂቾ 1ኛ ደ/ት/ቤት
በቀን 1/9/16 ሸዋበር 1ኛ ደ/ት/ቤት
በቀን 2/9/16 በታጅራ 2ኛ ደረጃት/ቤት
በቀን 5/9/16 መቂቾ ሚሊኒየም 2ኛ/ደ
በቀን 6/9/16 በህር 2ኛ ደ/ት/ቤት
በቀን 7/9/16 ብሩህ ተስፋ1ኛደ/ት/ቤ
በቀን 8/9/2016 ዶቦ ጡጦ 1ኛ ት/ቤት ማሳሰቢያ
በፕሮግራሙ ቀን ሁሉም አካል መረጃው በየት/ት /ቤቱ ኦርጂናል የት/ት መረጃ ከጀመረበት አሁን እስካለበት
ለምሰሌ ከቲቲአይ _ ማስተርስ የተቋም ሰርተፊኬት ዲፕሎማ ድግሪ 2ኛ ድግሪ እና እስቱደንት ኮፒ እንዲሁም የ10ኛ ወይም የ12ኛ ክፍል ኢንትራንስ
ሁሉንም ኦርጂናል የት/ት መረጃ
ይዞ መገኘት አለበት
በፕሮግራሙ ቀን መረጃው ይዞ በማይገኝ አካል በቀጣይ በሚገጥመው
ማነኛውንም ችግር ሁለቱም ጽ/ቤቶች ኃላፊነት የማይወስዱ መሆኑን እናሳውቃለን
Repost from ትምህርት ሚኒስቴር - Minstry Of Education Ethiopia
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሐምሌ 3 እስከ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ሐምሌ 9 እስከ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።
በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሰኔ 30-ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ሐምሌ 6-7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል።
✅የትምህርት ሚኒስቴር የተረጋገጡ ዜናዎችን ያጋሩ!
@education_Ministry
@education_Ministry
Repost from Yeka Sub City Education Office
Photo unavailableShow in Telegram
🪐የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ
🌟የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተገልጿል።
🟢የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ምክክር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል ።
🌟የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
🟠በዚህም በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን ይወስዳሉም ብለዋል።
⭐️የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (ዶ/ር) እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናውን በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
🌟ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚለቀቅላቸው ሲሆን ደጋግመው እንዲሞክሩና እንዲለማመዱ ይደረጋልም ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
🌟ለዚህም እንዲረዳ የአሰልጣኞች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸውም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
⭐️ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት እንደሚጀምርም በመድረኩ ተገልጿል።
✅EBC
🔠🔠🔠🅰️ 🔠🔠
✅ለሌሎች ሸር እናድርግ!!
👇👇👇👇👇👇👇👇
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/dam76